ch
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

前往频道在 Telegram

Addis abeba Ethiopia

显示更多
5 204
订阅者
-11024 小时
-1 9137
-2 77030
帖子存档
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጳጉሜ 04 ቀን 2015 ዓ.ም የሀገር ወዳዱ ቤተሠብ የውትድርና ህይወት ሃምሳ አለቃ መሠረት አበበ ትባላለች። በመከላከያ ሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት የሚዲያ አባል ናት ወደ ውትድርናው አለም የተቀላቀለችው በ2005 ዓ.ም ነው። ለሀገሯ እና ለህዝቧ ሠላም ዕውን መሆን እስከ ህይወት መሥዋዕትነት ለመክፈል በሠንደቅ ዓላማዋ ፊት ቃለ መሃላ ፈፅማ መለዮ ከለበሰች 11 ዓመታትን አሥቆጥራለች። አንዳንዴ ውትድርን በቤተሠብ ደረጃ የሚወራረስ ነው የሚሉ ሠዎች እንዳሉ እንሠማለን፤ በሌላ በኩል ደግሞ አይ አይደለም ለሀገር እና ለህዝብ ሠላም ብሎ  በራስ ፍላጎት የሚወሠን የተከበረ ሙያ ነው ብለው የሚሞግቱ ሠዎች እንዳሉም አጋጥሟችሁ ይሆናል። ሁለቱም አባባሎች ምንም አይነት ሥህተት የላቸውም።  ውትድርና ለሀገር ሉዓላዊነት መከበር ለሠንደቅ ዓላማ ከፍታ ለሀገር ዕድገት እና ለመላው ህዝብ ሠላም መከበር ሲባል ራስን አሣልፎ የመሥጠት የተከበረ እና የተወደደ ሙያ መሆኑ ሁሉንም ያሥማማል። የሃምሳ አለቃ መሠረት አበበ ታሪክም ይህንኑ እውነታ የሚያረጋግጥ ነው። ከስድስት በላይ ቤተሠቦቿ በውትድርና ህይወት ሀገርን እያገለገሉ የመጡ ናቸው። አባቷ ብርጋዲየር ጄኔራል አበበ ገብረህይወት እና እናቷ ምክትል መቶ አለቃ ዳሳሽ አዲስ ቀደም ሲል በነበረው ሥርዓት የኢትዮጵያ ሠራዊት ሆነው ሀገራቸውን ያገለገሉ ናቸው። ብርጋዲየር ጄኔራል አበበ እስከ ኮር አመራርነት ድረስ ተመድበው የመሪነት ሚናቸውን የተወጡ ሥለመሆናቸው እና በ1991 ዓ.ም ህይወታቸው እንዳለፈ ልጃቸው ሃምሳ አለቃ መሠረት ትናገራለች። ለወላጆቿ ልዩ ፍቅር እንዳላት እና በካምፕ ውስጥ ተወልዳ እንዳደገች የምትናገረው መሠረት አሁንም ለእናቷ ምክትል መቶ አለቃ ዳሳሽ ያላትን ፍቅር ከፊቷ በሚነበብ አንዳች ስሜት ታሥረዳለች። ታናሽ ወንድሟ ቢኒያም አበበ እና ባለቤቷ ሌተናል ኮሎኔል ጌታሁን አሠፋ አሁንም የመከላከያ ሠራዊት አባል ሆነው በተመደቡበት ቦታ ተልዕኳቸውን በውጤት እየፈፀሙ ይገኛሉ። ውትድርና ፈቅደው ወደው መተኪያ የሌላትን ህይወት ለሀገር ለሠንደቅ ዓላማ ክብር እና ለህዝብ ሠላም ሲሉ አሣልፎ የመሥጠት የተከበረ ሙያ ነው። ሥለሆነም ሃምሣ አለቃ መሠረት እና ቤተሠቦቿ ማለትም አባቷ፣ እናቷ፣ ታናሽ ወንድሟ፣ ባለቤቷ እንዲሁም ራሷ የመከላከያ ሠራዊት አባል ሆነው የኢትዮጵያን ሠላም ለማረጋገጥ በውትድርናው ሙያ መሠለፋቸው ሁሌም ቢሆን ያሥደሥተኛል ስትል ወኔ በተሟላበት አነጋገሯ ገልፃልናለች። እኛም ባለታሪኳን ሃምሳ አለቃ መሠረት አበበን እያመሠገን የሀገር ወዳዱ ቤተሠብ የውትድርና ህይወት ለሌላውም አርአያ እንደሚሆን በማመን 2016 ዓ.ም ለመላው ቤተሠቡ የሠላም የጤና የደሥታ እንዲሆንላቸው በዝግጅት ክፍላችን ሥም መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን ። መልካም በዓል። በውብሸት ቸኮል

#G20 አፍሪካ ህብረት " ቡድን 20 " ን በቋሚ አባልነት መቀለቀሉን ተከትሎ የቡድኑ ዝርዝር ይህን ይመስላል። 🇦🇷 አርጀንቲና 🇧🇷 ብራዚል 🇨🇦 ካናዳ 🇨🇳 ቻይና 🇫🇷 ፈረንሳይ 🇩�
#G20 አፍሪካ ህብረት " ቡድን 20 " ን በቋሚ አባልነት መቀለቀሉን ተከትሎ የቡድኑ ዝርዝር ይህን ይመስላል። 🇦🇷 አርጀንቲና 🇧🇷 ብራዚል 🇨🇦 ካናዳ 🇨🇳 ቻይና 🇫🇷 ፈረንሳይ 🇩🇪 ጀርመን 🇮🇳 ህንድ 🇮🇩 ኢንዶኔዥያ 🇮🇹 ጣልያን 🇯🇵 ጃፓን 🇰🇷 ደቡብ ኮሪያ 🇲🇽 ሜክሲኮ 🇷🇺 ሩስያ 🇸🇦 ሱዑዲ አረቢያ 🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ 🇹🇷 ቱርክ 🇦🇺 አውስትራሊያ 🇬🇧 ዩናይትድ ኪንግደም 🇺🇸 አሜሪካ 🇪🇺 አውሮፓ ሕብረት 🌍 #አፍሪካ_ሕብረት

👉 የኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ ወታደራዊ ትብብሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ‼️--ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የኢትዮጵያ እና ደቡብ አፍሪካ ወታደራዊ ትብብሮችና የልምድ ልውውጦች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ፡፡ ማርሻል ብርሃኑ ከልዑካን ቡድናቸው ጋር በደቡብ አፍሪካ የነባራቸውን የስራ ጉብኝት አጠናቀዉ ወደ አገር ቤት ተመልሰዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በበኩላቸው የሁለቱ አገራት ግንኙነት ረዥም ዘመናትን ያስቆጠረና ታሪካዊ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካ የነጻነት ታጋዮችና አመራሮች ስልጠናና ድጋፍ የሰጠች መሆኑ ጠቁመዋል። የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በብቃት በማስተናገድ ላደረገችው ትብብር ምስጋና አቅርበው በቀጣይም ወታደራዊ ትብብሮችና የልምድ ልውውጦች በዚህ ጠንካራ መሰረት ላይ በመመስረት ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። የደቡብ አፍሪካ የመከላከያ ሰራዊት ዋና አዛዥል ሩድዛኒ ማፍዋንያ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ አፍሪካዊያን ነጻ እንዲወጡ ፈር ቀዳጅና እገዛ ያደረገች መሆኗን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ወታደራዊ ትብብሮችንና የልምድ ልውውጦችን በማጠናከር ትብብሩን የላቀ ደረጃ ለማድረስ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል። የልዑካን ቡድኑ በቆይታዉ የልዩ ኃይል ማሰልጠኛ ማዕከል በመገኘት ዘመናዊ የአየር ኃይል አዉሮፕላኖችንና የልዩ ኃይል አደረጃጀቶችንና ትጥቆችን ጎብቷል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከደቡብ አፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትር ታንዲ ሞዲሴ፣ ከመከላከያ ሰራዊት ዋና አዛዥ ጄነራል ሩድዛኒ ማፍዋንያ፣ ከአየር ሃይልና ልዩ ኃይል ዋና አዛዦች፣ የጦር መሳሪያ እና ቴክኖሎጂ ላይ ከተሰማሩ ኩባንያዎች አመራሮች ጋር መክረዋል፡፡ የልዑካን ቡድኑ የአፓርታይድ ሙዚየምና ኔልሰን ማንዴላ ከመታሰራሳቸው በፊት ይኖሩ የነበረበትን ታሪካዊ መኖርያ ቤት ጎብኝቷል። በሙዚየም ውስጥ የሚገኘውን ኢትዮጵያ ለኔልሰን ማንዴላ የሰጠችውን  ሽጉጥና የኢትዮጵያ ፓስፓርትን መመልከታቸው ከደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ #የኢትዮጵያ_ክንድ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጳጉሜ 02 ቀን 2015 ዓ.ም በጀግኖች ሰማዕታት ደም ደምቃ በአፅማቸው ፍላፃ የተማገረች ሀገር ኢትዮጵያ!! ሀገራችን ኢትዮጵያ ሉአላዊነቷን ለመጋፋት ፤ ክብሯን ለመግፈፍ እና  የተፈጥሮ ሀብቷን ለመዝረፍ በተለያዩ ዘመናት  የመጡትን የውጭ ወራሪዎችን ተከላክላ  የቆየችው  በውድ  ልጆቿ  ክቡር  መስዋዕትነት ነው። ኢትዮጵያ የድል ቀን እንጂ ነፃ የወጣችበትን ቀን የማታከብረው በየዘመናቱ በተከፈለ የልጆቿ ውድ  መስዋዕትነት ነው። ኢትዮጵያ የጀግኖች ሀገር ነች። ጀግኖች ደግሞ ላመኑበት ነገር መስዋዕትነት ለመክፈል የቆረጡ ናቸውና ሀሌም ሲዘከሩና ሲታወሱ ይኖራሉ። ..አድዋ ዛሬ ናት አድዋ ትላንት   መቼ ተረሱና የወዳደቁት... በማለት የጀግኖችን አይረሴነት ያወሳችው ድምፃዊቷም  ለሀገራቸው ሲሉ በጀግንነት የወደቁ  ጀግኖች ሲዘከሩ እንደሚኖሩ ለማሳየት ነው። የመስዋዕትነት ቀን ሲዘከር በየዘመኑ ለሀገራቸው ክብርና ሉአላዊነት በክብር የወደቁት እያሰብን ብቻ ሳይሆን  ዘመኑ የሚጠይቀውን መስዋዕትነትም ለመክፈል የተዘጋጁ እልፍ ጀግኖች በፅናት መቆማቸውን በተግባር በታየበት ወቅት ላይ ሆነን ነው፡፡ የዘመኑም ትውልድ ለሀገሩ ያለውን ፍቅርና ክብር በተግባር አረጋግጧል፡፡ ለሀገር ሰላም አንድነትና ክብር ከጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን ጎን በመሰለፍ መላው ህዝባችን ያደረገውና እያደረገው የሚገኘው ድጋፍም የመስዋዕትነቱ አካል ነው፡፡ ሀገራችንን ለማፍረስ ካልሆነም ደካማ የሆነች ሀገር እንድትሆን ቀን ከሌት የሚሰሩ ጠላቶች ትላንትም ነበሩ። ዛሬም አሉ፡፡ በሚጠብቋት ፤ በሚወዷትና በሚሰዉላት ልጆቿ ጥረት ድካማቸው መና ፤ ህልማቸው ቅዠት ቢሆንም እንኳ!! የሀገራችንን ታሪክ መለስ ብለን ስናጤነው ከወራሪዎች ባልተናነሰ የግል ጥቅማቸውና ፖለቲካዊ ፍላጎታቸው ለማሳካት በሀገር ላይ የሚቆምሩ ጥቅመኞችን ጨምሮ  የውጭ ጠላቶችን ፍላጎት ለማሳካት  የተሰለፉ ባንዳዎች በተደጋጋሚ አጋጥመዋል። እስከ መስዋዕትነት በመታመን ሀገሩን ከሚጠብቀው ሰላም ወዳዱ የሀገራችን ህዝብ የወጣው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን ዛሬም  የሀገሩን  ሉአላዊነትና ህልውና  ለማፅናት በተሟላ ቁመና መገኘቱ ከንቱ ህልማቸውን አምክኖታል እንጂ !! በልቦናው ሀገሩን ተሸክሞ  መኖር ብቻ ሳይሆን ለሚሰዋው ጀግናው ሰራዊታችን ከአለም አቀፍ ተቋማትና ከተለያዩ ሀገራት ህዝቦች ያገኘው ፍቅርና ክብር የመስዋዕትነቱ ውጤት ነው። ሰላም ለራቃቸው የቅርብና የሩቅ  ሀገራት ያመጣው  ተስፋ በግልፅ የሚታይ ነውና! ለህዝቦች ሰላም በተሰለፈባቸው ሀገራትም የሰራዊታችን መስዋዕትነትን የሀገራችንን ታላቅነት የሚያወሱ ማስታወሻዎች በክብር ተቀምጠዋል፡፡  ሰራዊታችን ከተባበሩት መንግስታት እና ከአፍሪካ ህብረት በተደጋጋሚ የተሰጠው ሽልማት ፤ በደቡብ ኮሪያ  የቆመለት ሀውልት ፤ ከላይቤሪያ ፤ ከሩዋንዳ እና  ብሩንዲ  ህዝብና መንግስት የተሰጡት ሽልማቶች ከሀገራችን ባለፈ ሰላም ላጡ ህዝቦች በመስዋዕትነቱ ያመጣውን ውጤት የሚያወሳ ቋሚ ምስክር ነው። በሱዳን እና በሶማሊያ  የሚገኙ ህዝቦችም ሰራዊታችን በከፈለውና እየከፈለው በሚገኘው መስዋዕትነት ላገኙት ሰላም ምስክር ናቸውና በየሄደበት የሚሰጡት ክብርና ፍቅር የላቀ ነው፡፡ ሰራዊትና መስዋዕትነት ተለያይቶ አያውቅም፡፡  ለሀገር ህልውና ለሰው ልጆች ሰላም  የሚከፈል መስዋዕትነት ደግሞ  ክቡር መስዋዕትነት ነው፡፡ ጀግናው ሰራዊታችን  በሀገሩ የመጡበትን ጠላቶቹ እስከ መስዋዕትነት በመፋለም አንድ ህይወቱን ብቻ መስጠቱ ስለሚቆጨው  ነው በተሰሙ ቁጥር  የሚነዝር ስሜት የሚፈጥሩት  ስንኞችን በየቀኑ ከልቡ የሚያዜመው …..ኢትዮጵያ በኛ ደም ደምቃ በአፅማችን ፍላፅ ተማግራ      እንደታፈረች እንድትኖር ከዘመን ዘመን ተከብራ      ከመሞት በላይ እንሙት ደማችን ሺ ጊዜ ይፍሰስ      አየር አፈሯ ይባረክ ምን ጊዜም ስሟ ይታደስ!  በማለት ታፍራና ተከብራ እንድትኖር  በደሙ ያደመቃትንና በአፅሙ ፍላጻ የማገራትን ሀገሩን አፈሯ እንዲባረክ ስሟ እንዲታደስ ከመሞት በላይ ለመሞትና ደሙን በማፍሰስ በቁርጠኝነት መቆሙን የሚነግረን!!  የሀገራችንን አንድነት ፤ ሰላምና ሉአላዊነት ለመጋፋት የሚሞክሩ የውጭ ጠላቶቻችን ሆነ ቡድናዊ ፍላጎታቸውን በሀይል ለመጫን የሚያደርጉትን  እንቅስቃሴ እየመከተ ያለና በመስዋዕትነቱ ሀገር እያፀና  ያለ ጀግና የመከላከያ ሰራዊት መገንባት የተቻለውም ከአባቶቹ በወረሰው ጀግንነትና ሀገር ወዳድነት ነው። የዘመናችን ሀገር የመጠበቅ ተልዕኮ ፈተናው ብዙ ነው!!ፍላጎታቸው በየወቅቱ የሚለዋወጡ ከጥቅማቸው ውጭ ሀገራዊ ፍቅርና የሰላም ትርጉም የማይገባቸው ከሀዲ ባንዳዎች  ሰራዊቱን ባልዋለበት በማዋል የሌለውን ስም የሚሰጡ  የማህበራዊ ሚዲያ አርበኞች የበዙበት ዘመን ነው። ለሀገሩ ሉአላዊነትና ክብር ፤ ለመላው የሀገራችን ህዝብ ሰላም ከመዋደቅ ውጭ ሌላ ፍላጎት  የሌለውን ጀግና የሀገር ጠባቂ ሰራዊት የዳቦ ስም በማውጣት ስሙን ለማጉደፍ የተሰለፉት ጥቂት ባንዳዎች ከከፍታው ላይ ዝቅ የማያደርጉት ፤ የሚያጠነክሩት እንጂ ትጥቁን የሚያላሉት እንደማይሆን በተግባር ተፈትኖ አሳይቷል፡፡ እያሳየም ይገኛል። ወቅቱ የሚጠይቀው መስዋዕትነት ሀገራችንን በዕድገት አበልፅገን ፤ የተፈጥሮ ሀብታችንን አልምተን ፤ ያሉንን ታሪካዊ ፣ ባህላዊና ተፈጥሯዊ ፀጋዎቻንን አሳድገን  ለመጭው ትውልድ ምቹ የሆነች ሀገር ገንብተን ማቆየት እንጂ በየጊዜው በሚፈጠሩ አጀንዳዎች ተወጥረን ፤ በየቀኑ በሚፈለፈሉ ባልተረጋገጡና በውሸት መረጃዎች ተታለን ውዱ ጊዜያችንንና ሀብታችን ባለመሰዋት መሆን ይገባል፡፡ ወታደር ሀገር እንጂ ሰፈር የለውምና የሰፈር ጉልበተኞችን በመምከርና በማስታገስ ፤  የማህበራዊ ሚዲያ  ጡረተኞችና የሩቅ አዋጊዎችን  አጀንዳዎች ወደ ጎን በመተው  ለሀገራችን ሰላምና ዕድገት በመጣር ዘመኑ የሚጠይቀውን አነስተኛ መስዋዕትነት መክፍል ከእያንዳንዳችን የሚጠበቅ ተግባር ነው፡፡ ዘላለማዊ ክብር ለሀገራችን ዕልውና እና ሉአላዊነት ፤ ለህዝቦች ሰላም እና ዕድገት በክብር ለተሰው   እና በተሰለፉበት ሙያ ሁሉ በታማኝነትና  በቅንነት በማገልገል ለሀገራቸው መስዋዕትነት  ለከፈሉ ሁሉ ይሁን!!  ዘላለማዊ ክብር ለጀግኖች ሰማዕታት                         በብዙአየሁ ተሾመ

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በኬንያው የአየር ንብረት ጉባዔ ላይ ጠንካራ ትችት አቀረቡ የኤርትራ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሄደ ያለው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ “የህዝብ ግንኙነት” ስራ ላያ አተኩሯል ሲሉ ወቅሰዋል። ፕሬዝደንቱ ከምዕራባውያን ለአየር ንብረት ለውጥ መቋቋሚያ የሚሆን ድጋፍ መጠበቅ መቅረት ያለበት አካሄድ ነው ብለዋል። https://am.al-ain.com/article/president-isaias-strong-crticisim-africa-climate-summit

አርሰናል 3-1 ማንቸስተር ዩናይትድ ተጠባቂው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ በአርሰናል 3ለ1 ተጠባቂው ጨዋታ በአርሰናል አሸናፊነት ተጠናቀቀ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አራተኛ ሳምንት ጨዋታቸውን ያደ
አርሰናል 3-1 ማንቸስተር ዩናይትድ ተጠባቂው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ በአርሰናል 3ለ1 ተጠባቂው ጨዋታ በአርሰናል አሸናፊነት ተጠናቀቀ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አራተኛ ሳምንት ጨዋታቸውን ያደረጉት አርሰናል እና ማንችስተር ዩናይትድ በመድፈኞቹ አሸናፊነት ተጠናቋል። ማንችስተር ቀዳሚ ያደረገችውን ጎል በመጀመሪያው አጋማሽ በማርከስ ራሽፎርድ ሲያስቆጥር አምበሉ ኦዲጋርድ  የመድፈኞቹን ወዲያው አቻ ያደረገች ጎል አስቆጥሯል። በሁለተኛው አጋማሽ በጭማሪ ሰዓት አዲሱ ፈራሚ ዴክላን ራይስ እና ጋብሪኤል ጄሱስ አርሰናልን አሸናፊ ያደረገች ጎል አስቆጥረዋል። ማንችስተር ዩናይትድ በጋርናቾ አማካኝነት ጎል ቢያስቆጥርም በቫር ኦፍሳይድ ነው በሚል ተሽሯል። ቀደም ብሎ በተካሄደ ተመሳሳይ የሊግ ጨዋታ ሊቨርፑል አስተን ቪላን 3ለ0 እንዲሁም ክሪስታስ ፓላስ ወልቭስን 3ለ2 አሸንፈዋል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን ማንችስተር ሲቲ በ12 ነጥብ ሲመራ ቶትንሀም እና ሊቨርፑል በእኩል 10 ነጥብ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ እየመሩ ይገኛሉ።

#የ6_ቀኑ_ጦርነት #ግብፅና_እስራኤል ጊዜው 1967 ነው። ፕሬዝዳንት ገማል አብዱልናስር ግብፅ በደረሰባት ያልተጠበቀ ያልታሰበና በፍፁም አሳፋሪ የሆነ ሽንፈት እርርር ድብን ብለዋል። እናም ለመላው ግብፃዊያን " በዚህ ውርደት ውስጥ አስገብቻችሁ ሳለ እንደትስ የናንተ መሪ ሆኜ መቀጠል ይቻለኛል ስለሆነም ከስልጣኔ ራሴን አግልያለሁ " ሲሉ መርዶ ይሁን ብስራት አረዱት! ግና ተበሳጭተው ነው እንጅ ከስልጣን የመልቀቃቸው ዜና እንኳ ከአንጀታቸው አልነበረም። እናም በማግስቱ " በመሪነት እንድቀጥል ከፈለጋችሁ ህዝባዊ ድጋፋችሁን አሳዩኝ " በማለት ህዝቡን አደባባይ አስወጡትና በስልጣናቸው ቀጠሉ። እስራኤል በግብፅ ላይ የፈፀመቺው ድንገተኛ የአየር ጥቃት ግብፅን አሽመድምዷታል። እስራኤል ያንን ጦርነት እንደምትፈፅም የምታውቀው ምናልባት አሜሪካና ጥቂት አጋሮቿ ናቸው። የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤባን ወደ አሜሪካ በረረና ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆኝሰን " ግብፅን ልንወራት ነው " አላቸው።  ፕሬዳንቱም መቼ ? ሲሉ ጠየቁት። ቀጣይ ሳምንት አለና እስከነ ሰአቱ ነገራቸው። ምን ያክል የጦር ጄት አዘጋጅታችሗል? አሉት ለእስራኤሉ ሰው። እርሱም ከጀት እስከ ታንክ እስከ ወታደር ሁሉንም ለአሜሪካው መሪ ነገራቸው። ከኛ ምን ትፈልጋላችሁ? አሉ የአሜሪካው ሰው። ሚስተር ኢባንም የሚፈልጉትን ተናገሩ። እናም በቃ ፈፅሙት አሉና የአሜሪካን ፈቃድ ሰጧቸው። የእስራኤል አሜሪካ ሰራሽ የጦር አይሮፕላኖች የሞት መልእክተኛ ሚሳኤሎቻቼውን በጉያቸው ታቅፈው ቀጥታ ወደ ሜዲትራኒያን ባህር አቅጣጫ ቀዘፉ። ግብፅ እንቅልፍ ላይ ነች። ሲናይ በረሀ ላይ የፈሰሰው የግብፅ ጦር ተዘናግቶ ተቀምጧል። ምንም ነገር አልነበረማ ! በቅፅበት የእስራኤል አይሮፕላኖች ከሜዲትራኒያን ባህር ቁልቁል ወደ ግብፅ ተምዘገዘጉ። እናም ከሲናይ እስከ ካይሮ ከአሌክሳንድሪ እስከ ስዊዝ ግብፅን ያነዷት ጀመር። ግብፅን በጉያቸው በያዙት እሳት አፈገጓት። የግብፅ ጦር የሚይዘውን የሚጨብጠውን አጣ። ከ 420 የግብፅ የጦር አይሮፕላኖች ከ 300 በላዩ ነደዱ። የግንኙነት መስመሮች ሁሉ ተቆረጡና የግብፅ ጦር በገፍ ተማርኮ በሲናይ በረሀ በእስራኤል ሲነዳ አለም ተመለከተ። እስራኤል በ 6 ቀን ጦርነት ብቻ መላው ሲናይ በረሀን ተቆጣጥራ ግብፅን አሽመደመደቻት። እስራኤል ይህንን የድንገቴ ጦር የከፈተቺው ከግብፅ ጦርነት ተቃጥቶባት አይደለም። ይልቁንስ አረቦች ተባብረው ሊያጠፉኝ ያስባሉና ሳይቀድሙኝ ልቅደማቸው በሚል Preemptive attack እንጅ ! እናም በአሜሪካ ይሁንታና እገዛ እስራኤል ድል ድል ተቀዳጀች። ኢየሩሳሌምን ሙሉ ተቆጣጠረች የጎላን ተራሮችን ጠቀለለች የሲናይ በረሀንም የግሏ አደረገቻቻቼው። ስዊዝን አስገባች። እንኳንስ ግብፅን አረቦችን አንድ ሀገር አድርጌ አዋህዳቸዋለሁ ብለው የተነሱት ገማል አብዱልናስር የደረሰባቸውን ማመን አልቻሉም። ቅስማቸው ተሰበረ። ግና ሰውየው የዋዛ አይደሉምና ግብፅ አንገቷን ደፍታ መቀመጥ እንደሌለባት በማሰብ እስራኤልን መበቀል የሚችል ጦር መገንባት እንዳለባቸው አመኑ። እናም ግብፅን በመቶ ሺህ በሚቆጠር ጦር በሺህ በሚቆጠር ታንክና መድፍ በአየር ሀይል በባህር ሀይል ከአፍ እስካፍንጫዋ እንድትታጠቅ ያደርጓት ጀመር። ግብፅ ለበቀል መዘጋጀቷን ቀጠለች። አመት አመትን እየወለደ ጊዚያቶች ነጎዱ። ግብፅም አመቺ ጊዜ አመቺ ቦታ መጠባበቅን እንደያዘች ዝግጅትና እቅዷን በምስጢር እንዳዘጋጀች ቀጠለች። ጠላቷን በሰበረችባት ቦታ ለመስበር! ጊዜው እየቆጠረ 1973 ላይ ደረሰ። ግብፅ አፈሙዟን አሟሽታ ከሶሪያ ጋር ተመሳጥራ አቅጣጫዋን ወደ እስራኤል ቀሰረች። ለበቀል ....... ይቀጥላል !

የግል ሐኪምዎ የሆነው ሙዝ! 👉በስትሮክ የመሞት አደጋን ከ50-60 በመቶ ለመቀነስ ያስችላል!!! 👉ለስኳር ህመምና ለደም ማነስ ሙዝን መመገብ ይመከራል! በኢትዮጵያ እንደተገኘ የሚነገርለትና በዓለማችን በስፋት እየተመረተ ለምግብነት የሚውለው ሙዝ እጅግ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡ ሙዝ ከምግብ ይዘቱ በተጨማሪ ለተለያዩ በሽታዎች ፈውስ ሊያስገኙ የሚችሉ ንጥረ ነገሮችንም አካቶ ይዟል። ብዙዎቻችን ሙዝን ለምግብነት በማዋል ለሰውነታችን ሃይልና ሙቀት ለማግኘት እንደምንችል ከማወቅ የዘለለ ነገር አስበን አናውቅም፡፡ ነገር ግን ሙዝ በውስጡ የያዛቸው ተፈጥሮአዊ የስኳር ወይም የጣፋጭ ምንጭ የሆኑት ግሉኮስ፣ ስክሮስ፣ እና ፍሩክቶስ የተባሉት ንጥረነገራት ከሙዝ የፋይበር (የቃጫነት) ተፈጥሮ ጋር ተዳምረው መጠነሰፊ ጠቀሜታዎችን ይሰጣሉ። ከበርካታ የሙዝ ጠቀሜታዎች መካከል ጥቂቶቹን ከዚህ እንደሚከተለው ለማየት እንሞክራለን፡፡ ♦1. ለአእምሮ እድገት ሙዝ በውስጡ ከፍተኛ የፖታሺየም ንጥረነገርን ይዟል፡፡ ይህም ንጥረ ነገር የአንጐልን የሥራ ብቃት ለማሻሻል እና ለማሳደግ እንዲሁም ንቁና ጤናማ አዕምሮ እንዲኖረን በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ ♦2. ለስትሮክ በሙዝ ውስጥ ያለው ፖታሺየም፣ የደም ሥርዓትን በማስተካከል ባልታሰበ ሁኔታና በድንገት የሚከሰተውን የስትሮክ ችግር ለመከላከል ያግዛል። ሙዝ በሰው ልጆች የአመጋገብ ሥርዓት ውስጥ ተካቶ ዘወትር ለምግብነት የሚውል ከሆነ፣ በስትሮክ ምክንያት የሚመጣውን ድንገተኛ ሞትና የአካል ጉዳት ከ50-60 በመቶ ለመቀነስ ያስችላል፡፡ ♦3. ለደም ግፊት ሙዝ በተፈጥሮው በውስጡ የሚይዘው ዝቅተኛ የጨው መጠን በመሆኑ የደም ግፊትን ለማረጋጋት ይረዳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በውስጡ ያለው ፖታሺየም የደም ግፊትን ለማስተካከልና በግፊት ሳቢያ የሚከሰቱ ከባድ የጤና ችግሮችን ለመከላከል ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ ♦4. ለጨጓራ ህመም አብዛኛዎቻችን ሙዝ ከበድ ያለ ምግብ እንደሆነ በማሰብ፣ ሙዝ የጨጓራ ህመማችንን እንደሚያባብስብን ስንናገር እንደመጣለን፡፡ ይሁን እንጂ ሙዝ ለጨጓራ ችግሮች ሁነኛ መፍትሔ ነው። ሙዝ በባህርይው በጣም ለስላሳ በመሆኑ በጨጓራ ላይ መጨናነቅን የማይፈጥር ሲሆን የጨጓራ አካባቢን በመሸፈን፣ የጨጓራ ውስጥ አሲድን በማስተካከልና በማመጣጠን የጨጓራ ቁስለት እንዳይፈጠር ለማድረግ ያስችላል፡፡ ♦5. ለድብርት ሙዝ በውስጡ የሚይዘውና ትራይፕቶፋን የተባለው ንጥረ ነገር በሰውነታችን ውስጥ ሴሮቶኒን የባለ ሆርሞን እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ ይህ ሆርሞን አይነተኛ ተግባሩ ሰውነታችንን ከድካምና ከድብርት በማላቀቅ ወደተሻለ ስሜት ውስጥ እንድንገባ ማድረግ ነው፡፡ ♦6. ለሆድ ድርቀት በሙዝ ውስጥ የሚገኘው ፋይበር ለምግብ መፍጨት ሥርዓታችን ከፍተኛ ጠቀሜታን ይሰጣል፡፡ የምግብ መፍጨት ሥርዓትን የሚያከናውኑት የሰውነታችን ክፍሎች በቂ የውሃ መጠን እንዲኖራቸው በማድረግ ሆድ ድርቀትን ይከላከላል፡፡ አንጀት የተለሳለሰ እንዲሆን በማድረግ ከሰውነታችን መውጣት የሚገባቸው አላስፈላጊ ነገሮች (ቆሻሻዎች) እንዲወገዱ ለማድረግ ይረዳል፡፡ ♦7. ለስኳር ህመም ሙዝ በውስጡ ከፍተኛ ቫይታሚን B6 የያዘ ነው። ይህም በደም ውስጥ የሚኖረውን ከፍተኛ የስኳር መጠን እንዲቀንስ በማድረግ፣ በሰውነታችን ውስጥ የሚገኘውን የስኳር መጠን ለመቆጣጠር ያስችለናል፡፡ ከስኳር መብዛት ጋር ተያይዞ የሚከሰተውን የጠዋት ህመምንም ያስቀራል፡፡ ♦8. ሙዝና ደም ማነስ በሙዝ ውስጥ የሚገኘው የብረት ማዕድን ጠቀሜታው በደማችን ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው የሔሞግሎቢን ምርት እንዲኖር ማድረግ ነው፡፡ ይህም በሔሞግሎቢን እጥረት ሳቢያ የሚከሰተውን የደም ማነስ እንዳይከሰት ያደርጋል፡፡ ♦9. ሙዝ ለስካር ሙዝ ከወተትና ከማር ጋር ተደባልቆ ለምግብነት ሲውል በከፍተኛ መጠጥ ወይም በስካር ሳቢያ የሚከሰትን ሃንግኦቨር (ያደረ ድምር) በቀላሉ ያስወግዳል፡፡ በመጠጥ ሳቢያ የተጐዳን ሰውነት እንዲነቃቃና ብርታት እንዲያገኝ በማድረግ ረገድም ሙዝ ከፍተኛ ሚናን ይጫወታል፡፡ የሲጋራ እና መሰል ሱሶች ተጠቂ የሆኑ ሰዎች ሱሱን ለማቆም እንዲችሉ ሙዝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ ♦10. ለሞቃታማ አየር በሞቃታማ የአየር ንብረት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ሙዝን ቢመገቡ ሰውነታቸው ሙቀቱን እንዲቋቋም በማድረግ፣ የተረጋጋና የተስተካከለ የሰውነት ሙቀት እንዲኖረን ያደርገናል፡፡ ♦11. የሙዝ ተጨማሪ ጠቀሜታዎች በወባ ትንኝ የተነደፈ ሰው ወይንም በማንኛውም ተናካሽ ወይም ተናዳፊ ነፍሳት የተነደፈ (የተነከሰ) ሰው በሙዝ ልጣጭ የውስጠኛው ክፍል የተነደፈበትን (የተነከሰበትን) ቦታ በደንብ በማሸት እብጠቱን መቀነስ ይችላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ንድፍያው (ንክሻው) የፈጠረበትን የማቃጠልና የመለብለብ ስሜት ለማስወገድ ይችላል፡፡ 👉 ጫማዎን ከጠረጉና ቆሻሻውን ካስወገዱ በኋላ በሙዝ ልጣጭ ቢወለውሉት ጫማዎ እንደመስታወት ያበራልዎታል። 👉 ፍሪጅዎ መጥፎ ጠረን (ሽታ) ካመጣብዎ አንድ ሁለት ሙዞችን ያስቀምጡበት፡፡ የፍሪጅዎ ጠረን በቅጽበት ይቀየራል፡፡ 👉 ሰውነትዎ በድካም ወይም በህመም ከተጐዳና የምግብ ፍላጐት ከሌለዎ አንድ ሙዝ እንደምንም ይመገቡ፡፡ ሰውነትዎ ሲበረታና የምግብ ፍላጐትዎ ሲጨምር ይታወቅዎታል፡፡ በአጠቃላይ ሁላችንም እንደቀላል የምናየውና ብዙም ትኩረት የማንሰጠው ሙዝ ለከፍተኛ የጤና ችግር የሚዳርጉንን በሽታዎች ለመከላከልና ለማስወገድ ይረዳናል፡፡ ታዲያ ይህን የግል ሐኪምዎ የሆነ ፈዋሽ ፍሬ በፍሪጅ ውስጥ ከተው አያበላሹት፡፡ ንፋስ ያለበት ያልታመቀ አየር ለሙዝ የሚስማማ ነውና - በዚያ ያኑሩት፡፡ ------መረጃ ሐይል ነው! 👉 በሽርፍራፊ ሰከንድ የተሰራች ስህተት የሰውን ህይወት እንደምታጠፋ ሁሉ፡ በሰከንዶች ቅፅበት የደረሰች መረጃ ህይዎትን ለማትረፍ ሰበብ ትሆናለችና እባከዎት የሚለቀቁ ጤናነክ መረጃዎችን ለሌሎች ወገኖች ለማድረስ ሼር ቢያደርጉላቸው መልካምነት ነው፡፡ ተጨማሪ የተለያዩ የጤና ነክ መረጃዎች  እንዲደርስዎ የቴሌግራም ቻናሌን ይቀላቀሉ የኛ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር አዲስ የተሸከርካሪ ሰሌዳ በማዘጋጀት በአገልግሎት ላይ ማዋሉን አስታወቀ የመከላከያ ሎጅስቲክስ ዋና መምሪያ የሠራዊቱን አሁናዊ ዝግጁነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር አዲስ የተሸከርካሪ ሰሌዳ በማዘጋጀት በአገልግሎት ላይ ማዋሉን አስታወቀ የመከላከያ ሎጅስቲክስ ዋና መምሪያ የሠራዊቱን አሁናዊ ዝግጁነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎች እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጾ ለተዋጊ ክፍሉ ግዳጅ አፈፃፀም ተጨማሪ አቅም የሚሆኑ የተለያዩ ሞዴል ያላቸውን ቀላል ተሸከርካሪዎች ስታንዳርድ በማዘጋጀት ለዕዞችና ለክፍሎች የቁልፍ ርክክብ ማድረጉን አመልክቷል፡፡ የተሸከርካሪዎችን ቁልፍ ለሁሉም ዕዞች እና ለተለያዩ ተዋጊ ክፍል አመራሮች ያስረከቡት የመከላከያ ሎጅስቲክስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል ተቋማቸው መከላከያ የሠራዊቱን ዝግጁነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉና ተጨማሪ አቅም የሚሆኑ ተሸከርካሪዎችን ማደል መቻሉን ገልጸዋል። በየደረጃው ያሉ አመራሮች እና ሙያተኞች ለንብረቱ ደህንነት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት እየታየ ያለውን የንብረት አያያዝ ክፍተት በመቀነስ ጥንቃቄ በማድረግ ስምሪት በመስጠትና በመቆጣጠር ማስተዳደር እንዳለባቸውም ጠቁመዋል ሲል ዋልታ ዘግቧል።

በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ያለው የፅንፈኞች እንቅስቃሴ ስጋት ወደማይሆንበት ደረጃ ደርሷል፡- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ ኃይሎች አሁን ላይ ስጋት
በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ያለው የፅንፈኞች እንቅስቃሴ ስጋት ወደማይሆንበት ደረጃ ደርሷል፡-  ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ ኃይሎች አሁን ላይ ስጋት ወደማይሆኑበት ደረጃ መድረሳቸውን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ፡፡ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ከመከላከያ ሚዲያ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በሁለቱ ክልሎች ተከስተው የነበሩ የፀጥታ ችግሮችን የመከላከያ ሰራዊቱ ጥበብ በታከለበት ወታደራዊ እንቅስቃሴ እየቀረፈ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢታማዦር ሹሙ በአማራ ክልል የህዝቡን የመብት ጥያቄ ካባ በማድረግ ፍላጎቱን በኃይል ለማሳካት የተንቀሳቀሰው ኃይል ላይ እየተወሰደ ባለው እርምጅ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሆነው የሀሰት ፕሮፖጋንዳ የሚነዙ ኃይሎች፤ ለሀገርና ለህዝብ ሲል ውድ ህይወቱን እየከፈለ ሰላም የሚያረጋግጠውን ሰራዊት ስነ-ልቦና ያልተረዱ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ሰራዊቱ በተሰማራባቸው የግዳጅ ቃጣናዎች ሁሉ ህግ-መንግስታዊ ተልዕኮውን በአስተማማኝ እየተወጣም ነው ብለዋል፡፡ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ የፅንፈኞች የሀሰት ፕሮፖጋንዳን የተገነዘበው ህዝባችን ከመከላከያ ሰራዊቱ ጎን በመሆን ለሰላሙ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በሀሰተኞች ሴራ ተታለው ከፅንፈኞች ጋር የተሰለፉ ወጣቶች በሰላማዊ መንገድ ወደህዝቡ እንዲመለሱም ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ መከላከያ በ2015 የበጀት ዓመት ተልዕኮውን በሚገባ መፈፀሙን የገለጹት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ ለቀጣዩ በጀት ዓመትም እንደተቋም የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ከምን ጊዜውም በላይ ዝግጁ ነው ብለዋል፡፡

በሱዳን የሚገኙ የመረጃ ጠላፊዎች "X" በቀድሞ ስሙ ትዊተር የሚባለው ማህበራዊ ትስስር ገፅ ላይ ጥቃት አደረሱ። እራሱን "አኖኒመስ ሱዳን" ብሎ የሚጠራው የመረጃ ጠላፊ ቡድን ከ12 በሚበልጡ አገሮች
በሱዳን የሚገኙ የመረጃ ጠላፊዎች "X" በቀድሞ ስሙ ትዊተር የሚባለው ማህበራዊ ትስስር ገፅ ላይ ጥቃት አደረሱ። እራሱን "አኖኒመስ ሱዳን" ብሎ የሚጠራው የመረጃ ጠላፊ ቡድን ከ12 በሚበልጡ አገሮች ውስጥ ትዊተር በመባል ይታወቅ የነበረውን የማህበራዊ የትስስር ገፅ አገልግሎት እንዳይሰጥ ማድረጉ ተገልጿል። እርምጃው ኤሎን መስክ በጦርነት በምትታመሰው ሱዳን የስታርሊንክ ሳተላይት የኢንተርኔት አገልግሎትን እንዲከፈት ግፊት ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል። "X" ከሁለት ሰዓታት በላይ ከአገልግሎት ውጪ የነበረ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎች የድርጊቱ ተጠቂ ሆነዋል። የትስስር ገፁን የአገልግሎት መቆራረጥ የሚከታተለው መተግበሪያ በአሜሪካ እና እንግሊዝ ውስጥ ወደ 20ሺ የሚጠጉ ተጠቃሚዎች አገልግሎቱ  እንደተቋረጠባቸው መዝግቧል። ቡድኑ "በሱዳን ውስጥ ስታርሊንክን ክፈት" የሚል መልእክት ለኤሎን መስክ በቴሌግራም ያስተላለፈ ሲሆን X እና ስታርሊንክን የሚመራው ኤሎን መስክ የሳተላይት የኢንተርኔት አገልግሎትን በሱዳን ለማስጀመር እስካሁን ለጥያቄያቸው ምላሽ አለመስጠቱም ተገልጿል። ምንጭ ፦ ቢቢሲ አፍሪካ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም            የወታደራዊ ባንድ ከየት ወደ የት                                                  ወታደራዊ ባንዶች ዋነኛ ሃላፊነት እና ተግባራቸው ለወታደራዊ ተልዕኮ ማለትም የሠረዊቱን ከውጊያ በፊት ዝግጁነት ማገዝ  ማሳደግ እና በውጊያ ወቅት የማድረግ አቅምን መጨመር የሚያሥችል ወኔን መላበስ እንዲችሉ  የሥነ ልቦና ግንባታ ለመፍጠር ነው።  ወታደራዊ ባንዶች በአብዛኛው ክንዋኔያቸው በወታደራዊ ጉዳዮች እና  በውጊያ ቀጠናዎች የተወሰነ ነበር ማለት ይቻላል።     ከጊዜ በኋላ የወታደራዊ ውጊያ ቴክኒክ ከመቀየሩ ጋር ተያይዞ የወታደራዊ ባንዶችም አገልግሎትና ጠቀሜታ በመስፋፋቱ ወታደራዊ ባንዶች ዘርፈ ብዙ የሆኑ ግልጋሎቶችን እንዲስጡ የማድረግ ተግባር ተጀምሯል ፡፡ ወታደራዊ ባንዶች ከቀደምት ተግባራቸውና የሙዚቃ ስልት ክዋኔአቸው በመሳሪያ አወቃቀር፤በሙዚቃ ቅንብር፤በሙዚቃ አጨዋወት እና በአገልግሎት በርካታ ለውጦች እያሳዩ በመምጣታቸው በመላው አለም በስፋት እየተተገበረ ያለ የሙዚቃ ዘውግ እንዲሆን አስችሎታል፡፡ ወታደራዊ ባንዶች በተግባራቸው ለውጦች ማሳየት የጀመሩበትን ወቅት ስንዳስስ አሜሪካ በአንደኛው አለም ጦርነት በተፈጠረው ወታደራዊ ታክቲክ ለውጥ ወታደራዊ ባንዶች ከአውደ ውጊያ ተግባራቸው ውጪ ለማዝናናት ተግባር የሚውል የብራስ ባንድ አወቃቀር እውን በማድረግ  የተለያዩ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ለሰራዊቱ ማቅረብ ጀመረች ።በተጓዳኝም በሰልፍ እና የተለያዩ ወታደራዊ ክብረ በአላት ላይ ያገለግሉ ነበር፡፡ በዚሁ ሂደትም የሙዚቃ መሳሪያዎች ስብጥር መተግበር በመጀመሩ ውድ ዊንድ መሳሪያዎችን በማካተት ሙዚቃ መስራት ተጀመረ። በዚህ ጅማሮ በአብዛኛው በአለማችን የሚገኙ የወታደራዊ ባንዶች መሰረታዊ መለኪያ የተቀመጠላቸው ሆኖ በመሳሪያ አወቃቀር፤አጨዋወት ተግባራቱ እና ሁለንተናዊ አወቃቀር አሁን ባለንበት ዘመን የምናገኘውን ወታደራዊ ማርቺንግ ባንዶች ቅርጽ ለመፍጠር ተችሏል፡፡   የወታደራዊ ባንዶች ሙዚቃ በ21ኛው ክ/ዘመን  ከነበረበት የተለየ ሆኗል።  ወታደራዊ ባንዶች በአውደ ግንባሮች መገኘት አቁመዋል። ሆኖም የጦርነት ፕሮፓጋንዳ መሳሪያነት ሚናቸው ግን አልቆመም። በአሁኑ ወቅት ወታደራዊ ባንዶች በተለያዩ ሀገራዊ ክብረ በአላት ላይ፤ ወታደሮችንንና ህብረተሰቡን ማዝናናት፣ ማቀራረብ ፣ የወጣቶችን ሀገራዊ ፍቅር ከማጠናከር በተጨማሪ የውጪ መንግስታት የክብር አቀባበልና ሌሎች ልዩ ልዩ ቦታዎች ሙዚቃዊ ስራዎቻቸውን ማቅረብ ተግባራቸው ሆኗል፡፡    በዘመኑ ሙዚቃዊ አከዋወናቸው ሲገለጽ ‹‹ወታደራዊ ባንዶች ወኔ ቀስቃሽ ሙዚቃዎችን ሲያቀርቡ ባንዶቹ የባንዱ ሙዚቃ ቶን(የድምጽ ቃና) እራሱ የሃገር ኩራት መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል ፤ወታደራዊ ባንዶች በሂደት ባሳዩት ለውጦችም ከመሰረታዊ የሆርን እና ድራም ሙዚቃ በዜማ፤ህብረዜማ፤በሙዚቃ ቅንብር፤ በመሳሪያ አጨዋወት፤በቅርጽ በኩል በጣም ጥልቅ የሆነ ሙዚቃዊ ክዋኔዎች ላይ በጉልህ ይታያሉ።     በህዝብ መዝሙር በማርቺንግ ባንድ፤በብራስ ባንድ እና የኦርኬስትራ ቅርጾች የተለያዩ የሙዚቃ ዘውጎች  በተለያዩ ክብረ በአላት ፤በሰርግ ስነስርአት ጨምሮ በተለያዩ ሁነቶች ላይ መታየት በጣም ወሳኝ መድረኮች እየሆነ እንደመጣ ይገለጻል፡፡ መነሻ መሠረቱን ከዚሁ ያደረገው የመከላከያ ኦርኬስትራ እና ማርች ባንድ ታሪካዊ ጉዞስ ምን ይመሥላል ?  በቀጣይ ይጠብቁ። ከመከላከያ ኪነጥበባት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር

ለጥንቃቄ ያክል ስለ አዲሱ የመኪና ስርቆት ልዩ መረጃ👇 አሁን አሁን “መኪናዬን በሥርዓት ቆልፌ ካቆምኩበት (ፓርክ) ካደረኩበት ቦታ ንብረቶቼ ተሰረቁ” ፣ “መኪናዬን ካቆምኩበት አጣሁት እባካችሁ አፋ
ለጥንቃቄ ያክል ስለ አዲሱ የመኪና ስርቆት ልዩ መረጃ👇 አሁን አሁን “መኪናዬን በሥርዓት ቆልፌ ካቆምኩበት (ፓርክ) ካደረኩበት ቦታ ንብረቶቼ ተሰረቁ” ፣ “መኪናዬን ካቆምኩበት አጣሁት እባካችሁ አፋልጉኝ” እና የመሣሠሉትን ስሞታዎች መሥማት እየተለመደ መጥቷል፡፡ እንዲኅ ያለው ሁኔታ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በውጭ ሀገራትም እየተለመደ መምጣቱን ቫይራል ኒውስ ከሰሞኑ አስነብቧል፡፡ የድንቃድንቅ ዜና ምንጩ ታዲያ በመኪና ሌቦች ጥቅም ላይ ከሚውሉ የታወቁ የተለያዩ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች በተጨማሪ የሚያስገርሙ ፈጠራዎችን እንደሚጠቀሙ ፅፏል፡፡ እንደ ቫይራል ኒውስ መረጃ ሌቦቹ የሚጠቀሙት ሥልት “ሣንቲም” ወይም መሠል ቁራጭ “ኒኬል” ነው፡፡ እርስዎ ለጉዳይዎ መኪናዎን አቁመው ሲሄዱ ወይም የዕለት ውሎዎን ጨርሰው “ፓርክ” ሲያደርጉ ሌቦቹ ሥራቸውን ይጀምራሉ፡፡ ከሹፌሩ መግቢያ በር በተቃራኒ ባለው የተሳፋሪው በር እጀታ ጠጋ ብለው “ሣንቲም” ወይም “ኒኬል” ነገር እጀታው ላይ ያስገባሉ፡፡ ከዚያም በርቀት ሆነው መኪናው በሄደበት ሁሉ እየተከተሉ ሹፌሩ የሚያቆምበትን ቦታ ያያሉ፡፡ ከዚያም በሩን ከፍተው ከገቡ በኋላ ከፈለጉ በውስጡ ያለውን ንብረት መውሰድ አሊያም መኪናውን ነድተው ወደ ፈቀዱበት መሄድ ይችላሉ፡፡ ሌቦቹ “ሣንቲም” ወይም “ኒኬል” ነገር የሚያስገቡት ሹፌሩ በሩን ቢቆልፍም “ማዕከላዊ መቆለፊያው” (ሴንትራል ሎኪንግ ሲስተሙ)እንዳይሠራ ስለሚታገድ ነው፡፡ በመሆኑም አሽከርካሪ ከሆኑ ÷ ወደ መኪናዎ ከመግባትዎ በፊት በሹፌሩ በር ተቃራኒ በኩል ያለው የተሳፋሪ በር እጀታ ከማንኛውም ሣንቲሞች ወይም ቁራጭ ብረት ነገር የጸዳ መሆኑን ያረጋግጡ ሲል የመረጃ ምንጩ አሳስቧል።

የካይሮው የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ተጠናቀቀ። ~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ለሁለት ቀናት ሲካሔድ የቆየው የሕዳሴ ግድብን ሙሌትና ውሃ አለቃቀቅ የተመለከተው የመጀመሪያ ዙር ውይይት ተጠናቀቀ።
+2
የካይሮው የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ተጠናቀቀ። ~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ለሁለት ቀናት ሲካሔድ የቆየው የሕዳሴ ግድብን  ሙሌትና ውሃ አለቃቀቅ የተመለከተው የመጀመሪያ ዙር ውይይት ተጠናቀቀ። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ሙሌትና ውሃ አለቃቀቅን በተመለከተ በኢትዮጵያ፣ በሱዳንና በግብጽ ልዑካን መካከል ለሁለት ቀናት የተደረገው የመጀመሪያው ዙር የሦስትዮሽ ድርድር ዛሬ መጠናቀቁን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የልዑካን ቡድኑ ሁሉን ተጠቃሚ የሚያደርግ ስምምነት በሚደረስበት ሁኔታ ሃሳብ ተለዋውጠዋል። ሦስቱ አገራት የሦስትዮሽ ድርድሩን በመስከረም 2016 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ለመቀጠል ተስማምተዋል። ኢትዮጵያ በፍትሐዊ እና ምክንያታዊ መርህ መሠረት የራሷን ድርሻ እና ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ ድርድሩ በስምምነት እንዲቋጭ ጥረቷን እንደምትቀጥልም ተገልጿል። #ItIsMyDam

👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ 👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/CommandoAndAirborneCommand ሰብስክራይብ ያድርጉን 👇 https://www.youtube.com/@theredtigers_4034

#G20 አፍሪካ ህብረት G20ን እንዲቀላቀል ጥሪ ቀረበለት። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የ " አፍሪካ ህብረት " የቡድን 20 አባል እንዲሆን በዛሬው ዕለት ጥሪ ማቅረባቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። በሚቀጥለው ወር በሕንድ ፤ ኒው ዴሊ የቡድኑ መሪዎች ጉባኤ ይካሄዳል። ሞዲ ለአፍሪካ ህብረት ጥሪውን ያቀረቡት " ቢ20 የተሰኘው በቢዝነስ ፎረም እና የመስከረም ወሩ ጉባዔ መዳረሻ መድረክ ላይ ማደረጉት ንግግር ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ የዓለም አቀፉ የአቅርቦት ሰንሰለት ችግሮችን ለመቅረፍ ሀገራቸውን እንደመፍትሔ አቅርበዋል። የ20 ግዙፍ ኢኮኖሚዎች ስሪት የሆነው ቡድን 19 አገሮችን እና የአውሮፓ ህብረትን በአባልነት ያቀፈ ሲሆን ፣85 በመቶውን ዓለም አቀፉ ጥቅል የሀገራት ምርት መጠን እና ከዓለም ህዝብ መካከል ደግሞ ሁለት ሶስተኛውን ይሸፍናል። ይሁንና ከአፍሪካ የህብረቱ ብቸኛ አባል ደቡብ አፍሪካ ናት። በታህሳስ ወር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የአፍሪካ ህብረት የቡድን 20 ሀገራት G20 ቡድንን በቋሚ አባልነት እንዲቀላቀል እንደሚፈልጉ ተናግረው ነበር። በዛሬው ዕለት የወቅቱ የቡድኑ ጉባዔ አስተናጋጅ ሀገር ሕንድ መሪ ሞዲ ባለፈው አመት በአጠቃላይ 3 ትሪሊዮን ዶላር አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ያስመዘገበው ፓን- አፍሪካዊ ህብረት በቡድኑ አባልነት እንዲካተት ጥሪ አቅርበዋል። " ቋሚ አባልነት በመስጠት ራዕይ ውስጥ ለአፍሪካ ህብረት ግብዣ አቅርበናል " ሲሉ ተናግረዋል ። መቀመጫውን በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ያደረገው የአፍሪካ ህብረት 55 አባላት ያሉት ሲሆን በወታደራዊ አስተዳደር ስር የሚገኙ አምስት ሀገራት ግን በአሁኑ ጊዜ ከአባልነት ታግደዋል ሲል ቪኦኤ በዘገባው አስታውሷል። የቡድን 20 አባላት እነማን ናቸው ? 🇦🇷 አርጀንቲና 🇧🇷 ብራዚል 🇨🇦 ካናዳ 🇨🇳 ቻይና 🇫🇷 ፈረንሳይ 🇩🇪 ጀርመን 🇮🇳 ህንድ 🇮🇩 ኢንዶኔዥያ 🇮🇹 ጣልያን 🇯🇵 ጃፓን 🇰🇷 ደቡብ ኮሪያ 🇲🇽 ሜክሲኮ 🇷🇺 ሩስያ 🇸🇦 ሱዑዲ አረቢያ 🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ 🇹🇷 ቱርክ 🇬🇧 ዩናይትድ ኪንግደም 🇺🇸 አሜሪካ 🇪🇺 አውሮፓ ሕብረት ናቸው።