ch
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

前往频道在 Telegram

Addis abeba Ethiopia

显示更多
5 400
订阅者
-22624 小时
-2 2007
-2 65830
帖子存档
አምባሳደር ተሾመ ሹንዴ በሱማሌላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሾሙ! አምባሳደር ተሾመ ሹንዴ ለሶማሊ ላንድ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ የሹመት ደብዳቤያቸውን ማቅረባቸውን ተነግሯል። አምባ
+2
አምባሳደር ተሾመ ሹንዴ በሱማሌላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሾሙ! አምባሳደር ተሾመ ሹንዴ ለሶማሊ ላንድ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ የሹመት ደብዳቤያቸውን ማቅረባቸውን ተነግሯል። አምባሳደሩ ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ ከኢትዮጵያ መንግስት የተላከ የሹመት ደብዳቤና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ (ዶ/ር) የተላከ መልእክትም አድርሰዋል።አምባሳደር ተሾመ ሃርጌሳ ደርሰው የሹመት ደብዳቤያቸውን ሲያቀርቡ በፕሬዝደንት ሙሴ ቢሂ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የሶማሌላንድ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ለአዲሱ አምባሳደር የእንኳን ደህና መጡ መልካም ምኞታቸውን ገልፀው በቆይታ ግዜያቸው ለሁለቱ ሀገራት አንድነት ፣ ሰላም እና የጋራ ጉዳዮች ለሚሰሩት ስራዎች የቅርብ ድጋፍ እንደማይለያቸው አረጋግጠዋል። አምባሳደር ተሾመ ከፕሬዝደንት ሙሴ ቢሂ ጋር በነበራቸው ውይይት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የጸጥታ ጉዳዮች፣ የሁለቱን ወንድማማች ሀገራት ግንኙነት በማጠናከርና የወደፊት ትብብር ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገልጿል። ይህን ሹመት ተከትሎ እስካሁን ድረስ ከሞቃዲሾ መንግስት በኩል የተባለ ነገር የለም፡፡በተያያዘም የሱማሌላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የግብጽ ጦር በሶማሊያ መስፈሩን እቃወማለው ሲል መግለጫ አውጥቷል፡፡የጦሩ በቀንዱ መስፈርም ቀጠናዊ ቀውስን የሚያዋልድ፣ጦርነት የሚቀሰቅስና መሰል መዘዞችን የሚያስከትል ነው ያለው የሚኒስቴሩ መግለጫ ሃርጌሳ ሂደቱን እጇን አጣጥፋ ተቀምጣ አትመለከተውም ብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ወታደሮች በሶማሊያ የከፈሉትን የደም ዋጋ ማጣጣል ነውር ነው - አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ የኢትዮጵያ ወታደሮች በሶማሊያ የከፈሉትን የደም ዋጋ ማጣጣል ነውር ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
የኢትዮጵያ ወታደሮች በሶማሊያ የከፈሉትን የደም ዋጋ ማጣጣል ነውር ነው - አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ የኢትዮጵያ ወታደሮች በሶማሊያ የከፈሉትን የደም ዋጋ ማጣጣል ነውር ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ተናገሩ። አምባሳደር ታዬ የኢትዮጵያ ወታደሮች ለሶማሊያ እንደ ሀገር መቆም ሕይወት ሰጥተዋል፣ ላብ እና ደማቸውን አፍስሰዋል ብለዋል። ይሁን እንጂ አሁን ላይ የሶማሊያ መንግስት ባለስልጣናት ይህንን እውነት በማይመጥን መልኩ የኢትዮጵያ ወታደሮችን እያጣጣሉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የመልማት ፍላጎቷን እውን ለማድረግ ጎረቤት ሀገራት ማዕከል ያደረግ የውጭ ግንኙነት ትከተላለች ያሉት አምባሳድር ታዬ የትኛውም ሀገር ቅድሚያ ለጎረቤት መስጠት ካልቻለ የትኛውም እድገት ሊረጋገጥ እንደማይችል ጠቁመዋል። ሚኒስትሩ አክለውም የሶማሊያ መንግስት ባለስልጣናት እንደ ሀገር አስተዳዳሪ ሳይሆን እንደ አክቲቪስት እየሆኑ ነው ብለዋል። ይህም ትልቅ አደጋ እንዳለው ነው የገለጹት። በጎረቤት ሀገራት መካከል የሚኖር ግንኙነት የመንግስት ለመንግሥት ብቻ ሳይሆን የህዝብ ለህዝብ በመሆኑ ህዝቡ በባህል እና በቋንቋ ይተሳሰራል ብለዋል። ኢትዮጵያ አሁንም ከሶማሊያ ጋር ያላትን ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኛ ናት ያሉት ሚኒስትሩ እንደ ኢትዮጵያ ምልከታ በናይሮቢ እና በአንካራ የተደረገው ውይይትም ለውጥ እያመጣ እንደነበር አንስተዋል። በሶማሊያ ያለው አሸባሪ ቡድንን እንደ ቀላል አማጺ አድርጎ መውሰድ ይታያል፤ ይሄ ግን ፍጹም ስህተት ነው፤ ቡድኑ በጣም አድገኛ እና አጥፊ ነው ሲሉም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ሶማሊያም ይህንን የሽብር ቡድን በጋራ ሊታገሉና ሽብርተኝነትን አብረው ሊዋጉ ይገባል ብለዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አንድርያስ እሸቴ (ፕ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አንድርያስ እሸቴ (ፕ/ር) ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አንድርያስ እሸቴ (ፕ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አንድርያስ እሸቴ (ፕ/ር) ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። RIP😭😭😭😭 https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93

በሶማሊያ የአትሚስ የኃይል ሽግግር በቀጣናው ላይ አለመረጋጋት የሚፈጥር መሆን የለበትም ሲሉ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ አሳሰቡ ረቡዕ ነሐሴ 22 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በሶማሊያ ከአፍሪካ ኅብረት
በሶማሊያ የአትሚስ የኃይል ሽግግር በቀጣናው ላይ አለመረጋጋት የሚፈጥር መሆን የለበትም ሲሉ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ አሳሰቡ ረቡዕ ነሐሴ 22 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በሶማሊያ ከአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ሰላም ማስከበር ተልዕኮ (አትሚስ) በኋላ የሚደረገው የኃይል ሽግግር የአፍሪካ ቀንድን ወደ ከፍተኛ አለመረጋጋት እና ትርምስ ሊያመራ እንደማይገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ገለፁ።  የሚከናወነው የኃይል ሽግግር ከሁሉም በላይ በቀጠናው በሚገኙ እና አለምአቀፋዊ አሸባሪ ቡድኖች ላይ የተገኘውን ድል የሚያደበዝዝ እና አደጋ ላይ የሚጥል መሆን እንደሌለበትም ነው አምባሳደሩ የገለፁት፡፡  አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፤ በሶማሊያ የአትሚስ የኃይል ሽግግር በቀጣናው ላይ አለመረጋጋት የሚፈጥር እና ወደ ትርምስ የሚያመራ መሆን እንደማይገባው ግልፅ ሊሆን ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዛሬው ዕለት በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ባወጣው መግለጫ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን ለማተራመስ የሚደረግን እርምጃ በዝምታ እንደማትመለከት አስታውቋል፡፡

#GERD🇪🇹 ይህ የኢትዮጵያ ህዝብ የላብና ደም አሻራ ያረፈበት የኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ የአይን ብሌኑም ጭምር ነው። ተማሪው ፣ ሰራተኛው ፣ ወጣቱ ፣ አዛውንቱ ለዚህ ግድብ ካለው ላይ ፤ ከሚበለው ቀንሶ ሰጥቶ ያሰራው ለትውልድ የሚያወርሰው ሀብቱና ቅርሱ ነው። ይህ ግድብ ሀገር ውስጥ በየጊዜው በሚፈጠረው አለመረጋጋት ምክንያት ሀዘን፣ መከፋት፣ መበደል ሲመጣ እንኳን ሁሉም የውስጡን በውስጡ ይዞ " ሀገሬ ትቅደም " ብሎ ተጠናቆ በአይኑ ለማየት ሲል ብዙ ዋጋ የከፈለለት ነው። በፖለቲካ አቋም፣ በሃሳብ፣ በአመለካከት እየተለያየ እንኳ የሀገሩን ጥቅምና ግንድቡን የሚነካበት ነገር ሲመጣ ሁሉን ጥሎ ሽንጡን ገትሮ የተራከረለት ፣ እስከመጨረሻው ድረስም ዋጋ የሚከፍልለት ነው። ይህ ግድብ ገና ከመሰረቱ እንዳይገነባ ፤ ድጋፍም እንዳይመጣ ሲሯሯጡ የነበሩ ብዙ ናቸው። እንዳይሳካ ያልፈነቀሉት ድንጋይ ፤ ያልሄዱበት ቦታ የለም። ግን አልሆነም ፤ ወደፊትም አይሆንም። ዛሬም እነዚህ አካላት ለኢትዮጵያ እንደማይተኙ ግን ግልጽ ነው። ኢትዮጵያ " የሰው ድርሻ አንድም አልነካም፤ የራሴን ግን እጠቀማለሁ " ማለቷ የሚያንጨረጭራቸው ሀገራት በግንባታው ወቅት ዛቻ ሲያዘንቡ ፣ እንዲቆም ለማስፈራራት ሲሞክሩ ፣ በአንድም በሌላ በዓለም አቀፍ መድረክ በውስጥ እና በይፋ ጫና ለማድረግ ሲሰሩ እንደከረሙ የአደባባይ ሚስጥር ነው። ብዙ ብዙ ቢሞክሩም መክነው ቀርተዋል። አሁንም ግን ጩኸታቸው እንደቀጠለ ነው። ለማደናቀፍ የሚደረገው ጥረትም እንደዛው እንደቀጠለ ነው። አንዴ " የመሬት መንቀጥቀጥ ቢመጣ አይፈርሳል " ፤ አንዴ " ጥራቱ አስተማማኝ አይደለም ይደረመሳል " ፤ አልሆን ሲላቸው " በአየር እንመታዋለን ፣በቦንብ እናጋየዋለን " በማለት ብዙ ሲያወሩ ከርመዋል። ከወሬ የዘለል ግን ምንም ማድረግ አይችሉም። እዛው ያሉበት ሆነው የፈለጉትን ማሰብ ይችላሉ ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ እያለ ግን ማድረግ መንካት ግን ፈጽሞ አይቻልም። #Ethiopia #GERD #TikvahEthiopia ©ቲክቫህኢትዮጵያ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ የሰጠው መግለጫ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ቀጣናዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ አውጥቷል፡፡ የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡- በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ (አትሚስ) በቀጣይ የሚኖረው አዲስ የሰላም ተልዕኮ አወቃቀር ሁኔታ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ላይ አዲስ ስጋት ይዞ መምጣቱ ኢትዮጵያን የሚያሳስብ ሆኗል፡፡ የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለዚሁ አዲስ ሽግግር እየተዘጋጁ ባሉበት ወቅት፣ ቀጠናው ሊተነበይ ወደማይቻል ፈተና ውስጥ እየገባ ይገኛል፡፡ በሁኔታው ላይ ቀደም ሲል ኢትዮጵያን ጨምሮ በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ውስጥ ወታደር ያዋጡ አገሮች ተደጋጋሚ ጥሪዎችና አስተያየቶች ትኩረት አልተሰጣቸውም፡፡ የመከላከያ ሠራዊታችንን መልካም ስምና ዝናን እንዲሁም መስዋዕትነት የሚያጠለሹ ተከታታይ መግለጫዎች ሲወጡ ኢትዮጵያ በዝምታ እንድታልፍ ከአንዳንድ ወገኖች በኩል ፍላጐት መኖሩ ይታያል፡፡ ሌሎች ተዋናዮች የአፍሪካ ቀንድ ክልልን ለማተራመስ እርምጃ ሲወስዱ ኢትዮጵያ በዝምታ አትመለከትም፡፡ ይህም በመሆኑ በቀጣናው የብሄራዊ ደህንነቷን አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ሁኔታዎችን ሁሉ በንቃት እየተከታተለች ትገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ ለሶማሊያና ለአካባቢው ሰላምና ፀጥታ መስፈን፣ ለጋራ ዕድገት እና በክልሉ ያሉ ህዝቦች መካከል ያለውን የጠበቀ የእርስ በርስ ትስስር ይበልጥ እንዲጎለብት ያላሰለሰ ጥረት ስታደርግ ቆይታለች፡፡ ኢትዮጵያ ከሶማሊያ መንግስት ጋር ያለውን ወቅታዊ አለመግባባት ለመፍታት እንዲያስችል በተዘጋጁ የውይይት መድረኮች ላይም በንቃት ተሳትፎ አድርጋለች፡፡ በእነዚህ ንግግሮች ተጨባጭ ውጤቶችም ታይተዋል። የሶማሊያ መንግስት እነዚህን ሰላም ለማስፈን የሚደረጉ ጥረቶች  ከማጠናከር ይልቅ ቀጠናውን ለማተራመስ ከሚሹ የውጭ ኃይሎች ጋር እየሰራ ይገኛል፡፡ በሶማሊያ ለማሰማራት የታቀደውን አዲስ የሰላም ተልዕኮ የማዘጋጀት እና የመፍቀድ ኃላፊነት ያለባቸው አካላት ሁሉ በቀጠናው የሚገኙና ቀደም ሲል ወታደር አዋጭ የሆኑ አገራትን ተገቢ የሆኑ ስጋቶች ሁሉ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል፡፡ ለአጭር ጊዜ ፍላጎታቸው እና ከንቱ አላማቸው ሲሉ በክልሉ ውጥረትን ለማቀጣጠል የሚሞክሩ ኃይሎች ዕኩይ ተግባራቸው የሚያስከትሏቸዉን መዘዞች መሸከም ይኖርባቸዋል፡፡ ቀደም ሲል አህጉራዊ እና አለምአቀፋዊ አሸባሪ ቡድኖች ላይ የተገኘውን አበረታች ውጤት አደጋ ላይ የሚጥሉና የሚቀለብሱ ድርጊቶች ኢትዮጵያ አትታገስም።   ኢትዮጵያ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና ከሶማሊያ ህዝብ እና ከአለምአቀፉ ማህበረሰብ ጋር በመሆን በቀጠናው ሰላምና መረጋጋት ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን ለመከላከል አሁንም ቁርጠኛ አቋም አላት፡፡ ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቃል አቀባይ ጽ/ቤት   አዲስ አበባ፤ኢትዮጵያ

በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ የተሰጠ መግለጫ
በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ አንድ ኪሎ ቡና በ980.64 ዶላር (ከ102ሺህ ብር በላይ) በሆነ ዋጋ በጨረታ መሸጡ ተገለጸ በአለም አቀፍ ደረጃ በተካሄደ የባለ ልዩ ጣዕም የቡና ዉድድር የኢትዮጵያ አንድ ኪሎ ቡና በ98
የኢትዮጵያ አንድ ኪሎ ቡና በ980.64 ዶላር (ከ102ሺህ ብር በላይ) በሆነ ዋጋ በጨረታ መሸጡ ተገለጸ በአለም አቀፍ ደረጃ በተካሄደ የባለ ልዩ ጣዕም የቡና ዉድድር የኢትዮጵያ አንድ ኪሎ ቡና በ980.64 ዶላር (ከ102ሺህ ብር በላይ) በሆነ ዋጋ በጨረታ መሸጡ ተገለጸ ከቡናና ሻይ ባለስልጣን የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በኢትዮጵያ የተካሄደው የዘንድሮው ባለልዩ ጣዕም የቡና ቅምሻ ውደድር ለ4ኛ ጊዜ ሲሆን በተለያዩ የውደድሩ መርሀግብሮች ላለፉት ሰባት ወራት ተከናውኗል። “ባለልዩ ጣዕም የቡና ቅምሻ ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አገራችን ከመጣ 5 ዓመት” ሆነው ሲል የጠቆመው ባለስልጣኑ “የዘንድሮም ውደድር ለ4ኛ ጊዜ በተለያዩ የውደድር መርሀግብሮች ላለፉት ሰባት ወራት” መካሄዱን አስታውቋል። በአገራችን በተካሄደው በዚህ በ2024 ውድድር ላይ ደግሞ ዳግም “ታሪካዊ የሆነ የጨረታ ዋጋ ማግኘት ተችሏል” ሲል የገለጸው ባለስልጣኑ “በዚህ በዘንድሮው ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ ላይ ከተካሄደው የኦንላይን ጨረታ ሂደት ተወዳደሪ ለሆኑት ቡናዎች 4870 የተለያየ ዋጋ” መሰጠቱን ጠቁሟል። በዚህም “አንድ ኪሎ ቡና በ980.64 ዶላር ($445/ፓውንድ) ወይም ከ102ሺህ ብር በላይ በሆነ ዋጋ መሸጥ ተችሏልዕ ሲል አስታውቋል፤ “ይህም ዋጋ በኢትዮጵያ በእስከአሁን ከተካሄዱት ውደድሮች ሆነ በሌሎች መመዘኛዎችም እጅግ ከፍተኛና አዲስ ሪከረድ ሆኖ ተመዝግቧል” ብሏል። “ይህ ለአሸናፊዎቹ ብቻ ሳይሆን ለአገራችንም ትልቅ ድል በመሆኑ ሁላችሁንም በተለይም አርሶ አደሮቻችን እንኳን ደስ ያላችሁ” ሲሉ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) መልዕክት አስተላልፈዋል። ባለስልጣኑ በ980.64 ዶላር በሆነ ዋጋ በጨረታ የተሸጠው ቡና አይነትም ሆነ ከየትኛው የሀገሪቱ ክፍል የቀረበ ስለመሆኑ የገለጸው ነገር የለም።

#ሰበር_ዜና ከሰሞኑ በ ኢትዮጵያ አየር መንገድ በተፈጠረው ሁከት ከተያዙት መካከል ኤልያስ ድሪባ የተባለው ተከሳሽ 3 ጊዜ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ወንጀለኛ መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ በሽብርና በሲቪል አቪየሽን ሕግ ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ የተባለው ተጠርጣሪ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ከባድ ወንጀሎች ተከሶ ዳዊት ድሪባ በዳኔ በሚል ስም ሦስት ጊዜ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ደጋጋሚ ወንጀለኛ መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ። በሽብርና በሲቪል አቪየሽን ሕግ ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ የተባለው ተጠርጣሪ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ ከ1989 ዓ ም ጀምሮ እሰከ 1999 ዓ ም በተለያዩ ከባድ ወንጀሎች ተከሶ ዳዊት ድሪባ በዳኔ በሚል ስም ሦስት ጊዜ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ደጋጋሚ ወንጀለኛ መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 25 ቀን 1999 ዓ.ም በዋለው ችሎት በዘረፋ፣ በቅሚያ፣ በሌብነት፣ በቤት ሰብሮ ስርቆት እና በደንብ መተላለፍ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን ከፖሊስ የምርመራ ማህደር ማረጋገጥ ተችሏል። ተጠርጣሪው ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ ፣ ጀማል ኑሩ እና ዳዊት ድሪባ በዳኔ የሚሉ ስሞችን በመጠቀም 11 ጦር መሣሪያ መዝረፍ ወንጀል፣ 6 ቅምያ ወንጀል፣ 3 ሌብነት ወንጀሎች፣ 3 ሰው መግደል ወንጀል፣ 2 ስርቆትና ቤት ሰብሮ ስርቆት ወንጀሎች፣ አንድ ሐሰተኛ ሰነድ መገልገል ወንጀል፣ ከእስር ማምለጥ ወንጀል እና አንድ ደንብ መተላለፍ የወንጀል ሪከርድ በአጠቃላይ 28 የወንጀል ሪካርዶች ያሉበት እንደሆነና ከዚህ ውስጥ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት መጋቢት 24 ቀን በዋለው ችሎት ስድስት መዝገቦችን ሦስት ጊዜ አጣምሮ ሦስት ጊዜ በሞት እንዲቀጣ ውሳኔ የተላለፈበት መሆኑን ከፖሊስ የምርመራ ማህደር መገንዘብ ተችሏል። እንደገና የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ሚያዚያ 30 ቀን 2000 ዓ.ም በዋለው ችሎት በጦር መሣሪያ የታገዘ የዘረፋ፣ ከአስር ቤት የማምለጥና በሌብነት ወንጀል የዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ቅጠት ያስተላለፈት መሆኑን የፖሊስ የምርመራ ማህደር አመላክቷል። ተጠርጣሪው በውሳኔው መሠረት ማረሚያ ቤት የገባው ይግባኝ ጠይቆ ሞት ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ የተቀየረለት ቢሆንም በድጋሚ ይግባኝ በማለቱ ቅጣቱ ወደ 25 ዓመት ተቀንሶለት ለ17 ዓመታት በማረሚያ ቤት ከቆየ በኋላ በይቅርታ መፈታቱን ከፖሊስ የምርመራ ማህደር ማረጋገጥ ተችሏል። ምንጭ፦ ኤፍ ቢ ሲ

የግብፅ ወታደራዊ እቃ ጫኝ አውሮፕላኖች በሶማልያ መዲና ሞቃዲሾ ቁሳቁስ እና ወታደሮችን በዛሬው እለት ማራገፋቸው ታወቀ (መሠረት ሚድያ)- የአሜሪካ ስሪት የሆኑ C-130 ሄርኩለስ የግብፅ ወታደራዊ እቃ ጫኝ አውሮፕላኖች በሶማልያ መዲና ሞቃዲሾ ቁሳቁስ እና ወታደሮችን በዛሬው እለት ማራገፋቸው ተሰምቷል። በታማኝ የመረጃ ምንጮች ማህበራዊ ሚድያ ላይ የተለቀቁ ተንቀሳቃሽ ምስሎች እንደሚያሳዩት እነዚህ የግብፅ ባንዲራ ያለባቸው አውሮፕላኖች ሞቃዲሾ ደርሰው ይታያሉ። ከቅርብ ግዜያት ወዲህ ሶማልያ እና ግብፅ ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ የመጡ ሲሆን በተለይ ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ በወደብ አጠቃቀም ዙርያ የመግባብያ ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ ይህ ግንኙነታቸው ይበልጥ እንደጠነከረ የቀጠናው ተንታኞች ያስረዳሉ። ከሁሉም በላይ ግን ሶማልያ የግብፅ ጦር በአዲስ መልክ እየተደራጀ ባለው የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ሀይል ውስጥ ስምሪት እንዲያደርግ መፈለጓ ከኢትዮጵያ ጋር የባሰ ቅራኔ ውስጥ እንደሚከታት ተገምቷል። የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና ፀጥታ ምክር ቤት ይህን የግብፅ እና ሌሎች ሀገራት ስምሪት ያፀደቀው ሲሆን እ.አ.አ ከጃንዋሪ 1/2025 ጀምሮ በሶማልያ በመሰማራት ሲቪል ዜጎችን ከአልሻባብ ሀይሎች ጥቃት የመከላከል ስራ ተሰጥቶታል። ሂደቱ ገፍቶ ግብፅ ጦሯን በሶማልያ ካሰፈረች ሀገሪቱ ከደቡብ ሱዳን በመቀጠል በኢትዮጵያ ጎረቤቶች ያላት ሁለተኛ መገኘት ይሆናል። ቪድዮ: ሀሩን ማሩፍ መረጃን ከመሠረት!

#Ethiopia የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል በማለት በቁጥጥር ስር አውሎ የሽብር ወንጀል ምርመራ የከፈተባቸውን 6 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ማ
+5
#Ethiopia የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል በማለት በቁጥጥር ስር አውሎ የሽብር ወንጀል ምርመራ የከፈተባቸውን 6 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ማንነት የሚያሳይ ፎቶ ይፋ አድርጓል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋልኳቸው በሀገራችን ካለው የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ አውሮፕላን መብረር አይችልም " ያሉ የበረራ ባለሙያዎችን በማስገደድ በረራውን ለማስቀጠል በፈጠሩት አምባጓሮ እና ግርግር ወንጀል ተጠርጥረው ነው ሲል አስረድቷል። ነገ ፍርድ ቤት አቀርባቸዋለሁ ብሏል። ©tikvahethiopia

የፅንፈኝነት ጥጋቸው ለሌሎች ብሄረሰቦች ብቻ ሳይሆን ለራሳቸው ለአማራው እራሱ በግፍና ስቃይ የመግደላቸው መገለጫ በተግባር ተመልከቱ🤔

ከሚሴ‼️ አማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በነበሩት አቶ አህመድ አሊ ላይ ጥይት ተኩሶ በመግደል ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረው ግለሰብ ከትናንት በስቲያ መገደሉ ተሰምቷል።በመንግስት የፀጥ
ከሚሴ‼️ አማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በነበሩት አቶ አህመድ አሊ ላይ ጥይት ተኩሶ በመግደል ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረው ግለሰብ ከትናንት በስቲያ መገደሉ ተሰምቷል።በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች እጅ እንድሰጥ ቢጠየቅ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ደወይ ሀራዋ በተባለ አካባቢ በተተኮሰበት ጥይት ተመቶ ወዲያው ህይወቱ አልፏል ተብሏል። ይሄ  ልጅ ስሙ አህመድ ሼሁ ይባላል። ከአስተዳደሩ በፊት ታዋቂ ታዋቂ ሰዎችን እንደገደለ በአካባቢው ይነገራል። በቅርቡም አንድትን እናት ኬሚሴ ላይ እንደገደለ ይነገራል። https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93

                     የወታደሩ ህይወት      "ለሃገር እና ለህዝብ መሞት ታላቅ ክብር ነው!" እልፍ አዕላፍ ልጆቿ ለክብሯ ወድቀውላታል፤ለፍቅሯ ደምተውላታል፤ለነፃነቷ ተሰውተውላታል።ጠይቃቸው የነፈጓት ፈልጋ የከለከሏት አንዳች ነገር የለም።ውዱን ስጦታ ህይወትን ሰጥተዋታል፣እየሰጧትም ይገኛሉ። በሰጧት ህይወትም በክብር አኑረዋታል፣በነፃነት አፅንተዋታል። በጠላቶቿ ፊት የማይደፈር ግርማን አላብሰዋታል፤በታሪክ የከበረች፣የነፃነት ብርሃኗን ያላደበዘዘች አድርገዋታል። አዎ! ሃገር ማለትኮ በከፋቸው ጊዜ የሚረሷት፣ በጨነቃቸው ጊዜ የሚዘነጓት፣በየወንዙ የሚዋዋሉባት፣ በየሸንተረሩ ዋጋ የሚቆርጡላት፣ሰይፍ በተሳለ ጊዜ ይችንስ አናውቃትም?የሚሏት፣ከጠላት ተኩስ ለማምለጥ ፈፅመው የሚክዷት፣ በተደሰቱ ጊዜ ደግሞ የሚያስታውሷት፣ በተድላ ዘመን ከፍ ከፍ የሚያደርጓት ፣ጭንቅ በሌለ ዘመን ዘብሽ ነን የሚሏት አይደለችም። ሀገር ከምንም በላይ የሚወዷት፣ዋጋ የሚከፍሉላት፣ በጭንቅ ዘመን የሚፀኑላት፣በመከራ ዘመን ቀድመው የሚቆሙላት፣ከአንቺ በፊት እኛ እንውደቅላት የሚሉላት፣ ህይወት ገብረው ሰንደቋን የሚያውለበልቡላት፣ እስከመሰቀያው ድረስ በፅናት የሚከተሏት፣እስከ መቃብር ድረስ የሚታመኑላት ናት። የኢትዮጵያ ወታደርም ለፍቅር መሞትን፣ ለህዝቦች ነፃነት ተላልፎ መሰጠትን፣ከራስ በፊት ሌሎችን መውደድና ለህዝብና ለሀገር መሰዋትን ፣መከራ በመጣ የጭንቅ ቀን በቀረበች ጊዜም ነፃነትን በፈሰሰው ደሙ እያፀና ይገኛል።በሠላም እና በልማት የሚፀና ትውልድ ይኖር ዘንድ በገባው ቃልኪዳን ልክ ስለ ሃገርና ህዝብ እያለፈ ነው። ስለ ሃገር ፍቅር፣የነፃነት ዋጋ የማይገባቸው ሃገር አፍራሽ ባንዳዎችን አይቀጡ ቅጣት እየቀጣ እንደአመጣጣቸው እየመለሰ ትዕቢታቸውን እያስተነፈሰ ሀገር የማፍረስ እሳቤያቸውን እያመከነ ለሠላም ወዳዶች ምህረት እየሠጠ ከህዝብና ከፀጥታ ሃይሎች ጋር በጦምረት እየሠራ የሀገሩን እና የህዝቡን ሠላም የማረጋገጥ ልማቱን የማሳለጥ ተግባር ላይ የተሠማራ ነው የወታደሩ ህይወት። መከላከያ ሠራዊቱ መተኪያ የሌላትን ህይወቱን ለሀገርና ለህዝብ ሲል አሣልፎ የሚሠጥ ለሠንደቅ ዓላማው ክብር ለሀገሩ ፍቅር ሲል ምንጊዜም የሚታትር፣ የሚደክም፣ የሚቆሥል፣ የሚሞት ፣ለህይወት የማይሳሳ ከህዝብ አብራክ የወጣ የህዝብ ልጅ ነው ወታደሩ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልጇን በግፍ ለተነጠቀቸው ሕጻን ሄቨን እናት የመኖሪያ ቤት አበረከተ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልጇን በግፍ ለተነጠቀቸው ሕጻን ሄቨን እናት የመንግስት መኖሪያ ቤት
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልጇን በግፍ ለተነጠቀቸው ሕጻን ሄቨን እናት የመኖሪያ ቤት አበረከተ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልጇን በግፍ ለተነጠቀቸው ሕጻን ሄቨን እናት የመንግስት መኖሪያ ቤት አበርክቷል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ የሄቨንን እናት በማግኘት አጽናንተዋል:: ልጇን በግፍ ተነጥቃ ባለፈው አንድ ዓመት ፍትሕ ሳታገኝ ለቆየችው ሲስተር አበቅየለሽ የፍትሕ ሒደቱን ለመከታተል፣ያለችበት ሁኔታ የተሻለ እንዲሆንላትና ተጋላጭነቷን ለመቀነስ እንዲመች የከተማ አስተዳደሩ አንድ የመንግስት መኖሪያ ቤት አበርክቷል፡፡ ከዚህ ባለፈም በሙያዋ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እንድትሰራ መመቻቸቱን ነው ከንቲባ አዳነች የገለጹት፡፡ የህጻን ሄቨን ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ በመሆኑ ድርጊቱ ተገቢውን ፍትሕ ማግኘቱ የሌሎች ህፃናት ተጋላጭነትን ለመቀነስ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ከንቲባዋ አስገንዝበዋል፡፡ መሰል ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት እንዳይፈፀም የማህበረሰቡ የአመለካከት ለውጥ እንዲመጣና ችግሩ የጋራ ጉዳይ በመሆኑ ሁሉም ሃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡