የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
前往频道在 Telegram
5 066
订阅者
-25624 小时
-1 8217 天
-3 02830 天
帖子存档
በጃፓን ላይ ከተጣለዉ የአቶሚክ ቦምብ በሶስት እጥፍ የበለጠ የኒዉክሌር ጦር በቤላሩስ ሩሲያ ልታከማች ነዉ
የቤላሩስ ፕሬዝዳንት "መሳሪያዉን ለመጠቀም ዉሳኔ እንዳልሰጥ እግዚያብሄር ይጠብቀኝ " ብለዋል
የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ በሰጡት መግለጫ ሀገራቸው በሂሮሺማ እና ናጋሳኪ ከተጣሉ የአቶሚክ ቦምቦች "በሶስት እጥፍ የሚበልጡ" የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን ከሩሲያ እየተቀበለች እንደሆነ ጠቁመዋል። ቤላሩስ ሊደርስባት የሚችለውን ጥቃት ለመከላከል ወደ የጦር መሳሪያዉ አስፈላጊ እንደሆነ አስታዉቃለች።
ከቀናት በፊት ሩሲያ እንዳስታወቀችው ከሆነ ከሀምሌ ወር አንስቶ ታክቲካል የኒውክሌር ጦር መሳሪያን በቤላሩስ ምድር እንደምታሰማራ ገልፃለች። ይህን ለምዕራቡ ዓለም እንደ ማስጠንቀቂያ ተደርጎ ተወስዷል። ሉካሼንኮ እንዳስታወቁት ሚንስክ የጦር መሳሪያዎቹን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ገልፀዋል። "ሁሉም ነገር ዝግጁ ነው። የጠየቅነውን በጥቂት ቀናት ውስጥ ትንሽም ቢሆን የምናገኝ ይመስለኛል” ሲሉ ተናግረዋል።
ሉካሼንኮ በምዕራባውያኑ ሀገራት አነሳሽነት ጥቃት የሚሰነዘርብን ከሆነ ምላሽ ለመስጠት መሳሪያውን ከመጠቀም ወደኋላ እንደማይሉ አስጠንቅቋል። "ለምን የኒውክሌር የጦር መሳሪያእን እንደምንፈልግ ልንገራችሁ አንድም የውጪ ወታደር በቤላሩስ ምድር ላይ እግሩን ካሰረፈ እንጠቀምበታለን" ሲሉ ተናግረዋል።
“እግዚያብሄር እነዚህን መሳሪያዎች ለመጠቀም ውሳኔ እንዳልሰጥ ይጠብቀኝ። ነገር ግን በኛ ላይ ጥቃት ሲሰነዘር ማመንታት እንደማይኖር እወቁት ሲሉም አክለዋል። ከሶቪየት ኅብረት መፍረራረስ በኋላ ሩሲያ የጦር መሳሪያዎችን ስታንቀሳቅ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።
" ጥንቃቄ አድርጉ "
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፤ የተቋሙ አርማ የታተመባቸውን የኪስ ቦርሳዎች በማዘጋጀትና መታወቂያ በማስመሰል ለሕገወጥ ተግባራት ጥቅም ላይ ለማዋል ሙከራ ሲያደርጉ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገለፀ።
አገልግሎቱ በላከው መግለጫ ÷ የተቋሙ አርማ የታተመባቸው የኪስ ቦርሳዎችን ወይም ዋሌቶችን በማዘጋጀትና መታወቂያ በማስመሰል ለሕገወጥ ተግባራት ጥቅም ላይ ለማዋል ሙከራ ሲያደረጉ የነበሩ ተጠርጣሪ ግለሰቦች #እጅ_ከፍንጅ መያዛቸውን ገልጿል።
ኅብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግም ጥሪ ቀርቧል።
አገልግሎቱ ፤ በዚህ ሕገወጥ ድርጊት የተሰማሩ ተጠርጣሪ ግለሰቦች የተቋሙ አርማ የታተመባቸውን የኪስ ቦርሳዎችን ወይም ዋሌቶችን መታወቂያ አስመስለው በማዘጋጀት በተለያዩ አካባቢዎች ለማሰራጨት ሙከራ ሲያደርጉ እንደነበርና ካዘጋጇቸው የኪስ ቦርሳዎች ውስጥ #የተወሰኑት በአንዳንድ ግለሰቦች እጅ እንደገቡ መታወቁን አመልክቷል፡፡
እነዚህ ግለሰቦች የተቋሙ አርማ የታተመባቸውን የኪስ ቦርሳዎች እንደ መታወቂያ በማሳየት በሕገወጥ ተግባር መሰማራታቸውንና በተቋሙ ስም ያለአግባብ አገልግሎት ለማግኘት ሙከራ እያደረጉ መሆኑ እንደተደረሰበት አስታውቋል፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፤ የተቋሙ አርማ የታተመበትን የኪስ ቦርሳ ወይም ዋሌት ይዞ መገኘት ብሎም ሕገወጥ ለሆነ ተግባር ማዋል ሕጋዊ ተጠያቂነትን ያስከትላል ብሏል።
ይህ የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ አርማ የታተመበት የኪስ ቦርሳ በእጁ የገባ ግለሰብ በአካባቢው ለሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ እንዲያስረክብ ወይም በስልክ ቁጥሮች 0115543681 እና 0115543804 በመወደል እንዲያሳውቅ በጥብቅ አሳስቧል።
ይህን ተላልፎ የሚገኝ ማንኛውም ግለሰብም በሕግ ተጠያቂ እንደሚሆን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስጠንቅቋል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሰኔ 03 ቀን 2015 ዓ.ም
ከኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር የተሰጠ መግለጫ
ሰኔ 03/2015 ዓ.ም
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ቁልፍ እሴት ከሆኑት ቀዳሚውና ዋናው ከራስ በፊት ለህዝብና ለሃገር ጥቅም መቆም ነው፡፡
ዩኤስኤአይዲ (USAID) ሰሞኑን አጣርቻለሁ ብሎ ባወጣው መግለጫ ለሰብአዊ እርዳታ የመጣን እህል ከሌሎች መንግስታዊ አካላት ጋር በመሆን መከላከያ ሰራዊታችንም እንደተጠቀመ አድርጎ ያቀረበውን ሪፖርት የተለያዩ ሚዲያዎች ሲዘግቡት አስተውለናል፡፡
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጥብቅ ድስፕሊን የሚመራ ዘመናዊ ሰራዊት ነው፡፡ ሰብዓዊ ድጋፍ የሚደረግላቸውን ወገኖቹን ቀለብ ሊቀማ ቀርቶ፤ ከቀለቡ ቀንሶ የሚያካፍል ሰራዊት መሆኑን የሃገሩ ዜጎች ብቻ ሳይሆኑ በአጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሰላም ማስከበር በተሰማራባቸው ቦታዎች ሁሉ የዕለት ከዕለት ተግባሩ መሆኑን የደረሰላቸው ህዝቦች፤ መንግስታት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሁሉ የሚያውቁት ሰመ ጥር ህዝባዊ ሰራዊት ነው፡፡
አገራችን ኢትዮጵያ ለሰራዊቷ ደመወዝና ቀለብ መስጠት ከጀመረች፤ ቀዳሚ ነን ከሚሉ ሃገራት ተርታ የምትሰለፍ ነፃ እና ታሪካዊት ሃገር ናት፡፡
ሰራዊታችን ዘመናዊ ነው ከሚያስብሉት አንዱ ደግሞ ይኸው ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው የሎጅስቲክ ግዥ እና አቅርቦት ጉዳይ ነው፡፡ የሰራዊታችን ቀለብ ለሃገር ውስጥ ነጋዴዎች እድሉን በመስጠት በግልፅ ጨረታ ተወዳድረው ስንዴም ሆነ ሌሎች ምግብ ነክ ፍጆታዎች የሚቀርብለት በተሟላ አሰራር እና አመራር የሚመራ ሰራዊት ነው፡፡
የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት፡-
1ኛ/ ሠራዊታችን በቂ ሎጄስቲክ ያለው በዓለም አቀፍና በአገር ውስጥ ለተፈናቀሉትና በድርቅ ለተጎዱት በዓይነትና በገንዘብ የሚረዳ እንጂ ተቸግሮ ከአሰራር ውጭ የሚጠቀም አይደለም።
2ኛ/ ሠራዊታችን ማንኛውንም ዓይነት ምግብ በበጄቱ በሕግና በግልፅ ጫረታ ገዝቶ የሚጠቀም እንጂ ተቸግሮ የሕዝብ እርዳታ አካባቢ ሄዶ እርዳታ ላይ የሚሻኮትበት ዓይነት ድህነት የለበትም። ጥቆማ የሰጠ አካል እንኳ ቢኖር እስኪጣራ ሳይጠበቅ፤ እንደ ተቋምና እንደ ሠራዊት ስም የሚያጠፋ የሚዲያ ሽፋን መስጠት የኢትዮጵያን መከላከያ ሠራዊት ክብር ይነካል።
3ኛ/ ምንም እንኳ አገራችን በሚሊዮን የሚቆጠር እርዳታ ጠባቂ ሕዝብ ቢኖራትም ሠራዊቷን መመገብ የምትችልና በቂ ምግብና በጄት በመመደብ ሠራዊቱ ራሱ በሕግና በተቋም ሎጄስትክ አማካኝነት የምትመግብ አገር ናት። ሠራዊታችንም ኩሩና የችግረኞችን ስንዴ የማይሻማ ፕሮፌሽናል ሠራዊት ነው። ስለሆነም የእርዳታ ስንዴ የሚጠቀም ተቋም ወይም ዩኒት ወይም ወታደር የለንም።
4ኛ/ ዩኤስኤአይዲ (USAID) በሠጠው መግለጫ መሠረት ምናልባት የመከላከያ አባል የሆነ ወታደር በማይመለከተው ገብቶ ከመዋቅር ውጪ ሕግ የማስከበር ሥራውን ተጠቅሞ ከሌቦች ጋር በመተባበር እርዳታ ተሰርቆ እንዲወጣ በግል የተባበረ ካለ እና ተጣርቶ ከተገኘ የአገር መከላከያ ሠራዊት አመራር የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል።
መከላከያ ሰራዊት ለሃገሩም ሆነ ለዓለም አቀፍ ሰላም መከበር መሰዋትነት የሚከፍል ምስጉን ሰራዊት ሆኖ እያለ፤ በአገራችን ውስጥና በውጪ አገር ያሉ ጥቂት የአገር መከላከያ ሠራዊት ጥላቻ ያላችው ፅንፈኞች እንዳሉ እናውቃለን። መካላከያን የማጠልሸት ሥራ የቆየና የለመድነው ነው።
የመከላከያ ሠራዊታችንን ህዝባዊ ተፈጥሮ፣ አሰራርና ሥርዓት ሳይታወቅና መረጃ እንኳ ቢመጣ፤ አጣርቶ ሳይታወቅ፤ መረጃ የቀረበበት አካል ሳይጠየቅ፤ የሚዲያ ሽፋን መሰጠት ትክክል አይደለም ብለን እናምናለን። የሚመለከታቸው የእርዳታ ሰጪ ድርጅቶችና የኢትዮጵያ መንግሥት እንዲያጣሩ እንተባበራለን። ከተጣራ በኋላ ሁሉንም ለሕዝብ ይፋ እናደርጋለን።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር
የኢፌዴሪ መከላከያ ሰኔ 01 ቀን 2015 ዓ.ም
“ በዶሎ አልሸባብ ከሰረ ጀግኖቹ ነገሱ ! ”
የኢትዮጵያ ወታደር ጀግና ነው ፍርሃት ያልፈጠረበት። የጠላትን ቅስም ሰባሪነቱ የተመሰከረለት በሠንደቅ ዓላማው ፊት ቃል መዓላ ገብቶ ቃሉን በተግባር ያውላል። ተራሮች የማይበግሩት ፣ ዋሻዎች የማያቆሙት ፣ የበረሃው ንዲድ የማይበግረው የደጋው ቆፈን ከእርምጃው የማይገታው ጀግና የጀግና ልጅ ነው። ይህንኑ እውነታ ደግሞ ወዳጆቹ ብቻ ሳይሆኑ ጠላቶቹም ይመሰክሩለታል።
ወታደሮቿ ስለ ፍቅሯ ተራቡላት፣ ስለ ፍቅሯ ተጠሙላት፣ ስለ ፍቅሯ ከጫፍ ጫፍ ተንከራተቱላት፣ ከጣላቶቿ ጋር ተናነቁላት፣ ስሟን እያነሱ፣ ሠንደቋን እያወሱ ምሽግ ውለው ምሽግ አደሩላት፣ ከአንቺ በፊት እኔን ያድርገኝ እያሉ ቀደሙላት፡፡ ዝናብ መታቸው፣ በረሃው ገረፋቸው፣ አሜካላው ወጋቸው፣ ድካሙ በረታባቸው፡፡ ዳሩ አብዝተው ይወዷታል፣ ከነብሳቸው አስበልጠው ይሳሱላታልና ሁሉንም ስለ ኢትዮጵያ ፍቅር ብለው ረሱት፡፡
የኢትዮጵያ ወታደር የሀገሩን ሉዓላዊነት እና ድንበር ከማስከበር በተጨማሪ በቀጠናው ሠላም እንዲሰፍን እና መረጋጋት እንዲመጣ አሸባሪዎችን የገቡበት እየገባ ድባቅ ከመምታቱም በላይ የኢትዮጵያ ወታደር መጣ ደረሰ ሲባሉ መግቢያው እና መውጫው መላቅጡ ይጠፋቸዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ በአሸባሪነት ከተፈረጁ ቡድኖች መካከል የሚጠቀሰው አልሸባብ ውልደቱም ሆነ እድገቱ በምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ሶማሊያ ነው።
ይህ አሸባሪ ቡድን ጎረቤት ሀገር ሶማሊያን ብቻ ሳይሆን መላው አፍሪካን ለማተራመስ እና ለማሸበር የማይፈጥረው የጥፋት ሴራ እና ተንኮል የለም። በተለይ ደግሞ ምስራቅ አፍሪካን የትርምስ ቀጠና ለማድረግ ተኝቶ አይድርም።
ከሠሞኑ አልሸባብ በኢትዮጵያ ሶማሊያ ድንበር ዶሎ ካምባስ በተባለ ቦታ በሁለት መኪና ማለትም በአንድ አይሱዚ እና በአንድ ኮብራ መኪና ሙሉ ፀረ ሰውና ፀረ ተሽከርካሪ ፈንጆዎችን ጭኖ በሠራዊታችን ላይ ጉዳት ለማድረስ ቢሞክርም በኢትዮጵያዊያን የቁርጥ ቀን ልጆች ሁለቱ መኪናዎች እና ስድስት አሸባሪዎች ከነ ፈንጅዎቻቸው ጋር ዶግ አመድ ሆነዋል።
ይህ የድል ዜና ሲደመጥ ታድያ መላው ኢትዮጵያዊያንን ያስደሰተ ጀግናው ሠራዊታችን ክብሩ የተገለጠበት ሲሆን ለአሸባሪው የአልሸባብ ቡድን ደግሞ ኪሳራው እና ውርደቱ በአደባባይ የታየበት ነው።
የዶሎ ድል በአትሚስ ጥላ ስር የሚገኙትን እና የአትሚስ ድጋፍ ሰጪዎችን የሆኑትን የኢትዮጵያ ወታደሮችን ያኮራ ሲሆን በአትሚስ የሚተዳደሩ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራትንም በኩራት ያስጨበጨበ እና ያስደሰተ ከመሆኑም በላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጀግንነት በገሃድ የታየበትም ነው።
የኢትዮጵያ ወታደር በጎዳናዎች ሲያልፍ ቆሞ ሊጨበጨብለት ፣ ስሙ በተደጋጋሚ ሊጠራለት የሚገባ የጠላትን ቅስም የሰበረ ፣ የጠላትን ምኞት ከንቱ ያስቀረ ፣ ሀገሩን ያስከበረ ነውና የጀግንነቱ ልክ ከሚታሠበው በላይ ነው።
“ ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ለዘላለም ትኑር ! ”
የቀጣዩ ዓመት የመከላከያ በጀት 50 ቢሊዮን ብር ሆኖ ቀረበ!
ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከቀረበው 801.65 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ የፌዴራል መንግሥት በጀት ውስጥ ለመከላከያ ሚኒስቴር 50 ቢሊዮን ብር ሲመደብ ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የወደሙ ተቋማትና አገልግሎቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ ደግሞ 20 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙ ተገለጸ።
በ2015 በጀት ዓመት ለመከላከያ ሚኒስቴር 84 ቢሊዮን ብር ተይዞ የነበረ ሲሆን በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ባስከተለው ተጨማሪ ወጪን ለመሸፈን በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ወራቶች ቀርቦ ከጸደቀው የ122 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ውስጥም መከላከያ ሚኒስቴር የአንበሳውን ድርሻ በማግኘቱ የሠራዊቱ የ2015 አጠቃላይ በጀት ለመጀመሪያ ጊዜ መቶ ቢሊዮን ብር በላይ ተሻግሯል።
የሰሜኑ ጦርነት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መፍትሔ ማግኘቱን ተከትሎ መከላከያ ሚኒስቴር ለ2016 በጀት ዓመት 50 ቢሊዮን ብር እንደተያዘለት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረበው የቀጣዩ ዓመት ረቂቅ በጀት ለመረዳት ተችሏል።
ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከቀረበው ረቃቅ በጀት ውስጥ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የወደሙ መሠረተልማቶችን ወደነበሩበት ለመመለስ 20 ቢሊዮን ብር እንደተያዘም ሰነዱ ያመለክታል።ለ2016 በጀት ዓመት ለክልሎች ድጎማ 214 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲሆን በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ከሁለት ዓመታት
በላይ ከፌዴራል መንግስት የበጀት ድጎማ ያለገኘው የትግራይ ክልል ለቀጣዩ በጀት ዓመት 12.5 ቢሊዮን ብር ተመድቦለታል።
ለክልሎች ድጎማ ከተያዘው በጀት ውስጥ እንደሁልጊዜው ትልቁን ድርሻ የሚወስዱት ኦሮሚያ ፣ አማራና የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች ሲሆኑ ፤ እንደቅደም ተከተላቸውም ብር 71.9 ቢሊዮን ፣ ብር 45.1ቢሊዮን እና ብር 26.9 ቢሊዮን ተመድቦላቸዋል።
በተጨማሪም ፣ ሶማሌ 20.8 ክልል ቢሊዮን ብር፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝች ክልል 6.4 ቢሊዮን ብር፣ ሲዳማ ክልል 8.5 ቢሊዮን ብር ተደልድሎ በረቂቅ በጀቱ ቀርቧል፡፡በተመሳሳይ ፤ ለአፋር ክልል 6.3 ቢሊዮን ብር፣ ለቤንሻንጉል ክልል 3.8 ቢሊዮን ብር፣ ለጋምቤላ ህዝቦች ክልል 2.7 ቢሊዮን ብር፣ ለሃረሪ ህዝብ ክልል 1.5 ቢሊዮን ብር፣ ለአዲስ አበባ ከተማ አስታደዳር 5.2 ቢሊዮን ብር፣ ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳዳር 1.8 ቢሊዮን ብር ሆኖ በረቂቁ ተደልድሏል፡፡
Via Reporter
ከፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል የተሰጠ መግለጫ‼️
የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል በተለያዩ ጊዜያት የአዲስ አበባ ከተማን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ የተቀናጀ ኦፕሬሽን ሲያካሄድ ቆይቷል።
የጋራ ግብረ ኃይሉ ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ አንዳመለከተው፤ ግብረ ኃይሉ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ የፀጥታ ችግሮችን ለመፍጠር የተዘጋጁ ኃይሎች እንዳሉ ደርሼባቸዋለሁ ብሏል።
በአዲስ አበባ ከተማ ተከታታይ የተቀናጀ ኦፕሬሽን ስለሚያካሄድ ህብረተሰቡ ይህን አውቆ ትብብር እንዲያደርግ፤ በአካባቢው ፀጉረ ልውጦችን ሲመለከት ጥቆማ እንዲሰጥና አካባቢውን እንዲጠብቅ የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ አሳስቧል።
ህብረተሰቡ አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙት፤
👉 በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች፣
👉 በስልክ ቁጥር +251 111 11 01 11፣ +251 115 52 63 03፣ +251 115 52 40 77፣ +251 115 54 36 78 እና +251 115 54 36 81፣ +251 115 54 36 84፣ +251 115 54 38 04፣ +251 115 31 22 08፣ +251 115 31 22 23፣ +251 115 31 22 47፣ +251 115 31 22 20፣ +251 115 31 20 63፣ +251 115 31 20 33፣ +251 115 31 21 31፣ +251 115 31 22 21፣ +251 115 31 20 42፣ +251 115 31 20 05 ጥቆማዎችን በፍጥነት በመስጠት ወይም በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ ኃይሎች መረጃውን በአካል በማድረስ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።
የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ በቀጣይ የሚደርስበትን ውጤት ለህዝብ እየገለፀ እንደሚሄድ አስታውቋል።
የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል
ግንቦት 30 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ሰበር ዜና
አልሸባብ ዶሎ በተባለ አካባቢ ሊፈጽም የነበረው የሽብር ጥቃት ከሸፈ
ዛሬ ከረፋዱ አምስት ሰዓት አካባቢ አልሸባብ የተባለው አሸባሪ ቡድን በኢትዮ ሶማሊያ ድንበር አካባቢ በሚገኘው የኢትዮጵያ መከለከያ ሠራዊት ካምፕ በሁለት መኪናዎች ላይ የተጠመዱ ቦንቦችና ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎችን በማሰማራት ጥቃት ለመፈጸም ሞክሮ እንደነበር ተገለጸ፡፡
ቡድኑ ያሰማራቸው አጥፍቶ ጠፊዎችና ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ካምፕ ከመድረሳቸው በፊት በተወሰደባቸው እርምጃ የተደመሰሱ ሲሆን፤ የቡድኑ ዕኩይ ሴራም መክሸፉ ተገልጿል፡፡ ከስፍራው የሚገኙ ተዓማኒ ምንጮች እንዳመለከቱት፤ በኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይም ሆነ በንብረት ላይ ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም፡፡
የኮማዶና አየር ወለድ ዕዝ በጥገና ሙያ ያሰለጠናቸውን የሠራዊት አባላት አስመረቀ፡፡
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ መገናኛ እና ኢንፎርሜሽን መምሪያ በግንኙነት ሬዲዮ እና በጀኔሬተር ጥገና ለሁለት ወራት ያሰለጠናቸውን የሠራዊት አባላት አሥመርቋል።
የዕዙ የመገናኛ እና ኢንፎርሜሽን መምሪያ ሃላፊ ኮሎኔል አንበሱ ማርያም የስልጠናው አላማ በቂ ሙያተኛ በማፍራት በግንኙነት መሳሪያዎች ላይ የሚደርሰውን የብልሽት ችግር በፍጥነት እና በቅርበት በመፍታት የክፍሉን ግዳጅ የተሳለጠ ማድረግ ላይ መሠረት ያደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ተመራቂዎችም ይህንን ተገንዝበው በስራ ሂደት ውስጥ አቅማቸውን በተግባር ስራ እየገነቡ በየክፍላቸው የተጣለባቸውን ሙያዊ ሃላፊነት በብቃት እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
ስልጠናው በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር ልምምድ የተደገፈ መሆኑን የዕዙ የግንኙነት ሬዲዮ እና ጀኔሬተር ጥገና ቡድን መሪ ሻምበል ጥላዬ ሸንኮሩ በስልጠናው ሪፖርታቸው አብራርተዋል፡፡
ከአሳልጣኞች መካከል ምክትል መቶ አለቃ ደመላሽ ባንቲገኝ የክፍሎችን የጥገና ሞያተኛ ችግር በመፍታት የግንኙነት ቁሳቁሶችን ከብልሽት ለመከላከል እና ከተበላሹም በቅርበት ለመጠገን ታስቦ ትምህርቱ ከቅድም መከላከል ጥንቃቄ ጋር ለሰልጣኞች መሰጠቱን አውስተው ስልጠናውም በክፍሎች ውስጥ ሊያጋጥሙ ይችላሉ በተባሉ ችግሮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል፡፡
ከሰልጣኞች መካከል መሰረታዊ ወታደር ተሻገር አድማሱ በግንኙነት ሬዲዮ እና በጀኔሬተር ጥገና ለሁለት ወራት ስልጠና መሠጠቱን እና ከስልጠናውም በቂ እውቀት ማግኘቱን ገልፆ ወደ ክፍሉ ሲመለስ በግንኙነት ቁሳቁሶች ላይ የሚያጋጥሙ እውክታዎችን በማስወገድ የከፍሉን ግዳጅ ውጤታማ በማድረጉ በኩል የሚጠበቅበትን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
ግንቦት 29 ቀን 2015 ዓ.ም
የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ሃላፊ በብላቴ ኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ ማዕከል በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ።
በማሠልጠኛ ማዕከሉ በመገኝት እየተሰሩ የሚገኙ የመሰረተ ልማቶችን የጎበኙት የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀኔራል ደስታ አብቼ ሲሆኑ የአንፊ ቲያትር፣ደረጃውን የጠበቀ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ዝርጋታ፣የጥበቃ ማማ እንዲሁም የመፀዳጃ ቤት ግንባታዎችን ጎብኝተዋል። በቀጣይ በዕቅድ የተያዘውን የማሠልጠኛ ማዕከሉን ማስተር ፕላንም ተመልክተዋል።
ሌተናል ጄኔራል ደስታ ማሠልጠኛ ማዕከሉ ብቃት ያላቸው የኮማንዶ፣አየር ወለድ እና ልዩ ኃይሎች አመራር እና አባላትን በብቃት እያሠለጠን እንደሚገኝ ገልፀው፡፡ ማሠልጠኛውን ለማዘመን እና ተወዳዳሪ ለማድረግ የተጀመሩና እየተጠናቀቁ ያሉ መሰረተ ልማቶች ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡
የመሰረተ ልማት ዝርጋታው በማሠልጠኛ ማዕከሉ አመራር እና ኮንትራክተሮች እንዲሁም ሙያተኞች ስራው በታሰበውና በታቀደው መሰረት ተጠናቆ አገልግሎት መሥጠት እንዲችል የሚደረገውን ርብርብ ያደነቁት ሌተናል ጄኔራል ደስታ በቀጣይም ስራው በፍጥነት ተጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማሥቻል ጥረቱ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል።
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ምክትል አዛዥ ለውጊያ አገልግሎት ድጋፍ ሜጀር ጄኔራል ታገስ ላምቤቦ በበኩላቸው በማሠልጠኛ ማዕከሉ እየተገነቡ ያሉ መሰረተ ልማቶች በታቀደው መንገድ እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀው ግንባታው ሲጠናቀቅ ለታሰበው የዘመናዊ ሰራዊት ግንባታና ለስልጠና ጥራት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
የኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ ማዕከል አዛዥ ኮሎኔል ቦጃ አጋ በዕቅድ ተይዘው ከተጀመሩት መሰረተ ልማቶች መካከል አንፊ ቲያትር፣የመፀዳጃ ቤትና የጥበቃ ማማ እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ ገልፀው፡፡ሌሎችም በዕቅዳችን መሰረት እንዲጠናቀቁ ሁሉም አመራርና አባላት ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
ረቡዕ ጠዋት! ግንቦት 30/2015 ዓ.ም ዕለታዊ ዜናዎች
1፤ አገራዊ ምክክሩ በቀጣዩ ዓመት በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች እንደሚጀመር የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን መናገሩን ኢዜአ ዘግቧል። ኮሚሽኑ የተሳታፊዎችን መረጣና አጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ በተያዘው ዓመት ለማጠናቀቅ መወሰኑን መናገሩን ዘገባው አመልክቷል። የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች በያሉበት ተወካዮቻቸውን የሚመርጡበት አሠራር መዘርጋቱና ኮሚሽኑ ገልጧል ተብሏል። ኮሚሽኑ ለምክክሩ የለያቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች እያንዳንዳቸው ከየወረዳዎች 50 ተወካዮቻቸውን ለምክክሩ ይልካሉ መባሉን ዘገባው ጠቅሷል።
2፤ በደቡብ ክልል ሃዲያ ዞን ምሥራቅ ባዳዎቾ ወረዳ ደመወዛቸው በወቅቱ እንዲከፈላቸው በመጠየቃቸው የታሠሩ 19 የመንግሥት ሠራተኞች በ50 ሺህ ብር ዋስትና እንደተፈቱ ቪኦኤ ዘግቧል። ታሳሪዎቹ ከ40 ቀናት እስር በኋላ የተፈቱት፣ ክስ የሚያስመሠርትባቸው ማስረጃ ባለማቅረቡ እንደኾነ ዘገባው ጠቅሷል። ፖሊስ ግለሰቦቹን ያሠራቸው፣ በደመወዝ ጥያቄ ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ ለማስናሳት ሞክረዋል በማለት ነበር። ደቡብ ክልል ደመወዝ መክፈል የተሳነኝ፣ ለማዳበሪያ ግዢ ያዋልኩት ገንዘብ ስላልተመለሰልኝ ነው ይላል።
3፤ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና "ፕሪፔይ ኔሽን" የተባለው ዓለማቀፍ ኩባንያ የሥራ ትብብር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የሁለቱ ኩባንያዎች ስምምነት፣ በተለይ በውጭው ዓለም የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የሞባይል መደወያ የአየር ሰዓቶችን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ ያስችላቸዋል ተብሏል። "ፕሪፔይ ኔሽን" በዓለም ዙሪያ ከበርካታ ቴሌኮም ኩባንያዎች ጋር ተመሳሳይ የትብብር ስምምነቶች አሉት።
4፤ በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ ጸጋ በላቸው የተባለች ወጣት የባንክ ሠራተኛን በመጥለፍ የተጠረጠረው ዋና ሳጅን የኋላ መብራት ወልደማርያም በቁጥጥር ስር መዋሉን የመንግሥት ዜና አውታሮች ዘገበዋል። የክልሉ ጸጥታ ቢሮ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ያዋለው፣ በክልሉ በአገረ ሰላም ወረዳ በሚገኝ ጫካ ውስጥ እንደኾነ መግለጡን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር የዋለው፣ ከአንድ ክላሽንኮቭ ጠመንጃና ከአንድ ሽጉጥ ጋር ነው ተብሏል። ተጠርጣሪው የሀዋሳ ከንቲባ ጸጋዬ ተኬ የግል አጃቢ የነበረ ሲኾን፣ በጠለፋው ወንጀል መጠርጠሩን ተከትሎ ከሥራው እንደ ታገደ ቀደም ሲል እንደተገለጠ ይታወሳል።
5፤ የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ከሰሃራ በታች ባሉ ሦስት አገራት ጉብኝት ሊያደርጉ መኾኑን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። አል ሲሲ የሚጎበኙት፣ ዛምቢያ፣ ሞዛምቢክንና አንጎላን እንደኾነ ዘገባዎቹ አመልክተዋል። የፕሬዝዳንት ሲሲ ጉብኝት ዓላማ፣ አሕጉራዊ ትስስርንና የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር እንደኾነ ተገልጧል። ሲሲ ነገ ዛምቢያ በምታስተናግደው 22ኛው የኮሜሳ መሪዎች ስብሰባ ላይ ይሳተፋሉ ተብሏል።
6፤ ቦይንግ ኩባንያ 787- ድሪምላይነር አውሮፕላኖቹን ለደንበኞቹ ማቅረቡን እንደሚያዘገይ ማስታወቁን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኩባንያው ዘመናዊውን አውሮፕላኑን ምርት ለማዘግየት የወሰነው፣ በአውሮፕላኑ ሥሪት ላይ አዲስ እክል በማግኘቱ እንደኾነ መግለጡን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። የበረራ ሚዛን መጠበቂያቸው ላይ እክሉ የተገኘባቸው 90 አውሮፕላኖች ሲኾኑ፣ ኩባንያው እያንዳንዱን አውሮፕላን ለማስተካከል ሁለት ሳምንት ይፈጅብኛል ማለቱ መናገሩ ተገልጧል። አሁን በረራ ላይ ያሉ ድሪምላይነር አውሮፕላኖች ጥገና ያስፈልጋቸው እንደኾነ ግን ኩባንያው አላብራራም ተብሏል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የድሪምላይነር አውሮፕላን ባለቤት ነው። #ሼር በማድረግ ተባበሩን🙏
👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇
"ጥቅሙን ከሀገር ጥቅም አንፃር"
በቋንቋህና በእምነትህ የማትመካው የሀገር እና ህዝብ ሃብት የማትመዘብረው በምንም ምክንያት በሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ ሀገራት ስምሪት በሰው ልጆችን ክብር የማትነካው ወታደር ስትሆን ነው።ወታደር ጀግና እንጂ ጀብደኛ አይደለም።
አብዛኛው ሰው በተፈጥሮው ግለኝነት ያጠቀዋል። በትንሹ አይረካም። ጥሮ ግሮ የሆነ ከፍታ ላይ ሲደርስ ይሄኛው ስኬቱ ምንም ይሆንበታል። የሚቀጥለው ደረጃ ይናፍቀዋል።
ለራስ ሳይሆን ለሀገር ሲባል በቁጠባ መጠቀምን መካን ፤ንብረት ያላማባከን ፤ በአለባበስ ፣በአነጋገር አርአያ መሆን ፤የምታሳሳዋን ህይወት ለመስጠት መወሰን ፍርሃትን አሽቀንጥረህ ጥለህ ጀግና የመሆንን ማንነት የምትላበሰው ወታደር ስትሆን ነው።
ወታደር ስትሆን ለድካምህ ዋጋ አትተምንም። የደምና የህይወቴ ክፍያ ይሄን ያህል ነው ብለህ አትወስንም። ከፋኝ ብለህ አታኮርፍም።ደከመኝ ብለህ አታርፍም። አገኘሁ ብለህ አትዘርፍም። ከሥርዓት አትወጣም። ሥነሥርዓት አታዛንፍም።
ነጋዴው ትርፉን እያሰበ ተግቶ ይሠራል። ተማሪው የተሻለ ውጤት ለማምጣት በደንብ ያጠናል። መሐንዲሱ ግንባታውን በወቅቱና በልክ ለመጨረስ ይተጋል ወዘተ ወዘተ። ሐኪሙ የታመመን ለማዳን ይደክማል። ወታደር ከፊቱ መቁሰል የአካል መጉደል እና ሞት እንዳለ እያወቀ ከልቡ ይሠራል። ጠብመንጃ ባልያዘ እጁም ያርሳል ያርማል ያክማል ያለማል።
በተለይ የኢትዮጵያ ወታደር የክፍያው መጠን አያሳስበውም። የሚያሳስበው ሠንደቅ ዓላማዋ ዝቅ እንዳይል በልቡ ላይ የነገሰችው ሀገሩ ከልኳ እንዳትጎድል ብቻ ነው። ስኬቱን የሚለካው በሀገራዊ ሁለንተናዊ ስኬት እርካታ የወገኑ ሠላምና ደስታ ነው።
ወታደር የተለየ ማንነት ለሀገርና ህዝብ የተሠጠ በረከት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። በሙገሳ የማይኩራራ፤ ሐሜትና ስም ማጥፋት የማይፈራ፤ ለእይታ ሳይሆን ለዓላማው ስኬት ለገባው እውነት የሚሠራ የሀገርን መልክ የያዘ ህዝባዊ ሐይል ነው። ታሪክ እየሠራ ትውልድ እያፈራ ዘመን ተሻጋሪ የሆነ ተቋም ባለቤት ነው።
የማይላላ እምነት፣ የማይገደብ ፅናት፤ የማይነጥፍ ጀግንነት ፤የማይቀየር እውነት፤ እያደገ የሚሄድ ብርታት ባለቤት መሆን ነው። አቀበት ሲወጣ ቁልቁለት ሲወርድ በቆላና ደጋ ሲንከራተት በሐሩሩ ክብደት የብርዱ ክፋት አይማረርም ። ችግር ይፈታል እንጂ እናት ሀገሩ ላይ ችግር አይፈጥርም።
ወታደር ዓመቱን ሙሉ ሲሠራ የሚታየው ያፈሰሰው ላብ ፤የደከመው ድካም፤ የቁስሉ ህመም ሳይሆን የውድ ሀገሩ ከፍታ ከራሱ በላይ የሚወደው ህዝቡ እርካታ ነው። ወታደር ሀገሩ እንዳታንስ ይለፋል እንጂ አነሰኝ አይልም።
ወታደር ሐላፊነትና ተግባሩን ጠንቅቆ ያውቃል። ይማራል ይሰለጥናል። ያልገባውን ይጠይቃል፤ ያላወቀውን ያውቃል፣ በቆየ ቁጥር በዕውቀትና ክዕሎት በአስተሳሰብና መልካም ባህሪ ይልቃል እንጂ ያለቦታው አይገኝም። ዜጎቹን በሚከተሉት እምነት በያዙት የፖለቲካ አመለካከት አይመዝንም።
ወታደር የሚጣላው፣ ደሙ የሚፈላው፣ ከቅርብም ሆነ ከሩቅ፤ ከውጭም ሆነ ከውስጥ፤ ሀገሩን የሚጎዳ ተግባር ጎልቶ ሲወጣ አፍጥጦ ሲመጣ ነው። በህግ አግባብ የሚንቀሳቀስ ዜጋውን ሁሉ ያገለግላል። ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ለግል ወይም የቡድን ፍላጎት ሀገሩን ለመጉዳት የፈለገን ይታገላል።
ወታደር ሰው ነው። ግን ከሰው በላይ ይለፋል። ለሰው ልጆች ሲል ምናልበትም ያለ ጊዜው ያልፋል። በመድማቱ በመቁሰሉና በመስዋቱ ሀገርን ያተርፋል።
ወታደር የበቃ መምህር የተካነ ዶክተር በተግባርና በልምድ ያደገ መሐንዲስ አብራሪ የህግ ባለሙያ የአስተዳዳር ሰው የመገናኛ ጥበባኛ የሎጅስቲክ ሊቅ የተግባቦት ሠራተኛ ተኳሽ አስተዋይ መሪ ተመሪ መሠረታዊ ወታደር ባለሌላ ማዕረግ መሥመራዊ መኮንን ከፍተኛ እና ጄኔራል መኮንን የሌሎች ተቆጥረው የማይዘለቁ ሙያዎች ባለቤት ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ከሁሉም በላይ እስከ ሞት እየሠራ ከሁሉም ዜጋ በታች ክፍያ ይቀበላል። ጥቅሙን በሀገር ጥቅም ብቻ ያሰላል። ጥቅሙን ከሀገር ጥቅም አንፃር የሚያሰላ ነው ወታደር።
ፈይሳ ናኔቻ
#ልዩ_መረጃ‼👇👇👇
በጎጃም ደብረ ኤልያስ ሥላሴ ገዳም መሽገው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩት እስክንድር ነጋና ግብረዓበሮቹ ላይ በተወሰደው ርምጃ ክልሉን የማተራመስ ሴራቸው መክሸፉን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ።
በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ የሚገኘውን የሥላሴ ገዳም ከለላ በማድረግ መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ላይ በተወሰደው ርምጅ በእስክንድር ነጋና በግብረአበሮቹ ለውጊያ ሲውል የነበረው ምሽግ መሰበሩንና በ200 ታጣቂዎችም ላይ ርምጃ መወሰዱን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡
የታጣቂ ቡድኑ መሪና አስተባባሪ የነበረው እስክንድር ነጋና ጥቂት ግብረዓበሮቹ ከአካባቢው ለመሰወር ቢሞክሩም በዋናነት የመከላከያ ሠራዊት እንዲሁም የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ለማዋል እግር በእግር በመከታተል የተቀናጀ ኦፕሬሽን እያካሄዱ መሆኑንም ግብረ ኃይሉ ገልጿል፡፡
የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ፤ ባልደራስ በሚል የፖለቲካ ፓርቲ ሽፋን ሲንቀሳቀስ የቆየው እስክንድር ነጋ የተባለው ግለሰብ የሐሳብ የበላይነትን በማረጋገጥ ዓላማውን ማሳካት ሲሳነው በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ጊዜያት ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲሞክር እንደነበር አስታውሷል፡፡
ግለሰቡ ይህ እንዳልተሳካለት ሲያውቅ፤ መንግሥትን በኃይል ለመጣል በማቀድ የአማራ ሕዝባዊ ግንባር የተባለ አደረጃጀት በመፍጠር ሽመልስ ስማቸው፣ ሰውመሆን ወረታውና መንበሩ ካሴ ከተባሉ ግብረዓበሮቹ እንዲሁም ከሌሎች ጥቂት የክልሉ ጽንፈኛ ኃይሎች ጋር በመቀናጀትና በህቡዕ በመንቀሳቀስ ታጣቂዎችን ሲመለምል፣ ሲያደራጅና ስምሪት ሲሰጥ እንደነበር መግለጫው ጠቁሟል። ግንባሩን በሀገር ውስጥ ራሱ ሲመራ በውጭ ደግሞ ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ የተባለ ግለሰብ ያስተባብራል ያለው መግለጫው፤ ሁለቱ በፈጠሩት ትስስር በክልሉ የትጥቅ ትግል በማድረግ ሕዝቡን ወደማያባራ ጦርነት ለማስገባት ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውንም የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ማረጋገጡን አመልክቷል፡፡
መሠረቱን ምዕራብ ጎጃም ቡሬና አባይ በረሃ አካባቢ አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰቡ የሃይማኖት ሽፍንና እንደ ከለላ ለመጠቀም ከሌሎች የቡድኑ ታጣቂዎች ጋር ወደ ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ በማቅናት ከሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ በሥላሴ ገዳም አካባቢ ምሽግ ቆፍረው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል በህቡዕ ሲያሴሩ እንደነበር ያመለከተው የግብረ ኃይሉ መግለጫ፤ በተለይ የገዳሙ አስተዳዳሪ የሆኑትን አባ ኤልሳን ለዚህ ሕገወጥ ተግባር ሲጠቀሙ እንደነበር ጠቅሷል፡፡ አስተዳዳሪውም ከሃይማኖቱ አስተምህሮ ውጭ በገዳሙ ውስጥ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ እንዲደረግ ከመፍቀድ ባሻገር ከሌሎች መነኮሳት ጋር በማበርና የጦር መሣሪያ ጭምር በማንገብ ከጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ጋር ተሰማርተው እንደነበርም ጠቁሟል፡፡
መግለጫው አክሎም እነዚህ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን ሕግ የማስከበር ተልዕኮ ለማደናቀፍ በማለም የዜጎችን ሰላማዊ ሕይወት በሚያስተጓጉሉ ቅስቀሳዎችና ተግባራት ተሰማርተው መቆየታቸውን አስታውሷል፡፡ በአማራና በወለጋ አዋሳኝ አካባቢዎችም ግጭት እንዲቀሰቀስ ሲያደርጉ እንደነበርም አመልክቷል፡፡
የጥፋት ቡድኑ አባላት ሕገ ወጥ እንቅስቃሴውን እንዲያቆሙና በውይይት ወደ ሰላም እንዲመጡ ከክልል እስከ ወረዳ በሚገኙ አካላት ተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም አለመሳካቱን የጠቆመው መግለጫው፤ ይልቁንስ ገዳሙን ምሽግ በማድረግ በአካባቢው አስተዳደር፣ በፖሊስ፣በሚሊሻና በማኅበረሰቡ ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት ሲፈጽሙ መቆየታቸውን አስታውቋል፡፡ በሃይማኖት ሽፋን ፖለቲካዊ አጀንዳቸውን ለማስፈጸም እንቅስቃሴ ሲያደርጉ እንደነበር መታወቁንም አመልክቷል፡፡
አነዚህ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ከኅብረተሰቡ ባሕልና ዕሴት እንዲሁም ከሃይማኖታዊ አስተምህሮ ባፈነገጠ መንገድ በደብረ ኤሊያስ ወረዳ በሚገኘው ቅድስት ሥላሴ ገዳም ውስጥ ምሽግ በመቆፈር ሕዝቡ ቅዱስ የሚለውን ሥፍራ የጦር አውድማ በማድረግ ለማርከስ ቢጥሩም በዋናነት የሀገር መከላከያ ሠራዊት እንዲሁም የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በመቀናጀት በወሰዱት ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃ ሴራው መክሸፉን ያስታወቀው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረኃይል፤ በታጣቂዎቹ ጥቅም ላይ ሲውሉ የነበሩ የተለያዩ ከባድና ቀላል መሣሪያዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁሟል፡፡
200 የጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ታጣቂዎች መደምሰሳቸውነና የቀሩትም ከመማረካቸውና ከመሸሻቸው ውጪ፤ ቡድኑ የሐሰት ፕሮፓጋንዳ በሚነዛባቸው የማኅበራዊ ትስስር ገፆች በመንግሥት ጸጥታ አካላት በገዳሙና በምዕመናን ጉዳት እንዳደረሰ ተደርጎ የሚሠራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል፡፡
የሀገር መከላከያ ሠራዊትና የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በተቀናጀ መንገድ እርምጃ በወሰዱበት በዚህ ሕግ የማስከበር ስምሪት የአካባቢው ማኅበረሰብ መረጃ በመስጠትና በሌሎችም መንገዶች ያደረገው ትብብር የሚደነቅ መሆኑን ያመለከተው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ ለዚህም ምስጋናውን አቅርቧል፡፡
በቀጣይም ክልሉ ከጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ጸድቶ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲሰፍን ለሚደረገው ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ ኅብረተሰቡ የጋራ ጥረቱንና አጋርነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል
ግንቦት 26 ቀን 2015 ዓ.ም
ወሪ/ት ፀጋ በላቸውን ከተጠርጣሪ ወንጀለኛ ማስመለጥ መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታወቀ
ግንቦት 24/2015 በሲዳማ ብሔራዊ ክልል የፀጥታ ግብረ ኃይል በተደረገ የተቀናጀ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ ጠንካራ ክትትል ወሪ/ት ፀጋ በላቸውን ከተጠርጣሪ ወንጀለኛ ማስመለጥ መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው የፀጥታ ግብረ ኃይሉ ተጠርጣሪ ወንጀለኛ የኋላመብራት ወ/ማሪያምን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ባደረገው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ከትላንት ጀምሮ በምሥራቅ ጉጂ ዞን ቦሬ ወረዳ ጀምሮ ተጠርጣሪ ወንጀለኛውን በመከታተል እና መፈናፈኛ በማሳጣት በዛሬው ዕለት በሻፋሞ ወረዳ ሹሮ ቀበሌ ወሪ/ት ፀጋ በላቸውን ከግለሰቡ ማስጣል ተችሏል ብሏል።
ግለሰቡ ከሕግ ተጠያቂነት ለማምለጥ ወደ ጫካ የገባ ቢሆንም የፀጥታ ግብረ ኃይሉ ያልተቋረጠ ክትትል በማድረግ ተጠርጣሪ ወንጀለኛን በመከታተል ላይ እንደሚገኝም አስታውቋል።
ለዚህ ስምሪት መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ለብሔራዊ መረጃ ደኅንነት፣ ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል፣ ለሻፋሞ ወረዳ አስተዳደር እና የኅብረተሰብ ክፍል የክልሉ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ እና የፀጥታ ግብረ-ኃይሉ ምስጋና አቅርቧል።
ተጠርጣሪ ወንጀለኛውንም በቁጥጥር ሥር በማዋል ለሕግ ለማቅረብ በጫካው ውስጥ አሰሳ እየተካሄደ መሆኑን እና የሚገኙ ውጤቶችን ለመላው የሀገሪቱ እና የክልሉ ሕዝብ እንደሚያሳውቅ መገለጹን የሲዳማ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።
Special News : አሜሪካ ዩጋንዳ ላይ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል አስጠነቀቀች።
የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ፤ ኡጋንዳ ትላንት ያፀደቀችውን የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል የሚያደርገውን ህግ " አሳፋሪ እና ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት " በማለት ተቃወሙ።
ባይደን ፤ " ይህ አሳፋሪ ድርጊት በዩጋንዳ ውስጥ ያለው አስደንጋጭ የሰብአዊ መብት ረገጣ እና ሙስና የቅርብ ጊዜ እድገት አመላካች ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ፕሬዜዳንት ባይደን ፤ የአሜሪካ ብሄራዊ ደኅንነት ም/ ቤት የዩጋንዳው ሕግ አሜሪካ ከአገሪቱ ጋር ባሏት ግንኙነቶች ላይ ምን አንድምታ እንዳለው አጥንቶ እንዲያቀርብ አዘዋል ተብሏል።
ከህጉ ጋር በተያያዘ ፤ አሜሪካ ለኡጋንዳ የምትሰጠውን እርዳታና ኢንቨስትመንት ልታቆም እንደምትችል ባይደን አስጠንቅቀዋል።
የሕጉን ተፅኖ ከግምት በማስገባትም የዩጋንዳ የአጎዋ (AGOA) ተጠቃሚነት እንደሚገመገም አሳውቀዋል።
ፕሬዜዳንቱ በከባድ የሰብአዊ መብት ረገጣ ወይም ሙስና ውስጥ በተሳተፈ ማንኛውም ሰው ላይ #ማዕቀብ እና ወደ አሜሪካ የመግባት #እገዳን ጨምሮ ተጨማሪ እርምጃዎችን እያጤኑ ስለመሆኑ ተናግረዋል።
ከባይደን በተጨማሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አንቶኒ ብሊንከን ፤ ህጉን ተቃውመዋል ፤ መስሪያ ቤታቸውም የአሜሪካ ዜጎች ወደ ዩጋንዳ በሚያደርጉት ጉዞ ላይ መመሪያ እንዲያወጣ አዘዋል።
የባይደን አስተዳደር የዩጋንዳ ፓርላማ አፈ ጉባኤ " አኒታ አሞንግ " አሁን ያላቸውን የአሜሪካ መግቢያ ቪዛ መሰረዙ ተሰምቷል።
ከዚህ ቀደም የዩጋንዳ ፕሬዜዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ፤ #ምዕራባውያን አገራት የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን መብቶች #በአፍሪካ አገራት ላይ #በኃይል ለመጫን እየጣሩ ነው ሲሉ ተናግረው ነበር።
ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ " እንግዳ የሆነ ባህል / ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት እንድንፈቅድ ምዕራባዊያኑ #ማዕቀብ በመጣል ጫና ያሳድራሉ " ሲሉ ነበር የገለፁት።
ምንም እንኳን ምዕራባውያን ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት (ተመድን ጨምሮ) ፕሬዜዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ በዩጋንዳ ምድር የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል በሚያደርገው ረቂቅ ሕግ ላይ ፊርማቸውን እንዳያኖሩና እንዳያፀድቁ ማስጠንቀቂያዎችን ቢሰጡም ፕሬዜዳንቱ ትላንት መጠነኛ ማሻሻያ የተደረገበትን ሕግ በፊርማቸው በማኖር አቅፅድቀውታል።
