ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 543 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 332,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 157

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 543 名订阅者。

根据 27 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 -16,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.06%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.33% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 895 次浏览,首日通常累积 2 539 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 7

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 28 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 543
订阅者
-1624 小时
-97
+1030
帖子存档
photo content
+6

photo content
+4

የሳፕ ሲስተም በተቋሙ ወጥ የሆነ የአሰራር ስርዓት እንዲኖር እያደረገ ነው ………..///……….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሰራሮችን ለማዘመን እየተተገበረ ያለው የሳፕ ሲስተም በተቋሙ ወጥ የሆነ የአሰራር ሥርዓት እንዲኖር ማድረጉን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ተናገሩ፡፡ የደቡብ 1 ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እንደተናገሩት የሳፕ ሲስተም በሪጂኑ የሚከናወኑ የአስተዳደር፣ የፋይናንስና ተያያዥ ሥራዎች ወረቀት አልባ በሆነ አሰራር እንዲከወኑ በማድረግ ሥራዎችን ከማቀላጠፍ ባለፈ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ እያዳነ ይገኛል፡፡ የምዕራብ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ በቀለ በበኩላቸው የሳፕ ሲስተም ሪጂኑ ከሌሎች የተቋሙ የሥራ ክፍሎች ጋር የሚኖረውን ግንኙነት እንዲጠናከር ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ አሰራሩ ሪጅኑ በሥሩ ከሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ጋር የሚኖረውን የመረጃ ልውውጥ ለማቀላጠፍ ከፍተኛ ሚና መጫወቱን ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ኃይሉ ገለፃ የሳፕ ሲስተም ተግባራዊ ባይደረግ ኖሮ በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ጋር የሚደረጉ ግንኙነቶች ሊቋረጡ የሚችልበት ሁኔታ ይፈጠር ነበር፡፡ የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ በበኩላቸው እየተተገበሩ ያሉ የአሠራር ማዘመን ሥራዎች ተቋሙን ዲጂታላይዝ ለማድረግ እንደሚያግዙ ገልጸዋል፡፡ የአሰራር ሥርዓቱ በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ይስተጓጎል የነበረውን የመረጃ ልውውጥ ለማስቀጠል ከማስቻሉም ባለፈ የተጠያቂነት ሥርዓትን ለመዘርጋት ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡ የማዕከላዊ 1 ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወ/ማሪያም እንደገለጹት ደግሞ የአሰራር ሥርዓቱን ማዘመን ከሪጅኖች ወደ ዋናው መስሪያ ቤት የሚደረጉ ምልልሶችን በማስቀረት ሥራዎችን በተያዘላቸው መርሃ ግብር ለመፈጸም እያገዘ ይገኛል፡፡ እንደ ሪጅን ኃላፊዎቹ ገለፃ በመጀመሪያው ምዕራፍ ተግባራዊ የተደረጉ የሳፕ ሞጁሎች መረጃዎችን በአግባቡ አደራጅቶ ለመያዝ እና በተቋሙ ወጥና ተመሳሳይ የሆነ የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት አስችለዋል፡፡ በሁለተኛው ምዕራፍ የሚተገበረው "የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል" ሙሉ በሙሉ ሥራ ላይ ሲውል በሁሉም ሪጅኖች ወጥ የሆነ የኢንስፔክሽንና የጥገና የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት እንደሚያግዝ አስረድተዋል፡፡ ሥርዓቱ የጥገና ሥራዎች የሚከናወኑበት እና የመለዋወጫ ዕቃዎች የሚገኙበት ሁኔታን በቀላሉ ለማወቅና ለመከታተል እንደሚረዳም አስታውቀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

ግድቡ የጥራት ደረጃውን ጠብቆ እየተከናወነ ስለመሆኑ ተገቢው የቁጥጥርና ክትትል ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ……...///……... የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃ ጠብቆ እንዲከናወን ተገቢው የቁጥጥርና ክትትል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ቡድን መሪ አስታወቁ። የቡድን መሪው አቶ እሸቱ ወርቁ እንደገለፁት የግድቡን የጥራት ደረጃ ለማስጠበቅ ዘመኑ ያፈራቸው የሳይንስና ቴክኖሎጂ የአሰራር ሥርዓቶች ተዘርግተው ተግባራዊ እየተደረጉ ነው። የጥራት ደረጃውን ለማረጋገጥ የሚሰሩ የክትትል ሥራዎች በግንባታ ወቅት የሚፈጠሩ ጉድለቶችን ለመለየትና ለማረም እንደሆነም ነው ቡድን መሪው የገለፁት። በአሁኑ ወቅት የግድቡን የግንባታ የጥራት ደረጃ ለማረጋገጥ ከሥራ ተቋራጩና ከአማካሪ ድርጅቱ ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም ነው የጠቀሱት። በኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የኳሊቲ አሹራንስ ባለሙያ አቶ አረጋ ስለሺ እንደተናገሩት የጥራት ማረጋገጥ ሥራዎች የሚሰሩት ግድቡ በአማካይ ከ50 ዓመት በላይ ኃይል እያመነጨ እንዲቆይ ለማስቻል ነው። በአሁኑ ወቅት የግድቡ ግንባታ በተቀመጠለት የዲዛይንና የጥራት ማረጋገጫ መስፈርቶች መሰረት በከፍተኛ ርብርብ እየተገነባ እንደሆነም ነው አቶ አረጋ ያብራሩት። በስታንቴክ ኢንተርናሽናል የማማከር ሥራዎች የኳሊቲ አሹራንስ ባለሙያ አቶ ታደሰ ሀብቴ በበኩላቸው የግድቡ ግንባታ የጥራት ደረጃውን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ የማማከርና የድጋፍ ሥራዎች እየተሰሩ ነው። በግንባታ ወቅት ለሚፈጠሩ ችግሮች የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅረብ የማማከር ሥራዎች እንደሚሰሩም ነው ባለሙያው ያመለከቱት። እንደ ባለሙያው ገለፃ የሥራ ተቋራጩ የግድቡን ግንባታ ለማስፈፀም ያስቀመጣቸውን የዲዛይንና መሰል መስፈርቶች በማሟላት እያከናወነ ስለመሆኑ ጥብቅ የፍተሻና የሱፐርቪዥን ሥራዎች ይሰራሉ። ለግንባታ ሥራው በሚውሉ ግብዓቶች ላይ የላብራቶሪ ናሙና ምርመራዎች እንደሚደረጉ የጠቀሱት ባለሙያው ይህም የግድቡን የጥራት ደረጃ ለማረጋገጥ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ፕሮጀክቱ ያከናወናቸው ሥራዎች በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ቅቡልነቱ እንዲያድግ አድርጎታል ..........///…….... የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በአካባቢያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ሥራዎች ማከናወኑን የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ምክትል ሥራ አስኪያጁ ኢንጂነር አባይነህ ጌትነት እንደገለፁት የፕሮጀክቱ ግንባታ በአካባቢ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሊፈጥራቸው የሚችሉ አወንታዊ እና አሉታዊ ተፅዕኖዎች ጥናት ተደርጎባቸዋል። ከግድቡ ግንባታ ጎን ለጎን የአካባቢና ማህበራዊ ኃላፊነትን ለመወጣት የሚያስችሉ በርካታ የልማት ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል። በፕሮጀክቱ አካባቢ የሚኖረው ማህበረሰብ በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ የእኔነት ስሜት እንዲኖረው ለማድረግ 30 በመቶ የሥራ ዕድል መመቻቸቱንም ነው ኢንጂነሩ የገለፁት። የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ በበኩላቸው አካባቢው በርካታ የመሠረተ ልማት ችግሮች እንደነበሩበት አንስተዋል። የፕሮጀክቱ ግንባታ ከመጀመሩ አስቀድሞ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ግድቡ በሚያመጣው አወንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖዎች ዙሪያ ውይይቶች መደረጋቸውንም ነው የጠቀሱት። ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ከ85 ኪሎ ሜትር በላይ መንገድና በኦሞ ወንዝ ላይ 175 ሜትር ርዝመት ያለው ድልድይ መስራቱን አቶ ግዛቸው ተናግረዋል። የድልድዩ መገንባት በኦሞ ወንዝ ምክንያት ተራርቀው የቆዩ አጎራባች ወረዳዎችን ከማቀራረቡም በላይ የገበያ ትስስር በመፍጠር የግብርና ምርታማነት እንዲጨምር በር መክፈቱን ገልፀዋል። በፕሮጀክቱ የተገነቡት የውስጥ ለውስጥ መንገዶች፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ እና የጀነሬተር አቅርቦት እንዲሁም የቤተ-እምነት ግንባታዎች ፕሮጀክቱ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ቅቡልነቱ እንዲያድግ ማድረጉን ጠቅሰዋል። እንደ አቶ ግዛቸው ገለፃ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በላይኛውና ታችኛው የኦሞ ተፋሰስ ላይ እየተከሰቱ የሚገኙ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት እያከናወነ ነው። ይሁን እንጂ ለሚደርሱ አሉታዊ ተፅዕኖዎች ምላሽ ለመስጠት የተቋሙ አቅም ውስን በመሆኑ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የቀበሌ አስተዳደሮች እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር እንደሚጠይቅ ነው ሥራ አስኪያጁ ያመለከቱት። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ፕሪሚየር ሊጉን ሊቀላቀል ከጫፍ ደርሷል ........///......... በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ እየተሳተፈ የሚገኘው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ትናንት በተካሄደ 21ኛ ሳምንት ጨዋታ ተከታዩን ኦሮሚያ ፖሊስን በማሸነፍ ጣፋጭ ድል አስመዝግቧል። መርሐግብሩ ሊጠናቀቅ አምስት ጨዋታዎች ብቻ በቀሩት የከፍተኛ ሊግ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግን ለመቀላቀል ሁለት ነጥብ ብቻ ያስፈልገዋል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክን ብቸኛ የማሸነፊያ ጎል ልዑልሰገድ አስፋው 20ኛው ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር የጨዋታው ኮከብ በመሆን ተመርጧል። በሁለቱም ክለቦች በኩል ተመጣጣኝ የኳስ ፍሰት በታየበት በዚህ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በርካታ የጎል ዕድሎችን ከመፍጠር አንፃር ከተጋጣሚው የተሻለ ነበር። ሚያዝያ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከይርጋጨፌ ቡና ጋር የሚጫወተው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ጨዋታውን የሚያሸንፍ ወይም ተከታዩ ኦሮሚያ ፖሊስ ነጥብ የሚጥል ከሆነ አራት ጨዋታ እየቀረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን መቀላቀሉን ያረጋግጣል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ49 ነጥብ እና በ24 ንፁህ ጎል ከተከታዮ ኦሮሚያ ፖሊስ በ14 ነጥብ ርቆ ሊጉን እየመራ ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሚያዚያ 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

በሪጅኑ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ እየተሰራ ነው፤ .........//.......... በሪጅኑ ያለውን የኃይል አቅርቦት አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 1 ሪጂን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወ/ማርያም እንዳስታወቁት በሪጂኑ በሚገኙት በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች የኃይል ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡ የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት የማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግና የማሻሻል እንዲሁም የመቆጣጠሪያ ብሬከሮችን የማዘመን ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በለገጣፎ ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው ትራንስፎርመር የመትከል እንዲሁም በአዲስ ኖርዝ ማከፋፈያ ጣቢያ ደግሞ የማሻሻያ ሥራዎች መጀመራቸውን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡ እንደ አቶ ወንድወሰን ገለፃ በቦሌ ለሚ ማከፋፈያ ጣቢያ እና በለገጣፎ ማከፋፈያ ጣቢያ የኃይል ጭነት ሊያግዝ የሚችል የአቅም ማሳደግ ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በደብረ ብርሀን አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ የተጀመረው የማሻሻያ ሥራ በአሁኑ ወቅት ከ50 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። የደብረ ብርሃን አንድ የማከፋፈያ ጣቢያ የ33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር የብሬከር ቅየራ ሥራ መጠናቀቁን እና የ15 ኪሎ ቮልት ደግሞ እየተከናወነ መሆኑን ዳይሬክተሩ አመልክተዋል፡፡ የገፈርሳ፣ ሆርማት፣ ቤላ እና ሙገር ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የማሻሻያ ሥራ በቀጣዩ የበጀት ዓመት ለማከናወን መታቀዱንም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ ሪጂኑ ከሚያስተዳድራቸው 22 ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል የአዲስ ኖርዝ፣ ቤላ፣ ለገጣፎ፣ ደብረ ብርሃን አንድ፣ ወረገኑ እና ሱሉልታ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኃይል ጭነታቸው በአማካይ 80 በመቶ መድረሱን ጠቁመዋል። በጣቢያዎቹ ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራ ለማከናወን የሲቪል ሥራ ዲዛይንና የዋጋ ግምትን ጨምሮ ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ የማዕከላዊ 1 ሪጂን መሀል አዲስ አበባን ጨምሮ ከአዲስ አበባ በምዕራብ እስከ ሙገር፣ በሰሜን እስከ ገብረ ጉራቻ እንዲሁም በምስራቅ እስከ ደብረ ብርሃን ያሉ አካባቢዎችን ይሸፍናል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሚያዚያ 11 ቀን 2016 ዓ.ም Facebook Log in or sign up to view See posts, photos and more on Facebook.

photo content
+2

የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ 45 በመቶ ደርሷል ---////--- የብሄራዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ደቡባዊ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ 45 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስከያጅ አቶ መሐመድ ሽኩር አስታወቁ። የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ ሽኩር እናዳስታወቁት የፕሮጀክቱ የዲዛይን ሥራ 94 በመቶ፣ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች የማምረት ሥራ 58 በመቶ እና የሲቪል ግንባታ ሥራ 6 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የአምስቱም ሰብስቴሽኖች ዲዛይን ሥራ 92 በመቶ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች የማምረት ሥራ 54 በመቶ እና የሲቭል ግንባታ ሥራ 5 በመቶ ተጠናቋል፡፡ የወላይታ 2ኛ ጣቢያ ማስፋፊያ፣ ሽግዳን አዲስ፣ ጥርጋ አዲስ፣ አርባ ምንጭ 1ኛ ማስፋፊያ እና አርባ ምንጭ 2ኛ አዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ደረጃቸው 43.6 በመቶ መድረሱንም ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ የአርባ ምንጭ 2ኛ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ክፍል እና የትራንስፎርመሮች ማስቀመጫ የመሰረት ቁፋሮ ሥራዎች መጠናቀቁንና የመሰረት ኮንክሪት ሙሌትና ብረት የማቆም ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ የወላይታ 2ኛ ማስፋፊያ ጣቢያ የትራንስፎርመሮች ማስቀመጫ የመሰረት ኮንክሪት ሙሌት መጠናቀቁን፣ ብረት የማቆም ሥራዎች እና የ400 ኪሎ ቮልት ኢሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች የመሰረት ቁፋሮ ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውንም አቶ መሀመድ ተናግረዋል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ የዲዛይን ሥራ 98 በመቶ፣ የአሌክትሮ መካኒካል ዕቃዎችን የማምረት ሥራ 65 በመቶ እና ሲቪል ግንባታ ሥራ 7 በመቶ የደረሰ ሲሆን አጠቃላይ የግንባታ ስራው 46 ነጥብ 4 በመቶ መድረሱንም አቶ መሀመድ አብራርተዋል፡፡ 98 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች የቁፋሮ ስራ እና የ60 ተሸካሚ ምሰሶዎች የኮንክሪት ሙሌት ስራ በባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የተጠናቀቁ መሆናቸውንና ቀሪ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በብሄራዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ደቡባዊ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የደቡባዊ ኢትየጵያን የኃይል መሰረተ ልማት ማስፋፋትና መሻሻል፣ ከኦሞ ስኳር ፋብሪካዎች የሚመነጭን 189 ሜጋ ዋት ትርፍ ኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ብሄራዊ ግሪድ ማስገባት እና በአርባ ምንጭ ዙሪያ ሊገነባ ለታቀደው አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ በቂና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለማስገኘት ተቅዶ የተመሰረተ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑ ይታወሳል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሚያዚያ 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ተቋማችን በምስሉ ላይ በተገለጸው የስራ መደብ ላይ መስፈርቱን የሚያሟሉ የውጭ አመልካቾችን ባሉን ክፍት ቦታዎች ላይ አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈትሩን የ
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ተቋማችን በምስሉ ላይ በተገለጸው የስራ መደብ ላይ መስፈርቱን የሚያሟሉ የውጭ አመልካቾችን ባሉን ክፍት ቦታዎች ላይ አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈትሩን የምታሟሉ አመልካቶች አስፈላጊ የትምህርት ማስረጃችሁን በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው በድርጅቱ ዋና መ/ቤት በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። መልካም ዕድል!

በጣቢያው የነበረውን የኃይል መቆራረጥ ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሥራዎች ተከናውነዋል …..//… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሰሜን ሪጅን የሽሬ ማከፋፊያ ጣቢያን ደህንነት የሚያስጠብቅና የኃይል መቆራረጥን ለማስወገድ የሚያስችል የፓናል ቅየራ ሥራ መከናወኑን የጣቢያው ኃላፊ ተወካይ ገለጹ። ተወካይ ኃላፊው አቶ ሺሻይ ብርሃነ እንደገለጹት በጣቢያው ላይ የነበረው የፓናል ብሬከር በመበላሸቱ ምክንያት ትራንስፎርመሩን በቀጥታ ከባዝ ባር በማገናኜት ያለ ብሬከር ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል። ይህም ለጣቢያው ዕቃዎች ደህንነት ስጋት ከመሆኑም በላይ በአካባቢው ተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥ እንዲያጋጥም ምክንያት ሆኖ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ የፓናል ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት እና አቅምን ለማሳደግ በሰሜን ሪጅን የማከፋፊያ ጣቢያዎች ጥገና ክፍል የአራት ፓናል ቅየራ ሥራ ተከናውኖ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አቶ ሺሻይ ገልጸዋል። የፓናል ቅየራው በሽሬና አካባቢው ያገጥም የነበረውን የኃይል መቆራረጥ በመቅረፍ ተቋሙ ሊደርስበት የሚችለውን ኪሳራ ማዳን እንዳስቻለም አብራርተዋል፡፡ በሰሜን ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ጥገና ቢሮ የኤሌክትሪካል ኢንጅነሪንግ ፕሮቴክሽን ባለሙያ አቶ አባዲ ብርሃኑ በበኩላቸው የፓናል ቅየራው የሲቪል፣ የሜካኒካልና የኤሌክትሪካል ሥራ ሙሉ በሙሉ በሪጅኑ አቅም መከናወኑን ተናግረዋል። እንደ አቶ አባዲ ገለፃ በተቋሙ ባለሙያዎች በአራት ወር የተጠናቀቀው ሥራ በውጭ አካል ቢከናወን ኖሮ እስከ 8 ወር ድረስ ይወስድ ነበር። የአቅም ማሻሻያ ሥራው የደንበኞችን ፍላጎት ታሳቢ ባደረገ መልኩ መከናወኑን እና የቅየራ ሥራው የደንበኞች ኃይል ሳይቋረጥ መጠናቀቁን አስረድተዋል። ሥራው በራስ አቅም መከናወኑ በሠራተኞች መካከል የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር ከማድረጉም በላይ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጭ ማዳን እንዳስቻለ ገልጸዋል። አሁን ያለው ፖወር ትራንስፎርመር በሙሉ አቅሙ እየሰራ በመሆኑ በከፍተኛ የኃይል ጭነት ኃይል ሊቋረጥ እንደሚችል አቶ አባዲ ጠቁመዋል። በመሆኑም በቀጣይ በአካባቢው ያለውን የኃይል ፍላጎት መሰረት በማድረግ የጣቢያውን አቅም የሚያሳድግ ሥራ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። የሽሬ ማከፋፊያ ጣቢያ ሦስት ባለ 15 እና ሦስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አሉት። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

ጣቢያው በ9 ወራት ውስጥ ከአራት መቶ ዘጠና ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል ..........///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2016 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 491 ነጥብ 17 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ማመንጨቱን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ ታፈረ ሞገስ እንደገለፁት ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ለማመንጨት ካቀደው 577 ነጥብ 60 ጊጋ ዋት ሰዓት ውስጥ 491 ነጥብ 17 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማመንጨት የዕቅዱን 85 ነጥብ 04 በመቶ አሳክቷል። እንደ ኃላፊው ገለፃ ጣቢያው በዕቅዱ መስረት ያላመረተበት ምክንያት ግድቡ ከመጠን በላይ ውሃ አጠራቅሞ በመቆየቱ ውሃውን ለመልቀቅ፣ ለብዙ ዓመታት ተከማችቶ የቆየውን አፈርና ድንጋይ ለማውጣት እና በወንዙ ተፋሰስ ከ700 ሜትር-ኪዩብ በላይ የውሃ መሄጃ ቁፋሮ ለመስራት በርከት ያለ ጊዜ በመውሰዱ ነው። በተጨማሪም በተደጋገሚ በመቐለ መስመር በሚፈጠረው መቆራረጥ ተርባይን በሚወጣበት ግዜ በቮልቴጅ ምክንያት ለረጅም ሰዓታት ተርባይን ማስገባት ባለመቻሉ አፈጻጸሙ ዝቅ ማለቱን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ጣቢያው ካሉት አራት ተርባይኖች በሁለቱ ተርባይኖች ኃይል እያመረተ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ታፈረ በቀሪ ወራት በጥገና ላይ ያሉትን ቀሪ ሁለት ተርባይኖች ወደ ሥራ በማስገባት በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የተያዘውን ዓመታዊ ዕቅድ ለማሳካት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። እያንዳንደቸው 75 ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚችሉ አራት ተርባይኖች ያሉት የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 300 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

ጣቢያው በ9 ወራት ውስጥ ከአራት መቶ ዘጠና ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል ..........///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2016 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 491 ነጥብ 17 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ማመንጨቱን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ ታፈረ ሞገስ እንደገለፁት ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ለማመንጨት ካቀደው 577 ነጥብ 60 ጊጋ ዋት ሰዓት ውስጥ 491 ነጥብ 17 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማመንጨት የዕቅዱን 85 ነጥብ 04 በመቶ አሳክቷል። እንደ ኃላፊው ገለፃ ጣቢያው በዕቅዱ መስረት ያላመረተበት ምክንያት ግድቡ ከመጠን በላይ ውሃ አጠራቅሞ በመቆየቱ ውሃውን ለመልቀቅ፣ ለብዙ ዓመታት ተከማችቶ የቆየውን አፈርና ድንጋይ ለማውጣት እና በወንዙ ተፋሰስ ከ700 ሜትር-ኪዩብ በላይ የውሃ መሄጃ ቁፋሮ ለመስራት በርከት ያለ ጊዜ በመውሰዱ ነው። በተጨማሪም በተደጋገሚ በመቐለ መስመር በሚፈጠረው መቆራረጥ ተርባይን በሚወጣበት ግዜ በቮልቴጅ ምክንያት ለረጅም ሰዓታት ተርባይን ማስገባት ባለመቻሉ አፈጻጸሙ ዝቅ ማለቱን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ጣቢያው ካሉት አራት ተርባይኖች በሁለቱ ተርባይኖች ኃይል እያመረተ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ታፈረ በቀሪ ወራት በጥገና ላይ ያሉትን ቀሪ ሁለት ተርባይኖች ወደ ሥራ በማስገባት በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የተያዘውን ዓመታዊ ዕቅድ ለማሳካት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። እያንዳንደቸው 75 ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚችሉ አራት ተርባይኖች ያሉት የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 300 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 09 ቀን 2016 ዓ.ም Facebook Log in or sign up to view See posts, photos and more on Facebook.

photo content
+3