Goqa-ጎቃ (Ethio-news)
前往频道在 Telegram
All about Ethiopia!!! ሁሌም ስለ ኢትዮጵያ እንዲሁም አለም-አቀፍ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበረሰባዊ ዜና ከትንተና ጋር።
显示更多4 151
订阅者
无数据24 小时
-127 天
-8130 天
帖子存档
4 151
#Update
#ሶማሌላንድ #ከአትዮጵያ ጋር ያላት ግንኙነት በተፈራረመችው የመግባብያ ሰነድ መሰረት
እንደሚቀጥል ገለፀች!!!!
⚡️አዲሱ #የሱማልያላንድ ፕሬዚዳንት አቶ አብድራማን ሞሐመድ አብዱላሂ እንዳሉት "#በኢትዮጵያ እና #ሱማልያላንድ መካከል በመግባብያ ሰነድ የፀደቀ የሁለትዮሽ ስምምነት አለ፤ ፀንቶም ይቀጥላል። ነገር ግን #ኢትዮጵያ ከሶማልያ ጋር የምታደረገው ስምምነት እራሱን የቻለ የሁለቱ ሃገራት ጉዳይ ነዉ አኛ የሚያስረን ስምምነት አለን እስከ ፍፃሜውም አናየዋለን።"
💥በቅርቡ #በአሜሪካ ፓርላማ አንደ ነፃ ሀገር ለመታየት ሃሳብ የተነሳላት #ሱማልያላንድ እራሷን #ከሶማልያ ለይታ ማየቷ አና እንደ ገለልተኛ ሀገር መንቀሳቀሷ አንደቀጠለ ነው።
©Addis Standard
#ሶማልያ #ሶማልያላንድ #ኢትዮጵያ
Join Us
https://t.me/+6HHF7MBj0VUyMjVk
4 151
#Breaking_News
#የሩስያ የኒዩክለር መከላክያ ኃይል ዋና መሪ ሌትናል ጀንራል ጎር ኪራሎቭ በሞስኮ ተገደሉ!!!
⚡️ሌትናል ጀንራሉ ከነበሩበት መኖርያ መንደር በመውጣት ላይ ሳሉ በአካባቢው የነበረ ሞተር ላይ በተጠመደ ቦምብ ሲሆን የተገደሉት እስካሁን ጥቃቱን ማን እንዳደረሰ አልታወቀም።
💥ሌትናል ጀንራል ኢጎር ኪራሎቭ ሰኞ እለት የሩስያ መንግስት በመጠቀም የሚወቀሰውን የታገዱ ኬሚካል መሳሪያዎች በማሰራጨት በዩክሬን ክስ ቀርቦበት ነበር።
#ዩክሬን #ሩስያ #ጦርነት
Join Us
https://t.me/+6HHF7MBj0VUyMjVk
4 151
#Breaking_News
#ዊስኮንሰን #አሜሪካ በሚገኝ ክርስትያን ትምህርት ቤት ውስጥ አንዲት ተማሪ በከፈተችው ተኩስ የአንድ አስተማሪ አና የአንድ ተማሪ ህይወት አለፈ!!!
⚡️"The Abundant Life Christian School" በተሰኘው ትምህርት ቤት የምትማረው የ15 አመቷ ናታሊ ሩፕኖው ወይም በሌላ ስሟ ሳማንታ ትምህርት ቤቷ ውስጥ በከፈተችው ተኩስ የሁለት ሰዎችን ህይወት ስትቀጥፍ 6 ሰዎችን አቁስላለች። ከስድስቱ ሁለቱ በከፍተኛ ጉዳት አሳሳቢ ሁኔታ ላይ ሲሆኑ አራቱ መለስተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ጥቃቷን ከጨረሰች ቡሃላ ራሷን ያጠፋቸው ናታሊ ከነመሳሪያዋ ትምህርት ቤት ውስጥ ሞታ ተገኝታለች።
💥በዚህ ዓመት ብቻ 38 የትምህርት ቤት ጥቃቶች ያስተናገደችው አሜሪካ በዚህ ችግር ከዓመት አመት የምትፈተነው ብቸኛ ሀገር ሆናለች። ምናልባትም ይሄኛውን ጥቃት ለየት የሚያደርገው ብቸኛ ነገር አብዛኞቹ የመሳርያ ጥቃቶች በወንዶች ሲፈፀሙ ይህኛው በሴት ተማሪ መፈፀሙ ነዉ። አሜሪካ ለአመታት የመሳርያ ቁጥርጥር ህጎችን እንድታጠብቅ ለቀረቡላት ጥሪዎች በቂ ምላሽ አለመስጠቷ ዛሬም ቢሆን ዜጎች እና ተማሪዎች በስጋት እንዲኖሩ አድርጎል።
#አሜሪካ #የመሳሪያህግ #ትምህርትቤት
Join Us
https://t.me/+6HHF7MBj0VUyMjVk
4 151
#Update
#ጁባላንድ #ከሶማልያ ፈደራላዊ መንግስት ጋር በተደረገው ግጭት የያዘቻቸውን የጦር ምርኮኛዎችን ለፌደራል መንግስቱ አስተላለፈች!!!
⚡️#ጁባላንድ ባካሄደችው ምርጫ ምክንያት #ራስካምቦኒ ውስጥ በሀገሪቷ ፌደራል መንግስትና #በጁባላንድ አስተዳደር መካከል በተፈጠረው ግጭት የተማረኩት የፌደራል መንግስቱ ወታደሮች መጀመርያ #በኬንያ መንግስት እርዳታ አሁን ደግሞ በራሷ #በጁባላንድ ድጋፍ ወደ #ሞቃዲሾ ተሸኝተዋል።
💥#የጁባላንድ እርምጃ በክልሉ አና በፌደራል መንግስቱ መካከል ንግግሮች እንዳሉ የሚጠቁም ሲሆን ምናልባትም አለመግባባቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መንገዶች አየተከፈቱ አንደሆነ ማሳያ ነዉ።
©Garowe Online
#ሶማልያ #ጁባላንድ #ምርኮኛ
Join Us
https://t.me/+6HHF7MBj0VUyMjVk
4 151
#Update
ፕሬዝዳንት ዩን ለአቃቢ ሕግ ጥሪ አልታዘዝም አሉ!!
⚡️ባለፈው ሳምንት በፓርላማ ድምፅ ከስልጣን የተወገደው ፕሬዚዳንት ዩን ባወጀው ወታደራዊ አገዛዝ ምክንያት ለተከፈተበት የወንጀል ምርመራ አልተባበርም አለ።
⚡️የተከፈተበት ምርመራ አመጽ በመቀስቀ ፣ ስልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም እና የህዝብን መብት በመከልከል ክሶች ላይ የተመሰረተ ሲሆን በትላንትናው እለት አቃቢ ሕግ ለምርመራ ያቀረበለትን ጥሪ አልቀበልም በማለት አልቀረበም።
💥#ደቡብ ኮርያ በቅርብ አመታት ላሰፈነችው ዴሞክራሲ የሀገሪቷ ሕግ አውጪዎች ፣ የፓርቲ አባላት እንዲሁም ከ200,000 በላይ ህዝቦች በአደባባይ ሲሟገቱ የፕሬዚዳንቱ አምቢ ባይነት አነጋጋሪ ሆኗል። ነገር ግን ደቡብ ኮርያ ዴሞክራሲ በተቋሟት አና ህዝብ የሚጠበቅ አንጂ በአንድ ግለሰብ የሚወሰን አለመሆኑን ለዓለም አሳይታለች!!
#ደቡብ_ኮርያ #ዩን #ፓርላማ
Join Us
https://t.me/+6HHF7MBj0VUyMjVk
4 151
እስራኤል ሶሪያን ማጥቃቷን ቀጥላለች !!!!
⚡️#የሶሪያን መንግስት መውደቅ ተከትሎ በመካከለኛው ምስራቅ አዳዲስ ክስተቶች ሲፈጠሩ ቆይተዋል። በተለይም በቦታው ልዩ ፍላጎት የነበራት #እስራኤል ሶርያ ላይ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ልክ የራሷን ተልዕኮ አና ፍላጎት አያስፈፀመች ትገኛለች።
⚡️#እስራኤል #የሶርያን የአሳድ መንግስት መውደቅ ተከትሎ "በግዛቱ ስር የተከማቹ አና የተፈበረኩ መሣርያዎች በፅንፈኞች አጅ አንዲወድቅ አልፈልግም" በማለት የጦር ካምፖች አንዲሁም መሣሪያ ማከማቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ስታደርስ ቆይታ አሁን ላይ #በሶርያ ደቡብ ምዕራብ አካባቢ የሚገኘውን የጎላን ተራራዎች በቁጥርጥር ስር አውላለች።
💥#በሶርያ ስልጣን የያዘው ቡድን መሪ አህመድ አልሻዓራ ጉዳዩን ስያብራሩት #እስራኤል ፍላጎቷን ለማስፈፀም የተጠቀመችው የይምሰል ስጋት ቢሆንም #ሶርያ ከአሁን ወድያ በመልሶ ግንባታ የምትወጠር ለጦርነት አቅሙም ጊዜውም የሌላት ሀገር መሆኗን ገልፆ #ከእስራኤል ጋር ሊደረግ የሚችል ፍጥጫን ከወዲሁ አሽሽቷል።
#እስራኤል #ሶርያ #መካከለኛምስራቅ
Join Us
https://t.me/+6HHF7MBj0VUyMjVk
4 151
#Breaking_News
#ከአዲስ አበባ ወደ #ዱባይ እያመራ የነበረ #የአትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላን በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ወደ #አዲስአበባ ለመመለስ ተገዷል!!!!
አይሮፕላኑ በረራ ከጀመረ 30 ደቂቃ ቡሃላ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ወደ #አዲስአበባ ተመልሶ ቦሌ አለማቀፍ ማረፍያ በሰላም አርፏል።
አየርመንገዱ ተሳፋሪዎች እና የበረራ ሰራተኞችን በአስቸኳይ ከአይሮፕላኑ እንዲወርዱ ማድረጉን ገልፆ ማንም ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ አሳውቁአል።
#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያ_አየርመንገድ #አይሮፕላን
Join Us
https://t.me/+6HHF7MBj0VUyMjVk
4 151
+2
#Breaking_News
#Update
#የደቡብ ኮርያ ፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዩል በሀገሪቷ ፓርላማ ድምፅ ከመንበረ ስልጣናቸው ተወግደዋል!!!
⚡️ከሳምንት በፊት በተደረገ የፓርላማ ምርጫ ለሰዓታት ወታደራዊ አገዛዝ ያወጁትን ፕሬዚዳንት ዩን በጥቂት ድምፅ ማነስ ምክንያት ከስልጣን ማንሳት እንዳልተቻለ ይታወሳል።
⚡️ነገር ግን ከሳምንት በፊት በተቃውሞ ምርጫውን ያልታደሙት የዩን "PPP" ፓርቲ አባላት በዛሬው እለት በምርጫው ከመሳተፍ ባለፈም 12ት አባላት ዩን ከስልጣን እንዲወርድ ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
⚡️በህጋዊ አካሄዱ መሰረት ሕግ አውጪ ተቋሙ (ፓርላማ) የዩን ከስልጣን መገለል ላይ ድምፅ ቢሰጥም ውሳኔው ጊዜያዊ ይሁን ዘላቂ የሚወስነው ፍርድቤት ሲሆን ውሳኔውን ለማሳወቅ 180 ቀናት አሉት። ውሳኔው ዘላቂ እንዲሆን ከተፈረደ በ 60 ቀናት ውስጥ ለቀጣዩ ፕሬዚደንት ምርጫ ይካሄዳል።
💥#የደቡብ ኮርያ ህዝብ በውሳኔው አጅግ መደሰቱን በተለያየ መንገድ ሲገልፅ ቆይቷል። አሁን ላይ #ኮሪያውያንም ሆኑ የዓለም ሃገር ዜጎች አነጋጋሪውን የፍርድቤት ውሳኔ በጉጉት ይጠባበቃሉ።
#ደቡብ_ኮርያ #ዩን #ፓርላማ
Join Us
https://t.me/+6HHF7MBj0VUyMjVk
4 151
+1
#Update
በሁለቱ አገራት መካከል አንካራ ላይ የተደረሰው ስምምነት #ሶማሊላንድን የማይመለከት የሁለቱ አገራት ጉዳይ ነው።
- የሶማሊላንድ ቃል አቀባይ ሞሐመድ ፋራህ አብዲ
⚡️ቃል አቀባዩ እንደተናገሩት #በሶማልያ አና #በኢትዮጵያ መካከል #አንካራ ላይ የተደረሰው ስምምነት የሁለቱ ሀገራት ጉዳይ ሲሆን #ሶማሊላንድ ራሷን የቻለች ሌላ ሀገር እንደመሆኗ ጉዳዩ አይመለከታትም።
⚡️አክሎም ከሳምንታት በፊት ስልጣን የያዘው #የሶማሊላንድ መንግስት ለ"BBC Somalia" በሰጠው መግለጫ ገና ሥልጣን መረከቡ እንደሆነ አስታውሶ የቀድሞው መንግስት #ከኢትዮጵያ ጋር ያደረገውን የመግባብያ ስምምነት እንዳልተመለከተ ተናግሯል። ሆኖም ስምምነቱ #የሶማሊላንድን ጥቅም እንደሚያስጠብቅ ከታመነበት እንደሚሠሩበት፤ ካልሆነ ግን አንደሚቀር ገልፀዋል ።
⚡️በተቃራኒው ይህንን ተቃውመው የቆሙት #የሶማልያ መንግስት የማስታወቂያ ሚኒስቴር ዳውድ አዌይስ የወጣውን መግለጫ ያለመረዳት ችግር እንዳለ ግልፀው #የአንካራው ሰነድ ከዚህ ቀደም የነበሩ ማንኛውንም ስምምነቶች ውድቅ እንደሚያደርግ አሳስበዋል።
#ሶማሊላንድ #ሶማልያ #ኢትዮጵያ
©BBC
Join Us
https://t.me/+6HHF7MBj0VUyMjVk
4 151
የ2024 የዓመቱ ምርጥ ሰው፤ ዶናልድ ትራምፕ
ተመራጩ የአሜሪካን ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የጎርጎሪዮሳዊ ዓመት 2024 «የዓመቱ ሰው» ተባሉ። ትራምፕን በዓመቱ ሰውነት የመረጠው ታይም መጽሔት ነው። ዶናልድ ትራምፕን ለሁለተኛ ጊዜ ነው ታይም መጽሔት ይህን ስፍራ ያገኙት። ቀደም ሲል በ2018 ዓ.ም. ከሁለት ዓመታት በፊት በተካሄደው ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሊ በተመሳሳይ «የዓመቱ ሰው» ተብለዋል።
ታይም መጽሔት «የዓለም በጣም ኃያል ሰው» ያላቸው የ78 ዓመቱ ትራምፕ ዳግም ወደ ሥልጣን የመጡበትን መንገድም በአሜሪካ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ብሎታል። ታይም መጽሔት ሰማያዊ ሱፍ ሙሉ ልብስ ከቀይ ክራቫት ጋር መለያቸው ነው ያላቸው ዶናድል ትራምፕ፤ የመጀመሪያ የሥልጣን ዘመናቸው በጎርጎሪዮሳዊው 2020 ዓ.ም. የተካሄደውን የምርጫ ውጤት ለመቀልበስ ካፒቶል ላይ በተሞከረው ጥቃት ሳቢያ በውርደት መጠናቀቁን አስታውሷል።
ይህን ጨምሮ የተለያዩ ክሶች የቀረቡባቸው ትራምፕ ለእጩ ፕሬዝደንትነት እንደሚቀርቡ መግለጻቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤት ሲመላለሱ መክረማቸውን፣ ሆኖም በወንጀል መከሰሳቸው በምርጫው ድል ከማስመዝገብ እንዳላገዳቸውም አንስቷል። ትራምፕ ለድል ስኬታቸው የሕዝቡን መሠረታዊ ቅሬታዎች መጠቀማቸውን፤ ከታይም መጽሔት ጋር በነበራቸው ቃለመጠይቅ ገልጸዋል።
የታይም ዋና አዘጋጅ ሳም ጃኮብስ ስለውሳኔው ለአሜሪካው ኤንቢሲ መገናኛ ብዙሃን ሲገልጽ «በጥሩም ሆነ በመጥፎ ትራምፕ በ2024 በዜና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድረዋል» ነው ያለው። ባለፈው ኅዳር በአሜሪካ በተካሄደው ምርጫ ዶናልድ ትራምፕ የዴሞክራቲክ እጩ ካማላ ሃሪስን በማሸነፍ 47ኛው የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል።
ለዓመቱ ሰው ምርጫም፤ ተፎካካሪያቸው ዴሞክራቷ ካማ ሃሪስን ጨምሮ፤ የሜክሲኮ ፕሬዝዳንት ክላውዲያ ሺንባም፣ እስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የሟቹ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ አሌክሲ ናቫልኒ ባለቤት ሩሲያዊቷ የኢኮኖሚ ባለሙያ ዩሊያ ናቫልኒ እጩዎች ነበሩ።
©Dw
4 151
+3
የሶርያ አማፅያን መሪ የአሳድን አሰቃቂ እስር ቤቶች እንደሚዘጋ ተናገረ
⚡️የሶርያ እስር ቤቶች በተለይም ከ2011 የእርስ በርስ ጦርነት ቡሃላ ዘግናኝ ኢ-ሰባዊ ድርጊቶች የሚሰራባቸው የሞት ካምፖች ሁነው ቆይተዋል።
⚡️ህፃናት፣ ሴቶች፣ አዛውንት የአሳድ መንግስት ያለምንም ርህራሄ ተቃውሞት የቆመን ማንኛውንም ግለሰብ የሚቀጣበት ፤ የሚያሰቃይበት የሚገልበት እነዚህ ወህኒ ቤቶች ውስጥ 60,000 ሰዎችን በግፍ ተገድለዋል።
⚡️ከነዚህ ወህኒ ቤቶች መሃል በሰቅጣጭ ድርጊቶቹ ገዝፎ የወጣው "ሴድናያ" ወይም "The Human Slaughter House" በመባል የሚታወቀውን እስር ቤት ሶራውያን እየሰባበሩ ሲገቡ የሚያሳዩ ምስሎች በሶሻል ሚድያ ቫይራል ሆነዋል።
⚡️አሁንም ቤተሰቦቻቸው እንደ ድንገት ከመካከላቸው ተወስደው የታሰሩባቸው ዜጎች በተስፋ የወህኒ ቤቶቹን ደጆች ይመለከታሉ የእስር ቤት መዝገቦችን ያገላብጣሉ። አንዳንዶች ወዳጆቻቸውን አግኝተው ሲደሰቱ ሌሎች ማቅ ለብሰው ተቀምጠዋል!!
#ሶሪያ #አሳድ #ሴድናያ
Join Us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
+2
#Update
#Breaking_News
#ኢትዮጵያ እና #ሶማሊያ ስምምነት ላይ ደረሱ!!!!
⚡️በሁለቱ ሃገራት መሪዎች መካከል በቱርክ አንካራ የተደረገው ውይይት ስኬታማ ሆነ!!!!
⚡️"የአንካራ ስምምነት " የተሰኘው ስምምነት የሃገራቱ መሪዎች አንዱ የሌላኛውን ሉዓላዊነት አንድነት አና ነፃነት እውቅና ባረጋገጠ መልኩ በወዳጅነት ለጋራ እድገት እንደሚሰሩ የተስማሙበት ነዉ።
⚡️ስምምነቱ የሶማልያን የግዛት አንድነት በማይሽር መንገድ እትዮጵያ ዘላቂ የባህር በር እንድታገኝ የሚያደርግ ሲሆን የስምምነቱን ቀሪ ቴክኒካል ጉዳዮች አስከ ፊታችን የካቲት እንደሚጠናቀቁ ተገልጿል።
⚡️በተጨማርም የኢትዮጵያ ሰራዊት በሶማልያ ሰላም የማስከበር ተልዕኮውን ለመፈፀም የከፈለውን መሰዋትነት ሶማልያ እውቅና እንደምትሰጠው አረጋግጣለች።
💥ለአንድ ዓመት ያህል በቀጠናው ውጥረት ፈጥሮ የቆየው የባህር በር ጉዳይ መቀረፉ ለአፍሪካ ቀንድ ሃገራት ሰላም አና ዘላቂ እድገት አንድ እርምጃ ወደፊት የሚወስድ ውሳኔ ነዉ!!
#ሶማሊያ #ኢትዮጵያ #ስምምነት
Join Us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
#Breaking_News
#Update
#በጁባላንድ እና #ሶማልያ ሀይሎች መካከል ተኩስ ተከፈተ!!!
#አሜሪካ ከሰዐታት በፊት አሳሳቢ ብላ የፈረጀችው #በሶማልያ እና #ጁባላንድ መካከል የነበረው ውጥረት ባልተጠበቀ ፍጥነት ወደ ግጭት አምርቷል።
#በጁባላንድ አስተዳደር የጸጥታ ሀይሎች እና በአከባቢው በሰፈሩ #የሶማሊያ ፌደራል መንግስት ወታደሮች የተካሄደው ውጊያ ወደ አስከፊ ጦርነት ሊያድግ እንደሚችልም ተገልፆል ።
#ሶማልያ #ጁባላንድ #ኢትዮጵያ
Join us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
#Update
#የኢትዮጵያ አና #የሶማልያ መሪዎች #በቱርክይ አደራዳሪነት ሊነጋገሩ መሆኑ ተሰማ!!!
⚡️ከዚህ ቀደምም #ኢትዮጵያ #ከሱማልያላንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት #በሶማልያ አና #ኢትዮጵያ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት ስትሞክር የቆየችው #ቱርክይ አሁን ላይ የሁለቱንም ሃገራት መሪዎች ለምክክር ጋብዛለች።
⚡️#የሶማልያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ ለዚሁ ስብሰባ በትላንትናው እለት ወደ #ቱርክይ ማምራታቸዉ ሲሰማ #የኢትዮጵያ ጠ/ሚ አብይ አህመድም በስብሰባው እንደሚገኙ ይገመታል።
💥ከዚህ ቀደም በሃገራቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሮች መካከል የተደረገው 2 ዙር ውይይት ፍሬ ቢስ መሆኑ ባይዘነጋም ምን አልባት በመሪዎች መካክል የሚደረገው ውይይት መፍትሄ ይዞ እንደሚመጣ ተስፋ ተደርጓል።
#ሶማሊያ #ኢትዮጵያ #ቱርክይ
Join Us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
#Update
የኔታንያሁ የሙስና ክሶች ምን ደረሱ??!!
⚡️እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ #በእስራኤል ጠ/ሚ ቤንጃሚን ኔተንያሁ ላይ ተደጋጋሚ የሙስና ክሶች እንደቀረቡ ምን ያህሎቻችን አናውቃለን?
⚡️ለ8 አመታት ሲካሄድ በቆየ የፍርድ ሂደት ላይ ኔተንያሁ ከተለያዩ የሚድያ ጣብያ ባለቤቶች ጋር የነበረው ጉቦኛ ግንኙነት እንደዋና ክስ ቀርቦበታል።
⚡️ለእሱ አና ለቤተሰቡ "ቅን" አና የተሻለ የሚድያ ሽፋን ለማግኘት የተፎካካሪ ሚድያ ጣብያዎችን እንቅስቃሴ የሚገታ ሕግ ለማውጣት እስከመስማማት ድረስ የሄደው ኔተንያሁ በተጨማሪም ጉዳይ እንድያስፈፅምላቸው ከሚፈልጉ ባለሃብቶች ውድ ውድ ስጦታዎችን በመቀበል ፤ እንደ ሚኒስቴር ያገለግል በነበረበት ቦታዎች የግል ፍላጎቱን በማስቀደም እና እምነትን በመሻር ተከሶ ከጠቅላይ ሚኒስቴርነት ውጪ ከሁሉም የሚኒስቴር ስልጣኞቹ መገለሉ አይረሳም።
💥አሁንም ቢሆን ያልተቋጨው የፍርድ ሂደት ጠቅላይ ሚኒስቴሩ በዚህ ሳምንት ፍርድ ቤት እንዲቆም ማስገደዱ በሙሉ እስራኤል መነጋገርያ ሆኗል። አንዳንዶች በጦርነት መሃል ይህንን ማድረግ የሃገሪቷን እንዲሁም የመሪዋን ገፅታ ማጠልሸት ነዉ ሲሉ ሌሎች ደግሞ ኔታንያሁ ጊዜውን ሰበብ አድርጎ ከተጠያቂነት መዳን የለበትም በማንኛውም ሰዓት ፍትህ ትቅደም ይላሉ።
እርሶስ ምን ያስባሉ❓
#ኔታንያሁ #እስራኤል #ሙስና
Join Us:
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
#Update
ቴሌግራም የሩስያ የስለላ መሳሪያ ይሆን??!!
⚡️የዩክሬን አና ሩስያ ጦርነት ከጀመረ ድፍን ሶስት አመታትን ሊያስቆጥር ጥቂት ቀናት ብቻ ይቀሩታል። በዚህ ጦርነት ለተወራሪዋ ዩክሬን ቀዳሚ የመረጃ መለዋወጫ ገፅ ሆኖ ያገለገለው ቴሌግራም ሲሆን 70% የሀገሪቷ ዜጎች በድሮን የተጠቁ ቦታዎችን፣ መጠለያዎችን ፣ እንዲሁም እርዳታ የሚገኝበትን አካባቢዎች ለማወቅ ይጠቀሙበታል።
⚡️ሆኖም የዩክሬን ደህንነት ተቋም ሩስያ ውስጥ የተሰራውን የቴሌግራም መገልገያ ገለልተኝነት መጠየቅ ጀምሯል። መተግበርያው በሩስያ የሀሰት መረጃ አንዲሁም የሳይበር ጥቃቶች መሰንዘሪያ መሳሪያ ሆኗል ብለው የሚያምኑ የዩክሬን ብሔራዊ ደህንነት ባለሙያዎች ከዚህ ቀደምም በመስከረም ወር የመንግስት ባለስልጣናት መተግበርያውን ከስራ ስልካቸው እንድያጠፉ አዘዋል።
የኢንግሊዝ ደህንነት ቢሮም ይህንን ጥርጣሬ ይደግፈዋል።
⚡️ቴሌግራም የቀረበበትን ወቀሳ "ሩስያ የተጠቃሚዎችን መረጃ ማግኘትም ሆነ ማየት እንደማትችል አሳውቆ ቴሌግራም የዩክሬናውያንንም ሆነ የየትኛውንም ሀገር ህዝቦች መረጃ ደህንነት አንደምጠብቅ ገልጿል።
#ዩክሬን #ሩስያ #ቴሌግራም
©Deecan Herald
Join us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
#Update
"#ኢትዬጵያ #ጁባላንድን አያስታተቀች ነዉ!!!"
- #የሶማልያ መንግስት
⚡️#ሶማልያ እና #ጁባላንድ ራስ ገዟ #ጁባላንድ ባደረገችው ፤ #የሶማልያ ፌደራላዊ መንግስትን በማግለሉ "ኢ-ህገመንግስታዊ" በተባለው ምርጫ ምክንያት በመካከላቸዉ የነበረ ሁሉም የበረራ እና የግንኙነት መስመሮች ተቋርጠው ወታደራዊ ፍጥቻ ላይ መሆናቸው አይዘነጋም።
⚡️ታድያ ከአንድ ዓመት ወዲህ #ከሶማሌላንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት አንደ #ሶማልያ ቀንደኛ ጠላት መታየት የጀመረችው #ኢትዮጵያ አሁን ላይ #ለጁባላንድ መሳርያ በማቀበል ተከሳለች። የሶማልያ መንግስት ባወጣው መግለጫ መሰረት ባለፈው ሳምንት 2 መሳርያ የያዙ የኢትዮጵያ አይሮፕላኖች ወደ ጁባላንድ በረራ ስያደርጉ አንዱ የጁባላንድ ምክትል ፕሬዝዳንት ማህሙድ ሳኢድ አደንን ይዞ ወደ ኢትዮጵያ አምርቷል።
💥በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና አንዱ ሀገር የሌላኛውን አማፅያን መደገፉ የተለመደ ተግባር ነዉ። ሁሉም የቀንድ ሀገር አማፅያን ቢያንስ በአንድ ጎሮቤት ሀገር መንግስት ይደገፋሉ። #አትዮጵያም #ሶማልያን ተቃርነው የቆሙ ቡድኖችን በመደገፍ ስትወቀስ የመጀመሪያዋ አይደለም። ሆኖም አንደዚህ አይነት አንቅስቃሴዎች ለቀጠናው ሰላም አና ዘላቂነት ጠንቅ አየሆኑ መተዋል።
#ኢትዮጵያ #ሶማሊያ #ጁባላን
@BBC
Join us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
#Update
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመወለድ የሚገኝ የአሜሪካ ዜግነትን እንደሚከለክሉ ገለፁ!!!
⚡️በሀገሪቷ ህገመንግስት 14ተኛ አንቀፅ ላይ የተቀመጠው #በአሜሪካ መሬት ለተወለዱ ህፃናት ዜግነትን የሚሰጠው ሕግ ዶናልድ ትራምፕ ወደ ነጩ ቤተመንግስት በይፋ ሲገባ ከሚቀይረው ነገሮች አንዱ አንደሆነ አሳውቋል።
⚡️እ.አ. አ በ1868 የፀደቀው ይህ ሕግ #አሜሪካን የተለያዩ ዘሮች ሀገር አና መኖርያ ያደረጋት ቢሆንም አሁን ላይ በተደጋጋሚ "ስራችንን በስደተኞች አየተቀማን ነዉ" ሲሉ የሚሰሙት ቀኝ ዘመም ሪፐብሊካኖች ህጉን አጥብቀው ይቃወሙታል።
💥ዶናልድ ትራምፕ ገና ስልጣኑን ሳይዝ አነጋጋሪ ውሳኔዎችን ማስተላለፉን ቀጥሏል። በዶናልድ ትራምፕ #አሜሪካ አርግተኛ መሆን የሚቻልበት ነገር ቢኖር አስከዛሬ የነበረችው #አሜሪካ በቀጣይ 4 አመታት ውስጥ በከፍተኛ መጠን አንደምትቀየር ብቻ ነዉ።
#አሜሪካ #ትራምፕ #ዜግነት
Join Us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
+1
#በቻይና ምድር የመጀመርያው #የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ደብር ተሰየመች!!!
⚡️"ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም” ከተሰኘው ደብር መከፈት ጋራ የመጀመርያዋን የቅዳሴ ስነስርዓት በዛሬው አለት ያካሄደችው #የቻይናዋ ደብር የመጀመሪያዋ #ኢትዮጵያዊ ዲያቆንም በብፁዕ አቡነ ያዕቆብ ተሹሞላታል።
⚡️ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም በተካሄደው ቅዳሴ #ከቻይና የተለያዩ ክፍላተ ግዛት የተሰባሰቡ ምዕመናን፣ #ቻይናውያን እና ትውልደ #ቻይናውያን መሳተፋቸው ተገልፆል።
#ቻይና #ቤተክርስቲያን #የኢኦተቤ
©Al-Ain Amharic
Join us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
