የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
前往频道在 Telegram
5 461
订阅者
-40724 小时
-2 4147 天
-2 42630 天
帖子存档
" በመላው ሀገሪቱ የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት በተፈጠረ ችግር የተነሳ በመላው ሀገሪቱ የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።
ችግሩን በመፍታት የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ በኃይል ማመንጫዎች እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው ብሏል።
የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጠይቆ፤ ያሉትን መረጃዎች በፍጥነት የሚያሳውቅ መሆኑንም ገልጿል።
#EEP
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
የሶማሊያ መንግስት ወደ ጁባላንድ ኪስማዮ በረራ እንዳይደረግ ከለከለ፡፡
የሶማሊያ ፌደራል መንግስት ወደ ጁባላንድ አስተዳደር ዋና መቀመጫ ኪስማዮ ምንም አይነት በረራዎች እንዳይደረጉ መከልከሉ ተገልጿል።
በሶማሊያ ፌደራል መንግስቱ እና በጁባላንድ አስተዳደር መካከል የተፈጠረው ልዩነት እጅግ መካረሩን ተከትሎ የፌደራል መንግስቱ ወደ ኪስማዮ የሚደረጉ በረራዎች መከልከሉን የሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
የፌደራል መንግስቱ ከፍተኛ ቁጠር ያለው ወታደር ወደ ጁባላንድ አቅራቢያ እያሰፈረ መሆኑን የጠቀሙት ዘገባዎቹ÷ የሶማሊያ መንግስት ለአየር መንገዶች በሰጠው ቀጥታ መመሪያ ወደ ኪስማዮ እንዳይበሩ ተዕዛዝ ማስተላለፉን አመላክተዋል።
ከሶማሊያ መንግስት ቀደም ብሎ የጁባላንድ አስተዳደር በሶማሊያ የሚንቀሳቀሱ አየር መንገዶች ወደ ራስካምቦኒ ከተማ ምንም አይነት በረራ እንዳያደርጉ መከልከሉን ዘገባዎቹ አስታውሰዋል።
ብቁ አየር ወለዶችን በማፍራቱ ረገድ ማሠልጠኛው የሚጠበቅበትን እየተወጣ ነው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ብርጋዲየር ጄኔራል ከማል ኤቢሶ አየር ወለድ ጥምር ጀግንነትን የሚጠይቅ የላቀ ወታደራዊ ሙያ መሆኑን ገልፀው ብቁ አየር ወለዶችን በማፍራቱ ረገድ ማሠልጠኛውም የሚጠበቅበትን እየተወጣ ነው ብለዋል።
በቢሾፍቱ አየር ወለድ ትምህርት ቤት ተገኝተው የአየር ወለድ ስልጠናን ባስጀመሩበት ዕለት አየር ወለድ የግልና የቡድን ጥምር ጀግንነትን ያቀፈ ግዳጁን በጠላት ወረዳ ከጀርባ፣ በሰተ ግራ ወይንም ቀኝ ከአየር በመዝለል በግልም ሆነ በቡድን የሚፈፅም በመሆኑ በስልጠና ወቅትም ይህንን የሚመጥን ብቃት መላበስ ያሥፈልጋል ነው ያሉት፡፡
ብርጋዲየር ጄኔራል ከማል ኤቢሶ ማሰልጠኛ ማዕከሉ አለም በደረሰበት ቴክኖሎጅ በመጠቀም ብቁ አየር ወለዶችን የማፍራት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳለው አሰታውሰው አሁን ለሚያካሂደው ስልጠና የከፍሉ ድጋፍ እንደማይለየው በመግለፅ ሰልጣኙም በሚጠበቅበት ደረጃ ከባዱን የአየር ወለድ ስልጠና በፅናት መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
የኮማንዶና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል ዋና አዛዥ ኮሎኔል ቦጃ አጋ በበኩላቸው የአየር ወለድ ትምህርት ቤት በማዕከሉ ስር ከሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱና ከተመሰረተ 64 አመታትን ያሥቆጠረ መሆኑን ገልፀው በዚህ ጊዜ በርካታ የሀገር ባለውለታ ጀግና አየር ወለዶችን ማፍራቱን ተናግረዋል።
ከአሰልጣኞች መካከልም ሻለቃ አሉላ አባ እና ሻምበል አይዳ አላሮ አንድ ሰው አየር ወለድ ለመሆን ከኮማንዶ ስልጠና ጀምሮ በከባድና ፈታኝ የስልጠና ሂደት ውስጥ እንደሚያልፍ ገልፀው ባላቸው ብቃት በመታገዝ የሀገር አልኝታ የሆኑ ሀገርን የሚያሻግሩ እና ሙያዊ ብቃት ያላቸው አየር ወለዶችን ለማብቃት ጠንክረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ አብዱራህማን ሀሰን
ፎቶግራፍ አብዱራህማን ሀሰን
የሶማሊላንድ እና አሜሪካ የሁለትዮሽ ውይይት
ሶማሊላንድ እና አሜሪካ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር እና በቀጣናው ሰላም ማስፈንን ያለመ ውይይት አካሂደዋል፡፡
በአሜሪካ የሶማሊያ አምባሳደር ሪቻርድ ሪሌይ እና የምስራቅ አፍሪካ የፀጥታ ግብረ ሀይል ኮማንደር ሜጀር ጄኔራል ብሪያን ቲ ካሽ ማን የተመራ የአሜሪካ ከፍተኛ ልዑክ ከተመራጩ የሶማሊላንድ ፕሬዚዳንት ጋር በሀርጌሳ ተወያይቷል፡፡
በውይይቱ የአሜሪካ ልዑክ ሶማሊላንድ ያካሄደችውን ሰላማዊ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አድንቆ፣ አዲስ ለተመረጡት የሶማሊላንድ ፕሬዚዳንት አብዱራህማን ሞሃመድ አብዱላሂ ኢሮ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፏል፡፡
የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ግልፅ፣ አሳታፊ እና ዴሞክራሲያዊ ነበር ያለው ልዑኩ፤ ይህም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ከፍተኛ አድናቆት ማግኘቱን ገልጿል፡፡
በሶማሊላንድ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላም እና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዕድሎችን በተመለከተ እንዲሁም በሶማሊላንድ እና አሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙት ለማጠናከር ያለመ ምክክር አድርገዋል፡፡
አብዱራህማን ሞሃመድ አብዱላሂ ኢሮ÷ ከአሜሪካ ልዑክ ጋር ቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነትን ለማረጋገጥ፣ ዴሞክራሲን ለማስፋት ያለመ ምክክር ማድረጋቸውን በኤክስ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል፡፡
ውይይቱ ሶማሊላንድና አሜሪካ ያላቸውን የጋራ ተልዕኮ የሚያረጋግጥ ነው ማለታቸውን ሆርን ዲፕሎማት ዘግቧል፡፡
+3
የትላንቷ "ፀሐይ" አውሮፕላን‼️
✍️ "ፀሐይ" ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በፊት በኢትዮጵያ የተሰራች ብቸኛ አውሮፕላን ናት ፣
✍️ የ1930ዎቹ የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ጥረት ማሳያ ናት፣
✍️ "ፀሐይ" አውሮፕላን ከጣሊያን በየካቲት ወር 2016 ዓም ወደ ሀገሯ ተመልሳለች፣
የዛሬዋ "ፀሐይ 2" አውሮፕላን‼️
✍️ ''ጸሐይ 2 '' የተሰኘችና በአየር ኃይል የተሰራች አውሮፕላን ለበረራ ብቁ ሆናለች፣
✍️ አውሮፕላኗ ግዳጅን በብቃት መፈጸም የሚያስችል ቴክኖሎጂ የታጠቀች ናት፣
✍️ በኢትዮጵያ አየር ኃይል 89ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ላይ ለዕይታ በቅታለች
በሁለተኛው የጣሊያን ወረራ ወቅት ወደ ሮም ተወስዳ የነበረ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጣሊያን መንግሥት ጋር በተደረሰ ስምምነት ጥር 21 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ መረከባቸው ይታወሳል።
ማዕከሉ የተሰጠውን ሀላፊነት በብቃት እየተወጣ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 24 ቀን 2017 ዓ.ም
የኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ ማዕከል በፍፁም ጀግንነትና ፅናት የተሰጠውን ሀገራዊ ሀላፊነት በብቃት እየተወጣ እንደሚገኝ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ገልፀዋል፡፡
አዛዥ ይህንኑ የገለፁት ከማዕከሉ አመራሮችና አሰልጣኞች ጋር ስለ ማዕከሉ አጠቃላይ የማሰልጠንና የስራ ሂደት ላይ በተወያዩበት ዕለት ነው። ማሰልጠኛ ማዕከሉ ጠንከራ የሀገር ፍቅርና የማያወላዳ ህዝባዊ አመለካከት ያላቸውና ለዚህ አለማ አስፈላጊውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ የሆኑ ጀግና አመራሮችንና ተዋጊዎችን አሠልጥኖ እያበቃ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
የማዕከሉ አመራሮችና አባላት ሁለገብ ሆነው ያለ እረፍት በሠሩት ስራ ውጤት ማምጣት ተችሏል ያሉት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ሁሉም የማዕከሉ አባላት ይህንን ብቃት ጠብቀው የተሰጣቸውን ታሪካዊ አደራ በብቃት መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
በመድረኩም ከአሰልጣኞች ለተነሱት ጥያቄዎች ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን አሰልጣኞችም በሰጡት አስተያየት የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝን የማድረግ ብቃት ጠብቀው ለማስቀጠል ዛሬም ነገም ያለ ዕረፍት እንደሚሠሩ ገልፀዋል። የማይበገሩ ኮማንዶዎች፣ አየር ወለዶች፣ ፀረ-ሽብር ልዩ ሃይልና ጠንካራ አመራሮችን በብቃት በማሰልጠን ሃላፊነታቸውን በፅናት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
+2
ማዕከሉ የተሰጠውን ሀላፊነት በብቃት እየተወጣ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 24 ቀን 2017 ዓ.ም
የኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ ማዕከል በፍፁም ጀግንነትና ፅናት የተሰጠውን ሀገራዊ ሀላፊነት በብቃት እየተወጣ እንደሚገኝ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ገልፀዋል፡፡
አዛዥ ይህንኑ የገለፁት ከማዕከሉ አመራሮችና አሰልጣኞች ጋር ስለ ማዕከሉ አጠቃላይ የማሰልጠንና የስራ ሂደት ላይ በተወያዩበት ዕለት ነው። ማሰልጠኛ ማዕከሉ ጠንከራ የሀገር ፍቅርና የማያወላዳ ህዝባዊ አመለካከት ያላቸውና ለዚህ አለማ አስፈላጊውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ የሆኑ ጀግና አመራሮችንና ተዋጊዎችን አሠልጥኖ እያበቃ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
የማዕከሉ አመራሮችና አባላት ሁለገብ ሆነው ያለ እረፍት በሠሩት ስራ ውጤት ማምጣት ተችሏል ያሉት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ሁሉም የማዕከሉ አባላት ይህንን ብቃት ጠብቀው የተሰጣቸውን ታሪካዊ አደራ በብቃት መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
በመድረኩም ከአሰልጣኞች ለተነሱት ጥያቄዎች ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን አሰልጣኞችም በሰጡት አስተያየት የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝን የማድረግ ብቃት ጠብቀው ለማስቀጠል ዛሬም ነገም ያለ ዕረፍት እንደሚሠሩ ገልፀዋል። የማይበገሩ ኮማንዶዎች፣ አየር ወለዶች፣ ፀረ-ሽብር ልዩ ሃይልና ጠንካራ አመራሮችን በብቃት በማሰልጠን ሃላፊነታቸውን በፅናት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡
ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የካራማራ ኮርስ ሰልጣኝ ኮማንዶዎች ጋር ተወያዩ፡፡
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ 43ኛ ዙር የካራማራ ኮርስ ሰልጣኝ ኮማንዶዎችን በኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ ማዕከል ተገኝተው ገብኝተዋል ከሰልጣኙ ጋርም ተወያይተዋል፡፡
አዛዡ ለሰልጣኞች አሁናዊ የሀገራችንን አጠቃላይ ሁኔታን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ ህዝብን የጥቃታቸው ማዕከል አድርገው በኦሮሚያና በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱት አሸባሪው ሸኔና ፅንፈኛው ሀይል አከርካሪያቸው ተመትቶ በሁለቱም ክልሎች የተሸላ የሠላም ሁኔታ እየተፈጠረ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
የህግ የበላይነት ካልተከበረ ሀገር አይኖርም ዜጎችም ክብር አይኖራቸውም ያሉት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ በህዝብ ድምፅ እንጂ በጉልበተኞች የሚወጣና የሚወርድ መንግስት አይኖርም ሀገርን ለትርምስና ለብጥብጥ በመዳረግ ዜጎችን ለስደትና ለእልቂት የሚያጋልጥ በመሆኑ የህግ የበላይነት መከበር ለአንድ ሀገር የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ወሳኝ መሠረት ነው ብለዋል፡፡
ይህዝብ ጥያቄ በማስመሰል የሚመጣው ጎጠኝነት፣ አክራሪ ብሔረተኝነት እና ነጠላ ትርክት ለህዝቦች አንድነትና ለሀገር ህልውና አደገኛ መሆናቸውንና እነዚህ አስተሳሰቦች በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጭምር እየተደገፈ በተላላኪ ባንዳዎች ታጥቆ የሀገራችንንና የህዝቦቻችንን አንድነት ለመናድ ቢታሠብም በሀገር ወዳዱ የመከላከያ ሠራዊትና በህዝባችን ህልማቸው እየከሸፈ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የኮማንዶና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል ሀገር አሻጋሪ ጀግና አመራሮችና ተዋጊ የኮማንዶ፣ የአየር ወለድና የፀረ-ሽብር ልዩ ሀይል አናብስቶች መፍላቂያ መሆንን በማስታወስ የካራማራ ኮርስ ኮማንዶ ሠልጣኞች ስልጠናቸውን በተገቢው መንገድ በፅናት በመወጣት የኢትዮጵያንና የሕዝቦቿን ዕድገትና ብልፅግና ለማደናቀፍ የሚሞክረውን ማንኛውንም ሀይል በመመከት የአባቶቻችን ታሪክ ለማስቀጠል መዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትና የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ከፍተኛ አመራር የሰላም ስምምነት ተፈራረሙ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም
የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራር የነበሩት ጃል ሰኚ ነጋሳ መንግስት ያቀረበላቸውን የሰላም ጥሪ በመቀበል ነው ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋር በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት አዲስ አበባ ላይ በዛሬው ዕለት የሰላም ስምምነቱን የተፈራረሙት።
በመርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የሰላም ጥሪውን ተቀብለው ለመጡት ምስጋና አቅርበዋል።
ከጦረኞች በላይ ጦርነትን የሚያባብሱት ስለጦርነት የማያውቁ ናቸው ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ እኔ ካለኝ ልምድ አንፃር ጦርነት ጎጂ በመሆኑ የሰላምን መንገድ መርጣችሁ በመምጣታችሁ ልትመሰገኑ ይገባል ብለዋል።
ይህ አይነቱ ተግባር በሌሎች አካባቢዎችም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕስ መስተደድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በበኩላቸው የኦሮሞ ህዝብ በባህልና በወጉ መሰረት በሮቹን ጠምዶና ፈረሶችን ጭኖ በመውጣት ሰላም ይውረድ ባለው መሰረት ጥሪውን ተቀብላችሁ በመምጣታችሁ በራሴና በክልሉ መንግስት ስም አመሠግናለሁ ብለዋል።
አቶ ሽመልስ አብዲሳ የመከላከያ ሠራዊቱ ለሰላም ስምምነቱ ላበረከተው አስተዋፅኦም ምስጋና አቅርበዋል።
በዚህ ዓለም የሰው ልጅ የፖለቲካ ልዩነት ያለው መሆኑን ያወሱት የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራር ጃል ሰኚ ነጋሳ እኛም ያለንን የፖለቲካ ልዩነት በጠመንጃ ከመፍታት በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት ወስነን ነው ስምምነቱን የመረጥነው ብለዋል።
ይህ ስምምነት ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ እፎይታን እንደሚሰጥም ተናግረዋል።
በመረሀ-ግብሩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ጋዛሊ አባ ሲመል የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮምሽነር ሌተናል ጄነራል ዲሪባ መኮንን የኢትዮጵያ መከላከያ መረጃ አመራሮች አባገዳዎች ሀደ ሲንቄዎችና የሃይማኖት አባቶችና ታዋቂ አትሌቶች ተገኝተዋል።
”ፀሐይ 2 ” የተሰኘች አውሮፕላን ለበረራ ብቁ መደረጓ ተገለጸ
#Ethiopia | የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ( ዶ/ር) ተከታዩን መልእክት አጋርተዋል፡፡
በጸጥታና ደህንነት ተቋማት ያከናወነው የሪፎርም ስራ ኢትዮጽያን የሚመጥንና ዘመን ተሻጋሪ ተቋማትን ለመገንባት ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው። የኢትዮጵያ አየር ኃይል ደግሞ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ነው።
አየር ኃይሉ 89ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እያከበረ ባለበት በዚህ ወቅት ”ጸሐይ 2 ” የተሰኘችና በአየር ኃይሉ የተሰራች አውሮፕላን ለበረራ ብቁ አድርጓል።
አውሮፕላኗ ግዳጅን በብቃት መፈጸም የሚያስችል ቴክኖሎጂ የታጠቀች ናት።
ይህም አየር ኃይሉ በ2030 በአፍሪካ ስመጥር አየር ኃይል ለመሆን የያዘውን ራዕይ እውን ለማድረግ በትክክለኛ ጎዳና ላይ መሆኑን የሚያመላክት ነው።
+2
ፅንፈኛው ቡድን በሠራዊታችንና በአካባቢው የፀጥታ ሀይል ጥምር ክንድ ተመትቷል ሞራሉም ወድቋል።
ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም
የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢና የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ በደብረ ብርሃን ከተማ ከሠራዊቱ እና ከሌሎች የፀጥታ ሀይል አመራሮች ጋር በሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራው ፅንፈኛ ቡድንና አሸባው ሸኔ ሠራዊቱ ባደረገው ተከታታይ ስምሪት አከርካሪው ተመትቷል ቀሪውም ተበታትኗል ብለዋል። የፅንፈኛው ቡድን አባላትም ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ስለደረሰባቸው ለሠራዊቱ እጅ እየሰጡ ይገኛሉም ነው ያሉት፡፡
እኛ ክብርና ማዕረጋችን ህዝባችንና ሀገራችን ናቸው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ህዝቡ በከፍተኛ ደረጃ ሠራዊቱን እየደገፈ የሚገኝ መሆኑን ጠቁመው ፅንፈኛው በህዝብ ላይ በተከታታይ በሚፈፅማቸው ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እና በፀረ-ኢትዮጵያዊነት አስተሳሰቡ ከህዝቡ መነጠሉንና የፅንፈኛ ቡድን አመራሮች በብዛት በሠራዊቱ መደምሰሳቸውን አንስተዋል፡፡
የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት ዋና ሰብሳቢና የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ጠላት አሁን የተደራጀ ቁመና እንደሌለው ገልፀው በሰሜን ሸዋ ዞን ኮማንድ ፖስቱ ውጤታማ ስራ በመስራቱና ጠላትን በማሽመድመዱ በዞኑ ውስጥ በርካታ ትምህርት ቤቶች ተከፍተው የመማር ማስተማር ስራቸውን እያከናወኑ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡
በየቦታው የተበታተነው ፅንፈኛ ሀይል በመንግስት የቀረበለትን የሰላም ጥሪ ተቀብሎ ወደ ሰላማዊ ህይወቱ ለመግባት ፈቃደኛ ከልሆነ በተከታታይነት የመደምሰሱ ስራ እንደሚቀጥልም ሌተናል ጄኔራል ሹማ አመላክተዋል፡፡
በአፍሪካ ሀገራት አየር ኃይሎች መካከል ጠንካራ ትስስር እንዲኖር የኢትዮጵያ አየር ኃይል በትኩረት ይሰራል።
ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም
በአፍሪካ ሀገራት አየር ኃይሎች መካከል ጠንካራ ትስስር እንዲኖር የኢትዮጵያ አየር ኃይል በትኩረት ይሰራል ሲሉ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ተናገሩ።
"የተከበረች ሀገር የማይደፈር አየር ኃይል" በሚል መሪ ቃል ለ89 ጊዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የምስረታ ቀንን በማስመልከት የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦች በተገኙበት ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም በአየር ኃይል መኮንኖች ክበብ ተካሄዷል።
በፎረሙ ላይ የሞሮኮ፣ የዩጋንዳ፣ የታንዛኒያ፣ የማሊ፣ የኬንያ፣ የሩዋንዳ፣ የጂቡቲ፣ የናይጀሪያ፣ የኮንጎ ብራዛቪል እና የኒጀር አየር ኃይል አዛዦችን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች፣ የአቭዬሽን ካምፓኒ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል።
ፎረሙን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ይልማ መርዳሳ ፤ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ቴክኖሎጂ በየእለቱ እየዘመነና አዳዲስ መልኮችን እየተላበሰ የሚገኝ በመሆኑ የሀገር ሉዓላዊነት ማስጠበቅ የሚችል ጠንካራና ዘመኑን የዋጀ አየር ኃይል መገንባት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።
ፎረሙ በዘርፉ ያለውን ልምድ እና ተሞክሮ ለመለዋወጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረከትም ተናግረዋል።
በፎረሙም የአፍሪካ አየር ኃይሎች ማህበር ለመመስረት በሂደቱም ላይ በጋራ ለመስራት ጠንካራ መሰረት የምንጥልበት ነው ብለዋል።
ለአፍሪካ አየር ኃይሎች መጠናከር እና እድገት የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከአፍሪካ አገራት አቻዎቹ ጋር በትብብር ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነትም አንስተዋል።
በተለይም አየር ኃይሉ በቴክኖሎጂ አቅም ግንባታና በሰው ኃይል ልማት ረገድ ከተለያዩ አቭዬሽን ተቋማትና ከአፍሪካ ሀገራት አየር ኃይሎች ጋር በጋራ ለመስራት ተነሳሽነት ያላቸው መሆኑንም ተናግረዋል።
ለፎረሙ ተሳታፊዎች ስለ አየር ኃይል አካዳሚ ገለፃ ያደረጉት ምክትል አዛዥ ለአየር ኃይል አካዳሚ ኮሎኔል ገዛኸኝ ነጋሽ አካዳሚው በውስጡ የመሠረታዊ ውትድርና ትምህርት ቤት፣የቴክኒክ ትምህርት ቤት ፣ የበረራ ትምህርት ቤት እና የአመራር ትምህርት ቤትን ያቀፈ መሆኑን ገልፀዋል።
ከዚህ ቀደም የተለያዩ አፍሪካ ሀገራት አብራሪዎችንና ቴክኒሽያኖችን አሠልጥኖ ከማስመረቁም በተጨማሪ በቀጣይም በአፍሪካ ተመራጭ የስልጠና ማዕከል በመሆን የአፍሪካ ኩራት የሆነ አየር ኃይል ለመገንባት በትኩረት እንደሚሰሩም ተናግረዋል።
በፎረሙ ላይ የተሳተፉ የተለያዩ ሀገራት አየር ኃይል አዛዦች የሚመሩትን የአቭዬሽን ተቋም ወቅታዊ ሁኔታ እና የደረሱበትን የዝግጁነት ደረጃ በሚመለከት ገለፃ አድርገዋል።
በፎረሙ ላይ የተሳተፉት የወታደራዊ የአቭዬሽን ትጥቆች አምራች ተቋማት ኃላፊዎች በበኩላቸው የአቭዬሽን ኢንዱስትሪው የደረሰበትን ፈጣን እድገትና ዘመናዊ አየር ኃይል ለመገንባት ተቋሞቻቸው ያላቸውን ፍላጎትና አቅም በተመለከተ ለፎረሙ ተሳታፊዎች ገለፃ አድርገዋል።
በአየር ኃይል መኮንኖች ክበብ ሲካሄድ የነበረው ፎረም የተጠናቀቀ ሲሆን ከሰዓት በኋላ በሐረር ሜዳ ሲኒማ አዳራሽ ከፎረሙ ተሳታፊዎች ጋር በሚከናወን የፓናል ውይይት የአፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም የሚጠቃለል መሆኑ እና 89ኛው የአየር ኃይል የምስረታ ቀን በዓል ህዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው የአየር ኃይል ሐረር ሜዳ ስታዲየም በሚከናወኑ የተለያዩ መርሃ ግብሮች የሚጠናቀቅ መሆኑም ተገልጿል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
+1
"ግብፆች መርዳት ከፈለጉ ለምን ፍልስጤሞችንና ሌሎች ዓረብ አገሮችን አይረዱም ?" - አምባሳደር አብዱላሂ መሐመድ ዱአሌ
አምባሳደር አብዱላሂ መሐመድ ዱአሌ ፤ የሶማሌላንድ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ልዩ መልዕክተኛ ግብፅ በቀጣናው ስለምታደርገው እንቅስቃሴ ምን አሉ ?
(ለሪፖርተር ጋዜጣ ከተናገሩት የተወሰደ)
" የግብፅ እንቅስቃሴ በግልጽ ጣልቃ ገብነት ነው፡፡ ግብፅ ወደ ሶማሊያ መሣሪያ እያሠራጨች ነው፡፡
በመሣሪያ እየታመሰ ባለ ቀጣና ውስጥ ሌላ መሣሪያ እንዲመጣ አንፈልግም፣ በሶማሊያ እያንዳንዱ ግዛት መሣሪያ ተበትኗል፡፡ ነገር ግን ሶማሊያውያን መሣሪያ የተራቡ አይደሉም፡፡
ሶማሊያን ለመጠበቅ በርካታ አገሮች ማለትም ኢትዮጵያ፣ ብሩንዲ፣ ኡጋንዳና ሌሎች ልጆቻቸውን ገብረዋል፣ ውድ ቤተሰቦቻቸውን፣ ገብረዋል፡፡ አሁን በድንገት ግብፅ መጥታ አለሁላችሁ ብትል አይሠራም፡፡
ሶማሊያ የምትባል አገር መጀመሪያ የራሷን የቤት ሥራ ትሥራ፣ ቤቷን ትጠብቅ፡፡
ሶማሌላንዶች ከሕዝብ ገንዘብ ሰብስበን በጀት መድበን አገር እያስተዳደርን ያለን ሰላማዊ አገር ነን፡፡ ከማንም ለምነን አይደለም አገር የምንመራው፡፡
ሶማሊያን ተመልከት ማን እንደሚደግፋቸው፡፡ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ዕርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ናቸው፡፡
የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ ኢትዮጵያንም ሶማሌላንድንም ከማን ጋር ስምምነት መፈጸም እንዳለባቸው ሊነግሯቸው አይገባም፡፡ ግብፆች መርዳት ከፈለጉ ለምን ፍልስጤሞችንና ሌሎች ዓረብ አገሮችን አይረዱም ? አሁን ግብፅ መሣሪያና ወታደር በአውሮፕላን እየጫኑ እያመጡ ነው፡፡
ይህ የግብጽ ጣልቃ ገብነት ትልቅ ሥጋት ነው፡፡ ለሶማሌላንድ ጭምር አደጋ ነው፡፡ ይህን ሥጋት ለአፍሪካ ኅብረትና ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ፣ እንዲሁም ለኢጋድ አሳውቀናል፡፡
#Somaliland #Egypt
+3
የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ ለሠራዊቱ አሥፈላጊ የሆኑ የጋርመንት ውጤቶችን እያቀረበ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም
የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ ለሠራዊቱ አልባሳት እንዲያመርት ታልሞ በ1980 ዓ.ም ተመሰረተ። ዛሬ በ2017 ዓ.ም 37 ዓመቱን አስቆጥሯል። በዚህ 37 ዓመት ጉዞው ኢንዱስትሪው የሚጠበቅበትን ለሀገር አበርክቷል ማለት አይቻልም።
በ2010 ዓ.ም ለውጥ መደረጉን ተከትሎ በሁሉም ሴክተሮች የሪፎርም ስራዎች ተካሂደዋል። ከነዚህም አንዱ የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ ነው።
ይህ ሪፎርም ኢንዱስትሪው እጅግ በሚያስመሰግን ሁኔታ ደረጃ ላይ እንዲደርስ አድርጎታል። ኢንዱስትሪው የሰራዊቱን አልባሳት ከማቅረብ በሻገር ለሲቪል ማህበረሰቡ የተለያዩ አልባሳቶችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብ ጀምሯል። ኢንዱስትሪው ለጊዜው በአዲስ አበባና በአዳማ ከተማ ሱቆችን ከፍቶ ለማህበረሰቡ ማቅረብ ጀምሯል።
የአዳማ ጋርመንት ኢንዱስትሪ ከሚያመርታቸው ምርቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ የወታደራዊ አልባሳት፣ የተለያዩ ዩኒፎርሞች፣ የስራ ልብሶችና ቦርሳዎች፣ የመከላከያና የፖሊስ ማዕረግ ምልክቶችና አርማዎች፣ የፁሑፍ ቀረፃ /ENGRAVING PRODUCTS/ የመኝታ ከረጢት፣ ከሸራ ከቆዳና ከጥብጣብ ውጤቶች የሚሰሩ ትጥቆች፣ የወታደራዊና የሲቪል ተሽከርካሪ መሸፈኛዎች፣ የተለያየ መጠን ያላቸው ድንኳኖች፣ ከቆዳና ከሸራ የሚሰሩ የሴፍቲ ማቴሪያሎች፣ የተለያዩ መጠን ያላቸው ጅንስ ሱሪዎች፣ ቲሸርትና ሸሚዞች ይገኙበታል።
ኢንዱስትሪው በሙያው ከፍተኛ ልምድ ባላቸው ሠራተኞች በመታገዝ ችግር ፈች በሆነ አግባብ ተቋማዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ የሚገኝ መሆኑም ተገልጿል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን የድጋፍ ሠልፍ ተካሂዷል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 15 ቀን 2017 ዓ.ም
በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ነዋሪዎች በዛሬው እለት ጦርነት ሰልችቶናል ሰላም እንፈልጋለን ፣ መከላከያ ሠራዊትን አለማክበር የሚሞትለትን ሀገር እንደመድፈር ይቆጠራል የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን በመያዝ በነቂስ ወጥተው ለሠላም ያላቸውን ድጋፍ ገልፀዋል።
ነዋሪዎቹ በድጋፍ ሰልፉ ላይ ካስተላለፏቸው መፈክሮች መካከል ፡-
👉 እኛ አርሶ አደሮች ሰላምና ልማት ፈላጊዎች እንጂ ጦርነት ናፋቂዎች አይደለንም!
👉 መከላከያ ሠራዊትን አለማክበር የሚሞትለትን ሀገር እንደመድፈር ይቆጠራል!
👉 የራስን ወንድም በመግደል የአማራ ህዝብ ጥያቄ አይፈታም!
👉 ህፃናት ልጆቻችን ከታወጀባቸው ድንቁርና ወጥተው የመማር መብታቸው ይከበር!
👉 ሰላም ስንኖረው ቀላል ስናጣው ደግሞ ከባድ ነውና ለሰላማችን ዘብ እንቆማለን!
👉 ሰላም የሚሰፍነው በጋራ መሥራት ስንችል ነው የሚሉና ሌሎች የሰላም ጥሪን የያዙ መፈክሮችን በማሰማት ለሠላም የድጋፍ ሰልፍ ማካሄዳቸውን አሚኮ ዘግቧል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
+4
ሃገራዊ የልማት ስራዎች በተገቢዉ መንገድ እንዲከናወኑ ሠራዊቱ ህይወቱን ጭምር እየሰጠ ነዉ።
ሌተናል ጀኔራል ሹማ አብደታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 14 ቀን 2017 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽ ስራዎች ኮርፖሬሽን አመራሮች እና አባላት የሰሩትን ስራ ስናይ ለሀገራዊ እድገት፣ ለህዝቦች ብልፅግና እና የልማት ስራ ደጋግሞ መሞት ካስፈለገ መሞት እንዳለብን ያሳያል ሲሉ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ሹማ አብደታ ተናግረዋል።
ኮርፖሬሽኑ ካለዉ የሰዉ ሃብት አስተዳደር ጋር በተያያዘም በርካታ የነገ ሃገር ተረካቢ ወጣት ኢንጅነሮች እና መሃንዲሶች የተዋቀረ መሆኑና የታጠቃቸዉ ዘመኑ የደረሰባቸዉ የቴክኖሎጅ ውጤቶች ጠንካራ መሰረት ያለዉ መሆኑን ያሳያል ሲሉ ገልፀዋል።
ሃገራዊ የልማት ስራዎች በተገቢዉ እና በተፈለገው መንገድ እንዲከናወን ሠራዊቱ ህይወቱን ጭምር እየሰጠ ነዉና ይህን ሠላም የማረጋገጥ ሥራውን በቀጣይም አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ዮናስ አያሌዉ በበኩላቸዉ ሃገር ሲገነባ በአንድ ተቋም ብቻ አይደለም ፤ ጀግናዉ የሃገር መከላከያ ሰራዊትም እኛ የልማት ስራዎችን ስንሰራ ሰላምና ደህንነታችንን ሌት ተቀን የሚያረጋግጥልን በመሆኑ ለስኬቶቻችን መሠረቱ ሠራዊታችን ነው ብለዋል።
ድርጅቱ በሀገራዊ ሪፎርሙ መሠረት እንደገና መነሳቱን የተናገሩት ዋና ስራ አስፈጻሚው በመጪዎቹ አምስት አመታትም ድርጅቱ ከሃገር አልፎ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ኢንቨስት እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
