ch
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

前往频道在 Telegram

Addis abeba Ethiopia

显示更多
5 344
订阅者
-22624 小时
-2 2007
-2 65830
帖子存档
የሚሊሺያ ሃይሉ ከሠራዊቱ ጋር በመሆን የቀጠናውን ሠላም እያረጋገጡ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 28 ቀን 2016 ዓ.ም በደቡብ ወሎና በሰሜን ሸዋ አጎራባች አካባቢዎች የሚገኙ የሚሊሺያና የአ
የሚሊሺያ ሃይሉ ከሠራዊቱ ጋር በመሆን የቀጠናውን ሠላም እያረጋገጡ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 28 ቀን 2016 ዓ.ም በደቡብ ወሎና በሰሜን ሸዋ አጎራባች አካባቢዎች የሚገኙ የሚሊሺያና የአድማ ብተና አባላት ከመከላከያ ሠራዊት አባላቱ ጋር በመሆን የቀጠናውን ሠላም ለመመለስ እየሠሩ መሆኑን አንድ ከፍተኛ የሠራዊቱ አዛዥ ገልፀዋል። የሚሊሺያና የአድማ ብተና አባላቱ በመከላከያ ሠራዋቱ የወሠዱትን ወታደራዊ ሥልጠና ተጠቅመው የሚሥተዋለውን የሠላም እጦት ወደ ነበረበት ለመመለስ እየሠሩ መሆናቸውንም አሥታውቀዋል። በቅርቡ ሠላም ለማረጋገጥ ሥልጠና የወሠዱት ሚሊሺያዎች ዛሬ ጀማ በተባለው ቦታ ከፅንፈኛው ጋር ተዋግተው 17 ክላሽና 01 ብሬን ማርከው መመለሳቸውንም አዛዡ ተናግረዋል። መንግስት በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ሠላም ለማምጣት እየሠራ ባለበት አሁን ላይ ሠላምን ወደ ጎን ትተው ወደ ጫካ የገቡ ፅንፈኞችን ለመታገል በርካታ የአድማ ብተና እና የሚሊሺያ ሃይል ሥልጠና መጀመራቸውም ታውቋል። በዚህ መሠረት አሁን ላይ በደቡብ ወሎ ኮምቦልቻና አካባቢው 250 እንዲሁም በደሴ 250 በድምሩ 500 አድማ ብተና ሠልጣኞች ዛሬ ሥልጠና መጀመራቸውን ከሥፍራው በደረሠን መረጃ ተመላክቷል ።

የውትድርና ሙያ ከሌላው የሙያ ዘርፍ የበለጠ ሙያዊ ስነ-ምግባርና ዲሲፕሊን የሚጠይቅ ነው ሲሉ ሌተናል ጀኔራል ሹማ አብደታ ገለፁ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 25 ቀን 2016 ዓ.ም ከኮማንዶና
+2
የውትድርና ሙያ ከሌላው የሙያ ዘርፍ የበለጠ ሙያዊ ስነ-ምግባርና ዲሲፕሊን የሚጠይቅ ነው ሲሉ ሌተናል ጀኔራል ሹማ አብደታ ገለፁ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 25 ቀን 2016 ዓ.ም    ከኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ እንዲሁም ከሪፐብሊካን  ጥበቃ ሃይል ክፍለ ጦሮች ለተወጣጡ የበታች ሹሞች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሠጠ ነው ፡፡    በሥልጠና ቦታው የተገኙት የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ሹማ አብደታ የውትድርና ሙያ በባህሪው ውስብስብ በመሆኑ አስቸጋሪ ግዳጆችን በብቃት መፈፀምና የህይወት መስዋዕትነትን የሚጠይቅ በመሆኑ በአላማው ትክክለኝነት በማመን ራስን በዲስፕሊን ማነፅና መሠል ከሌሎች ሙያዎች የተለየ ባህሪ ያለው ሥለመሆኑ ገልፀዋል ፡፡    ወታደራዊ ባህርያት እና ወታደራዊ ሙያ በስልጠና እለት በእለት በምንሰራቸው ስራዎች በተቋማዊ አሰራሮች እና መምሪያዎች በተቋሙ ቁልፍ ዕሴቶች በሚያገኘው ትምህርት እየተቀረፀ እየዳበረ የሚሄድ መሆኑንም  አስገንዝበዋል፡፡    ወታደራዊ መሪ በወታደራዊ ባህልና ጨዋነት ታንፆ የተሰጠውን ተልዕኮ በሃላፊነት ስሜት ግልፀኝነት በመፍጠር ለግዳጅ እራሱን ዝግጁ ማድርግ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ ያለጠንካራ ባ/ማ ጠንካራ ዕዝ ብሎም ጠንካራ መከላከያ ሊኖር ስለማይችል የረጅም ጊዜ ልምዳችሁን ተጠቅማችሁ በሞራልና ስነ-ልቦና ራሳችሁን በማብቃት በሃላፊነት መንፈስ መስራት ይገባችኋል ያሉት ሌተናል ጄኔራል ሹማ ሠልጣኞች እንደ መሪ በኢትዮጵያዊነት ላይ የማያወላውል ጠንካራ አቋምና እምነት በመያዝ መስራት ይገባችኋል ሲሉም ተናግረዋል፡፡ ዘገባው የዕዙ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ክፍል ነዉ

"የአይበገሬው የኮማንዶዎች አባት" የሚል መፅሐፍ ተመረቀ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በደራሲና ጋዜጠኛ ወንድወሰን መኮንን የተዘጋጀውና በሌተናል ኮሎኔል ደስታ ኃይለገብር
+3
"የአይበገሬው የኮማንዶዎች አባት" የሚል መፅሐፍ ተመረቀ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በደራሲና ጋዜጠኛ ወንድወሰን መኮንን የተዘጋጀውና     በሌተናል ኮሎኔል  ደስታ ኃይለገብርኤል ወይም አቦይ ደስታ የወታደራዊ ህይወት ታሪክ ላይ ያተኮረው መፅሐፉ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ በተገኙበት ተመርቋል። ከመፅሐፍ ምረቃ በኃላ ንግግር ያደረጉት ሌተናል ጄኔራል ሹማ መፅሐፉ የአሁኑ ትውልድ ፅናትን፣ ብርታትን፣ ጀግንነት ፣ አይበገሬነትንና ለሀገር ያላቸው ጥልቅ ፍቅር ማስተማሪያ መሆኑን ተናግረዋል። የመፀሐፉ ደራሲ ጋዜጠኛ ወንድወሰን መኮነን  መፅሐፉን ለመፃፍ ያነሳሳቸው አቦይ ደስታ ያላቸው የሀገር ፍቅርና ዕድሜያቸውን በሙሉ ለሀገር በከፈሉት ዋጋ የዘመኑ ተምሳሌት በመሆናቸው ይህ ታሪክ ተደብቆ እንዳይቀር ነው በማለት ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም የመፅሐፍ ምረቃው ላይ ተገኝተው ስለ መፅሐፉ ሃሳብ ያቀረቡት ከፍተኛ መኮንኖች በመፅሀፉ የባለታሪኩ ግለ ታሪክና  ሀገር ወዳድነት ለሀገራቸው የከፍሉት ዋጋና ጥንካሬያቸው የጥሩ ተምሳሌት አባትና ጀግና ወታደራዊ መሪ መሆናቸው ያሳየና መፅሐፉ የብዙ ጀግኖች ታሪክ ተደብቆ እንዳይቀር ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በመፅሃፉ ምርቃት ላይ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች የሰራዊቱ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን ለመፅሀፉ መታተም የላቀ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት በተለይም ለኮማንዶና አየር ወለድ እዝ ምስጋና ቀርቧል። ዘገባው  የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ የሠራዊት ሥነ-ልቦና ግንባታ ክፍል ነው

የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይል ያሰለጠናቸውን የክብር ዘብ አባላት አስመረቀ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይል በኢፌዴሪ አየር ኃይል ያሰለጠናቸውን የክብር
+3
የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይል ያሰለጠናቸውን የክብር ዘብ አባላት አስመረቀ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይል በኢፌዴሪ አየር ኃይል ያሰለጠናቸውን የክብር ዘብ አባላት በዛሬው ዕለት አስመርቋል። በምርቃቱ ተገኝተው ሽልማት በመስጠት ንግግር ያደረጉት የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የዛሬ ተመራቂ የክብር ዘብ አባላት የሰራዊቱ ቁመና እና ስነ-ስርዓት ነፀብራቅ መሆናችሁን አውቃችሁ የሚሰጣችሁን ኃላፊነት በትጋት ልትወጡ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡ የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይሉ የክብር ዘብ አባላት ለምረቃ እንዲበቁ ላደረጉ የአየር ኃይል ፣ የመከላከያ ስነ-ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት አመራሮችና ባለድርሻ አካላትም ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይል አዛዥ ሜጄር ጄኔራል አብድሮ ከድር የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይሉ በሀገራችን የሚካሄዱ ስብሰባዎች ፣ሀገራዊ ክብረ በዓላት በሰላም እንዲከናወኑ የተሰጠውን ኃላፊነት በትጋት እየተወጣ መሆኑን ጠቁመው የዛሬ ተመራቂ የክብር ዘብ አባላት በአካል ብቃትና ፣በወታደራዊ ሥልጠና የሚሰጣቸውን ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስችል በቂ አቅም መጨበጣቸውን ተናግረዋል፡፡ በዕለቱ ለስልጠናው መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት ሽልማት የተሰጠ ሲሆን ተመራቂ የክብር ዘብ አባላትም በስልጠና ያገኙትን አቅም በመጠቀም የሚሰጣቸውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

"ፀሐይ" እ.አ.አ በ1935 በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰራ አውሮፕላን። "Tsehay" is the first aircraft built in Ethiopia in 1935. “ፀሐይ” አውሮፕላን ጥር 21፣ 2016 ዓ.ም፣ዛሬ የጣልያን መንግሥት "ፀሐይ"ን ለኢትዮጵያ መንግሥት ያስረከቡበት የታሪካዊ ሁነት ቀን ሆኗል። "ፀሐይ" በ1935 ዓ.ም ሄር ሉድዊግ ዌበር የተባለው ጀርመናዊ ኢንጂነር እና የንጉሱ ፓይለት በወቅቱ ከነበሩ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን በኢትዮጵያ የተሰራ የመጀመሪያው አውሮፕላን ነው። ስያሜውም የቀዳማዊ ኃይለስላሴን ልጅ ልዕልት ፀሐይን ለማሰብ የተሰጠ ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ላለፈው አንድ አመት ጊዜ ከጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ ሜሎኔ ጋር አውሮፕላኑ ወደ ኢትዮጵያ ስለሚመለስበት ሁኔታ ትልቅ ጥረት እና ሰፊ ንግግር ሲያደርጉ ቆይተዋል። ፀሐይ ባለሁለት መቀመጫ እና ሁለትዮሻዊ መቆጣጠሪያ ያለው ብሎም የባለከፍተኛ ኃይል ሞተር ባለቤት ተደርጎ የተሰራ አውሮፕላን ነበር። "ፀሐይ" ኮምፓስ፣ የአብራሪ መቆጣጠሪያዎች፣ ሁለት ያለ ፍሬን ማቆሚያ የተገጠሙ የማረፊያ ሽክርክሪቶች የነበሩትም ነው። ሞተሩ ባለሰባት ሲሊንደር ዋልተር ቪነስ ሲሆን የውሃ ማቀዝቀዣ ስርዓት የነበረው የ115 የፈረስ ጉልበት ባለቤትም ነበር። "ፀሐይ" ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በፊት በኢትዮጵያ የተሰራ ብቸኛ አውሮፕላን ነው። ፀሐይ በውስን ሃብት እና ስፍራ በጊዜው የነበሩትን አናፂዎች እውቀት እና የእጅ ጥበብ በመጠቀም የተሰራ አውሮፕላን ሲሆን የ1930ዎቹ የአቪየሽን ጥረት ማሳያ ሆኖ የተረፈን አውሮፕላን ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መረጃ አመልክቷል።

ዓድዋ የነጻነት ዉሃ ልክ! "እምዬ ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይዉደም!" ያለዉ ማን ነበር? የአዉሮፓ ወራሪ ሀይሎች እንደ ጎርጎሲያኑ የዘመን ቀመር ከ1884-1885 መካከል በዛሬይቱ ሀገረ ጀርመን በበርሊን ከተማ አፍሪካን የመቀራመት ዉይይት ሲያካሂዱ በነበሩበት ወቅት ወደ አፍሪካ የምንሄደዉ ለተቀደሰ ዓላማ (benevolent purpose) ነዉ የምል አንድ አስቂኝ አቋም ነበራቸዉ፡፡ በመሆኑም ወደ አፍሪካ መጥተዉ አፍሪካን ያለ አፍሪካዊያን ፍላጎት ቅኝ የሚገዙት የላቀ የበጎ አድራጎት (philanthropy) ተግባራት ለአፍሪካ ህዝብ ማበርከት ስላስፈለጋቸዉ መሆኑን በወቅቱ ባዘጋጇዋቸዉ ሰነዶች ሳይቀር አስፍረዋል (Matthew 2015: 34) እስካሁንም ድረስ ወራሪነትን የሚያንቆለጳጵሱ ሀይሎች ከቅርብም ከሩቅም አልታጡም፡፡  አጀንዳቸዉ ግን ዉስጠ-ወይራ ነበር፡፡ ልክ በአፋቸዉ እንደተናገሩትና በስምምነቶቻቸዉ እንዳሰፈሩት ፍላጎታቸዉ አፍሪካን ከተቀሩት አህጉራት ጋር በንግድና በመሳሰሉት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች በማቆራኘት የአፍሪካን ህዝብ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ሳይሆን የአፍሪካን ማዕድናት፣ ዉሃዎች፣ የእርሻ መሬቶች፣ ነዳጅና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶችን መበዝበዝ ነበር፡፡ ፍላጎታቸዉ በዚህ ብቻ አይቆምም፤ የአፍሪካን ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክ፣ የኑሮ ዘዬና ስነ-ልቦናን በማክሰም በራሳቸዉ መተካት ነበር፡፡ እነዚህን የጭቆና ተግባሮቻቸዉን በገዙዋቸዉ የአፍሪካ ሀገራት ላይ ተጨባጭ ማድረግ ችለዋል፡፡  ኢትዮጵያዊያን ግን ያኔም ቢሆን ነቄዎች ነበሩ፡፡ “ዓለም አቀፋዊነትን እዉን እናደርጋለን” በሚል ሽፋን ሉዓላዊ ሀገራትን የመዉረር የምዕራባዊያንን ሴራ በልኩ በመረዳት ነዉ በተባበረ ክንድ መክተዉ መመለስ የቻሉት፡፡  የእኛም ትዉልድ መንቃት አለበት፡፡ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከታሪካዊ ጠላቶቻችንና ከዉስጥ ጀሌዎቻቸዉ የሚቃጣብንን የስነ-ልቦና ጥቃት ቀልብሰን የኢትዮጵያን ብልጽግና፣ ሰላምና ልዕልና በሚያጸኑ አጀንዳዎች ዙሪያ እንደ ንብ ተሰባስባን ለጋራ ሀገር ግንባታ መረባረብ አለብን፡፡ እኛ እያለን አባቶቻችን ሳይማሩ የገነቡልንን ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያችን ታሪካዊ ጠላቶቻችንና የታሪክ አተላዎች ማፍረስ አይችሉም፡፡ የፖለቲካ ልዩነት ያለ፣የነበረና መቼም ቢሆን የሚኖር ነው፡፡ በኢትዮጵያ ግን ልዩነት አይኖረንም፡፡ ኢትዮጵያ የጋራ ማንነታችን ናት! እምዬ ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይዉደም ያለዉ ማን ነበር?

#FoodandAgricultureOrganization #UN የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ  የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያ ተሸለሙ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ ሽልማት የተሰጣቸው ዛሬ በጣልያን፤ ሮም ከተማ ነው። በተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት (FAO) ፤ ሮም ውስጥ ባሰናዳው ዝግጅት ዶ/ር ዐቢይ ፤ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያደረጉ ላለው ጥረት የከበረውን አግሪኮላ ሜዳልያ እንዳበረከተላቸው ተነግሯል። የፋኦ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ኩ ዶግዩ ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለፋኦ ከፍተኛ ሽልማት ለሆነው አግሪኮላ ሜዳልያ ሽልማት በመብቃታቸውን " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል። ይህ ሽልማት መሪዎች እና ሌሎችም የዓለማችን እውቅ ሰዎች የምግብ ዋስትናናን ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ድህነትን ለመቀነስ ለሚያደርጉት የተሳካ ጥረት የሚሰጥ እንደሆነ ጠቁመዋል። በዚህም የአግሪኮላ ሜዳሊያ ለጠ/ ሚኒስትሩ እየተበረከተው ፦ * በኢትዮጵያ ገጠርና ኢኮኖሚ ልማት ላይ ላበረከቱት አስተዋፅኦ * በተለይም " በስንዴ፤ ምግብ እራስን መቻል ፕሮግራም " ባደረጉት የግል ድጋፍ * በኢትዮጵያ አረንጓዴ ሌጋሲ (Green Legacy) ስራ መሆኑን አስረድተዋል። ከዚህ ባለፈ ዋና ዳይሬክተሩ " ባለፉት 5 አመታት ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለችውን አስደናቂ እድገት ተመልክቻለሁ " ማለታቸው ተነግሯል። ይህ ሊሆን የቻለው " በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጡ ውጤታማ፣ ተጠያቂነት ያለውና የተረጋጋ አመራር ነው " ያሉት የፋኦ ዋና ዳይሬክተር ፤ ተመልክቼዋለሁ ያሉት እድገት የተመዘገበው " ባለፉት ዓመታት በነበሩ አስቸጋሪ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ውስጥ ነው ፤... ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን እንደ አህጉር ለአፍሪካም ይልቅ መልዕክት ነው " ማለታቸው ተሰምቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በበኩላቸው የተሰጣቸውን ሽልማትና እና እውቅናን ተከትሎ ባሰራጩት መልዕክት ምስጋና አቅርበው ፤ " ከፍ ያለ ጠቀሜታ ባላቸውና የኢንደስትሪ ግብዓት በሆኑ የግብርና ምርቶች ላይ ማተኮራችን ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እያስገኘልን ይገኛል። የምግብ ሉዓላዊነት ጉዟችንን በፅናት እናስቀጥላለን " ብለዋል። የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያን በተሸለሙበት ወቅት የፋኦ አመራሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ እና የተለያዩ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተው ነበር ተብሏል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከፋኦ ድረገፅ ነው ያገኘው።

ጀግንነታችን የማይቀየር ቋሚ ቅርስ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 19 ቀን 2016 ዓ.ም የነፃነት ቀን የሚያከብሩ ሀገሮች በቅኝ ገዥዎችና በወራሪዎች የተሸነፉ ክብርና ነፃነታቸውን አጥተው የቆ
+2
       ጀግንነታችን የማይቀየር ቋሚ ቅርስ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 19 ቀን 2016 ዓ.ም የነፃነት ቀን የሚያከብሩ ሀገሮች በቅኝ ገዥዎችና በወራሪዎች የተሸነፉ ክብርና ነፃነታቸውን አጥተው የቆዩበትና በአንድ ክፉ አጋጣሚ አንገታቸውን የደፉት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ከሁሉም ሀገራት በላይ በተደጋጋሚ የመወረር ሙከራ ቢደረግባትም ህዝቦቿ የማይንበርከኩ አንገት የሚያስደፋ ታሪክ የማይሸከሙ በመሆናቸው በየዘመናቱ በሚከፍሉት መስዋዕትነት የድል እንጂ የሽንፈት ታሪክ ኖሯቸው አያውቅም፡፡ እኛ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላትም የተገኘነው፣ የምንመስለው የምናገለግለው ይህንኑ ህዝብ ነው፡፡ህዝባችንን የምንመስል ከጀግንነቱና ፅናቱ ከሀገራዊ ፍቅሩ የማንጎድል የህዝባችን መከታ ነን፡፡ አሁን ላይም የውጊያ አውዱ ሠፍቶ ፤ጠላቶቿ የግላቸውን ጥቅም በማሥቀደም ቢበራከቱም ፤የብቻዋ የሆኑ እሴቶቿን ለመግታት ፤ጥቅሟን ለማሳጣት የሐሰት ወሬ ቢነዙ ዛቻ ቢደረድሩ ፤ ቢሸልሉ ቢፎክሩ እንደለመዱት ባንዳ ከመሆን ወጪ የሚያመጡት የሚለውጡት አንዳችም ነገር አይኖርም። ምክንያቱም ጠብመንጃ በማንሳት በሃይል ሊመጣ የሚችል ነገር ስለሌለ። የኢትዮጵያ ሠራዊት የሀገሩ ልክ የህዝቦቹ መልክ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ልኳ ዘመናትን ተሻግሮ የሚታይ ከፍታና ህዝቧ ደግሞ ታሪኩ የውጭ ጠላት ሲመጣ የተቀየመው ይቅር ተባብሎ ፤ሞፈርና ቀንበሩን ሰቅሎ ፤ስንቁን ቋጥሮ፤ ከብረት የጠነከረ አንድነት ፈጥሮ በጀግንነት ፅናት መዋጋትና መርታት ነው፡፡  የኢትዮጵያ ሠራዊትም አብሮት ከመጣው የጀግንነት ታሪክ ጋር ተዳምሮ ህዝቡ የሠጠው ጀግንነት እንደተጠበቀ ሆኖ መቼም ቢሆን የማይፋቅ አብሮት የሚዘልቅ የጀግንነት ውርስ ባለቤትም ነው፡፡ይሄ ውርስ ደግሞ የሚታደስ እንጂ የማይቀየር ቋሚ ቅርስ ነው፡፡ በፈይሳ ናኔቻ

የኮማንዶና የአየር ወለድ ዕዝ ሰልጥኖ አሰልጣኝ በራሪ ነብር አየር ወለዶችን አስመረቀ፡፡     የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 18 ቀን 2016 ዓ.ም የኮማንዶና የአየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል የሰልጥኖ አሰልጣኝ በራሪ ነበር አየር ወለዶችን አስመርቋል ፡፡ በምርቃቱ በመገኘት ለተመራቂዎች የደረት ክንፍ (ዊንግ) እና የክንድ አርማ ያለበሱት የዕዙ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ናቸው፡፡    የአየር ወለድ ክፍል ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ እጅግ ደፋርና ጨዋ በስነ-ምግባራቸው የተመሰገኑ አባላትን በመመልመል ለግዳጅ የሚያዘጋጅ ክፍል መሆኑን ጠቁመው ሰልጣኙም ስልጠናውን ካጠናቀቀ በኃላ የሚሰጠውን ግዳጅ በውስብስብ ቦታዎች ሁሉ በመግባት በድፍረትና በቆራጥነት ከአውሮፕላን በፓራሹት በመዝለል የጠላትን ኃይል በማዛባትና መምታት የሚችል ነው ብለዋል። ሌተናል ጄኔራል ሹማ አየር ወለድ ክፍሉን ከበባዎችን ሰብሮ የመውጣት ግዳጅን ተቀብሎ በጀግንነት የሚፈፅም፤ በታማኝነት ግዳጁን ያለማወላወል በታላቅ ስነ-ምግባር በሙሉ ኃላፊነትን የሚወጣ ፤ለቁልፍ እሴቶች ተገዢ የሆነ ቃሉን በማክበር ክፍሉን በልዩ ፍቅር የሚወድ ፤ፍርሃትን በማስወገድ ድፍረትን የሚላበስ ስቃይን፤ ርሃብን፤ውሃ ጥምን በመቋቋም ግዳጅን የሚወጣ መንፈሰ ጠንካራ ነው በማለት ገልፀወታል፡፡    የአየር ወለድ ሃይል ለሀገሩ ራዕይ መሳካት ያለማቋረጥ የሚሰራ ፣የተዘጋውን በር የሚከፍት፣ የዘገየውን ውጊያ የሚያፈጥን ፣የውጊያን ማርሽ ቀያሪ ፣ድንበር ተሸጋሪ ውጊያዎች ሲገጥሙ ፈጥኖ በመንቀሳቀስ የጠላትን ቁልፍ ትስስሮች የሚያወድም፣ ጠላት የሚጠቀምባቸውን መንገዶች ሁሉ እና የስበት ማዕከል የሚበጣጥስ ኃይል በመሆኑ እሱን መሰል አባላቶችን መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡ ሰልጣኞች ይህንን ውስብስብ ድፍረትና ብቃት የሚጠይቀውን ስልጠና በብቃት አልፋችሁ ለዛሬ የደረት ክንፍ (ዊንግ) መልበሻ ቀን ደርሳችኋል፤ የአየር ወለድ ስልጠና ግቡ የደረት ክንፍ ወይም ዊንግ መልበስ ብቻ ሳይሆን የሚሰጠውን ግዳጅ በፓራሹት በመዝለል መፈፀም የጠላትን ሀይል አዛብቶ በመደምሰስ ለወገን ኃይል ድጋፍ ማድረግ ነውና እንደምታሳኩት አምናለሁ ሲሉም ገልፀዋል። የዛሬ ተመራቂዎች ሀገርና መንግስት የሚሰጣችሁን የአየር ወለድ ሰልጣኝ የማፍራት ግዳጅ እና ነባሩን  አሰልጣኝ የመተካት ግዳጅ በተገቢው በመወጣት የሀገራችንን ሰላም የማስጠበቅ ሚናችሁን ማጠናከር ይገባችኋል ሲሉም ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ አሳስበዋል፡፡    የማሠልጠኛ ትምህርት ቤቱ አዛዥ ሻለቃ ፀጋዬ ካሱ  ሰልጣኞች በልበ ሙሉነት ድፍረት ከጥንከሬ የሚጠይቀውን ስልጠና አጠናቀው ለዛሬ የደረሱት የአሠልጣኙን ትዕዛዝ በማክበር መሆኑን ገልፀው የደረት ክንፍ (ዊንግ) መልበስ ብቻውን የአየር ወለድ ሰልጣኝ ግብ አይደለምና ቀጣይ በሚሠጠው ግዳጅ የሚለካ መሆኑን በመገንዘብ ከተመራቂዎች ብዙ መሥራት ይጠበቃል ብለዋል።  ዘገባው የዕዙ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ክፍል ነው፡፡

#ሶማሌላንድ " ከአካባቢው ጋር በተያያዘ ሰፊ ሌላ ዓላማ ላላቸው #ግብፆች ምን አስጨነቀን ? " - አምባሳደር አብዱላሂ ሞሀመድ ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ የተፈራረሙትን የመግባቢያ ስምምነት ለማጠናቀቅ " አሁን ከሁለቱም ወገኖች የቴክኒክ ኮሚቴ በመዋቀር ላይ ነው " ሲሉ በኢትዮጵያ የሶማሊላንድ ተወካይ አምባሳደር አብዱላሂ ሞሀመድ ተናገሩ። አምባሳደር አብዱላሂ ይህን ያሉት ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ነው። የሶማሊላንዱ ተወካይ ፦ " ጉዳዩን ለማጠናቀቅ አሁን ከሁለቱም ወገኖች የቴክኒክ ኮሚቴ በማዋቀር ላይ ነን። እና ይህ ቀድሞውኑ በሂደት ላይ እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ። (ፊርማውን ትከትሎ) ግንኙነቶች ነበሩ። በሁለቱ ሀገሮች መካከል ጉብኝቶች ነበሩ። የውጭ ጉዳይ እና የአለም አቀፍ ግንኙነት ሚኒስትራችን ባለፈው ሳምንት ነው የተመለሱት። እሳቸው እዚህ (አዲስ አበባ) ከእኔ ጋር ነበሩ። ዋና ተግባራቸውም ጉዳዩ መሠረት እንዲይዝ ከኢትዮጵያ አቻዎቻቸው ጋር ለመምከር ነበር። ይዋል ይደር እንጂ ሁለቱ ኮሚቴዎች ወደ ስራ እንዲገቡ እናደርጋለን። ስለዚህ ይህ በጣም በቅርቡ ይከናወናል ብዬ አስባለሁ " ብለዋል። ሶማሊላንድ አለምአቀፍ እውቅና ያገኘ ባይሆንም ባለፉት 30 ዓመታት ፦ * ራሱ የሚቆጣጠረው ድንበር ፣ * የራሱ ሰንደቅ ዓላማ ያለው * ምርጫ ሲያካሂድ የነበረ ፣ * ሕዝቡንም ሲያስተዳድር የቆየ መንግሥት መሆኑን ነው ሲሉ ተናግረዋል። ከሶማሊያ እና ሌሎች ሀገሮች የተነሳውን ተቃውሞ እንዴት እንደሚመለከቱት የተጠየቁት አምባሳደሩ ፦ " የዓረብ ሊግ፣ ግብፅና ሶማሊያን በተመለከተ፣ በኔ እምነት በዚህ ረገድ ምንም ማድረግ የማይችሉ ይመስለኛል። ያለቀለት የተደመደመ ጉዳይ ነው። ከአካባቢው ጋር በተያያዘ ሰፊ ሌላ ዓላማ ላላቸው ግብፆች ምን አስጨነቀን " ብለዋል። በመግባቢያ ስምምነቱ መሠረት ሶማሌላንድ በአፀፋው ምን ታገኝ እንደሆንም ተጠይቀው ፥ " ለሶማሌላንድ ዕውቅና መስጠት። ይህ እርግጥ ነው። የዚህ ፕሮግራምም አካል ነው። የስምምነቱም ክፍል እና አካል ነው " ብለዋል። አምባሳደር አብዱላሂ ሶማሊያ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የቀጣናው አለመረጋጋት ምንጭ ናት ብለዋል። ይልቁንም ሶማሊላንድ ለቀጣናው መረጋጋት ጉልህ ድርሻ ያላት መሆኑን ገልፀዋል። " ኢትዮጵያም፣ ድንበሯም እንዲከበር እንጠብቃለን። ሁለተኛ ፣ ሶማሊላንድ በሕግ የፀና እውቅና ያለው ግዛት ሆኖ መታወቅ አለበት። ምክንያቱም እኛ የአካባቢው ጂኦ ፖለቲካዊ መረጋጋት አካል እና ባለድርሻ ነበርን። ባለፉት አመታት አልሸባብን እና ሽብርተኝነትን እየተዋጋን ነበር። " ብለዋል። የሶማሊላንድ የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር አብዱላሂ ሞሀመድ ፤ " ሶማሊላንድ የሌሎች ሀገሮችም ድጋፍ አላት " ሲሉ ተናግረዋል። " ሶማሊላንድ በቀጣዩ የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ይህንን ጉዳይ በሚገባ ትይዘዋለች " ያሉት አምባሳደሩ ፤ " ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ወዳጆችም አሉን። ከ5 የተለያዩ ክልሎች፤ ለጉዳያችን በጣም በጣም አዎንታዊ አመለካከት ያላቸው አባል ሀገራት (የአፍሪካ ሕብረት) አሉን። " ብለዋል። " እኛ ሕጋዊ ጉዳይ አለን ፣ የሞራል ጉዳይም አለን ፣ የሚቀረው የፖለቲካ ጉዳይ ብቻ ነው። ለአካባቢው እና ለአህጉሪቱ የምናደርገው በጎ አስተዋፅኦ ተዘንግቷል። የትኛውም አካል የህዝባችን ውሳኔ ላይ ሊወስን አይችልም። ህዝባችን ሕዝበ ውሳኔ አድርጎል። 97.5 በመቶው ነፃ ሀገር መሆንን በመደገፍ ድምጽ ሰጥቷል " ሲሉ ሃሳባቸውን ደምድመዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ ቃለምልልስ እና መረጃ የዶቼ ቨለ ሬድዮ መሆኑን ያሳውቃል።

የራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት ምን አሉ ? የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ከሶማሌላንድ ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ሰፋ ያለ የሶማልኛ ቋንቋ ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር። በዚህም ቃለምልልስ ወቅት በርካታ ጉዳዮች ተነስተዋል። ከነዚህም ውስጥ ፦ * ከኢትዮጵያ ጋር ስለተደረገው ስምምነት * ከሶማሊያ እየተነሳ ስላለው ተቃውሞ * ስለ ግብፅ መሪ እና የአረብ ሊግ መግለጫ * ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ የሉዓላዊ ሀገርነት እውቅና ትሰጥ እንደሆነ ...የሚሉና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮችን ተስተዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ከሰፊ ቃለምልልሱ ወሳኝ ያላቸውን የፕሬዜዳንቱን ቃል ተመልክቷል። ፕሬዜዳንት አብዲ ባሂ ሙሴ ፤ " ለኢትዮጵያ ባህር ኃይል የባህር ኃይል ጦር ሰፈር የሚሆን ትንሽ መሬት በሊዝ ይሰጣል " ያሉ ሲሆን " ስምምነቱ ኢትዮጵያ ለገቢና ወጪ ምርቶች #የበርበራ ወደብን እንደምትጠቀም ይገልጻል " ብለዋል። " ይህ የባህር ሃይል ጦር ሰፈር ለወታደራዊ አገልግሎት ብቻ የሚውል እና ምንም አይነት የንግድ እንቅስቃሴዎች ወይም ሸቀጦችን መጓጓዣ የማይጨምር መሆኑን አጽንኦት መስጠቱ ወሳኝ ነው " ሲሉም ተናግረዋል። " በዚህም ሳቢያ በስምምነቱ ዙሪያ በሶማሊያ በኩል የሚነሳው ተቃውሞ በተዛባ መረጃ ላይ የተመሰረተ ይመስላል። " ሲሉ አክለዋል። ፕሬዜዳንቱ ፤ " በእርግጠኝነት ! በስምምነቱ ኢትዮጵያ እንደ ሉዓላዊ ሀገር ለሶማሌላንድ እውቅና ትሰጣለች። " ያሉ ሲሆን " በይፋ የሚፈረመው የስምምነት ሰነድ የሶማሌላንድን እውቅና በግልፅ ይጠቅሳል። የዚህ ስምምነት ይዘት ሶማሊላንድን እንደ የተለየ አካል በመቀበል ማረጋገጫ ይሰጣል ፤ ይህ እውነታ በሰነዱ ውስጥ በግልፅ ተቀምጧል " ሲሉ አሳውቀዋል። ፕሬዜዳንቱ ከሶማሌላንድ ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ያደረጉት የሶማልኛ ቃለምልልስ ወደ እንግልዘኛ ቋንቋ ተተርጉሞ በዚህ ቀርቧል ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-26 (ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ የፕሬዜዳንቱን ቃለምልልስ ወደ እንግሊዘኛ ቋንቋ ተርጉሞ ይፋ ያደርገው የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት መሆኑን ያሳውቃል) 👉 subscribe ማድረጓን እንዳይረሱ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://www.youtube.com/@Commando_2016

👉 subscribe ማድረጓን እንዳይረሱ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://www.youtube.com/@Commando_2016

ሶማሊላንድ ምን አይነት ግዛት ናት? የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 17 ቀን 2016 ዓ.ም ሱማሊላንድ ርዕሰ ከተማ - ሃርጌሳ ስፋት - 177 ሺህ ስኩዌር ኪሎሜትር የህዝብ ብዛት - 5 ነጥብ 7 ሚሊየን ቋንቋ - ሶማሊኛ፣ አረብኛ፣ እንግሊዝኛ ሶማሊላንድ የሶማሊያው ወታደራዊ መሪ ዚያድ ባሬ ከስልጣን በተወገደ ማግስት ከሶማሊያ ተነጥላ ነጻ ሀገር መሆኗን አውጃለች። ዚያድ ባሬ ኢሳቅ በተሰኘው የሶማሊላንድ ጎሳ አባላት ላይ የተከተለው ፖሊሲ ለውድቀቱ አንዱ ምክንያት ተደርጎ ይነሳል። ሶማሊላንድ ዚያድ ባሬ እንደተወገደ በ1991 ከሶማሊያ መገንጠሏን ብታውጅም ሞቃዲሾም ሆነ ሌሎች ሀገራት እንደነጻ ሀገር እውቅና አልሰጧትም። አለማቀፉ ማህበረሰብ እውቅና ባይሰጣትም ሉአላዊ ሀገራት የሚያሰኙ ተግባራትን መፈጸም ከጀመረች ሶስት አስርት አመታት ተቆጥረዋል። ራስ ገዟ ግዛቷ ከ1996 ጀምሮ የሶማሊላንድ ፓስፖርት አስተዋውቃለች፤ ህገመንግስት አጽድቃ፣ ምክርቤቶች አዋቅራም በየአምስት አመቱ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እያካሄደች ነው (ነጻነቷን ካወጀች ጀምሮ ሶስት ምርጫዎችን አድርጋለች)። ከሀገራት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለመመስረት ጥረት እንደምታደርግም ትገልጻለች። በአሜሪካ፣ ብሪታንያ፣ አረብ ኤምሬትስ እና ታይዋን ጉዳይ ማስፈጸሚያ ቢሮዎች አሏት። የሶማሊያ መንግስት ግን እንግሊዝ በሞግዚትነት ያስተዳደረቻት ሶማሊላንድ “ከእናት ሀገሯ ሶማሊያ አልተነጠለችም፤ የግዛቴ አካል ናት” በሚለው አቋሙ እንደጸናች ያለች ይመስላል። ሶማሊላንድን የሚመሩት ሙሴ ቢሂ አብዲ በህዳር ወር 2017 በተካሄደ ምርጫ አሸንፈው አህመድ ሲላንዮን ተክተዋል። ቢሂ የገዥው ኩልሚየ ፓርቲ መስራችና መሪው ሲላንዮ በ2010ሩ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ካሸነፉ በኋላ የፓርቲው ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል። ከቅኝ ግዛት እስከ ነጻ ሀገር ምስረታ 1888 - ብሪታንያ ከወቅቱ የሶማሊላንድ መሪዎች (ሱልጣኖች) ጋር ስምምነት ደርሻለሁ በማለት አካባቢውን የቅኝ ግዛቷ አካል አድርጋ አወጀች 1899 - ሞሀመድ አብዱላህ የሃይማኖት አባት በብሪታንያ አገዛዝ ላይ አምጸው ደርቪሽ የተባለ ግዛት መስርተው ተዋጉ፤ በ1920 ተሸነፉ 1991 - የቀድሞዋ የብሪቲሽ ሶማሊላንድ ከሶማሊያ ሪፐብሊክ ተነጥላ ነጻ ሀገር መሆኗን አወጀች 2001 – 97 በመቶ ህዝቧ የሶማሊላንድ ህገ መንግስትን አጸደቀ ። 2016 - ሶማሊላንድ ከሶማሊያ የተነጠለችበትንና ነጻነቷን ያወጀችበት 25ኛ አመት ተከበረ፤ ይሁን እንጂ ለራስ ገዟ ግዛት እውቅና የሰጣት የለም ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ከተላቀቀች በኋላ የቅኝ ግዛት ድንበሯን አስጠብቃ መቆየቷን የምትገልጸው ሶማሊላንድ እንደሀገር የሚያስቆጥሩ ነገሮችን ሁሉ አሟልቻለሁ ትላለች፤ ሀገራት እውቅና እንዲሰጧትም ብርቱ ጥረት በማድረግ ላይ ትገኛለች። በአባቱ ወልደማርያም