የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
前往频道在 Telegram
5 461
订阅者
-40724 小时
-2 4147 天
-2 42630 天
帖子存档
https://youtu.be/NPfZYeC9Rvg?si=T2O0iYiz-j6-KX1_
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ አክሲዮን ማህበር አደራጅ ኮሚቴ በቅርቡ ምሥረታውን እውን እንደሚያደርግ አስታወቀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አነስተኛ የፋይናንስ ሥራ አዋጅ ቁጥር 626/2001 (በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1164/2012) ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ለማቋቋም የሚፈቅድ መሆኑን በመመርኮዝ በመከላከያ ሠራዊት ፋዉንዴሽን አስተባባሪነት ባሳለፍነው ዓመት የካቲት ወር ጀምሮ የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም የአክሲዮን ሽያጪ እየተከናወነ ይገኛል።
የአድዋ ድል አክሲዮን ማህበር አደራጅ ኮሚቴ ፀሃፊ አቶ ያለው መኮነን ባለቤትነቱ የመከላከያ ሠራዊት የሆነውን የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ አክሲዮን ማህበር ለመመሥረት ባለፉት ስምንት ወራት ለመሠብሰብ ከታሠበው ሁለት ቢሊዮን ብር 88% ማሳካት መቻሉንና 39.600 የአክሲዮን ሽያጪ መከናወኑን ገልፀዋል።
በዋነኝነት የአደራጅ ኮሚቴው ከሚመለከተው የባለድርሻ አካላት ጋር የአክሲዮን ማህበሩን በቅርብ ጊዜ ለመመሥረት እየሠራ መሆኑን የገለፁት አቶ ያለው የአክሲዮን ሠነዶችን አሟልቶ ማቅረብ ላይ እየታዩ ያሉ ክፍተቶች በተሎ እንዲሟሉም ጠይቀዋል።
የአክሲዮን ማህበሩ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዲዳ ሁንዴ የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ለመመሥረት የሚያበቃው ከፍ ያለ ካፒታል መያዙን ፣ ብሄራዊ ባንክ የሚጠይቀውን መሥፈርት ማሟላት መቻሉን ገልፀው ሠነድ የማሠባሠብ እና የማጣራት ብሎም ኦዲት የማድረግ ሥራ እየተካሄደ እንደሚገኝ አሥረድተዋል።
ከአክሲዮን ማህበሩ ምስረታ ጋር ተያይዞ የአደረጃጀት እና ሌሎች መመሪያዎችን የማዘጋጀት የማጠናቀቅ እና ሥራ ላይ የማዋል ቀሪ ሥራዎች በሂደት ተግባራዊ እንደሚሆኑም ተናግረዋል።
የአድዋ ድል አክሲዮን ማህበር ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ ኮሎኔል ያዴሳ ገላ በበኩላቸው አብዛኛው የአክሲዮን ሽያጩ መከላከያ ሠራዊቱ በባለቤትነት መግዛቱን እና ተቋሙም ሠራዊቱ ተጠቃሚ መሆን እንዲችል ማመቻቸቱን ገልፀው የአክሲዮኑን ሠነድ ማቅረብ ላይ ክፍተቶች መኖራቸውን እና ወኪሎች በአጭር ጊዜ ሠነድ ማሥገባት እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል።
የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ እና ቀሪ ሥራዎችን ለማፋጠን የህግ ሙያተኞች ህጋዊ ውክልና ወሥደው ከሠራዊቱ ተወካዮች ጋር እየሠሩ መሆናቸውንም ገልፀዋል።
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
+1
በሰሜን ሸዋ ዞን ሀገረ ማሪያም ከሰም ወረዳ ከህብረተሰቡ ጋር ውይይት ተደርጓል።
የኮማንዶና አየር ወለድ እዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ሽማ አብደታ እና የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ በተገኙበት ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም በሚል መሪ ቃል በሀገረማሪም ከሰም ወረዳ ከሚገኙ ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተካሂዷል።
ሌተናል ጀኔራል ሹማ አብደታ ሰላም ለሁሉም አስፈላጊ ነው የአማራ ህዝብ በጣም ታላቅ ህዝብ ነው አሁን የተፈጠረውን ፅንፈኝነት ተከትሎ ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራው ፅንፈኛ ቡድን የአማራን ህዝብን አየዘረፈ ፣ እያዋረደ እና እየገደለ ይገኛል ብለዋል።
ይህን ተግባር እንዲፈፅም በከፍተኛ ደረጃ እየደገፉ ያሉ የከተማው ነጋዴዎች እና በመንግስት መዋቅር ውስጥ የተሰገሰጉ እንዳሉ ይታወቃል እነዚህን የመልቀም እና ለህግ የማቅረብ ሰራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በመቀጠልም ጫካ ያለው ሀይል መደራደር የፈለገ በግልም ይሁን በቡድን በመረጠው ቦታ መደራደር ይችላል ፤ አልደራደርም ለሚለው ቡድን የመደምሰስ ሰራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሽ አለማየሁ በሰሜን ሽዋ ዞን የተሰማራው ፅንፈኛ ሀይል እየዘረፈ እና እየገደለ ለመክበር ያቀደ ነው ለማሳያነትም ከ15.000 ኩንታል በላይ ለገበሪው ሊደርስ የነበረ ማዳበሪያ ተዘርፏል በርከት ያሉ ህፃናት ፣ ሴቶች እና ባለሀብቶች ታግተው ብር ተሰብስቦላቸዋል በክልሉ በርካታ አመራሮች በዚሁ ከሀዲ ቡድን ተገለዋል ለገዛ ወገኑ እንኳን የማያዝን አረመኔ መሆኑን ላለፈው አንድ አመት አይተናል ሲሉ ተናግረዋል ።
ተወያዮች ጫካ የሚገኘው ፅንፈኛ ሀይል የኛው ልጅ ነው መክረን ለመመለስ እና ለማስታረቅ እንሰራለን ከዛ ካለፈ ግን ከሰራዊቱ ጎን እንቆማለን እንታገለዋለን ሲሉ ሃሳባቸውን ሰጥተዋል። ዘገባው የኮማንዶ ክፍለጦር ነው።
"እንዳይደገም ሁሌም እንዘክራለን!" ችግሮችን በከፍታ ተመልካች፤ ፀረ ኢትዮጵያን በፅናት መካች፦
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 24 ቀን 2017 ዓ.ም
አንዳንድ ያልተገቡ ተግባራት የሀገርን ቅስም
እስከመስበር የሚዘልቅ መራር ሀዘን ጥለው የሚያልፉ ይሆናሉ።
የጥቅምት 24ቱ የሰሜን ዕዝ ጥቃት ሲታወስ ገላጭ ቃል ቢጠፋ አይገርምም።
ከጥቃቱ በኀላም እንደሀገር የደረሰብን የታሪክ ስብራት መጥፎ አሻራው አሁንም ጎልቶ ይታያል።
ዋነኛው ጉዳይ ግን ያለፈን ቁስል በቂም በቀል ስሜት በቁስል አካኪነት ማላዘን ሳይሆን ዳግም በኢትዮጵያ ሰማይ ስር "እንዳይደገም" ከስህተት መማሩ ነው ለሀገርም ለመላው ዜጋም ጥቅም አስገኚ የሚሆነው።
ታዲያ "እንዳይደገም" ሲባል ነገሩን ከነአካቴው መርሳት አይደለም።ምክንያቱም ብዙዎች ያለቁበት መዘዙም ወደለየለት ጦርነት አምርቶ በሰላም እስኪቋጭ በደሃ አቅማችን ክቡሩን የወገን ህይወት እስከጥሪት ለእሳት የዳረገብን ነውና አስታውሰን ልንማርበት ግድ ይለናልና ነው።
እናም ታዲያ ዘንድሮ በመላው ሰራዊታችን የጥቅምት 24ቱ የሰሜን ዕዝ ጥቃት ሲታወስ ድርጊቱ እንዲፈጸም ገፊ ምክንያት የሆኑ የስህተት መንገዶችን ማሰብ ቀዳሚው ነው።
የስህተት መንገዱ ከታወቀ በኃላ ደግሞ ይህንን የስህተት መንገድ ዳግም ማንም ማለፍ እንዳይችል አድርጎ ጥርቅም አድርጎ መዝጋት።
የስህተት መንገዱ ምንድነው ያልን እንደሆነ...
ሠራዊት የሚደራጀው የሀገርን ሉዓላዊነት ከየትኛው ጥቃት በመከላከል፣ሀገራዊ ብሄራዊ ጥቅምን በዘላቂነት መጠበቅና ሀገርን አፅንቶ ማስቀጠል ነው።
ይህንን ለማከናወን ደግሞ የውትድርና ፕሮፌሽናሊዝም መርህ ላይ ጸንቶ መቆም ግድ ይላል።የውትድርና ፕሮፌሽናሊዝም ወሳኝ መርህ ደግሞ ከሀገር ብሄራዊ ጥቅምና ህገ-መንግስታዊ ተልዕኮ ውጭ ከብሄርና የፖለቲካ ብሎም ሌሎች ውግንናዎች ነጻ የመሆን ወሳኝ ጉዳይ ነው።
የጥቅምት 24 የሰሜን ዕዝ ጥቃትን የወለደው ታዲያ የውትድርና ፕሮፌሽናሊዝም መርህን አሽቀንጥረው በጣሉ፣በሰንደቅ ዓላማቸው ፊት የገቡትን ቃል-ኪዳን የሻሩ፣ከሀገር ይልቅ ለብሄርና ፓለቲካ ውግንና በተገዙ ሰራዊቱን ክደው በገዛ ጓዳቸው ነፍጥ ባነሱ አካላት መሆኑ ይታወቃል።
እናም በተቋም ደረጃ ዘንድሮ ጥቅምት 24 ሲታሰብ ገለልተኝነት በውትድርና ሞያ የማይጣስ ቀይ መስመር መሆኑን በአንክሮ በማጤንና ሠራዊቱም በዚህ ቁልፍ መርህ እየተገነባ መሆኑን በደንብ በማሳየት ጭምር ነው። የማይደገመው ይህ ሲሆን ነውና።
ሠራዊቱ የዘንድሮውን የጥቅምት 24 አሳዛኝ ክስተት አስቦ ሲውልም "ችግሮችን በከፍታ እየተመለከተ፤ ጸረ-ኢትዮጵያን በጽናት በመመከት የጋለ ሞራል ነው።ሁሌም ሀገርን ባስቀደመ ገለልተኝነት ጽኑ ቃል-ኪዳን።
በአስቻለው ሌንጫ
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
ፅንፈኛው ቡድን በምንም መመዘኛ ቢለካ ለአማራ ህዝብ ጥቅም የሚሆን አንግቦ የተነሳው ዓላማም ሆን ዕቅድ የለም
ሌተናል ጄኔራል በላይ ስዩም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም
በደቡብ ወሎ ዞን፣ ደሴ እና ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር 3ኛ ዙር የብልፅግና አመራሮች ስልጠና ማጠቃለያ በመገኘት ፅንፈኛውን የማፅዳት ዘመቻው ያለበትን ሂደት እና በቀጣይ ከሁሉም አመራሮች ምን ይጠበቃል የሚለውን የቀጣይ ሥራ በተመለከተ የመከላከያ ዘመቻ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል በላይ ስዩም ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ፅንፈኛውን በተመለከተ የተሟላ መረጃ ሊኖር እንደሚገባ ይህ ሃይል በህዝብ ላይ በተቋማት ላይ የሠላም ፀር መሆኑን በግልፅ እያሳዬ የሚፈፅመውን እኩይ ተግባር ማወቅ አስፈላጊ እንደሆነም ገልፀዋል።
ለህዝብ ተመራጭ የሆኑ አመራሮች ለመረጣችሁ ህዝብ ታማኝ እና መስዋዕትነት ጭምር ለመክፈል ቁርጠኛ መሆናችሁን በምትሠሩት ሥራ ማረጋገጥ አላባችሁ ያሉት ሌተናል ጄኔራል በላይ ያለ ሠላም ምንም ነገር እንደሌለ ተረድታችሁ ለሠላም መሥራት ይገባችኋል ነው ያሉት።
ፅንፈኛው ቡድን በምንም መመዘኛ ቢለካ ለአማራ ህዝብ ጥቅም የሚሆን አንግቦ የተነሳው ዓላማም ሆን ዕቅድ የሌለው ዘራፊ ቡድን መሆኑን በግልፅ መረዳት እንደሚያሥፈልግም አንስተዋል።
የፖለቲካ አመራሩ እና መከላከያ ሠራዊቱ በመቀናጀት ህዝብን ደጀን ሊያደርጉ የሚችሉ ስራዎችን በመስራት ዞኑን ብሎም ክልሉን ከዚህ ዘራፊ እና ፅንፈኛ ቡድን ነፃ ማውጣች ለነገ የማይባል ስራ አድርጎ ለለውጥ መሥራት ውጤት ላይ መድረስ ህዝብን ማሳተፍ ተገቢ መሆኑን አመላክተዋል።
በማጠቃለያው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር አብዱ ሁሴን ብርጋዲየር ጀኔራል ዘውዱ ሰጥአርጌና የሠራዊቱ እና ስቪል አመራሮች ተገኝተዋል። መረጃውን ያደረሠን የመከላከያ ዘመቻ ዋና መምሪያ ነው።
በኮምቦልቻ ሪጅኦፖሊታን ከተማ አስተዳደር ከልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር የሰላም ኮንፈረንስ ተካሄደ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም
በኮምቦልቻ ሪጅኦፖሊታን ከተማ አስተዳደር ከሃይማኖት አባቶች፣ ከሃገር ሽማግሌዎች፣ ከወጣቶች እንዲሁም ከልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከተውጣጡ ሲቪል ማህበረሰብ ጋር የሰላም ኮንፈረንስ ተካሂዷል።
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት አፈጉባኤ ክብርት ወይዘሮ ፈንቱ ተስፋዬ በቀዳሚነት ስለዕለቱ የሰላም ኮንፈረንስ እና ከኮንፈረንሱ ስለሚጠበቁ ውጤቶች እንዲሁም ዓላማውን በተመለከተ ማብራሪያ ሠጥተዋል።
ሠላም ወዳዱ የኮምቦልቻ ከተማ ነዋሪ ለሠላም ቅድሚያ በመሥጠት በርካታ የልማትና የሠላም አጋዥ ሥራዎችን ሲሠራ መምጣቱን የገለፁት አፈጉባኤዋ ያለ ሠላም ምንም አይነት ሥራ ሊሠራ እንደማይችል ሁሉም ተገንዝቦ የሠላም እጁን መዘርጋት አለበት ነው ያሉት።
አሁን በተጨባጭ በከተማው ያለው ሰላም ምን ደረጃ ላይ ነው፣ ሰላማችንን ሁሌ አንፃራዊ እያልን የምንቀጥለው እስከመቼ ነው፣ አንፃራዊ ሰላምን ወደ ዘላቂ ሰላም ለማሸጋገር መንግስትና ህብረተሰቡ እንዴት ተቀናጅተው ቢሰሩ ይሻላል የሚሉት መሠረታዊ ነጥቦች በወይዘሮ ፈንቱ ተስፋዬ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን መግባባት ላይም ተደርሷል።
የመከላከያ ዘመቻ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል በላይ ስዩም የፅንፈኛውን ሃይል ድርጊት በደንብ መረዳትና መገንዘብ እንደሚያሥፈልግ፤ ፅንፈኛውን እየመሩ ያሉ መሪዎች ለአማራ ህዝብ ይህ ነው የሚባል የሰሩት ስራ አለመኖሩን፤ ይልቁንም በተለያዬ ጊዜ አጋጣሚውን በመጠቀም የግል ሃብት ማካበቻ ያደረጉ ዘራፊዎች መሆናቸውን ተናግረዋል።
ይህ ዘራፊ ቡድን በሰራዊታችን ላይ ይቅር የማይባል ግፍ ፈፅሟል የአማራ ክልሉ ህዝብም ማን ምን እንደሰራ በግልፅ ያውቃልና ይህን የሠላምና የልማት ፀር የሆነ ቡድን ለህግ ማቅረብና መደምሰስ የሁሉም ሃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ ሌተናል ጄኔራል በላይ ገልፀዋል።
ተሳታፊዎች በበኩላቸው ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት የአካባቢውን ሰላም ለማስፈን እየከፈለ ያለው የህይወት መስዋዕትነት በታሪክ የማይረሳ መሆኑን ገልፀው የከተማው ማህበረሰብ እና የከተማው አመራር ላቅ ያለ ክብር እንደሚሰጠው ተናግረዋል። በማንኛውም ጊዜ ከመከላከያ ሠራዊቱ እና ከፀጥታ ሃይሉ ጎን ተሠልፈው ሠላማቸውን እንደሚያረጋግጡም ተናግረዋል።
በዕለቱ "የፅንፈኞች ሴራ" የተሰኘው ዶክመንታሪ ፊልም ለእይታ የበቃ ሲሆን የሰላም ኮንፈረንስ ተሳታፊዎች ከዶክመንተሪ ፊልሙ በመነሳት ፅንፈኛው ሃይል የፈፀመውን እና በመፈፀም ላይ ያለውን እኩይ ተግባር በግልፅ እንዲረዱ ተደርጓል። መረጃውን ያደረሰን የዘመቻ ዋና መምሪያ ነው።
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
#EthiopianAirlines🇪🇹
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመታዊው APEX Passenger Choice Awards 2025፣ ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ “ Best Overall in Africa award ” ሽልማት ማሸነፉን አሳውቋል።
አየር መንገዱ ፦
🛫 በምርጥ የበረራ ላይ መስተንግዶ፣
🛫 በምርጥ የበረራ ላይ መዝናኛ አገልግሎት፣
🛫 በምርጥ የበረራ ላይ የምግብ እና መጠጥ አገልግሎት፣
🛫 በምርጥ የአውሮፕላን ውስጥ መቀመጫ ምቾት
🛫 በምርጥ የበረራ ላይ ገመድ አልባ ኢንተርኔት አገልግሎት ዘርፎች ከአፍሪካ ምርጡ አየር መንገድ በመሆን ተሸልሟል።
ይህ በ “ Airline Passenger Experience Association ” (APEX) የመንገደኞችን ድምፅ መሰረት በማድረግ ለአየር መንገዶች ዕውቅና የሚሰጥበት ነው።
በአቪዬሽን ኢንደስትሪውም ትልቅ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሽልማቶች አንዱ እንደሆነ አየር መንገዱ ገልጿል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ኢትዮጵያ በብሪክስ ጉባኤ በሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ሚዛናዊ አቋም አሳይታለች - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር
**
ኢትዮጵያ በብሪክስ ጉባኤ በሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ያላትን ሚዛናዊ አቋም በግልጽ ማሳየቷን በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴሬክሂን ተናግረዋል፡፡
አምባሳደሩ ሀገሪቱ በጉባኤው ላይ ብሔራዊ ጥቅሟን የሚያስጠብቁ ኃሳቦችን ማንጸባረቋንም ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ በብሪክስ ያላት ተሳትፎ ለጋራ ዕድገት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴሬክሂን ጠቁመዋል፡፡
የሀገሪቱ የብሪክስ ተሳትፎ ከምጣኔ ኃብታዊ ዕድገት ባሻገር ለህብረቱ ዓላማ መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ከሰሞኑ በሩሲያ ካዛን ከተማ የተካሄደው 16ኛው የብሪክስ ጉባኤ ፍትኃዊ የዓለም ሥርዓት መፍጠር የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
የኢፌዲሪ መከላከያ ሠራዊት
👉ኢትዮጵያ ከዛሬ 117 ዓመታት በፊት ጥቅምት 15/1900 ዓ.ም የጦር ሚኒስቴር አቋቋመች
👉በዚህም ጥቅምት 15 የሠራዊት ቀን ሆኖ ይከበራል
👉ሠራዊቱ በኃይልም በአደረጃጀትም እያደገ የመጣ ነው
👉የሠራዊቱ አባላት ሀገርን ያፀኑ ዳር ድንበርን ያስከበሩ ጀግኖች ናቸው
👉ሠራዊቱ የሀገር መፅናት ምልክት ነው
👉ሕይወቱን እየገበረ ሰላምን የሚያፀና ነው
👉የሀገር ብልፅግናን ባልተቋረጠ መንገድ እውን ያደርጋል
👉ሠራዊቱ የአንድነት ምልክት፤ ከየትኛውም ፖለቲካዊ ውግንና የፀዳ ነው
👉የሰላም ምንጭና የሀገር ጠባቂ ነው
👉ታሪክ ጠገብና በትውልድ ቅብብሎሽ እየተገነባ የመጣ ነው
#የመከላከያ_ሠራዊት_ቀን
#ኢትዮጵያ
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
ኢራን የአሜሪካን ደህንነት ሰብራ የሞነቸፈቺው መረጃ በጣም ጨዋታ ቀያሪ ነው።
👉ይህ የደህንነት መረጃ እስራኤል ኢራንን እንደት ማጥቃት እንዳለባት ፤ ምን አይነት ጥቃት መፈፀም እንዳለባት ፤ የትኞቹን የኢራን ኢላማዎች መምታት እንዳለባት ፤ ኢራንን ለማጥቃት ኑክሌየር መጠቀም አለመጠቀሟን ፤ አሜሪካና አጋሮቿ ምን አይነት የማጥቃትና የመከላከል እገዛ ለእስራኤል ማድረግ እንዳለባቸው የሚያትት ሰፊ የስለላ መረጃ ነው የኢራን ሀከሮች ሰብረው በመግባት የሞነቸፉት።
👉ይህ መረጃ የሚቀመጠው አምስት አይኖች " Five eyes" በሚል ጥምረት በሚታወቁት በአሜሪካ ፤ እንግሊዝ ፣ ካናዳ፣ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ ብቻ ቢሆንም ኢራን በርብራ ሰብራው ገብታለች። የጠላቶቿን እቅድም በሙሉ አግኝታዋለች።
👉በዚህ የተደናገጡት አሜሪካና እስራኤል በከፍተኛ ሁኔታ አደገኛ ክስተት ነው የተከሰተው ያሉ ሲሆን ጉዳዩን እያጣሩ መሆኑን ገልፀዋል።
👉የሆነው ሆኖ የጠላትን እቅዶች ማግኘት እጅግ ትልቅ ድል ነውና ኢራን አሳክታዋለች።
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
