የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
前往频道在 Telegram
5 461
订阅者
-40724 小时
-2 4147 天
-2 42630 天
帖子存档
+3
የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ለ9 ዘርፎች የምልመላ ማስታወቂያ አውጥቶ ተመልክተናል።
1.ለመደበኛ ሰራዊት
2.ለልዩ ወ/ዊ ሙያ
3.ለሳይበር ሙያተኞች
4.ለህግ ሙያተኞች
5.ለመሃንድስ ሙያተኞች
6.ለጤና ሙያተኞች
7.ለተለያዩ የሎጀስቲክስ ሙያተኞች
8.ለፋይናንስና ግዥ ሙያተኞች
9.ለኢንጂነሪንግ፣ለጤና ሳይንስ እና ለሪሶርስ ማናጅመንት ትምህርት የሚገቡ ተማሪዎች እና ሌሎች በፍላጎት የሚመዘገቡ ሙያተኞች የሚመለመሉ ይሆናል።
📌አጠቃላይ የምልመላ መስፈርቶች
1.የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስትን የተቀበሉ፣ በህዝቦች ሉአላዊነትና አንድነት የሚያምኑና አገራቸዉን ለማገልገል ሙሉ ፍቃደኛ የሆኑ።
2.ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅቶች ወገንተኝነት ነፃ የሆኑ።
3.ከአሁን በፊት የመከላከያ፣ የፖሊስ እና የክልል ልዩ ሃይል አባል ያልነበሩ።
4.አሁን ካለው ወቅታዊ የአገራችን ሁኔታ በመነሳት የፅንፈኞቹ ፋኖና ሸኔ አባልና ደጋፊ ያልሆኑ
5.በወንጀል ይሁን በፍታብሔር ተከሶ የፍርድ ቤት ክርክር የሌለባቸው፣
6.ዜግነት ኢትዮጵያዊ የሆኑ።
7.መሰረታዊ የዉትድርና ስልጠና ወስዶ ከተመረቁ በኋላ ለ7 አመት ለማገልገል ውል ለመፈፀም ፍቃደኛ የሆኑ።
8.የተስተካከለ ቁመና የእግር፣ የእጅ፣ የአንገት፣ የወገብ መሰበር እና ሌሎች ችግሮች የሌለባቸው።
9.የአይን፣ የአፍንጫ፣ የጆሮ፣ የጥርስ እና የከንፈር መሰንጠቅ ችግር የሌለባቸው።
10.ከቲቪ፣ ከሚጥል በሽታ፣ ከስኳር፣ ከደም ግፊት፣ ከኪንታሮት እና ከእንቅርት በሽታዎች ነፃ የሆኑና ሌሎች በተቋሙ የሚሰጡ የጤና ምርመራዎችን ማለፍ የሚችሉ
11.ቁመት ለወንድ 1.60 ለሴት 1.55 ሜትር እና ከዚያ በላይ የሆኑ።
12.ክብደት ለወንድ ከ45-70 ለሴት ከ 40-60 ኪ/ግራም የሆኑ።
📌 ሙያተኛን በተመለከተ፡-
1.ለሙያተኞች ለያንዳንዱ ሙያ በተቀመጠዉ የመመልመያ መስፈርት መሠረት ይሆናል
2.ዕድሜ ለመደበኛ ከ18 እስከ 24 ሲሆን ለሙያተኞች በትምህርት ያሳለፉት ጊዜ ግምት በማስገባት እስከ 26/27 ሊሄድይችላል
3.ለሙያተኞች ለያንዳንዱ ሙያ በተቀመጠዉ የመመልመያ መስፈርት መሠረት ይሆናል
4.ዕድሜ ለመደበኛ ከ18 እስከ 24 ሲሆን ለሙያተኞች በትምህርት ያሳለፉት ጊዜ ግምት በማስገባት እስከ 26/27 ሊሄድይችላል፡፡
📌 ለልዩ ወታደራዊ ሙያ (ለኮማንዶ) ለሚመለመሉ
➣የትምህርት መስፈርት በተመለከተ፡-
ለሁለቱም ፆታ ተመልማዮች 10ኛ ክፍል ያጠናቀቁና ከዚያ በላይ የሆኑ በተጨማሪም የ8ኛ ክፍል የሚኒስትር ካርድ ማቅረብ የሚችሉ
➣አካላዊ መስፈርት፡-ቁመት ለወንድ 1.67 ለሴት 1.62 ሜትር እና ከዚያ በላይ የሆኑ
➣ክብደት ለወንድ ከ45-70 ለሴት ከ 40-60 ኪ/ግራም የሆኑ
📌በመከላከያ ዩኒቨርስቲ ለሪሶርስ ማኔጅመንት ትምህርት የሚገቡ ተመልማዮች የትምህርት መመልመያ መስፈርት
➤በማህበራዊ ወይም በተፈጥሮ ሳይንስ በ2014፣ 2015 እና 2016 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ማለትም 300 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ
➤በማህበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት የ2014 እና የ2015 ሪሜዲያል ተምረው ያለፉ፣
➤በማንኛውም የትምህርት መስክ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በመደበኛ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም በመማር ላይ የሚገኙና የየሴሚስተሩን የትምህርት ውጤት ሪፖርት ማቅረብ የሚችሉ፣
📌በመከላከያ ዩኒቨርስቲ ለኢንጂነሪንግና ለጤና ሳይንስ ትምህርት የሚገቡ ተመልማዮች የትምህርት መመልመያ መስፈርት
➤በተፈጥሮ ሳይንስ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ወስዶ/ወስዳ በ2014፣በ2015 እና በ2016 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ያስመዘገቡ ማለትም 350 እና ከዚያ በላይ ዉጤትያለው/ያላት
➤በተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት የ2014 እና የ2015 ሪሜዲያል ተምረው ያለፉ
➤በተፈጥሮሳይንስየትምህርት መስክ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በመደበኛ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም በመማር ላይ የሚገኙና የየሴሚስተሩን የትምህርት ውጤት ሪፖርት ማቅረብ የሚችሉ
📌ለሳይበር ሙያተኞች የትምህርት መመልመያ መስፈርት
➤በኮምፒውተር ሳይንስ፣በኮምፒውተርኢንጂነሪንግ፣በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣በኮምፒተር ኔትወርክ ና ሃርድዌር፣በኢንፎርሜሽን ሲስተም፣በሳይበር ደህንነት፣በኮምፒውተር ኔትወርክ ና ኢንፎርሜሽን ሴኩሪቲ፣ከታወቀ የትምህርት ተቋም የተመረቁ የመጀመሪያ ዲግሪ ና ከዚያ በላይ ያላቸው፣
➤የጤንነት ሁኔታ፡- ሙሉ ጤንነቱ በሃኪም የተረጋገጠ
ወደ መከላከያ ሳይበር ገብቶ/ገብታለመስራት ፍላጎት ያለው/ያላት
➤የሳይበር ሙያ የሚጠይቀውን ሙያዊ ዲስፕሊን የሚያሟላ/የምታሟላ
➤ሌሎች ሙያዎች ለህግ ሙያተኛ ተመልማዮች የትምህርት መመልመያ መስፈርት ለጤና ሙያተኞች የትምህርት መመልመያ መስፈርት፤
📌ለምህንድስና ሙያተኞች የትምህርት መመልመያ መስፈርት
➝ለተለያዩ የሎጀስቲክስ ሙያዎች የትምህርት መመልመያ መስፈርት
➩ ለአውቶመካኒክ
➩ለጀነራልመካኒክ
➩ለአውቶሞቲቭኢንጂነር
➩ለዳቦ ማሽን ና ጀኔሬተር ጥገና
➩ለመለዋወጫ መስሪያ ዕቃግ/ ቤት ባለሙያ (ሳፕላይሙያተኛ)
➩ለማሽኒስት ባለሙያ
➩ለታፕሴሪ
➩ለቀለም ቀቢ
➩ለጎሚስታ
➩ለእጥበት ና ግሪስ
➩ለምግብ ጥናት ባለሙያ (Food nutrition)
➩ለሳፕላይ ሙያተኛ
➩ለትራንስፖርት ማናጅመንት
➩ለቴክስ ታይል (ኢንዱስትሪ) ኢንጅነሪንግ ሙያተኛ
➩ለጋርመንት ኢንጅነሪንግ ሙያተኛ
📌➝ለፋይናንስ፣ ለበጀት፣ ለግዥና ንብረት አስተዳደር ሙያተኞች የትምህርት መመልመያ መስፈርት
➥ለፋይናንስ ሙያተኞች
➥ለግዥ ሙያተኞች
➥ለበጀት ሙያተኞች
➥ለንብረት አስተዳደር ሙያተኞች
📌➝ለኪነ-ጥበብ እና ስፖርት ዘርፍ የትምህርት መመልመያ መስፈርት
ለኪነ-ጥበብ ዘርፍ
➦ለስፖርት ዘርፍ
➦በተጨማሪም የግብርና ሙያተኞች (እርሻ)
➦አጠቃላይ የምልመላ መስፈርቶችን ማሟላት እንዳለ ሆኖ በምዝገባ ወቅት ኦሪጅናልና ኮፒ የትምህርት ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
📌የምዝገባ ቦታና ጊዜ
1.የወረዳ ተመዝጋቢዎች በየአከባቢያቸዉ ባሉ የቀበሌ፣ የወረዳ አስተዳደርና የፀጥታ ወይም የሚሊሻ ፅ/ቤት ፖሊስ ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ የሚመዘገቡ ይሆናል
2.የምዝገባ ጊዜዉ ከሚያዚያ 01 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይሆናል
3.ሚያዚያ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ዞን የማጓጓዥያ ቀን ይሆናል
4.በሁሉም የምዝገባ ጣቢያዎች ዝርዝር የመመልመያ መስፈርቶች ተለጥፎ ይገኛል።
ሚያዚያ 2017 ዓ.ም
🔽 📹
ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ
+5
ሰበር ዜናው ቀጥሏል
የጎጃሙ ጽንፈኛ ቡድን እያለቀ ነው። ከውስጥ ለፀጥታ ኃይል እየተሰጡ ያሉ መረጃዎች ኦፕሬሽኑን እያሳኩት ይገኛሉ።
ትናት በገደብ ስልጠና እና ስብሰባ ላይ የነበሩት 126 ታጣቂዎች የተደመሰሱ ሲሆን ዛሬም በአደባባይ ስብሰባ ላይ የነበሩት 135 ስብሰባ ላይ እያሉ አንድም ሳይቀር ተደምስሰዋል። ከተደመሰሱት ውስጥ የትኞቹ አመራሮች እንዳሉ እየጣራ ነው::
የመከላከያ ሰራዊት በጽንፈኛው ቡድን የስልጠና ማዕከል ላይ በወሰደው እርምጃ አንድ የሻለቃ አመራርን ጨምሮ በርካታ ታጣቂዎች ተደምስሰዋል!
ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ለሰላም ጀርባውን በመስጠት ህዝብን እያሰቃየ በሚገኘው ጥገኛ እና ጽንፈኛ ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል። በዚህም መሰረት ሰራዊቱ ዛሬ ሚያዚያ 09/2017 ዓ.ም በምስራቅ ጎጃም ዞን እናርጅና እናውጋ ወረዳ ገደብ አካባቢ በስልጠና ላይ በነበሩ የፀረ-ሰላም ቡድኑ አባላት ላይ በወሰደው እርምጃ አንድ የሻለቃ አመራርን ጨምሮ ከአርባ በላይ የቡድኑ አባላት የተደመሰሱ መሆናቸው ታውቋል። በተጨማሪም በእርምጃው አሁንም ብዛት ያለው ታጣቂ የቆሰለ መሆኑና የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል ተገልጿል። የጽንፈኛው ቡድን አመራሮች የጓደኞቻቸውን አስ*ከሬን ለማንሳት እንኳን በማይችሉበት ደረጃ እርምጃው ጠንካራ እንደሆነ እየገለጹ ይገኛሉ። ለሰላም አሻፈረኝ ያለውን ይህንን ከሃዲ እና ጸረ ህዝብ የሆነ ቡድን ጀግናው ሰራዊት በሚገባው ቋንቋ እያናገረው ይገኛል። የጽንፈኛው አባላት አሁንም ያላቸው ምርጫ ሁለት ነው እጅ ሰጥቶ ወደ ሰላማዊ ህይወት መመለስ አሊያም የማይቀረውን የሞት ጽዋ መጎንጨት! ይኸው ነው!
+4
ከአገልግሎት ውጪ የነበረውን የፕሬዝዳንት መንግሥቱ ሃይለ ማርያም አውሮፕላን ጠግኖ ጥቅም ላይ ማዋል መቻሉ ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 08 ቀን 2017 ዓ.ም
የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ሃይለ ማርያም አውሮፕላን ከተጣለበት ጥሻ በማንሳት አፕግሬድና ኦቨር ሆል በማድረግ ከ37 ዓመት በኋላ የበረራ አገልግሎት እንዲሠጥ ማድረጋችን በተቋሙ በሁሉም መስክ ውጤታማ ሥራ እየተሠራ ሥለመሆኑ ማሳያ ነው ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገልፀዋል።
አውሮፕላኑ አሥፈላጊውን ጥገና አግኝቶ መብረር እና ወደ ኃይል መመለስ እንዲችል በሰጠነው መመሪያ መሠረት ለተሳተፋችሁ የአየር ሃይል አመራሮች ቴክኒሺያኖች የመከላከያ ድጋፍ ሰጪ ሁሉ አመሠግናለሁ ሲሉ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ምስጋና አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ አየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው አየር ሃይል በሰው ሃይል ግንባታ ፣ትጥቆችን ማሣደግና ከዘመኑ አቅም ላይ ማድረስ፣ መሠረተ ልማቶችን ተቋሙን በሚመጥን ልክ ማሥፋፋት ትኩረት የተሠጠባቸው መሠረታዊ ነጥቦች መሆናቸውን ገልፀው አውሮፕላኑን ጠግኖ ወደ ኃይል መመለስ የዚሁ አንድ አካል ነው ብለዋል።
ዳሽ ፋይፍ ወይም ቡፋሎ በሚል መጠሪያ የሚታወቀውና ለቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም አገልግሎት ይሠጥ የነበረውን አውሮፕላን ከአንድ ዓመት ጊዜ በላይ አሥፈላጊውን ጥገና በአየር ሃይል ቴክኒሺያኖች በመሥጠት ከሰላሣ ሰባት ዓመት በኋላ ለበረራ ማብቃት እንደተቻለ ተናግረዋል።
ለትራንስፖርት ፣ለፓራሹት ዝላይ፣ የካርጎ አገልግሎት መሥጠት የሚችለው አውሮፕላን ተጠግኖ ወደ ኃይል እንዲመለስ የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ለሠጡት ድጋፍ ሙያተኞች ላደረጉት ሙያዊ አበርክቶ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ምስጋና አቅርበዋል።
በውብሸት ቸኮል
+3
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሊጠናቀቅ 1.34% ብቻ ነው የቀረው‼️
ግንባታው የተጀመረው መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም ነበር።
የኢትዮጵያዊያን አንድነትና የይቻላል መንፈስ የታየበት ሀገራዊ ፕሮጀክት ነው። ለመጪው #ትውልድም የይቻላል መንፈስን ሲያንጸባርቅ የሚኖር ፕሮጀክት ነው።
👉 የዓባይ ግድብ በአሁን ላይ ኃይል በማመንጨት ላይ ነው፣
👉 74 ቢሊዮን ኪዮቢክ ሜትር ውሃ በመያዝ ትልቁ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ይሆናል፣
👉 ግድቡ ሲጠናቀቅ 78 ደሴቶች ይፈጠራሉ፤
👉 ግድቡ በዓመት ከ10 እሰከ 15 ሺህ ቶን አሳ ማምረት የሚያስችል ነው፣
👉 የዓባይ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይልን በማመንጨት ከአፍሪካ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፣
👉 ለቀጠናው ህዝቦች ትስስር፣ ለአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ ቁልፍ ሚና አለው፣
👉 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሽፋንን 75 በመቶ ያሳድጋል፣
👉 ለአፍሪካ ሀገራት በራስ አቅም ልማት መነቃቃት ተምሳሌት የሆነ ፕሮጀክት ነው፣
#Ethiopia
+1
ጄኔራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንትነትን ሲረከቡ የፈረሙት " የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር የተልዕኮ አፈጻጸም የቃል ኪዳን ሰነድ " ምን ይላል ?
1. የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው የመመለስ ሂደት፣ በጅምር ያለው እንዲጠናቀቅ እና በቀሪ አካባቢዎችም #በፍጥነት እንዲተገበር ማድረግ፤
2. በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት ትጥቅ የመፍታት እና የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋም ተግባር በአፋጣኝ እንዲጠናቀቅ ማድረግ፤
3. በክልሉ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን ማድረግ፤ ለሕዝብ ደኅንነት፣ ለሰላም እና ለጸጥታ ጠንቅ የሆኑ ጉልህ ሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ማድረግ፤ ለዚህም ተገቢውን የቁጥጥር እና የሕግ ማስከበር ሥራ መሥራት፤
4. መደበኛ የልማት ሥራዎች፣ መንግሥታዊ እና ማኅበራዊ አገልግሎቶች፣ እንዲሁም የመልሶ ግንባታ ሥራዎች እንዲሣለጡ ማድረግ፤
5. ከሕገ መንግሥታዊ እና ከሕጋዊ ሥርዓት፣ #ከሀገር_ሉዓላዊነት እና ከፕሪቶርያ ስምምነት ያፈነገጡ ግንኙነቶች እና እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ማድረግ፤
6. ክልሉ ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ዝግጁ እንዲሆን ማድረግ፤ በክልሉ የሲቪክ እና የፖለቲካ መብቶች ተግባራዊ የሆኑበት፣ የፖለቲካ ብዝኃነትን የሚያስተናግድ ደሞክራሲያዊ ዐውድ እንዲፈጠር መሥራት፤
7. የክልሉ ሕዝብ፣ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች እና የፖለቲካ ተዋንያን #በሀገራዊ_የምክክር_ሂደት እንዲሳተፉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት፤
8. የክልሉ መንግሥታዊ የሚዲያ እና የኮሙኒኬሽን እንቅስቃሴዎች የሀገሪቱን ሕዝቦች ትሥሥር እና መልካም ግንኙነት የሚያጠናከሩ፣ ሕግ እና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን የሚያስከብሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ፤
ጄነራል ታደሰ ወረደ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝደንት በመሆን ሥራቸውን ሲጀምሩ ከላይ የተዘረዘሩትን ኃላፊነቶችን በትጋት እና በታማኝነት ለመወጣት ቃል ገብተው #ፈርመዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
ሞባይል ስልክ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ አገልግሎቱን ለማግኘት ያስፈልጉ የነበሩት አስገራሚ መስፈርቶች
(ከWasihune Tesfaye የFacebook ገፅ የተወሰደ)
ግንቦት 9, 1991 ዓ.ም ቴሌ ለወራት ሲያስተዋውቅ የከረመውን የሞባይል ስልክ አገልግሎት መስጠት የሚጀምርበት ቀን ነበር።
እና በዚያን እለት ግንዛቤው የነበራቸው ባለሃብቶች ለኢትዮጵያ አዲስ የሆነውን ሞባይል ስልክ አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን ወደ ቴሌ ቢሮዎች በጠዋት መምጣት ጀምረዋል።
በቢሮው መግቢያ ላይ አንድ ማስታወቂያ ተለጥፏል። ሲም ካርድ ለመውሰድ ሲመጡ ኦሪጅናል እና ኮፒ የመኖሪያ ቤት ካርታ ይዘው መምጣት እንዳለባቸውና የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን የቤት ካርታቸውን ማስያዝ እንዳለባቸው የሚገልጽ ማስታወቂያ ።
በነገሩ የተስማሙና ቀድመው መረጃውን ያገኙ ሰዎች የቤት ካርታቸውን እያስያዙ ለሲም ካርዱና ቴሌ በብቸኝነት ያስመጣው የነበረውን ይህን በፎቶው የሚታየውን ትልቅ የኢሪክሰን ቀፎ 5ሺ ብር አካባቢ እየከፈሉ መውሰድ ጀመሩ። የዚያኑ እለትም የመጀመሪያዎቹ ባለሞባይሎች በአዲስ አበባ ከተማ ይታዩ ጀመር።
እነዚህ ጥቂት የከተማችን ባለሞባይሎች በሱሪያቸው ቀበቶ ላይ በታሰረ የቆዳ ቦርሳ ያንጠለጠሉትን ትልቅ ሞባይል እያየ ማን ያልተገረመ ነበር። በነገራችን ላይ ከነዚህ ቴሌ ከሚያስመጣቸው ስልኮች ውጭ በሌላ ቀፎ መጠቀም ፈፅሞ የተከለከለ ሲሆን በኢትዮጵያ ብቸኛው የሞባይል ቀፎ ሻጭ ቴሌ ብቻ ነበር ።
ቆየት ብሎ ታድያ የሞባይል ስልክ መጠቀም ፈልገው ነገር ግን የቤት ካርታ የሌላቸው ባለሃብቶች ቅር መሰኘታቸውን የተረዳው ቴሌ የቤት ካርታ ላላቸው የተመዘገቡ ባለሃብቶች ስልክ ሰጥቶ እንደጨረሰ ካርታ ለሌላቸው መስመር ፈላጊዎች 50 ሺህ ብር በማስያዝ ሲም ካርድ መውሰድ እንደሚችሉ አስታወቀ።
በጥቂት ወራት እድሚው የሞባይል ስልክን አስፈላጊነቱን የተረዱ ሰዎች በርከት በማለታቸው 50 ሺ ብር አስይዞ ሞባይል የሚወስደው የ አዲስ አበባ ባለሃብት ተበራከተ።
በዚያን ጊዜ የሞባይል አገልግሎት የሚሰራው በ 100KM ራዲየስ ብቻ ነበረና የሞባይል ስልክ ብቸኛ መናሃሪያ አዲስ አበባ ከተማ ብቻ ነበረች። ( ከአዲስ አበባ ከመቶ ኪሎ ሜትር በላይ ከራቀ ሞባይሉ አይሰራም።) 🤔
ከዚህ በሁዋላ ቴሌ ለብዙ ወራት ሲም ካርድ መሸጥ አቁሞ ላሉት ጥቂት ባለሞባይሎች አገልገሎቱን ለማዳረስ ኔት ወርክ በማስፋፋት ስራ ላይ ተጠምዶ ከቆየ በሁዋላ ከአዲስ ማስታወቂያ ጋር ብቅ አለ።
ቴሌ በአዲሱ ማስታወቂያው ብዛት ያላቸውን ሲም ካርዶች ያለምንም ማስያዣ በቀበሌ መታወቂያ ብቻ መስጠት ሊጀምር እንደሆነና በተጨማሪም የሞባይል ተጠቃሚው ቴሌ በብቸኝነት ከሚሸጠው ኤሪክሰን ስልክ ውጭ በፈለገው ስልክ መጠቀም እንደሚችል ገልጾ ምዝገባ ጀመረ። በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች አገልግሎቱን ለማገኘት በመመዝገባቸውም ሲም ካርድ ለማገኘት ከ6 ወር እስከ አንድ አመት መጠበቅ ግድ ነበር ።
በዚህ ወቅት የሲምካርድ ዋጋ ከአምስት ሺህ ብር ወርዶ 550 ብር ከዚያም 440 ብር፣ 365 ብር፣ 169 ብር ይሸጥ ነበር። ይህን ተከትሎም የሞባይል ቀፎዎች በግለሰብ ሱቆች ውስጥ መሸጥ ጀመሩ ።
ዛሬ ላይ ሁሉ ነገር ቀላል ሆኖ ከየትኛውም ሱቅ ልንገዛው የምንችል እቃ ከመሆኑ በፊት ሲም ካርድ ተመዝገበው ደርሷቸው የቀፎ መግዣ ካጡ ሰዎች ሲሙን በወር ከ70 እስከ 100 ብር መከራየት ይቻልም ነበር ።
እናንተስ መጀመሪያ የያዛችሁት ስልክ ምን አይነት ነበር? ለመጀመሪያ ቀን ስልክ ስታወጡ የነበራችሁ ስሜት?
በመጀመሪያ ቀን የት ደወላችሁ? ከሞባይል ጋር በተያያዘ ያጋጠማችሁ?
Source link
#BREAKING
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
ጠቅላይ ሚኒስተሩ ተመልሰዋል❗️
"ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ህዝቦች ያላትን ድጋፍ አጠናክራ ትቀጥላለች" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ህዝቦች ያላትን የድጋፍ ቁርጠኝነት አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፣ ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዚዳንት ቤንጃሚን ቦል ሜል ከወንድሜ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ይዘውት የመጡትን መልእክት ተቀብያለሁ ብለዋል።
ከምክትል ፕሬዚዳንቱ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በደቡብ ሱዳን ወቅታዊውን የጸጥታና የፖለቲካ ችግሮች ለመፍታት፣ ሁሉን አቀፍ ቀጣናዊ አካሄድ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ህዝቦች ያላትን የድጋፍ ቁርጠኝነት አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉም ገልጸዋል።
#BREAKING
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
እስራኤል አንድ የሃማስ የጦር አዛዥን ሊባኖስ ውስጥ መግደሏን አስታወቀች
የእስራኤል ጦር ዛሬ እንዳስታወቀው በደቡባዊ ሊባኖስ ሲዶን ግዛት ውስጥ ሃሳን ፋርሃት የተባለ የሃማስ ታጣቂ ቡድን አዛዥ መግደሉን ገልጹዋል፡፡
የሊባኖስ የጤና ሚኒስቴር እንደገለጸው እስራኤል በሲዶን ግዛት በሚገኝ ህንጻ ላይ በፈጸመችው ጥቃት የሶስት ሰዎች ሂወት ማለፉን አስታውቁዋል፡፡
የሊባኖሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናዋፍ ሳላም ቢሮ እንደገለጸው የእስራኤል ጥቃት ባለፈው አመት በአሜሪካ አደራዳሪነት በእስራኤልና ሄዝቦላህ መሃል የተፈጸመውን የተኩስ አቁም ስምምነት ህግ የጣሰ ነው ብሉዋል፡፡
ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ የተኩስ አቁም ስምምነቱ በእስራኤል እየተጣሰ እንደሆና በሄዝቦላህ ይዞታ ስር በሚገኙት የቤሩት ደቡባዊ ክፍሎች ላይ በእስራኤል
የሚፈጸሙት የሮኬት ጥቃቶች እየጨመሩ እደሚገኝ የሊባኖስ የጠቅላይ ሚንስተሩ ጽፈት ቤት ስለመግለጹ የዘገበው ዘ ስትሬት ታይምስ ነው፡፡
#BREAKING
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
የነጭ ሽንኩርት የጤና ጥቅሞች
====================
✔ በነጭ ሽንኩርት ውስጥ የሚገኝ ንጥረ ነገር በፈንገስ ምክንያት ለሚከሰቱ የቆዳ ሕመሞች መድኃኒትነት አለው፡፡
✔ በከፍተኛን ደረጃ ባክቴሪያንና ቫይረሶችን የማጥፋት ብቃት ያለው የምግብ ዓይነት ነው፡፡
✔ ነጭ ሽንኩርት በውስጡ የደም መርጋትን የሚከላከል ንጥረ ነገርን ይይዛል፡፡
✔ የደም ግፊት መጨመርን ይከላከላል፡፡
✔ ከዕድሜ መጨመር የተነሳ የሚከሰት የደም ቧንቧ ጥበትን የመከላከል ጥቅም ያለው ነጭ ሽንኩርት ይህንን በማድረግ በደም ቧንቧ ጥበት ምክንያት የሚከሰት የልብ ሕመምን ይከላከላል፡፡
✔ በሰውነታችን ውስጥ ያለውን የኮሌስትሮል መጠን በመቀነስ በደም ቧንቧ ላይ የሚገኘውን የስብ መጠን እንዲቀንስ ያድርጋል፡፡
✔ ሰውነታችን በአለርጂ እንዳይጠቃ የማድረግ አቅምም አለው፡፡ በሰውነት ላይ ለሚወጣ ሽፍታና በአንዳንድ ነፍሳት ምክንያት የሚወጣንን ሽፍታም ይከላከላል፡፡
✔ ነጭ ሽንኩርት በጉንፋን የመያዝ ሁኔታን በከፍተኛ ደረጃም ይቀንሳል፡፡ከተያዝንም በኋላ እንዳይበረታብንና ቶሎም እንድንድን ይረዳል፡፡
✔ ነጭ ሽንኩርት በሰውነታችን የሚመነጨውን የኢንሱሊን መጠን መጨመርና በደም ውስጥ የሚገኙትን የስኳር መጠን በመቆጣጠር ለስኳር ሕመም ጠቀሜታነት ይሰጣል፡፡
✔ የተፈጨ ነጭ ሽንኩርት ጥርሳችንን በሚያመን ቦታ ላይ በማድረግ ባክቴሪያዎችን ማጥፋትና ሕመምን የመቀነስ ጥቀም አለው፡፡
🔍🔍▬▬ Share ▬
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
+2
አሜሪካ ህውሃት አንድ ቡድን ላይ ማዕቀብ እንደምትጥለ ተሰምቷል።
አሜሪካ በሕወሓትና በትግራይ ጸጥታ ኃይሎች ውስጥ ሥልጣን ባላቸው አንዳንድ ግለሰቦች ላይ ማዕቀብ ልትጥል እንደምትችል አንድ የአገሪቱ ባለሥልጣን እንደነገሩት ጠቅሶ ዘ ኢኮኖሚስት መጽሄት ሰሞኑን ባወጣው ዘገባ አስነብቧል።
አሜሪካ ማዕቀብ ለመጣል እያሰላሰለች ያለችው፣ ትግራይ እንዳትረጋጋ እንቅፋት በኾኑና ክልሉ በድጋሚ ጦርነት እንዲያመራ እያደረጉ ይገኛሉ በምትላቸው ግለሰቦች ላይ እንደኾነ ባለሥልጣኑ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
አሜሪካ ማዕቀብ መጣልን እንደ አማራጭ ያየችው፣ የተወሰኑ የትግራይ ክልል ጸጥታ ኃይሎች ወታደራዊ አዛዦች ጌታቸው ረዳ በሚመሩት ጊዜያዊ አስተዳደር ላይ ከሳምንታት በፊት የመፈንቅለ ሥልጣን ሙከራ ማድረጋቸውን ተከትሎ እንደሆነ መሆኑን በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።(Wazema)
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
