ch
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

前往频道在 Telegram

Addis abeba Ethiopia

显示更多
4 648
订阅者
-23224 小时
-1 7917
-3 26430
帖子存档
ሐምሌ 29 ቀን 2014 ዓ.ም የጸጥታ ኃይሉ በወሰደው እርምጃ 24 የአልሸባብ አመራሮችን ጨምሮ ከ800 በላይ የቡድኑ ተዋጊዎች ተደመሰሱ። የጸጥታ ኃይሉ በወሰደው እርምጃ እስካሁን ባለው ሂደት 24 የአልሸባብ አመራሮችን ጨምሮ ከ800 በላይ የሽብር ቡድኑ ተዋጊዎች መደምሰሳቸውን ጊዜያዊ የጸጥታ ኮማንድ ፖስት አስታወቋል፡፡ ድሽቃን ጨምሮ በርካታ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውም ነው የተገለጸው፡፡ የመከላከያ ኃይል ስምሪት ኃላፊና የጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ አስተባባሪ ሜጀር ጄነራል ተስፋዬ አያሌው እና የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል አዛዥ ኮሚሽነር ጄነራል መሃመድ አህመድ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ የአልሸባብ የሽብር ቡድን ከሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ ሰርጎ ለመግባት ያደረገው ሙከራ በፀጥታ ኃይሉና በሕዝቡ የተቀናጀ እርምጃ ሙሉ በሙሉ ከሽፏል። ሜጀር ጄነራል ተስፋዬ እንደሚሉት፤ ኢትዮጵያን ለማተራመስ የሚሹ የውጭ ጠላቶች የውስጥ ባንዳዎችን በመቅጠር ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡ እቅዳቸው እንዳሰቡት አልሳካ ሲላቸው በአሁኑ ወቅት አልሸባብን ከኋላ በመደገፍ ከንቱ ሙከራ ማድረጋቸውንም ነው ያብራሩት፡፡ ይህም ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጸጋዎችን ተጠቅማ ለመልማት የጀመረችውን ተስፋ ሰጪ ሥራ ለማደናቀፍ ያለመ ሙከራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በዚህም አልሸባብ ኢትዮጵያና ሶማሊያ በሚዋሰኑባቸው አካባቢዎች የተወሰነ ኃይሉን በ16 ተሽከርካሪዎች በመጫንና የተወሰነውን ደግሞ ጨለማን ተገን አድርጎ በእግር ወደ ኢትዮጵያ ሰርጎ በማስገባት ጥቃት ለመፈጸም መሞከሩን ነው የገለጹት፡፡ ነገር ግን የመከላከያ ሰራዊቱ ከሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ጋር በመቀናጀት በወሰደው እርምጃ ወደ ኢትዮጵያ ሰርጎ ለመግባት የሞከሩ የሽብር ቡድኑ አመራሮችን ጨምሮ ተዋጊዎቹ ሙሉ ለሙሉ ተደምስሰዋል ነው ያሉት፡፡ የኢፌዲሪ አየር ኃይል የተመረጡ ኢላማዎችን ነጥሎ በመምታት የሽብር ቡድኑ ለረዥም ጊዜ እጠቀምበታለሁ ብሎ ያዘጋጀውን የሎጂስቲክስና ጦር መሳሪያ ክምችት ያወደመ ሲሆን፤ የሽብር ቡድኑን አመራሮችም መደምሰስ ችሏል፡፡ በዚህም የሚከተሉት የሽብር ቡድኑ አመራሮች መደምሰሳቸው ተገልጿል:- 1) ፉአድ መሐመድ ከሊፍ -የአልሸባብ ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳ ኃላፊ 2) አብዱልአዚዝ አቡሙስ -የአልሸባብ ቃል አቀባይ 3) አብዲኑር ኢሴ -የቦኮል ዞንና የኢትዮጵያ ድንበር አዋሳኝ ኃላፊ 4) ሸክ ለአብ ሶማሊያዊ -የደቡብ ምስራቅ ሎጂስቲክ ኃላፊ 5) አቡ ሙሳ - ምክትል አፈጉባኤ 6) አሊ መሃመድ ሃሰን - የአልሸባብ ማዕከላዊ ኮሚቴ አማኒያት ሁለተኛ ሰው 7) አደም -ወደ አገር ውስጥ ሰርጎ ለመግባት የሞከረው የሽብር ቡድኑ ምክትል አዛዥ ) ሙክታር ጋብ - ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል 9) አሚር አብደላ (መሃመድ አብዱላሂ) - ሞርጋቤ ካምፕ የአልሸባብ ስልጠና ኃላፊ 10) ኢንጂነር ጀሃድ ስሬዋን (ሙጃሂድ ፈይሰል) - በብሉፍላይ ካምፕ የማሠልጠኛ ኃላፊና የፈንጅ ኃላፊ 11) ሼክ ሁሴን በርደሌ - የባይና ቦከል ዞን ቀረጥ ሰብሳቢ 12) ሼክ ሃሰን ኑኖ -የታችኛው ሸበሌ ጀበሃ ዘመቻ ኃላፊ 13) ያሲን ደሬ - አሚር 14) ሳላህ ደሬ - የባይ ዞን የአልሸባብ ትምህርት ኃላፊ 15) አቡሠላም - የቦኮል ዞን የአልሸባብ ሰብሳቢ 16) ሃምዚ አቡዱላሂ - የባይ ዞን መረጃ ኃላፊ 17) አብዱላሂ ሃጅ - የባይና ቦኮል ዞን ወታደራዊ አዛዥ 18) ሙክታር ቦሮ - አሚር 19) አብዱረሽድ ጋቦ- አሚር 20) አብዱኪም ገዱደ- አሚር 21) ሙክታር ጋብ - የቀጣና ዘመቻ ኃላፊ 22) አዩብ ዳውድ - አሚር 23) አሊ አደን---አሚር 24) ሃሰን መሃመድ--አሚር ናቸው። እንደ ሜጀር ጄነራል ተስፋዬ ገለጻ፤ የጸጥታ ኃይሉ ያከናወነው ኦፕሬሽን የመከላከያ ሠራዊት፣ የአየር ኃይል እንዲሁም የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይልና ሕዝብ ጀግነነትን በተግባር ያረጋገጠና ኢትዮጵያን ለመድፈር የሚሞክሩ ኃይሎች ደጋግመው ማሰብ እንዳለባቸው ትምህርት የሰጠ ነው፡፡ የክልሉ ነዋሪዎች የጸጥታ ኃይሉን ደጀን ሆነው በመደገፍ ረገድ አኩሪ ተግባር ማከናወናቸውንም አብራርተዋል፡፡ አሁን ላይ የሽብር ቡድኑ በውስጥ ያዘጋጃቸው ሴሎችን የማጥራት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል አዛዥ ኮሚሽነር ጄነራል መሐመድ አህመድ የሽብር ቡድኑ አቶ፣ የድ፣ ኤልበርዴና ወሻ በተባሉ የጠረፍ አካባቢዎች ጥቃት ለመፈጸም መሞከሩን ተናግረዋል። በወቅቱ የመከላከያ ሰራዊቱና ሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በጀግንነት በመዋጋት የኢትዮጵያ አለኝታነታቸውን በተግባር አሳይተዋል ነው ያሉት፡፡ በዚህም የአልሸባብ 24 ቁንጮ አመራሮችን ጨምሮ 813 የሽብር ቡድኑ ተዋጊዎች መደምሰሳቸውን ጠቅሰው፤ አልሸባብ በዚህን ያህል ቁጥር በአንድ ጊዜ ኮር አመራሮቹ ሲገደሉበት ይህ የመጀመሪያ ጊዜ ሊሆን እንደሚችልም ነው የጠቆሙት፡፡ የሽብር ቡድኑ ተዋጊዎቹን ወደ ኢትዮጵያ አስርጎ ለማስገባት የተጠቀመባቸው ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ በርካታ የጦር መሳሪያዎች መውደማቸውንም ተናግረዋል፡፡ ድሽቃን ጨምሮ በርካታ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውንም እንዲሁ፡፡ አጠቃላይ በኦፕሬሽኑ የሶማሌ ክልል ሕዝቦች የየትኛውም የጥፋት ቡድን ተባባሪ አለመሆናቸውን በተግባር ያሳዩበትና የጸጥታ ኃይሉም አገሩን ለመጠበቅ ሁሌም ዝግጁ መሆኑ በተግባር ያረጋገጠበት መሆኑንም በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡ መረጃው የኢዜአ ነው

፨ ቻይና ከታይዋን እስከ ጃፓን ያለውን ቀጠና በሚሳኤል እያናወጠቺው ነው ። ክስተቱ ሩሲያ ዩክሬይንን ከመውረሯ በፊት ከምታደርገው የጦር እንቅስቃሴ ጋር ፍፁም ይመሳሰላል ። አሁን የቻይና ጦር የሚገኘ
+1
፨ ቻይና ከታይዋን እስከ ጃፓን ያለውን ቀጠና በሚሳኤል እያናወጠቺው ነው ። ክስተቱ ሩሲያ ዩክሬይንን ከመውረሯ በፊት ከምታደርገው የጦር እንቅስቃሴ ጋር ፍፁም ይመሳሰላል ። አሁን የቻይና ጦር የሚገኘው ከታይዋን ክልል ውስጥ ነው ። ከበባውም ተጠናክሮ ቀጥሏል ። ቻይና ኑክሌር የተሸከሙ ሚሳኤሎቿን ሳይቀር አሰማርታለች ። ፨ ቻይና ካስወነጨፈቻቼው ሚሳኤሎች ውስጥ አምስቱ የጃፓን ቀጠና ውስጥ አርፈዋል ይህም ጃፓንን አስደንግጧል ። ጃፓን ድርጊቱን ያወገዘች ሲሆን ቻይና ከዚህ ድርጊቷ እንዲትቅጠብም መክራለች ። ፨ ቻይና በናንሲ ፔሎሲ ላይ ማእቀብ ጥላለች ። ማእቀቡ በፔሎሲ ላይ ብቻ ሳይወሰን የፔሎሲን ቤተሰቦችም ጭምር የሚያካትት ማእቀብ ነው ። የማእቀቡ ዝርዝር ገና ይፋ አልተደረገም ። ማእቀብ የመጣል ሱስ ያለባት አሜሪካ የቻይናን ማእቀብ አስተናግዳለች ። ፨ የቻይና ሀከሮች የታይዋንን በርካታ የሳይበር ጥቃቶችን እያደረሱ ሲሆን በዚህም የታይዋን መከላከያና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ድረገፆች ከአገልግሎት ውጭ ሆነዋል ። #Seid_Mohammed_Alhabeshiy

የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል ተቆራርጦ የቀራውን የአሸባሪውን ቀሪቶች በማጽዳት የተሳከ ኦፕሬሽን አካሄዳል:: የሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ አሸባሪው አልሸባብ የኢትዮጲያ ድንበር ላይ ወረራ ከከፍተበት ጊዜ ጀም
+2
የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል ተቆራርጦ የቀራውን የአሸባሪውን ቀሪቶች በማጽዳት የተሳከ ኦፕሬሽን አካሄዳል:: የሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ አሸባሪው አልሸባብ የኢትዮጲያ ድንበር ላይ ወረራ ከከፍተበት ጊዜ ጀምሮ በወሰደው እርምጃ ከ 800 በላይ የአልሸባብ ሚሊሻወች ሲገደሉ ከ 100 በላይ የአሸባሪው ሚሊሻዎ አባለት ተማሪከዋል:: የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል የአልሸባብን ቀሪቶች ማፀዳት በሚል በወሰደው ልዩ ኦፕሬሽን በየጫከው በየጋራ ሸንተሩ ተቆርጦ የቀሩትን የአሸባሪው አልሸባብ ቅሪቶችን በማሳደድ እጅ አልሰጠም ያለውን ኃይል በመደምስስ እጅ የሰጠውን በመማሪክ የተሳካ አፕሬሽን አካሄዳል:: የሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ ወደ ኢትዮጲያ ድንበር የገባውን የአሸባሪ አልሸባብ በመደምሰስ ተበታትኖ በየቦታው ተቆረጦ የቀሩትን የአሸባረው አልሸባብ ቅሪቶችን ለማጽዳት በምሥራቅ አንበሶቹ በተወሰደ የማጽዳት ኦፕሬሽን የሶማሌ ክልል ሃይል በአሳየው የላቀ ጀግንነት አሸባሪው አልሸባብ በገባበት ጓድጋድ በመግባት እጅ አልሰጥም ያለውን በመደምሰስ እጁ የሰጠውን አሸባሪ በዚህ መልኩ ስብስቦ ገቢ በማድረግ የሃገሩን ዳር ድንበር በማሰከበር ወደር ያሌለው ጀግንነቱን አስመሰከራል::

የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ስራዎችን በትብብር ለመስራት ተስማሙ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ስራዎችን በት
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ስራዎችን በትብብር ለመስራት ተስማሙ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ስራዎችን በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ። የትብብር ስምምነቱ በቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ማልማት፣ በምርምር እና ልማት፣ በሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ የሰው ኃይል ልማት እንዲሁም ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመስራት የሚያስችል መሆኑን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና አስረድተዋል። የዩኒቨርሲቲው ኮማንዳንት ሜ/ጀኔራል ሃብታሙ ጥላሁን በበኩላቸው ስምምነቱ ሁለቱ ተቋማት ያላቸዉን የሰዉ ኃይል እና ሃብት በቅንጅት በመጠቀም ለሃገራዊ ስኬት በጋራ ለመስራት ያስችላቸዋል ብለዋል፡፡ ስምምነቱን ተፈፃሚ ለማድረግ ከሁለቱ ተቋማት የቴክኒክ ኮሚቴ ተደራጅቶ ወደ ስራ መግባን የመከላከያ ሰራዊት መረጃ ያመለክታል

ለኢትዮጵያ እጅግ ጠቃሚ የሚሆነው ስምምነት እ.አ.አ 2ዐ15 በግብፅ ፣ ሱዳንና ኢትዮጵያ መካከል የተፈረመው DOP “Declaration of Principles” በመባል የሚታወቀው የዓለም አቀፍ ህግን መሠረት ያደረገና አስር ዝርዝር ነጥቦችን የያዘ ሶስቱንም የተፋሰሱ ሀገራትን ተጠቃሚ የሚያደርግ ስምምነት ታሪካዊና ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርግ ስምምነት ነው ፡፡ ዶ/ር Dawd Temam ከ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት፣ ሐይድሮሊክና ውሃ ምህንዲስና ት/ት ክፍል።

የአባይ ወንዝ እውነተዎች በዶ/ር ዳውድ ተማም 👉በምድራችን 263 ወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ይገኛሉ፡፡ ረዥም ርቀትን በመጓዝና በርካታ ሀገራትን በማቋረጥ ቀዳሚ የሆነው እኛ አባይ የምንለው ናይል ወንዝ ነው፣ 665ዐ ኪ.ሜ ይጓዛል ፣11 ሀገራትን ያካልላል ፣አባይ ወንዝ በዓለም ረዥም ርቀት በመጓዝ የሚስተካከለው ባይኖርም ደቡብ ሱዳን ሀገር ሆና ከመውጣቷ በፊት 1ዐ ሀገራትን በማቋረጥ የሚስተካከለው በአውሮፖ የሚኘው ዳኑብ (Danube) ወንዝ ነበር፡፡ ናይልን 3 ወንዞች ተጣምረው ይፈጥሩታል ከብሩንዲ ሰንሰላታማ ተራሮች የሚነሳው ነጭ አባይ፣ ከኢትዮጵያ የሚመነጨው ጥቁር አባይ እና የኢትዮጵያ ድንበርን ተሻግሮ ሱዳን ሲደርስ አትባራ በሚል በሚጠራው ተከዜ ወንዝ ነው፡፡ እነዚህ ሦስት ወንዝች ካርቱም ላይ ከተገናኙ በኋላ ናይል ይሰኛሉ፡፡ የሱዳንና የግብፅን በረሃዎችን አቋርጦ ረዥሙ የናይል ጉዞ እስከ ሰሜናዊ ግብፅ በመዝለቅ በሚድትራኒያን ባህር ዳርቻ ይጠናቀቃል፡፡ የናይል ወንዝ 84BM3 የውሃ ሀብት እንዳለው ጥናቶች ይጠቁማሉ 86 በመቶ ያህሉ ማለትም 56BM3 የውሃ ሀብት የሚሄደው ደግሞ ከኢትዮጵያ ነው ከዚህ ውስጥ የአባይ ወንዝ ብቻውን 53 በመቶ ይሸፈናል፣ የአባይ ታላቅነት ሚስጥርም ከዚህ ይጀምራል፡፡ በአማራ ክልል ሰካላ በሚሰኝ አካባቢ የሚገኘው ሰንሰላታማው የጮቄ ተራራ እንደ ራስዳሸንና ባሌ ተራሮች ከፍታው መለያው አይደለም፣ ትንሹ ጮቄ ግን የታላቁ አባይ ወንዝ መፈጠሪያ ነው፡፡ ከዚህ ተነስቶ ግልገል አባይ ይባልና ወደ ጣና ሐይቅ ይገባል፡፡ ከጣና ሲወጣ ሌሎች ወንዞች ይቀላቀላሉ ማለትም መገጭ፣ ጉመራ እና ርብ ወንዞች ይቀላቀሉታል፡፡ አባይን አባይ የሚያሰኘው ቦታ አሁን የህዳሴ ግድብ የሚሰራበት ቦታ ላይ ነው፡ ትልቁ ለአባይ ገባር ወንዝ ዲዴሳ ወንዝ ነው 18 በመቶ በመሸፈን ፣ ቀጥሎ ዳጉስ ከዚያም በለስ ወንዝ ነው፣ እነዚህ ሦስት ወንዞች አባይን የሚያገኙት ከግድቡ ከፍ ብሎ ነው። በአጠቃላይ አባይን አባይ የሚያሰኙ 16 ንዑስ ተፋሰሶች ናቸው፡፡ አባይ ከመነሻው አንስቶ ካርቱም ላይ ከነጭ አባይ ጋር እስኪቀላቀል ድረስ 145ዐ ኪ.ሜ ይጓዛል በኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ 82ዐ ኪ.ሜ ይሸፍናል፡፡ አባይ ለሀገራችን ስልታዊ ጠቀሜታ አለው ሲባል በሀገራችን ውስጥ ከሚገኙ 12 ተፋሰሶች በገፀ-ምድር ውሃ ፍሰት 5ዐ በመቶውን ይሸፍናል፣ በኃይል አለኝታ ደግሞ ካለን የኃይል አለኝታ እስከ 4ዐ በመቶ ይሸፍናል፡፡ የሀገራችን የመሬት ገፅታ ስፋት 2ዐ% ይሸፍናል ወደ 25% የሚሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚኖረው በአባይ ተፋሰስ ውስጥ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የአባይ ወንዝ መፈጠሪያ ትሁን እንጂ ለዘመናት በአባይ የመጠራት እንጂ የመልማት ዕድሉ አልነበራትም፣ ማንኛውም ሀገር ባለው ወሰንና ወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ሌሎች የተፋሰሱ ሀገራትን በማይጎዳ መልኩ በውሃው ሀብቱ የመልማት ተፈጥራዊ እና ህጋዊ መብት አለው፣ ኢትዮጵያ የአባይ ወንዝን ከሌሎቹ የተፋሰሱ ሀገራት ጋር እንዲሁም ሌሎችን በማይጎዳ መልኩ በተናጠል እንዳታለማ ያደረጓት በ ዋናነት ሁለት ምክንያቶች ናቸው፡፡ የመጀመሪያው ውጫዊ ተፅኖ ሲሆን ሁለተኛው ውስጣዊ የአቅም ውስንነት ነው፣ የአባይ ተፋሰስ ሀገራትን በቀኝ ገዢነት ያስተዳድሩ የነበሩ ሀገራት በውሃ ሀብቱ ግብፅን ብቻ ተጠቃሚ እንድትሆን በተለያየ ጊዜ ያደረጉ ስምምነቶች እንዲሁም ከቅኝ አገዛዝ በኋላ የግብፅ መንግስታት ኢትዮጵያ የዓባይን ወንዝ ለማልማት የገንዘብ ድጋፍና ዕርዳታ እንዳታገኝ ማድረጋቸው በውጫዊ ተፅኖነት ይጠቀሳል፡፡ እ.አ.አ ከ189ዐ - 195ዐ ድረስ የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት ቀኝ-ገዢዎች በዋናነት እንግሊዝ ፣ ፈረንሳይና ጣሊያን በዓባይ ውሃ አቃቀም ላይ ከ6 ጊዜ በላይ ስምምነቶችን አድርገዋል፡፡ ሁሉም ስምምነቶች ግን በአንድ ነገር ይመሳሰላሉ ኢዮጵያንና ሌሎች የራስጌ ተፋሰስ ሀገራትን ያገለሉና በዋናነት ግብፅን በተከታይነት ሱዳንን ተጠቃሚ ያደረጉ በመሆናቸው ፣ ከሁሉም በላይ ግን እ.አ.አ 1929 እና 1959 ግብፅና ሱዳን የናይል ውሃን ብቸኛ ተጠቃሚ እነሱ መሆናቸውን የደነገጉበትን የእርስ በእርስ ስምምነት አድርገዋል፡፡ በ1929 ኢዮጵያን ወሮ የበረው የፋሺስት ጣሊያን መንግስት በዓባይ ወንዝ ላይ ምንም ዓይነት ልማት ላለማኬሄድ ከእንግሊዝ ቀኝ ገዢዎች ጋር ተፈራርመዋል፣ እ.አ .አ1959 ደግሞ ለናይል ውሃ ምንም ዓይነት አስተዋፅኦ የሌላቸው ሁለት ሀገራት በትነት የሚባክነውን የወንዙን ውሃ ተቀናሽ አድርገው ግብፅ 55.5BM3 ሱዳን ደግሞ 18.5BM3 ውሃ ለመጠቀም ስምምነት አደረጉ፣ 86 በመቶ የናይል ውሃ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያንና ሌሎቹን የራስጌ ተፋሰስ ሀገራትን ጭራሽ መኖራቸውን በመዘንጋት ስምምነት አድርገዋል፡፡ እስከ ዛሬ በአባይ ውሃ ላለመልማታችን በሁለተኛነት ምክንያት የሆነው ደግሞ በወንዙ ላይ ልማትን በራስ ሀብት ለማከናወን የሚያስችል አቅም ማጣታችን ነው ይሄን ለማስቀረት የኢትዮጵያ መንግስት ሁለት አቅጣጫዎችን ተከትሎዋል የመጀመሪያ ውስጣዊ አቅምን በገንዘብና በሰው ሀብት ልማት ማጠናከር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አካባቢያዊና አለም አቀፋዊ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ነው፡፡ በዓባይና በተፋሰሶቹ የኢትዮጵያ የመልማት ጥያቄ አመርቂ በሆነ መልኩ 46ዐ MW ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው ጣና በለስ ዘርፈ ብዙየኃይል ማመንጫ እና በቆጋ ወንዝ ላይ የመስኖ ልማት ኘሮጀክት ግንባታ መመለስ ተጀምሮ አላቆመም ይበልጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ላብና አሻራ ወደ ሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለመገንባት መነሻ ሆነዋል፡፡ በአባይ ፍታሃዊ የውሃ ክፍፍል እንዲኖር የኢትዮጵያ መንግስት የተከተለው 2ኛው አቅጣጫ ደግሞ አካባቢውና ዓለም አቀፋዊ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ነው፡፡ የአባይ ራስጌ ተፋሰስ ሀገራት ግብፅና ሱዳንን ብቸኛ ተጠቃሚ ያደረጉና ሌሎቹን ያገለሉ የውሃ አጠቃቀም ስምምነቶች ተሸረው ሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት ፍትሃዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችል ስምምነት እንዲፈጠር ከ1ዐ ዓመታት ላላነሰ ጊዜ ጥረት ተደርጓል፡፡ ለመነሻም የሚሆን “Nile’ Basin Initiative” የተሰኘ የሽግግር ኘሮግራም እ.አ.አ በ1999 ዓ.ም ተቋቋመ፣ ዋናው አለማውም የተቀረፁ ኘሮጀክቶች በተፋሰሱ አገሮች መካከል መተባበርን እንዲፈጥር እና በንዑስ ተፋሰስ ደረጃ ለምሳሌ ምሥራቅ ናይል ተብሎ ኢትዮጵያ ሱዳንና ግብፅ ያሉበት ኤርትራ በተመልካችነት ያለችበት የጋራ ኘሮጀክቶችን ለማልማት እና አብሮ ለመሥራት ጥናቶች እንዲደረጉ የታሰበ የነበረ ቢሆንም እዚህ ግባ የተባለ ነገር አልተሰራም፡፡ አለም አቀፍ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች መርሆችን መሠረት የደረገውን የናይል ሁሉን አቀፍ የስምምነት ማዕቀፍ በማርቀቅና በመጨረሻም አብላጫው የተፋሰሱ ሀገራት እንዲቀበሉት በማድረግ ሰፊ የዲኘሎማሲ ሥራ ተሰርቷል፣ የስምምነቱ ማዕቀፍ እ.አ.አ 2ዐዐ2 ዓ.ም ጀምሮ በኡጋንዳ እንቴቤ ለአንድ ዓመት ክፍት ሆኖ ቆየ፣ የተፋሰሱን ሀገራት ወደ የጋራ ልማት እንዲያመሩ ያስችላል የተባለው የስምምነት ማዕቀፉን ከተፋሰሱ ሀገራት 6ቱ ተቀብለው ፊርማቸውን ከአኖሩ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ፣ ኬንያ ፣ ታንዛኒያ፣ ኡጋንዳ፣ ሩዋንዳ እና ብሩንዲ ይገኛሉ፡፡

በአሸባሪው ሸኔ ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
+2
በአሸባሪው ሸኔ ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

#China ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ እና ሱዳን ስለ ቻይና-ታይዋን ጉዳይ ምን አሉ ? #ኢትዮጵያ ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰሞኑን የቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን የው
+2
#China ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ እና ሱዳን ስለ ቻይና-ታይዋን ጉዳይ ምን አሉ ? #ኢትዮጵያ ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰሞኑን የቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ለኢዜአ ተናግረዋል። አምባሳደር መለስ ፤ ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ስታራምድ የቆየችውን የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋሟን እንዳጸናች መሆኑን ተናግረዋል። " የኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ያሉት " አምባሳደር መለስ፤ " ከቻይና ጋር በነበረን ግንኙነት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስታት አፅንተው የያዙት አቋም ነው " ብለዋል። አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያ ለ #አንድ_ቻይና ፖሊሲ ፅኑ አቋም አላት ያሉ ሲሆን ፖሊሲውን ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው የተመድና የአፍሪካ ህብረት የሚያራምዱት አቋም መሆኑን ገልፀዋል። #ሱዳን ሱዳን ለአንድ ቻይና መርህ ድጋፏን እንደምትሰጥ አሳውቃለች። ታይዋንም የቻይና ግዛት አካል መሆኗን ገልጻለች። ሱዳን ፤ ቻይና ሉዓላዊነቷን እና የግዛት አንድነትዋን በመጠበቅ ረገድ የምታደርገውን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍም አስታውቃለች። #ኤርትራ ኤርትራ የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን ያደረጉት ጉዞ ከዓለም አቀፍ ህግና መርህ ያፈነገጠ ነው ብላለች። የአፈጉባኤዋ ድርጊት የቻይና መንግስት ሉዓላዊነት ደንቦችን እና ድንጋጌዎች እንዲሁም " የአንድ-ቻይና " ፖሊሲ የሚጻረር እና የቻይናውያን ውህደት ሂደትን የሚያደናቅፍ ነው ስትል ገልፃለች። ኤርትራ፤ አሜሪካ ቻይናን ለመቆጣጠርና ለመያዝ ጥረት እያደረገች ነው ብላ ድርጊቱ አጸያፊ ነው ብላለች። #CGTN #ENA #AlAIN #Shabait

27 የቻይና ወታደራዊ አውሮፕላኖች በድጋሚ የታይዋንን አየር ክልል ጥሰው ገቡ የቻይና ተዋጊ አውሮፕላኖች ዛሬም የታይዋንን አየር ክልል ጥሰው መግባታቸው ተገለጸ። ሲጂቲኤን እንዳስታወቀው 27 የቻይና
27 የቻይና ወታደራዊ አውሮፕላኖች በድጋሚ የታይዋንን አየር ክልል ጥሰው ገቡ የቻይና ተዋጊ አውሮፕላኖች ዛሬም የታይዋንን አየር ክልል ጥሰው መግባታቸው ተገለጸ። ሲጂቲኤን እንዳስታወቀው 27 የቻይና ሱ35 ጄቶች የታይዋንን የአየር ክልል ጥሰው ገብተዋል። ቻይና የጦር ጀቶቿን ወደ ታይዋን መላኳ ዋሸንግተንንና ቤጅንግን ወደ ጦርነት እንዳያስገባ ተሰግቷል። የአሜሪካ ምክር ቤት አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ፤ ቻይና ግዛቴ በምትላት ታይዋን ጉብኝት ማድረጋቸውን ተከትሎ ቤጅንግ አውሮፕላኖቿን ወደ ታይዋን እየላከች ነው። ቻይና የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን እንዳይሄዱ ስታስጠነቅቅ ብትቆይም ፔሎሲ ግን ታይዋን ቆይተው ተመልሰዋል። ቻይና አውሮፕላኖቿን ወደ ታይዋን ማሰማራት የጀመረችው ከፔሎሲ ጉብኝት አስቀድሞ ነበር። አፈ ጉባዔዋ ታይዋንን ለቀው ከወጡ በኋላም የቻይ አውሮፕላኖች በታይዋን የአየር ክልል ላይ እየበረሩ ነው። ቻይና፤የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ጦሯ “ዝም ብሎ እንደማይቀመጥ ማስጠንቀቂያ ስትሰጥ ነበር።ከቻይና በተጨማሪም ሩሲያ እና ሰሜን ኮሪያም የፔሎሲ ጉብኝትን ጉብኝት ኮንነው ነበር። የቻይና የጦር አውሮፕላኖች ወደ ታይዋን በመግባታቸውና በፔሎሲ ጉብኝት ምክንያት ታይዋን ለሶስት ቀናት ከፍተኛ የውጊያ ጥንቃቄ ማወጇ ይታወሳል። የቻይ ውጭ ጉዳይ ሚኒሰትር ዋንግ ይ ታይዋንን ነጻ ሀገር አድርጎ ማሰብ " ቀይ መስመር ማለፍ ነው" ብለዋል።

ሌተናል ጀኔራል ብርሀኑ በቀለ በቀጠናው ፀጥታና ደህንነት ጉዳይ ላይ ለመነጋገር ሶማሊላንድ ገቡ‼️ ጄኔራሉ መኮንኑ በሶማሊላንድ ሃርጌሳ ኢጋል ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ፤ የሶማሊላንድ ጀኔ
ሌተናል ጀኔራል ብርሀኑ በቀለ በቀጠናው ፀጥታና ደህንነት ጉዳይ ላይ ለመነጋገር ሶማሊላንድ ገቡ‼️ ጄኔራሉ መኮንኑ በሶማሊላንድ ሃርጌሳ ኢጋል ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ፤ የሶማሊላንድ ጀኔራል መኮንኖች አቀባባል አድርገውላቸዋል። ጀኔራል መኮንኑ በኢትዮጵያና ሶማሊላንድ መከከል እንዲሁም በቀጠናው ሊኖር ስለሚገባው የጋራ የፀጥታና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ስለሚኖር ትብብር፤ ከሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት፣ ወታደራዊ አመራሮች እና ከብሔራዊ ደህንነት ዳይሬክተሩ ጋር በዝርዝር መወያየታቸውን ከመከላከያ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

ሐምሌ 27 ቀን 2014 ዓ.ም የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የቻይና የመከላከያ ሰራዊት የተመሰረተበትን 95ኛ አመት ክብረ በዓል በማስመልከት የእንኳን
ሐምሌ 27 ቀን 2014 ዓ.ም የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የቻይና የመከላከያ ሰራዊት የተመሰረተበትን 95ኛ አመት ክብረ በዓል በማስመልከት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉ፡፡ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፣ ባስተላለፉት መልዕክት የቻይና የመከላከያ ሰራዊት የሀገሩን ሉአላዊነት፣ ፀጥታና ጥቅም ከማስከበር አልፎ ለአለማችን ሰላምና መረጋጋት እያደረገ ላለው በጎ ሚና ያላቸውን አድናቆት ገልፀዋል፡፡ ቻይናና ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት የዘለቀ ታሪካዊ ወዳጅነት እንዳላቸው ያወሱት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ፤ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ በመመስረት በሀገራቱ መካከል ያለው ግንኙነት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በባህል፣ በትምህርት እና በጤና መስኮች ከፍተኛ ዕድገት እያሳየ መምጣቱን ገልፀዋል፡፡ ሁለቱ ወዳጅ ሀገራት በወታደራዊ ዲፕሎማሲና ትብብር ላይ ከፍተኛ ዕድገት ላይ እንደደረሱ የገለፁት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ያላቸውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እየተሰራም እንደሚገኝ አረጋግጠዋል፡፡

፨ የቻይና ጦር ታይዋንን ከቧል ። የምትራቀቅበት J-20 የጦር ጀቷ የታይዋን ዙሪያ እየቃኘ ነው ። የቻይናው ምስራቅ 21ኛ እዝ ከሰፈሩ ተነስቶ ወደ ታይዋን እየተጓዘ ይገኛል ። ቻይና ጦሯ በተጠንቀቅ
+1
፨ የቻይና ጦር ታይዋንን ከቧል ። የምትራቀቅበት J-20 የጦር ጀቷ የታይዋን ዙሪያ እየቃኘ ነው ። የቻይናው ምስራቅ 21ኛ እዝ ከሰፈሩ ተነስቶ ወደ ታይዋን እየተጓዘ ይገኛል ። ቻይና ጦሯ በተጠንቀቅ ቆሟል ። ፨ ሁለቱ የቻይና ጦርጄት ተሸካሚ መርከቦቿ ቦታቸውን ለቅቀው ወደ ዘመቻ ተሰማርተዋል ። ጥቃት ለመፈፀም የሚጠብቁት ትእዛዝ ብቻ መሆኑን የቻይናው Global times አሳውቋል ። ፨ አሁን 21 የቻይና ጦር ጀቶች ወደ ታይዋን ጥሰው ገብተዋል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል ። እናም ምን አይነት ጥቃት እንደሚፈፅሙ በአጭር ጊዜ ውስጥ ይታወቃል ። ፨ለዚህ ሁሉ መካረር መንስኤ የሆነቺው የአሜሪካዋ አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ አሁን ከታይዋን ካለ ቻይና ፈቃድ መውጣት አትችልም ምክንያቱም የታይዋን አየር ክልል ዙሪያውን በቻይና ተከቧልና ! ፨ አሜሪካ ደቡብ ምስራቅ ፓስፊክ ውቅያኖስ ላይ ያለው ጦሯ እንዲንቀሳቀስ አዛለች ። ይህ ጦር የአሜሪካው የጦርጄት ተሸካሚ መርከብ ሮናል ድሬገንን ያካትታል ። ለታይዋን ብላ አሜሪካ ጦርነቱ ውስጥ ትዘፈቅ ይሆን ? የምናየው ይሆናል ! ፨ ሩሲያ ከቻይና ጎን እንደምትቆም አረጋግጣለች ። ቻይና ማንኛውንም አይነት እርምጃ የመውሰድ መብትና ስልጣን እንዳላት የገለፀቺው ሩሲያ በየትኛውም መልኩ ከቻይና ጎን እሰለፋለሁ ብላለች ። ኢራን በበኩሏ አሜሪካን ያወገዘች ሲሆን ከቻይና ጎን መቆሟንም አሳውቃለች ። ፨ ውጥረቱን ተከትሎ የአሜሪካ የአክሲዮን ገበያ አሽቆልቁሏል ። ኢኮኖሚዋም እንዳይናጋ አስግቷል ። ይህ በእንድህ እንዳለ የሩሲያና የቻይና ጦር መርከቦች በጃፓን አቅራቢያ በጋራ እየቀዘፉ መሆናቸውን ጃፓን አሳውቃለች ። #Seid_Mohammed_Alhabeshiy

ቻይና የፔሎሲን የታይዋን  ጉብኝት ተከትሎ በደሴቷ ላይ ተከታታይና የተመረጡ ወታደራዊ እርምጃዎችን እንደምትወስድ አስታወቀች።   የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ የቻይናን ተደጋጋሚ እና ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ወደጎን በመተው ማምሻውን አወዛጋቢውን የታይዋን ጉብኝታቸውን ጀምረዋል።   የቻይና የመከላከያ ሚኒስቴር ለአፈ ጉባዔ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት በሰጠው ምላሽ፥ በታይዋን አቅራቢያ ተከታታይ ወታደራዊ ዘመቻ ከዛሬ ጀምሮ እንደሚያካሂድ አስታውቋል።   የአገሪቱ የመከላከያ ሚኒስቴር የቻይና ባለስልጣናት “እጅግ የከፋ አደገኛ” ያሉትን የአፈጉባዔ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ተግባራዊ መሆን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ ይፋ እንዳደረገው፥ የቻይና ሕዝብ ነፃነት ሠራዊት በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ ከዛሬ ጀምሮ በታይዋን ሰርጥ ተከታታይ የሆኑና የተመረጡ ወታደራዊ እርምጃዎች ይወሰዳል ብሏል።   የሠራዊቱ ቃል አቀባይ የሆኑት ዉ ኩያን ለቻይና መገናኛ ብዙሃን በሰጡት ማብራሪያ፥ ወታደራዊ እርምጃው የአገሪቱን ብሄራዊ ክብር፣ ሉዓላዊነትና አንድነት ለማስከበር፣ የውጭ ጣልቃገብነትን ለመመከት፥ የታይዋንን ነፃነት ከገንጣዮች ለመከላከል በቆራጥነት የሚወሰድ እርምጃ እንደሆነም ነው ያስታወቁት።   የሠራዊቱ የምሥራቅ ዕዝ የምድር፣ የባህር ሃይልና የአየር ምድቦች በወደቧ ሰሜናዊ፣ ደቡብ ምዕራብና ደቡብ ምሥራቅ አካባቢዎች የተቀናጀ ወታደራዊ ዘመቻ እንደሚያካሂዱም ነው ቃል አቀባዩ ያብራሩት።   የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በአፈጉባኤዋ ጉብኝት ላይ በሰጡት አስተያየት፥ የያዝነውን ዓመት ጨምሮ ከዚህ ቀደም ባሉት ጊዜያት ሁሉ በርካታ የአሜሪካ ባለሥልጣናት እና የምክር ቤት አባላት ታይዋንን ሲጎበኙ ቆይተዋል ብለዋል፡፡   በመሆኑም አፈጉባዔዋ ታይዋንን ለመጎብኘት ከወሰኑ ቻይና በተለየ መልኩ ጉዳዩን ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ የምትመራበት ምክንያት የለም ብለዋል፤ ለሚከተለው ቀውስ እራሷ ቻይና ተጠያቂ እንደምትሆንም ነው ያስጠነቀቁት።   የአሜሪካ ብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት ቃል አቀባይ ጆን ከርቢ በበኩላቸው ÷ ቻይና የአፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲን ጉብኝት ሰበብ አድርጋ በታይዋንና አካባቢው ፀብ-ጫሪ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ለማጠናከር መሞከሯ ተቀባይነት የሌለው ነው ብለዋል።   የአሜሪካው ዘ ኒውዮርክ ታይምስ ናንሲ ፔሎሲ ትናንት ሲንጋፖር መግባታቸውን ዘግቦ በመርሐ ግብራቸው መሠረትም ታይዋንን ይጎበኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክቷል፡፡

የአሜሪካ ኮንግረስ አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ወደ ታይዋን ለማረፍ መቃረባቸውን ተከትሎ ቻይና አካባቢውን ለሲቪል በረራዎች ዝግ አድርጋለች፡፡ የናንሲ ወደ ታይዋን ማምራት በአካባቢው ከፍተኛ ውጥረት ያነገሰ
የአሜሪካ ኮንግረስ አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ወደ ታይዋን ለማረፍ መቃረባቸውን ተከትሎ ቻይና አካባቢውን ለሲቪል በረራዎች ዝግ አድርጋለች፡፡ የናንሲ ወደ ታይዋን ማምራት በአካባቢው ከፍተኛ ውጥረት ያነገሰ ሲሆን ታይዋንም የህግ ስርአቷን ጠበቅ ማድረጓን አስታውቃለች፡፡ ናንሲ ፔሎሲ የሚገኙበት አውሮፕላን በታይዋን የጦር ጀቶች ከመታጀባቸው ባሻገር፣ የአሜሪካ 4 የባህር ሃይል መርከቦች ማምራታቸውን የአሜሪካው መከላከያ መስሪያ ቤት ፔንታጎን አስታውቋል፡፡ የቻይና የጦር ጀቶች በተደጋጋሚ የታይዋንን የአየር ክልል ሲጥሱ መዋላቸውን ሪፖርቶች አመላክተዋል፡፡

የታይዋን መንግሰት ድረ ገጽ ተጠለፈ ቻይና ወታደራዊ እርምጃ እወስዳለሁ ማለቷን ተከትሎ የአሜሪካ ጦር ወደ ታይዋን ቀርቧል የታይዋን መንግሰት ድረ ገጽ በመጠለፉ ምክንያት ስራ ማቆሙ ተስመቷል። አፈ ጉ
የታይዋን መንግሰት ድረ ገጽ ተጠለፈ ቻይና ወታደራዊ እርምጃ እወስዳለሁ ማለቷን ተከትሎ የአሜሪካ ጦር ወደ ታይዋን ቀርቧል የታይዋን መንግሰት ድረ ገጽ በመጠለፉ ምክንያት ስራ ማቆሙ ተስመቷል። አፈ ጉባኤ ናንሲ የሲንጋፖር ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ታይዋን እንደሚገቡ የታይዋን መንግስታዊ እና የግል ብዙሀን መገናኛዎች በመዘገብ ላይ ናቸው።   ፔሎሲ ታይዋንን ከጎበኙ ጦሯ “ዝም ብሎ እንደማይቀመጥ” ቻይና አስጠንቅቃለች ታይዋን ለሶስት ቀናት ከፍተኛ የውጊያ ጥንቃቄ አወጀች የአውሮፕላን በረራውችን መረጃ በመስጠት የሚታወቀው ፍላይት ራዳር 24 የተሰኘው ተቋም ናንሲ ፔሎሲን የሚያጓጉዘው አውሮፕላን የበረራ አቅጣጫው ወደ ታይዋን እንደሆነ ጽፏል። አስቀድማ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን ከጎበኙ እርምጃ እወስዳለሁ ያለችው ቻይና የአየር እና የባህር ሀይል ጦሯን ወደ ታይዋን አቅርባለች። በቻይናው ግሎባል ታይምስ ላይ ትንታኔዎችን በመጻፍ የሚታወቀው ሁ ጂያን የአሜሪካ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ናንሲ ፔሎሲን አጅበው ወደ ታይዋን ለማስገባት ካሰቡ ይህ አሜሪካ በግልጽ በቻይና ላይ ወረራ እንደፈጸመች ይቆጠራል። የቻይና ጦርም አውሮፕላኑን መምታት እንዳለበት በትዊተር ገጹ አስፍሯል። የአሜሪካ እና ቻይና የጦር አውሮፕላኖች እና የባህር ላይ ወታደሮቻቸውን ወደ ታይዋን አቅርበዋል።

አሜሪካ የአልቃኢዳውን መሪ ዶክተር አይመን አልዘዋሂሪን መግደሏን ገለፀች ። ግብፃዊው የአልቃኢዳ መሪና የበርካታ ኦፕሬሽኖችና ዘመቻዎች አቀናባሪ ዶክተር አይመን አልዘዋሂሪ የተገደለው በአፍጋሃኒስታኗ
+1
አሜሪካ የአልቃኢዳውን መሪ ዶክተር አይመን አልዘዋሂሪን መግደሏን ገለፀች ። ግብፃዊው የአልቃኢዳ መሪና የበርካታ ኦፕሬሽኖችና ዘመቻዎች አቀናባሪ ዶክተር አይመን አልዘዋሂሪ የተገደለው በአፍጋሃኒስታኗ ዋና ከተማ ካቡል መሆኑ ዛሬ ሌሊት ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በታላቅ ደስታ ተሞልቶ ተናግሯል ።ፕሬዚዳንቱ " ዛሬ ፍትህ ሰፈነ ! ከዚህ በሗላ ይህ ሽብርተኛ አይኖርም " ሲል NO MORE በማለት ይህ ለአሜሪካ ታላቅ ድል መሆኑን አብስሯል ። ታሊባን የአፍጋኒስታን መንግስትነትን ከተቆጣጠረ በሗላ ሸህ አይመን አልዘዋሂሪ እንደተዘናጋ በአፍጋኒስታን ምቾት እንደተሰማው የሚገልፀው ተመራማሪው ኮሊን ክላርክ ይህም ለአሜሪካ ጥቃት አጋልጦታል ብሏል ። አሜሪካ ጥቃቱን የፈፀመቻው በድሮን መሆኑንም አሳውቃለች ። አፍጋሃኒስታንን የሚመራው ታሊባን በበኩሉ ጥቃቱን " የሉአላዊነት ጥሰት " በማለት የአሜሪካን ድርጊት ያወገዘ ሲሆን አሜሪካ በበኩሏ ታሊባንን " ስምምነታችንን በመጣስ አሸባሪወችን ያስጠለለ " በማለት አውግዛለች ። አሜሪካ አይመን አልዘዋሂሪን ለጠቆማት 25 ሚሊዮን ዶላር መድባ የነበረ መሆኑ ይታወቃል ሲል የዘገበው አልጀዚራ ነው ።

#አመለካከትህን_በመቀየር_ህይወትህን_ቀይር ✅ በቻይና ውስጥ እጅግ ባለጸጋ የሆነው “ጃክ ማ” ሲሆን 39 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሀብት አለው ። ጃክ ማ እንዲህ ይላል፡- ‘’ገንዘብና ሙዝን ከዝንጀሮዎ
#አመለካከትህን_በመቀየር_ህይወትህን_ቀይር ✅ በቻይና ውስጥ እጅግ ባለጸጋ የሆነው “ጃክ ማ” ሲሆን 39 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሀብት አለው ። ጃክ ማ እንዲህ ይላል፡- ‘’ገንዘብና ሙዝን ከዝንጀሮዎች ፊት ብታስቀምጥ ዝንጀሮዎች ሙዙን ይመርጣሉ ። ምክንያቱም ገንዘብ ብዙ ሙዝ እንደሚገዛ አያውቁም! ✅ አብዛኛው ሰው ላይ ተመሳሳይ ሙከራ ብታደርጉና በአንድ የተወሰነ የግል ስራ (ቢዝነስ) እና በወር ደመወዝ መካከል ምርጫቸው ምን እንደሆነ ብትጠይቁ አብዛኛው ሰው ወርሃዊ ደመወዝ ያለው ስራን ይመርጣል ። ምክንያቱም ትንሽም ቢሆን የግል ስራ (ቢዝነስ) ከወርሃዊ ደሞዝ የበለጠ ገቢ እንደሚያመጣና ህይወት የሚቀይረው ይህ እንደሆነ ስለማያውቁ ነው ። ✅ ሰዎችን ለድህነት ከሚዳርጉት ነገሮች አንዱ ከግል ስራ (ቢዝነስ) የሚመጡትን እድሎች ማየት አለመቻላቸው ነው ። ምክንያቱም በህይወት ዘመናቸው ሁሉ በትምህርት ቤቶች የሚማሩት ስራ ማለት ሁልጊዜ ለወርሃዊ ደመወዝ መስራት መሆኑን ነው ። ለራሳቸው ከመስራት ይልቅ ለሌሎች መስራትን ብቸኛ አማራጭ እንደሆነ ተምረዋል! እውነት ነው የወር ደሞዝ ከድህነት ይጠብቅሃል ። ነገር ግን ሀብትን እንዳታገኝ ያደርግሃል ። ✅ በህይወቴ ከጠዋቱ 2 ሰዓት እስከ 12 ሰዓት የሚሰራ ተቀጣሪ ሰው ሀብታም ሆኖ አይቼ አላውቅም ።’’ ይላል ጃክ ማ ። እውነት ነው እኛም አገር ያለው ነባራዊ እውነታ ይሕ ነው ። ምክንያቱም ተቀጥረህ በምታገኘው የወር ደመወዝ ሀብት ፣ ጥሪት ፣ ቤትና ራስህን ለውጠህ ሌላ ሰው መርዳት አትችልም ። እርግጥ ነው የወር ደመወዝ ሲኖርህ የምትፈልገውን ማድረግ ባትችልም በገቢህ ልክ መኖርን ትለምደዋለህ ። ለማንኛውም በሥራ ፍለጋ ጊዜ ከማባከን በትንሹም ቢሆን የግል ስራ የምትጀምሩበትን የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል።