EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 539 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 340,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 161 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 539 名订阅者。
根据 28 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 1,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 24.98%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.34% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 882 次浏览,首日通常累积 2 539 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 29 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 539
订阅者
-424 小时
-147 天
+130 天
帖子存档
15 539
ጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት 6 ወራት የዕቅዱን 91 ነጥብ 8 በመቶ ኃይል አመንጭቷል
..........///.........
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ስድስት ወራት 3 ሺ 240 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ሀብታሙ ሠሙ እንደገለፁት ጣቢያው ለማመንጨት ካቀደው 3 ሺ 527 ነጥብ 06 ጊጋ ዋት ሰዓት ውስጥ 3 ሺ 240 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማመንጨት የዕቅዱን 91 ነጥብ 88 በመቶ አሳክቷል።
በስድስት ወሩ ውስጥ ጣቢያው ያመነጨው ኃይል ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ14 በመቶ ብልጫ እንዳለው ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ አፈፃፀሙ ከዕቅዱ አንጻር ያነሰው በክረምቱ ወራት ወደ ግድቡ የገባው ውሃ በቂ ስላልነበረ ውሃ ለመያዝ ሲባል ኃይል ማመንጨት በመቀነሱ ነው ብለዋል።
አሁን ላይ በቂ ውኃ ወደ ግድቡ በመግባቱ በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት ከዕቅድ በላይ አፈጻጸም ለማስመዝገብ አልያም የታቀደውን ኃይል ለማመንጨት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አቶ ሀብታሙ ገልጸዋል።
ታኅሣሥ 8 ቀን 2009 ዓ.ም ተመርቆ ወደ ሥራ የጀመረው የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 1 ሺ 870 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን እያንዳንዳቸው 187 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንቸት አቅም ያላቸው 10 ተርባይኖች አሉት።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 24 ቀን 2016 ዓ.ም
15 539
ጣቢያው በራስ አቅም በርካታ የጥገና ሥራዎች ማከናወኑን ገለጸ
……..///………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 6 ወራት በራስ አቅም በጣቢያው የኖዝል ጥገና እና የማቀዝቀዣ ፓምፖችን እድሳት ጨምሮ በርካታ የጥገና ሥራዎችን ማከናወኑን አስታወቀ።
የጣቢያው የጥገና ኃላፊ አቶ አሸናፊ ተስፋዬ እንደገለፁት በዩኒት 2 እና 3 የሚገኙትን ሹል ጫፍ ያላቸው የውሃ መቆጣጠሪያ ኖዝሎችን በጣቢያው ባለሙያዎች በጣቢያው ወርክሾፕ የመጠገን ሥራ ተከናውኗል፡፡
ጣቢያው ካሉት አራት ዩኒቶች መካከል ቀደም ሲል የዩኒት አንድ የኖዝል የጥገና ሥራ በኢትዮጵያ አየር መንገድ መከናወኑን አስታውሰዋል።
ይሁንና አየር መንገድ እንዲህ ዓይነት የሞደፊኬሽን ሥራዎችን በቋሚነት ሥለማይሰራ ከማዕከል የሜካኒካልና የኤሌክትሪካል ቴክኒካል ቡድን ተዋቅሮ ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡
በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 6 ወራት የዩኒት 4 ስድስት ኖዝሎችን በጣቢያው ወርክሾፕ በማከናወን ለሥራ ዝግጁ የማድረግ ሥራ መሰራቱን ጠቁመዋል።
እንደ አቶ አሸናፊ ገለጻ በጣቢያው ባለሙያዎች አቅም የሁሉም ዩኒቶች የማቀዝቀዣ ፓምፕ እና ፊልተሮችን የማጽዳት ስራ በማከናወን ፓምፖች በሚፈለገው አቅም እንዲሰሩና የጀኔሬተር የማቀዝቀዝ ስራ በአግባቡ እንዲሰራ ተደርጓል፡፡
የሰርቨር ቤት፣ የሰዊች ያርድ፣ የቢሮዎች፣ የመቆጣጠሪያ ክፍል እና ለመሳሰሉት የሙቀት መጠን የመቆጣጠር እና የማቀዝቀዣ መሳሪያዎች ጥገና መከናወኑንም ገልፀዋል።
በተጨማሪም በጣቢያው የዩኒቶች ስሊፕ ሪንግ ኮምፓርትመንት የማጽዳት፣ የተበሉ ካርበን ብረሾች በአዲስ የመተካት ሥራ መተካቱን ኃላፊው አስታውቀዋል።
በ2016 በጀት ዓመት በራስ አቅም የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የሠራተኞችን አቅምና በራስ መተማመን ከማሳደጉም በተጨማሪ ተቋሙ ለውጭ ባለሞያ ያወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጭንና የጊዜን ብክነትን በማስቀረት በኩል ከፍተኛ ሚና መጫወቱን አቶ አሸናፊ ተናግረዋል።
ጣቢያው ከጀርመኑ ቮየት ኩባንያ ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት ጥገናን ጨምሮ ሌሎች ሥራዎቹን የሚያዘምን ኦን ኮል ቪዲዮ፣ ኦን ኬር አሴት ማኔጅመንት ሲስተምና ኦን ኬር አኩስቲክስ የተሰኙ ዘመናዊ ቴክኖሎጅዎችን ተግባራዊ ማድረጉን መዘገባችን ይታወሳል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም
15 539
በሪጅኖች የማመንጫ ጣቢያዎች የጥገና ሞጁልን ለመተግበር እየተሰራ ነው
..........///........
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሁሉም ሪጅኖች የጥገና ሥራዎችን ለመስራት የሚያግዘውን የሳፕ ሜንቴናንስ ሞጁል ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የቴክኒካል ድጋፍ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አበባው ያለው እንደለፁት በሁለተኛው ምዕራፍ የሚተገበረው የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል በዋናነት በኃይል ማመንጫዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች እንዲሁም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
በሳፕ የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የአሰራር ሥርዓቶችን አስመልክቶ ከሁሉም ሪጅኖች ለተውጣጡ መሐንዲሶች የግንዛቤ ማስጨበጫና መረጃ የመሰብሰብ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።
ለመሐንዲሶቹ እየተሰጠ የሚገኘው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በዘርፉ የሚገኙትን መረጃዎች ወጥነት ባለው መልኩ ለመሰብሰብና ለማደራጀት ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የአሰራር ሥርዓት ሪያላይዜሽን ወደሚባለውና መረጃዎች ወደ አንድ ቋት የሚሰበሰቡበት ሂደት ወየረም ላይ መድረሱን ጠቅሰዋል።
ከሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ የአሰራር ሥርዓት ጋር ተያይዞ ተቋማዊ የለውጥ አስተዳደር ሥራን የሚመራ የትግበራ ቡድን መዋቀሩን ያስታወቁት ዳይሬክተሩ ቡድኑ የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ እንደሚገኝም ነው አቶ አበባው ያብራሩት።
ከየሪጅኖቹ የተውጣጣው የመሐንዲሶች ቡድን ሥራውን ሲያጠናቅቅ የዘርፉን መረጃዎች ቁልፍ የመረጃ ቋት በማዘጋጀት የመሰነድ ሥራዎችን እንደሚያከናውን ጠቅሰዋል።
በቀጣይም የአሰራር ሥርዓቱን በራስ አቅም በሁሉም የተቋሙ ሪጅኖች ተግባራዊ ለማድረግ ተከታታይነት ያላቸው ሥልጠናዎችን ለመስጠት መታቀዱንም ገልፀዋል።
የአሰራር ሥርዓቱን ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም ሪጅኖች በትብብር መስራት እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል።
እንደ አቶ አበባው ገለፃ የአሰራር ሥርዓቱ በዘርፉ የሚገኙትን ንብረቶች የሚመዘግብ ከመሆኑም ባሻገር በዕቅድ ላይ የተመሠረቱ የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ይረዳል።
የጥገና ሞጅሉ የፍተሻና መለኪያ መሳሪያዎች የጥራት ደረጃን ለማወቅ፤ በተቋሙ ውስጥ የሚገኙ ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ፤ የውጭ ምንዛሬ ለማዳን እንዲሁም የሥራ ጥራትን ለመጨመር እንደሚያግዝም ነው አቶ አበባው የተናገሩት።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 22 ቀን 2016 ዓ.ም
15 539
ከአዳዲስ ክልሎች የሚቀርቡ የኃይል ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተሰራ ነው
………///………..
ከደንበኞች የሚቀርቡ የኃይል ጥያቄዎችን በአግባቡ ለመመለስ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንዳስታወቁት የአዳዲስ ክልሎች አደረጃጀቶችን ተከትሎ በአሁኑ ወቅት በሪጅኑ ያለው የኃይል ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡
ከደንበኞች የሚቀርቡ የኃይል ጥያቄዎችን በአግባቡ ለመመለስና ፍላጎቱን ለማሟላት የማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግና የማሻሻል፣ የተጨማሪ ወጪ መስመርና ብሬከሮችን የማዘጋጀት፣ የማዘመን እንዲሁም በአዲስ የመቀየር ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
ሪጅኑ አገልግሎት ከሚሰጥባቸው አካባቢዎች መካከል በቅርቡ በተዋቀረው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ያለው የኃይል ፍላጎትና ጥያቄ ከፍተኛ እንደሆነ ገልፀው ጥያቄውን ለመመለስ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በሚዛን ማከፋፈያ ጣቢያ እያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያላቸው ሦስት ወጪ መስመሮችን በማዘጋጀት በሚዛን አማን፣ ምዕራብ ኦሞና ሌቃ በተሰኙ አካባቢዎች ሲነሱ የነበሩ የኃይል ጥያቄዎችን መመለስ እንደታቻለም አቶ ጌታሁን አስታውሰዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ በቅርቡ በሚዛን ቴፒ እና በቦንጋ አካባቢዎች የቀረበውን ተጨማሪ የኃይል ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡
የሚዛን ማከፋፈያ ጣቢያ ካለው አቅም 80 በመቶ የሚሆነው ጥቅም ላይ በመዋሉና የኃይል ጥያቄውን በቀሪው አቅም ለመመለስ አዳጋች በመሆኑ በጣቢው ላይ የማሻሻያ ሥራዎችን ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በሪጅኑ 400 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያላቸው 11 ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚገኙ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለው 263 ሜጋ ዋቱ ብቻ ነው፡፡
የደቡብ ምዕራብ ሪጂን የጋምቤላ እና የደቡብ ምዕራብ ክልሎችን ሙሉ በሙሉ፤ ከኦሮሚያ ሦስት ዞኖችን እንዲሁም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አንድ ዞን እንደሚያካልል ከሪጅኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 22 ቀን 2016 ዓ.ም
15 539
ፕሮጀክቱ ከተለያዩ አካባቢዎች ለመጡ ወጣቶች እና ለሀገር በቀል ሥራ ተቋራጮች የሥራ ዕድል ፈጥሯል
………////………
የመቱ - ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለተውጣጡ ዜጎች እና ለሀገር በቀል የሥራ ተቋራጮች የሥራ ዕድል መፍጠሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ተቆጣጣሪ ገለፁ።
ተቆጣጣሪው አቶ ፍቃዱ ቂጤሳ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ ለአካባቢው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከሚኖረው ፋይዳ ባለፈ ለስድስት የተለያዩ ሀገር በቀል የሥራ ተቋራጮች እና ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለተውጣጡ 140 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል።
ፕሮጀክቱ መላ ኢንጂነሪንግ፣ አብዲ ቦሩ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ፣ ሠላም ኤሌክትሮ ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ፣ ሴሚከን አይሲቲ ሶሉሽን እና ኮንስትራክሽን፣ ሀና ወርቁ ጀኔራል ኮንስትራክሽን እና ኢምፓየር ንግድና ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ለተሰኙ ሀገር በቀል የሥራ ተቋራጮች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም አቶ ፍቃዱ አስታውቀዋል።
የኢምፓየር ንግድ እና ኢንጅነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሳይት ኢንጂነር እና አስተባባሪ አቶ እያየሁ ጌጤ እንደገለፁት በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ መሳተፋቸው በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሥራ ተቋራጮች ተወዳዳሪ እና ሥመ ገናና በመሆን ድርጅቱ በቀጣይ ራሱን ችሎ የሚሰራበትን ዕድል ለማስፋት ያግዛል።
ድርጅቱ የ44 የማስተላለፊያ መስመር የኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎችን የመሰረት እና የተከላ ሥራ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ሥራዎችን በሁለት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ በትጋት እየሠሩ እንደሆነም አመላክተዋል።
ሥራው የጅርጅቱን አቅም በማጠናከር በቀጣይ የሚያከናውናቸውን ሥራዎች በተሻለ ጥራትና በወቅቱ እንዲፈፅም ለመዘጋጀት እንደሚረዳ አቶ እያየሁ ተናግረዋል።
በፕሮጀክቱ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች መካከል አቶ አማረ አንጉሎ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ በአካባቢያቸው ተጀምሮ የሥራ ዕድሉ ተጠቃሚ በመሆናቸው የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ኑሮ እንደቀየረላቸው ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት ሥራ በማጣት በአልባሌ ቦታዎች ይውሉ ለነበሩ የአካባቢው ወጣቶች ፕሮጀክቱ የሥራ ዕድል በመፍጠር የብዙዎችን ህይወት እየለወጠ ይገኛል ብለዋል።
ወጣት ኢሳያስ መኮንን እና አስማማው ደሳለኝ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በፈጠረው የሥራ ዕድል ለመሳተፍ ከሳውላ እና ከቴፒ እንደመጡ ገልፀው ፕሮጀክቱ ከዚህ በፊት ሥራ አጥ ሆነው ይደርስባቸው የነበረውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውሶችን ቀርፎላቸዋል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 21 ቀን 2016 ዓ.ም
15 539
ጣቢያው ከሁለት የኃይል ምንጮች ኃይል መቀበሉ የኃይል መቆራረጥ ችግሮችን አስቀርቷል
………///……..
የመቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከሁለት የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ኃይል መቀበል መቻሉ የኃይል መዋዠቅና መቆራረጥ ችግሮችን እንዳስቀረ የጣቢያው ኃላፊ ተወካይ ገለፁ፡፡
ተወካዩ አቶ ሰይድ አህመድ እንደገለፁት ማከፋፈያ ጣቢያው ከፊንጫ እና ከጊቤ 1 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የወጡ መስመሮችን በበደሌ ማከፋፈያ ጣቢያ በአንድ በማስተሳሰር ኃይል እየተቀበለ ይገኛል፡፡
የሁለቱ ማመንጫ ጣቢያዎች ኃይል በአንድ ከመተሳሰሩ በፊት ጣቢያው ከ2001 ዓ.ም. እስከ 2010 ዓ.ም. ባሉት ዓመታት ከፊንጫ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ብቻ ኃይል ሲያገኝ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡
እንደ አቶ ሰይድ ገለጻ ከፊንጫ ኃይል ሲያገኝ በነበረበት ጊዜ በመስመሩ ላይ የተለያዩ ምክንያቶች ችግሮች ሲከሰቱ በጣቢያው ላይም የኃይል መቆራረጥ ሲያጋጥም ቆይቷል፡፡
በጣቢያው ላይ የሚስተዋለውን የኃይል መዋዠቅና መቆራረጥ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ከጊቤ 1 ማመንጫ ጣቢያ ከሚወጣው መስመር ጋር እንዲገናኝ መደረጉን ተወካዩ አስታውሰዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ጣቢያው ከሁለቱ ማመንጫ ጣቢያዎች ኃይል እንዲያገኝ በመደረጉ የኃይል መቆራረጡን ማስቀረት እንደተቻለም ገልፀዋል፡፡
የመቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከ1970ዎቹ ጀምሮ በዲዝል ጀነሬተር እንዲሁም ከ1984 እስከ 2001 ዓ.ም ባሉት ዓመታት ከሶር የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ኃይል ሲያገኝ መቆየቱን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
የመቱ ማከፋፈያ ጣቢያ 40 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ያለው ሲሆን አሁን ላይ ጣቢያው መስጠት ከሚችለው አቅም እያቀረበ ያለው ግማሽ ያህሉን ብቻ ነው፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 20 ቀን 2016 ዓ.ም
15 539
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
የሥራ መደቡ መጠሪያ - ሾፌር IV
የመመዝገቢያ ቦታ - ኮተቤ ብረታ ብረት ፋብሪካ ፊት ለፊት በሚገኘው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት
ዝርዝር መረጃው ተያይዟል፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 20 ቀን 2016 ዓ.ም
15 539
ጣቢያው ጊዜን ቆጣቢና ችግር ፈቺ የሆኑ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመተግበር አሰራሩን እያዘመነ ነው
………///………
የግልገል ጊቤ 2 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ሥራ ለማዘመን የሚያስችሉ ዘመናዊ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ሹመት በላቸው እንደተናገሩት የጣቢያውን የዕለት ተዕለት ሥራዎች፣ የቁጥጥር ሥርዓቱን እና የቴክኒክ ድጋፍ ሥራዎችን የሚያሳልጡ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
ቴክኒካል የሆኑ የድጋፍ ሥራዎችን በምስል በተደገፈ መልኩ ከሌላ አካባቢ ሆኖ ከርቀት ለመከታተል፣ ከሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር የባለሙያ ድጋፍ ወይም ማማከር ሲያስፈልግ ከቦታው ላይ ሆኖ ድጋፍ ማግኘትና ችግሩን መቅረፍ የሚቻልበት ኦን ኮል ቪዲዮ የተባለ ቴክኖሎጂ በጣቢያው በሙከራ ደረጃ መተግበሩን ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል።
አቶ ሹመት እንዳሉት ቴክኖሎጂው መቆጣጠሪያ ክፍል መሄድ ሳያስፈልግ የትኛውም ቦታ ላይ ሆኖ የጣቢያውን የምርት መጠን፣ የማሽኖችን የሙቀት ሁኔታ፣ የጥገና ሂደትን መከታተልና ያጋጠሙ ችግሮችን በፍጥነት በመለየት ለመፍታት ያስችላል።
በሌላ በኩል በጣቢያው ላይ ከዕቅድ ጀምሮ የመለዋወጫ ዕቃ አቅርቦቱን፣ የዕቃ ግምጃ ቤት አስተዳደርን፣ የመረጃ አያያዝ እና ሪፖርት የማድረግ ስራዎችን የሚመራ ኦን ኬር አሴት ማኔጅመንት ሲስተም በጣቢያው መተግበሩን ገልጸዋል።
በጣቢያው ማሽኖች ላይ ትክክለኛ ያልሆነ ድምጽ ሲሰማ ያለውን ችግር በቀላሉ መለየት እንዲቻልና የጣቢያውን የቁጥጥር ስርዓት ማዘምን የሚያስችል ኦን ኬር አኩስቲክስ የተሰኘ ቴክኖሎጂንም ተግባራዊ መደረጉንም አብራርተዋል፡፡
በጣቢያው በቮይት ኃይድሮ የተጀመሩ አሰራሮችን የማዘመን ፕሮጀክቶች ለመፈጸም የዳታቤዝ ዝግጅት፣ የዳታ ማደራጀት፣ መረጃ የመሰብሰብና የትንታኔ ስራዎች ክንውን፣ የተለያዩ የአይ ሲ ቲ መሳሪያዎች ግዥና ተከላ እና የኦን ላይን ስልጠናዎች በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ 6 ወራት መከናወናቸው ተገልጿል።
ቴክኖሎጂዎቹ በጣቢያው መተግበራቸው አሰራሮች በማዘመን የጣቢያውን አስተማማኝነት መጨመሩን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ ጊዜንና ወጭን ከመቆጠቡም በላይ ችግሮችን ለይቶ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ማስቻሉንም ተናግረዋል።
የግልገል ጊቤ 2 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ዋና ሥራ ተቋራጩ ሳሊኒ ኢምፕሪጂሎ ሲሆን የጀርመኑ ቮይት ኃይድሮ ከኃይል ማመንጫውና ማከፋፊያ ጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ጋር በተገናኘ ያሉ ሥራዎችን ማከናወኑ ይታወቃል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 20 ቀን 2016 ዓ.ም
15 539
የፕሮጀክቱ የኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎች ተከላ በተያዘው ወር መጨረሻ ይጀመራል
…….///……..
የመቱ - ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ተከላ በጥር ወር መጨረሻ እንደሚጀመር የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ ሲኖ ሀይድሮ ኮርፖሬሽን አስታወቀ።
የተቋራጩ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀይማኖት አዳነ እንደገለፁት የማስተላለፊያ መስመሩ በሚያልፍበት አካባቢ ከአካባቢያዊ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ጋር በተያያዘ ተጨማሪ ጥናት እንዲካሄድ በዓለም ባንክ በኩል ምክረ ሃሳብ በመቅረቡ ፕሮጀክቱን በወቅቱ መጀመር አልተቻለም።
70 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ በተያዘለት መርሃ ግብር ለማጠናቀቅ በአራት ንዑስ ሥራ ተቋራጮች ተከፋፍሎ እየተከናወነ እንደሆነ የሳይት ሥራ አስኪያጁ አቶ ሀይማኖት አዳነ ጠቁመዋል።
እንደ አቶ ሀይማኖት ገለፃ የማስተላለፊያ መስመሩ ከሚኖሩት 174 የኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎች መካከል የ75 ምሶሶዎች መትከያ የጉድጓድ ቁፋሮ እና የ67 ምሰሶዎች የመሰረት ተከላ ተከናውኗል።
የኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎችን የተከላ ሥራ ከሁለት ሳምንት በኋላ ለመጀመር ዕቅድ መያዙን የተናገሩት ሥራ አስኪያጁ የመሰረት ሥራውን እስከ ሰኔ 2016 ዓ.ም መጨረሻ እንዲሁም የምሶሶና የገመድ ዝርጋታ ሥራውን ደግሞ እስከ መስከረም 2017 መጨረሻ ለማጠናቀቅ መታቀዱን አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅት የማስተላለፊያ መስመሩ የግንባታ ሥራ 27 በመቶ መድረሱን ጠቁመው ሥራዎችን በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሠረት ለመፈፀም ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመቱ- ማሻ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የሲቪል ሥራዎች ተቆጣጣሪ አቶ ፍቃዱ ቂጤሳ በበኩላቸው በተለያዩ ምክንያቶች የዘገየውን ሥራ በመጀመር እስከ ጥር 2017 ዓ.ም ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
በነባሩ የመቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የማስፋፊያ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ እና በአሁኑ ወቅት ሥራው ከ85 በመቶ በላይ መድረሱንም አመልክተዋል፡፡
ለማስተላለፊያ መስመሩ ግንባታ በዓለም ባንክ የሚሸፈን ከ6 ነጥብ 34 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ እና ከ2 መቶ 97 ነጥብ 78 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቧል።
የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ሲኖ ሃይድሮ በተባለ የቻይና ኩባኒያ እየተከናወነ ሲሆን በአማካሪነት ደግሞ ኢ ኤል ሲ የተባለ የጣሊያን ኩባንያ እየተሳተፈበት ይገኛል፡
የፕሮጀክቱ አካል የሆነው የማሻ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ 79 በመቶ የደረሰ ሲሆን አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ደግሞ 53 በመቶ ደርሷል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 18 ቀን 2016 ዓ.ም
15 539
ጣቢያው ባለፉት 6 ወራት ለማመንጨት ካቀደው በላይ ኃይል አምርቷል
………///………..
የአመርቲ ነሼ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ስድስት ወራት ለማመንጨት ካቀደው የ19 ነጥብ 1 በመቶ ተጨማሪ ኃይል ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ጋሹለ ቁምቢ እንደተናገሩት ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት 112 ነጥብ 97 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዶ 134 ነጥብ 62 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨት ችሏል፡፡
ይህም ከዕቅዱ የ19 ነጥብ 16 በመቶ ወይም የ21 ነጥብ 65 ጊጋ ዋት ሰዓት ጭማሪ ያለው መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡
በግድቡ ውስጥ ያለው የውሃ መጠን በቂ በመሆኑና ተርባይኑ በአስተማማኝ ሁኔታ በመስራቱ ከዕቅዱ በላይ ማሳካት እንደተቻለ ሥራ አስኪጁ ገልጸዋል፡፡
ጣቢያው ያመነጨው ኃይል ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የተወሰነ ቅናሽ ማሳየቱን አቶ ጋሹለ አስታውቀዋል፡፡
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ በጣቢያው የአንዱ ተርባይን ፓወር ትራንስፎርመር ላይ ጥገና ስለሚያስፈልገው ዕቅዱ በአንዱ ዩኒት መመንጨት የሚችለውን ታሳቢ ተደርጎ በመታቀዱ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ6 ነጥብ 18 ጊጋ ዋት ሰዓት ቅናሽ ሊያሳይ ችሏል፡፡
በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 230 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ያነሱት ሥራ አስኪያጁ በግድቡ ያለው የውሃ መጠን በቀጣዮቹ 6 ወራት ለማመንጨት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት በቂ መሆኑንም ተናግረዋል።
ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የአመርቲ ነሼ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ እያንዳንዳቸው 48 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ሁለት ተርባይኖች አሉት፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 17 ቀን 2016 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
