403
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
የበዓል ገጠመኝ
✍🏾 በእድል
.
.
.
ኮንዶሚኒየም መኖር ችግር ነው! ሁሉም ዶሮና በጉን በሩ ላይ አስሮ ብሎካችንን ኤልፎራ አስመ ስሏታል። እኔም ትናንት ሚስቴ በግ ካልገዛህ እያለች ስትነተርከኝ ጥቂት ብር ይዤ በግ ልገዛ ብወጣ አንድ ቀውላላ በግ ነጋዴ ሁለት ፊታቸው
ላይ ከባድ ድብርት የሚታይባቸውን ከሲታ በጎች ይዞ ቆሞ አገኘሁና ጠጋ ብዬ
«ልትሸጣቸው ነው?» አልኩት
«እና ሐገር ላስጎበኛቸው ነው ካገሬ ይዣቸው የወጣሁት?»አለኝ
«እንደው ኩነኔ አይሆንም እነዚህን መግደል?» ስለው ፈጠን ብሎ
«አንቀህ ነው እንዴ ምትገድላቸው?» አለኝ
«አይ ያው በቢላም ቢሆን ...» ብዬ ሳልጨርስ
«ወንድሜ ካሳዘኑህ ውሰድና በጉዲፈቻ አሳድጋቸው» አለኝ
«እሺ ስንት ነች እቺ?» አልኩት ወደአንዷ እየጠ ቆምኩ «በግ ታውቃለህ ማለት ነው። በጣም አስተዋይ በግ ነች እሷ» ብሎ ጀርባዋን መታ መታ ሲያደርጋት ወደጎን ፍንግል አለችና አቧራ ዋን አራግፋ ተነሳች።
«እኔ አስተውሎቷ ምን ይሰራልኛል ላስተምራት አይደለም እኮ ምወስዳት» ስለው
«ሁለት ሺህ ብር ክፈል» አለኝ
«ሁለት ሺህ ብርማ አታወጣም»
«በርግጥ ላታወጣ ትችላለች ነገር ግን እኔ ሁለት ሺህ ብር ነው የሚያስፈልገኝ»
«ቀንስና ልውሰድልህ» አልኩት
«አይ ወዳጄ በጓን ግን አይተሃታል? ውስጠ ወይራ እኮ ነች። መፍዘዟን አትይ። በዚያ ላይ በእንክ ብካቤ ነው ያደለብኳት»
«ጭራሽ ደልባ ነው እንዲህ የከሳችው?»
«አዎና! በርግጥ እኔ ስብእናዋ ላይ ነው የሰራሁት። በጥሩ ስነምግባር ነው ያሳደግኋት» አለኝ ቆፍጠን ብሎ። ሳቄን ለመቆጣጠር እየሞ ከርኩ «አንድ ሺህ ብር ትሸጥልኛለ ...?» ብዬ ሳልጨርስ«ውሰዳት!» አለኝ በደስታ ተሞልቶ።
ምነው ዝም ባልኩ ብዬ በይሉኝታ አንድ ሺህ ብር ሰጥቼው በጓን ይዤ ልሄድ ስል መራመድ አቅቷት በቀስታ ስታዘግም «ቃሬዛ ቢኖርኮ ደግ ነበር» አለኝ ሰውዬው በጉን በሃዘን እየሸኘ። ተበሳጭቼ ዝም ብዬው ስሄድ
«ወንድሜ እንደው ለነፍስ ትሆንሃለች መጀመሪያ የህክምና እርዳታ አርግላት» አለኝ መንገድ ላይ በጓን ያየ ሁሉ ከንፈሩን እየመጠጠ ያልፋል።
አንዳንዱ እኔን እያየ አንገቱን በሃዘን ይነቀንቃል። በግ ላርድ ሳይሆን እንደአብርሃም ልጄን ልሰዋ ይዤ እየሄድኩ ነው ያስመሰሉት ። ሽምቅቅ እንዳልኩ ቤት ደረስኩ። ሚስቴ በጓን
እንዳየቻት
«ምንድነው ይዘህብኝ የመጣኸው?» ብላ ጮኸች። በጩኸቷ ከኔ ይልቅ የደነገጠችው በጓ ነች። አይኗን አስለምልማ መሬት ወደቀች! የመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ ላደርግላት ሞከርኩ።
አልነቃ ስትለኝ በአፌ ትንፋሽ ልሰጣት ሳጎነብስ ሚስቴ «በዚህ አፍህ እኔ ከንፈር ጋር ድርሽ እንደማትል እወቀው!»ስትለኝ
ቀና ብዬ መጨረሻዋን ማየት ጀመርኩ ..ውይይ! አረፈች! በጣም የሚያሳዝን ሁኔታ ነው የገጠመኝ
ጎበዝ።ለሚስቴ «ያ ሙታን አስነሳለሁ ሚለው ተሻለኝ ጓዶቼ?
«ቆይ ግን ...የግድ ስጋዋን ለመብላት እኛ ልንገድላት ይገባል እንዴ? ያው ሞት ሞት ነው። በቢላም ሞተች በድንጋጤ ያው መሞቷ አይቀ ርም!» ስል ሚስቴ ሶስት ግዜ አማትባ «በል አውጥተህ ጣል» አለች። እኔ ግን ተስፋ አልቆ ረጥኩም! እቺን በግ እኮ ስጋዋን ፈልጌ ሳይሆን እንደበግ እንድትተውን ነው የገዛኋት። አክተር ደሞ አይሞትም ኦህኦህኦህኦህህ! ተመስገን! ነቅታለች ጎዶች «እልልልል ...» (አሉ እትዬ ዘርፌ የቤት እቃ (ማማሰያ ሳይቀር) እየሰረቀ ያሰለቻቸው ልጃቸው ሲታሰር)
እንዲህ ነው እንጂ በግ! ዝም ብሎ መሞት አለንዴ? እኛ ሳንፈቅድላትማ አትሞታትም! አልኩ ለሚስቴ (አንዳንዴኮ እንደ አፍሪካ መሪዎች ሚያደርገኝ ነገር አለ)ሚስቴ መንቃቷን ስታይ «በል ቶሎ እረድልኝ» ብላ የአሉላ አባነጋን ሻሞላ የሚያህል ቢላ ይዛ መጣች።
«አሁን ለዚች በግ ይሄን የሚያህል ቢላ መጠቀም ተመጣጣኝ እርምጃ ነው ብለሽ ታስቢያለሽ?» አልኳት።
«ወሬውን ተወውና ሳትሞት እረዳት»
የሚል ቀጭን ትዛዝ ሰጠችኝ! ሻሞላውን ተቀብዬ ወደበጓ ስጠጋ አይኗን ከፈት አርጋ ቢላውን አየት አረገችና እንደሰው እንባዋ ባይኗ ሞልቶ ፀጥ አለችላችሁ! በቃ ሞተች!ብቻ በጣም የሚያሳዝን ጉዳይ ነው የገጠመን ወገን! ከሚስቴ ጋር ያደርኩትን አዳር አዳር አትበሉት። ለሊት ላይ ጠጋ ብዬ እያቀፍኩ...
«አይዞን እኛ ጤና የሚቀጥለው በዓል ምን የመሰለ ሙክት ነው ምናርደው» ስላት እንደ አለቃ ገብርሃና ገፍትራ ከግድግዳጋር አጋጨችኝ!
ኤጭ አሁንስ መረረኝ! ጌታ ሆይ ትመጣለህ ወይስ እኔ ልምጣ?🚶🏽♂🚶🏽♂🚶🏽♂
💚💛❤እንኳን አደረሳችሁ 💚💛❤
@Marsilas_23🥀
@Hayitiye 🦋🦋
እናት ናችሁ።በጣም ነው የምወዳቹ በጣም ትንከባከቡናላቹ
ቤታችንን ትጠብቁልናላቹ ብዙ ነገረ ነው ያረጋችውልን።
ሁላችሁንም እወዳችዋለው በጣምም ማናችሁም በጭራሽ
እንዳታዝኑ። ወደ እናንተ ከተመለስኩ ደስታው የእኔ ነው።
ካልሆነም አትዘኑ። ዛሬ ወይም ነገ ምንም ሳልሆን ምንአልባት
እመለስ ይሆናል እኮ እንዲሁ ስለፈራው ነው። ጊዲዮን ምንም
ቢላቹ ማናችሁም በጭራሽ ወደ እሱ እንዳመጡ ስቃዩ የአዳም
ነው ምክንያቱም አዳምን ለመጉዳት መጀመሪያ አዳም
የሚወዳቸውን ስዎች እንደሚጎዳ አውቃለሁ" አለችና ከዶክተር ጋራ
ስላጋጠማት ነገር አጠር አድረጋ ፃፈች ሁሉም እንባ አረገፉ አዳም
ማንበብን ቀጠለ።እና የምወዳቹ የምትወዱኝ ከሆነ ያልኳችውን
አድረጉ እወዳችዋለው ሁሌም በውስጤ አላቹከ ዲና ይላል
፨ አዳም አለቀስ "እኔ አልቻልኩም በቃ አልቻልኩም" አለ ቦስ
ደብዳቤውን አነሳው ከጀረባውም ፁሁፋ አገኘ። "የኔ ውዶች
ያልነገርኳቹ ነገረ አለ። ያኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ጠዋት ውሀ እረጭቼ
ከእንቅልፋቹ የቀሰሰቀስኳቹ እለትን አስታወሳቹ ከእዛን ቀን ጀምሮ
ያሳለፍነውን ነገረ በእየቀኑ እፅፈው ነበር ወደ መፅሀፍ የመቀየረ
ሀሳብም ነበረኝ። ግን እናንተ ጨርሱት የማውቀው ሂስ( የልቦለድ
ገምጋሚ) አሉት ሊቁ ጻውሎስ ይባላሉ አድራሻቸው ከስረ የፃፍኩት
ነው። ቪዲዮም አለ ሁሌም ጠዋት ስትነሱ ስቀስቅሳቹ እቀርፃቹ
ነበረ። የመጀመሪያ ቀን ለቦስዬ አሳይቼው ነበረ እዩት አንብቡት
ትወዱታላቹ አደራ መፅሀፉን አሳትሙት የእራስጌ ቁም ሳጥን ላይ
አላቹ " ይላል ይህንን ቦስ ጮክ ብሎ አነበበ።
፨ ሄዋን ድምፅ እያወጣች አለቀስች በጣም ሁሉም አለቀሱ ቤቱ
በለቅሶ ተሞላ። ሀዘን ሀዘን ሀዘን ሀዘን ጭንቀት ጭንቀት ጭንቀት
ጭንቀት ለቅሶ ለቅሶ ለቅሶ ለቅሶ ሁሉም በተመሳሳይ ሰአት
እያስተናገዱ ነው። ቦስ ስልኩን ከ ጠረጴዛው አንስቷ ዲና ስልክ
ላይ ደወለ።,'ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጪ ነው' ይላል ቦስ
ስልኩን ወረውረው ከግድግዳው ጋራ አመሳሰለው። የቦስ ስልክ
ግድግዳው ላይ ተበታትኖ መሬት እረገፈ። ልክ እንደ ልቡ ስልኩም
ተበታተነ ፤ልክ እንደ ሀሳቡ ስልኩ በተለያየ አቅጣጫ ተበታተነ።
ቦስ ከዛ ደንዝዞ ዝም አለ። ከእዛን ስአት በኋላ ከዛን ደቂቃ በኋላ
ቤቱ በዝምታ ተዋጠ።
፨ጥጥ ቢወድቅ እንኳን ግዙፋ ነገረ እንደወደቀ የሚስማበት
ይመስላል። የአዳም ስልክ ጮከ ማንሳት አቅቶት እጁ ተንቀጠቀጠ
ሄዋን ስልኩን ከአዳም ተቀበለችው ምክንያቱም ማንሳት አቃተው
ሄዋን "ሄሎ አለች።" ኦኦኦኦኦኦ ዡሌታችን ሀሀሀሀሀሀሀ ምነው
ድምፅሽ እንደ በረዶ ቀዘቀዘ አጫዋችሽን ወሰዱብሽ ኣኣኣ የሆነ
ዘፈን ትዝ አለኝ ልጅ እያለን የምንዘምረው"።
" አረ አምሳለ ኧረ አምሳለ
ኧረ ሆይ ኧረ ሆይ
ኧረ እንዴት ነሽ(2)
አለሁ በመከራ እባዬን ሳዘራ
ለምን ታዘሪያለሽ አንድ አጫዋችሽስ
አንድ አጫዋቼማ ጌዲዮን ቀማኝ
ሀሀሀሀሀሀ እ ሀሀሀሀሀሀ ትስሚያለሽ አሁን የስልኩን ዳታ ክፈች
እና የማሳያቹ ነገር አለ ትይንቱን ትወጅዋለሽ" አላት ሄዋን
በፍጥነት ዳታ አበራች ወዲያው በቪዲዮ ተደወለ። አነሳችው።
፨ ሁሉም ወደ ስልኩ ተሰብስበው አፈጠጡ። ጥቁር በጥቁረ
የለበስና በፊቱ ላይ ማክስ ያረገ ስው ዲናን እያዳፋ አመጣት ከዛ
እየጎተተ ጣላት። አዳም "አይሆንምምም" ብሎ ጮከ። ቦስ
"አትጎትታትት" አለ" ቁሚ" አላት በጩከት ስውየው ዲና በግድ
ቆመች። ቦታው መብራት አለው መጋዘን ይመስላል። አዳም እና
ሌሎቹ በጣም ተደናግጠው ማየት ጀመሩ።አንድ ሌላ ሰው መጥቶ
ለጎታቹ ሽጉጥ አቀበለው። ጎታቹ ሽጉጡን ወደ ዲና አቀባሎ እራቅ
ብሎ ቆሞ አነጣጠረው
ጊዲዬን ተኩሰው የሚል ድምፅ ከሳቅ ጋራ አወጣ። ቦስ እራሱን
ስቶ ወደቀ።
ይቀጥላል...
@Hayitiye 🦋
😘አለሜ ነሽ😘
✍️እድል
🔥ክፍል 38
"""
"""
"""
"""
ሄዋን፣አዳምና ቦስም ተኝተው ስለነበረ መልክቱን አላዩትም። ዲና በጠዋት
ውሀ እረጭታ ስታስነሳቸው እንጂ አስደንጋጭ መልክት
በስልካቸው ልካላቸው አንብበው አያውቁም....ሄዋን ከእንቅልፎ እንደነቃች የሌሊት ልብሷን ቀይራ
ወደ ሳሎን ሄደች።
ስልኳን ከእስማርት ቲቪው ጋራ አገናኝታ የዘወትር ልምዷን የሆነውን በጠዋት መዝሙር የመስማትና አብራ የመዘመር ፍቅሯን ልትወጣ መዝሙር ለመክፈት
ስልኳን ስትነካካ ቅድም ከቲቪው ጋር ለማገናኘት ስትሞክር ያላየችው አሁን ያስተዋለችው መልዕክት እንዳላት ምልክቱን አየች... ። የላኪው ማንነት ዲና ስለሆነች ግራ እየተገባች
"ምንድነው?" ብላ ከፍታ
ለማየት ወደ መልክት መፃፊያ እና መላኪያው ጋራ ሄደች። ሄዋን
አነበበችው አይኗን ማመን ተሳናት ህልም ቅዠት ቀልድ መሰላት
ሮጣ ወደ ዲና ክፍል ሄደች ዲና የለችም፤ ወደ በረንዳ ሄደች
አሁንም ዲና የለችም፤ መታጠቢያ ቤት ሄደች ዲ ና የለችም።
ሄዋን ዲናናናናናናናናናናናናናናናናናና ብላ ጮኸች። ቦስ ፣አዳም
ሰራተኖቹ እና ዘበኛው ተሯሩጠው ሄዋን ወዳለችበት መፀዳጃ ቤት
ሄዱ።
፨ አዳም "ምነው ምን ተፈጠረ?" አለ። ስልካችውን እዩት ዲና ዲና
ዲና መልክት ልካላችዋለች አለቻቸው። ቦስ እና አዳም
እየተሯሯጡ ወደ ክፍላቸው ሄዱ። ስራተኞቹ ሄዋንን ይዘው ሳሎን
ወስደው አስቀመጧት። አዳም እና ቦስ ስልካቸውን ካስቀመጡበት
አውጥተው መልክቱን አነበቡ። አዳም ከክፍሉ ወጥቶ ወደ ውጪ
ወጣ ቦስም ተከተለው። ሄዋን "የት ነው የምትሄዱት" አለችው....
"ዲና እንዲህ ሆና እንዴት አስችሎኝ እቀመጣለው ያን ምንም
እንዲያረገኝ አልፈቅድም በቃ" አለ።ቦስም "አዎ እኔም ዲናዬን
አጥቼ መኖር አልችልም" አለ። ሄዋን "አይ አትሂዱ የእናንተ መሄድ
ነገሩን ያብሰዋል እንጂ በጭራሽ አያቀለውም። ትንሽ እንታገስ እና
ከዛ መወሰን ያለብንን እንወስናለን" አለች። ሄዋን ንግግሯን
እንደጨረሰች የአዳም ስልክ ላይ መልዕክት ገባ። ወዲያው
አውጥቶ አየው። የማያውቀው ቁጥር ነበረ። መልክቱ እንዲህ
ይላል "ስላም ላንተ ይሁን አዳም ሰለ ዲና ሀሳብ አይግባክ" ።
ሄዋን ከተቀመጠችበት ሶፋ ብድግ ብላ ከአዳም እጅ ላይ ስልኩን
መንጭቃ ጮክ ብላ አነበበቸው።
፨ ቦስ "ማነው እንዲህ ያለው እየቀለዱብን ነው አውቀው ነው አ?"
አለ። ሄዋን "አይ እኔ ግን የተለየ ሀሳብ ነው ያለኝ።ምን አልባት
የጊዲዮን ጠላት ሊሆን ይችላል" አለች። አዳም "ሲጀመር እኮ እሱ
ወዳጅ ሳይሆን አሽርጋጅ ነው ያለው" አላት። ቦስም "እና ምን
እናድርግ ቆይ ምን ይሻላል ኧረ መላ ፍጠሩ ዝም ብለን እጃችንን
አጣምረን እንቀመጥ ወይ እሺ ካልሆነ አስቀመጥኩት ያለችውን
ነገር እናንብበው" አለ። ሄዋን "አይ አይሆንም መታገስን መልመድ
አለብን ከእዚህ በኋላ ትግስት ያስፈልገናል እሺ አሁን ልሄድ ብላቹ
የት ነው የምትሄዱት?" አለች።ቦስ "የትም በቃ ምን እንደሚፈጠር
እስቲ እንናያለን ዲና ካለችው ሰዓት ካለፍ ግን ወደ ፓሊስ ጦቢያ
ነው የምንሄደው እሺ" አለ።አዳም "አይ ወዳጄ ሞኝ የዋህ ገራገር
ነክ ልበል እስካሁን ይህ ነገር የጠፍኝ መስሎክ ነው ግን
ስለማይሆን ነው የትኛውም ፓሊስ ጣቢያ የጌዲዮን ስዎች ነው
ያሉት። ለመክሰስ እንደምትፈልግ ነገረካቸው ከተስማሙ በኋላ
የምትከሰው ሰው እሱ መሆኑን ሲያውቁ ይሸሹካል መቼም
የማይሆን ነገር ነው። እንደምታስበው ቀላል አደለም እንጂ ቢሆን
ኖሮ እኔ ድሮ ነበረ የማሳስረው እንኳን መረጃ ሳይኖርክ ቢኖርክም
መቼም አይሰሙክም" አለ። ቦስ "ቆይ ታዲያ ምን ተሻለ?" አለና
የለበስውን ቲሽርት እስከሆዱ በብስጭት ገለፀው። አዳምም
"ምንም ምንም ማረግ አንችልም በቃ ቁጭ ብለን መጠበቅ ብቻ"
አለ።
፨ ቦስ ዲና ስልክ ላይ ደወለ። "የደወሉላቸውን ደንበኛ አሁን
ማግኘት አይችሉም እባኮ ትስሽ ቆይተው ይደውሉ" ይላል።
ደጋግሞ ሞከረ ግን የዲናን ድምፅን መስማት አልቻለም።አዳምም
ሄዋንም በተደጋጋሚ ሞከሩት ግን ስልኳ አይስራም። በጣም ተጨነቁ ፣ተንጎራደዱ፣ተቁነጠነጡ ፣አለቀሱ የማይደረስ ቀን
፤የማይነጋ ለሊት ፤የማይሄድ ወንዝ የለምና ስአትም ሰአት እየተካ
የሚጠብቁት ስአት ደረሰ።
፨ምሽት 1:00 አዳም "አሁን በጭራሽ መታገስ አልችልም"
አለና።ዲና መኝታ ቤት ገባና ቁም ሳጥኑን ከፍቶ ወረቀቱን ይዞ
ሳሎን መጣ። ሄዋን ቦስ እና ሰራተኞቹ በጉጉት ምን እንደሚል
ለመስማት ወደ አዳም
አፈጠጡ አዳምም ተስገብግቦ እና ቸኩሎ ከፈተው ጮክ ብሎ
ማንበብ ጀመረ።
፨ "ዛሬ ከእናንተ መለየቴን ሳስበው በጣም ከፍኝ ፤እጅክ አድረጌ
እወዳችዋለሁ። ቦስዬ አንተን ደሞ አፈቅረካለው አንዳንዴ
ከምንወዳቸው ጋራ ለዘላለም የምንኖረ ይመስለኛል። ብዙ
የአብሮነት ጊዜ እንደምናሳልፍ እኔም አስቤው ነበረ። ቦስዬ
የማልዋሽክ ነገረ ቢኖረ ገና አዳምዬ ፎቶክን ሲያሳየኝ ካንተ ጋራ
ጥሩ ፍቅር ውስጥ እንደምገባ ልቤ ነግሮኝ ነበር።እና ሆነ ቀለበት
አሰርክልኝ ያኔ በጣም ደስ ብሎኝ ነበረ ከዛ ደሞ እንዳገባክ
ስትጠይቀኝ ደስ አለኝ። በጣም ተመኝቼ ያልሆነው ነገር ቢኖር
ለዘላለም ሚስትክ የልጆክ እናት አለመሆሄ እና አንተን የማይዘልቅ
ፍቅር ውስጥ መክተቴ ነው። አዳም 'ትክክለኛ ፍቅር አንዴ
ይይዛል' ብሎኛል።ዝረዝሩን አዳምን ጠይቀው"። የሚለውን አዳም
ሲያነበው ሁሉም ፈገግ አሉ። አዳም ማንበቡን ቀጠለ "የኔ ውዶች
ሁሌም ፈገግ በሉልኝ ይህንን ቦታ ስታነብት ፈገግ እንደምትሉ
አውቃለው ። ቦስዬ ልብክ እንደሚሰበር አውቃለው ግን ቦስዬ በቃ
ምን ላድረግ።
፨ አምዳዬ አንተ አንተ ደሞ ከፈጣሪ የተሰጠከኝ ወንድሜ ስጦታዬ
ነክ።የህይወት መምህሬ ነክ ፍቅሬን እንዳውቅ ፈጣሪ የሰጠኝ
አንተንም መጀመሪያ ቀን ሳይክ ብዙ ነገር እንደምታስተምረኝ አውቄ
ነበረ። እና አልተሳሳትኩም አስተምረከኛል።
፨ሄዋንዬ የኔ ጩኸታም የኔ ሳቂታ ሳቂታዬ ሁሌም ሳቂልኝ እሺ
እንዲህ ስልሽ ፈገግ እንደምትይ አውቃለው" ይላል ሄዋን
እውነትም ፈገግ ብላለች አዳም ማንበብን ቀጠለ "ሄዋንዬ አንቺ
ማለት ደሞ ስለፍቅረ እንድማረ ር ምክንያት የሆንሽኝ ነሽ። ማለቴ
ያው ለማለት የፈለኩት ያው እንኳን ታመምሽ እያልኩሽ አደለም።
ከአንቺ ጋራ በጣም የተቀራረብንበትን እና የሳቅንበትን ቀን
ታስታውሽዋለሽ በጋራ ሻውር የወሰድንበትን ቀን እኔ ደስተኛ
ነበርኩ። አንቺም እንደዛው ትውስታሽ በመመለሱ ያከበርንበትን ቀን
፤ ፀጉራችንን ስንሰራራ አዳምና በቦስ ሲያናድዱን ወይ አንቺ ወይ
አኔ መኝታ ቤት ቁጭ ብለን የምናማቸው ነገረ አይ የኔ ነገር
ሚስጥር አወጣው አደል እና ጥሩነትሽን መቼም ቢሆን አረሳውም
አንቺም ልክ እንደ አዳም ስጦታዬ ነሽ አሁን የምሄድበት ስአት
እየደረስ ሰለሆነ ለሰራተኞቻችን የምወዳቸው ስዎች በጋራ ልፅፍ
ተገድጃለሁ።" የሚለው ጋራ አዳም ሲደረስ ሁሉም ፈገግ አሉ።
አዳም ማንበብን ቀጠለ።
፨"እናንተ ማለት ደሞ በቃ ምን ብዬ እንደምገልፆቹ አላውቅም
እናንተን ሰራተኞች ስል በጣም ይከፍኛል በጣም እናንተ ማለት
በቃ የእኛ ተንከባካቢ ፤መጋቢ ፤ሲከፋን አባባይ፤ በቃ ልክ እንደ
እርሱ ግን ስለመተላለፋችን ቆሰለ፤
ስለ በደላችን ደቀቀ፤
የደህንነታችንም ተግሳፅ በእርሱ ላይ ነበር፤
በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን። ኢሳ 53፥5
@Hayitiye 🦋🦋
ለሁለቱም እንሰረላቸው" ብሎ ጠይቆት ነበረ። አዳም ግን አይሆንም
ለፍቅረኛሞች ቀን ነው የማስርላት ብሎ ግግም አለ። ቦስ
ሊጫነው አልፍለገም እና ተወው። ሄዋን ከተመራቂ ተማሪዎች
አንደኛ ጎበዝ እና ቆንጆ ነበረች። ሳቂታ ተጫዋች ፍንድቅድቅም
ጭምር እና ደሞ ተሸላሚ ነበረች።
፨ሁሉም በድሬደዋ ከተማ ላይ ፏ እያሉ ነው። አዳም ፣ዲና፣
ዶክተር፣ ዶክተርሉሊት ፣ቦስ ፣ ሄዋን፣ የዲና ጓደኞች እና
ሰራተኞቹ። ምርጡን ሆቴል አዘግተው ግማሽ ለሊቱን ሲጨፍሩ
አመሹ። የሆነ ሰአት ላይ ቦስ ማይኩን ይዞ መድረክ ላይ ወጣ።
ቦስ "አንዴ አንዴ ትንሽ ጊዜ ስጡኝ" አለ። ሁሉም ምን ሊናገር ነው
ብሎ በጉጉት መጠባበቅ ጀመሩ። ወደ ዲና እያየ "ነይ ወደዚህ"
አለ ፈገግ ብሎ።ዲና በግራ መጋባት ወደ እሱ ቀረበች።
፨ ቦስ ተንበረከከ ዲና አሁንም ግራ እንደገባት ነው።ቦስ እንዲ
አለ። "ዲናዬ አንቺ ማለት ለእኔ በህይወቴ ትልቅ ዋጋ ካላቸው
ስዎች በላይ ቦታ ያለሽ ነሽ። እናማ ባለፈው ህይወታችን ፍቅረኛዬ
ሁኒ ብዬ ጠይቄሽ ጥያቄዬን እንደተቀበልሽኝ አሁን ደማ ሚስቴ
ባለቤቴ ሁኒ ስልሽ ምን እንደምትይኝ ለመስማት ጓግቻለሁ ዲናዬ
ታገቢኛለሽ" አላት ውድ የአልማዝ ቀበት ከፊቷ አቀርበላት። ዲና
እንደፈዘዘች ቀረች። አለቀሰች በጣምምም የደስታ እንባ ከዛ እጆን
ዘረጋችለት ቦስ በቀስታ የቃል ኪዳን ቀለበቱን እጇ ላይ ስካላት።
፨ ሁሉም አጨበጨቡ ሄዋን ሮጣ ሄዳ አቀፈችው እቅፍ ፤ጭምቅ፤
አረገቻት "እንኳን ደስ አለሽ እህቴ ላንቺ በጣም ደስ
ብሎኛል" አለቻት። አዳምም ወደ ዲና መጣና አቅፎ "እንኳን ደስ
አለሽ ዲናዬ እህቴ" አላት። ዲና አዳም እና ሄዋንን እንዲሁም ቦስን
ሁሉንም በጋራ አቅፋ አመሰግናለው አለቻቸው። ከዛ ፕሮግራሙን
ካቆመበት ቀጠሉ።
፨ ሁሉም ዲናን እንኳን ደስ አለሽ እያሉ ሳሟት። የደስታ ምሽት
አሳለፉ ከዛም በተያዘላቸው ክፍል ገብተው ሁሉም ተኙ የደስታ
እንቅልፍ ፤የፌሽታ እንቅልፍ፤ ሁሉም ጭንቀቱን ማራገፍ ባይችል
እንኳን የተወበት ነበር። ምሽቱ በእንቅልፍ አለፈ። ልክ ከንጋቱ
2:30 ሲሆን ሁሉም ሆቴሉ በእስፔሻል ባዘጋጀላቸው ቁርስ ላይ
ታደሙ።
፨ከሰአት በእየግል መኪናቸው ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ። የሄዋን
የምርቃት ዝግጅት እና የዲና ያልታሰበ የቃልኪዳን ቀበት ስነስርአት
በእዚህ መልኩ አበቃ።
ይህ ቀን መቼም ላይረሳ ሁሉም ጭንቅላት ላይ ተፃፈ።
፨ይህ ከሆነ በሳምንቱ። ለሊት 12:35 ላይ የዲና ስልክ ጠራ።
የማታውቀውን ስልክ ቁጥር መገመት ለእሷ ቀላል ነው። ያው
ጌዲዮን ነው አነሳችው ። "ትሰሚኛለሽ እንደምትፏክሪው
የማትፈሪኝ ከሆነ ከ30 ደቂቃ በኋላ ነይ በርሽ ላይ መኪና
እልክልሻለው" አላት። ዲና ብትፍራም "እሺ ጥሩ እመጣለው
ጠብቀኝ" ብላ ስልኩን ዘጋችው። ዲና በጣም ፈራች ስልኳን
እንደያዘች የስልክ ቁጥረ ማውጫው ላይ የባለ ላዳውን ቁጥረ
አውጥታ ደወለች።ብዙ ሳይጠራ አነሳውና እንቅልፍ ባከረደደው
ድምፅ አቤት አላት። ዲና እየተርበተበተች "ስስስስማማ ጌዲዮን
ከ 30 ደቂቃ በኋላ ላግኝሽ አለኝ እኮ" አለችው። "ኣ አምላኬ ምን
ይሳንካል በጣም ደስ ይላል ሰጠብቀው የነበረው ነገር ደረስ።
በጣም አሪፍ እየውልሽ አሁን ምንም መፍራት አይጠበቅብሽም
ለቤተሰቦችሽ ቤተ ክረስቲያን አልያም ደሞ ጓደኛዬ ታማ ብለሽ
ውጪ እና አግኝው" አላት። ባለ ላዳው። ዲና "ፈጣሪዬ ይረዳኝ እሺ
በቃ" አለች። ባለ ላዳውም "አይዞሽ በቃ አሁን ስልኩን ዝጊው
ሁሌም ከጎንሽ እንደሆንኩኝ አስቢ ደሞ የምትወጃቸውን ሰዎች
ከሰቀቀን ለማዳን እንዲሁም አስቢ" አላት። ዲና "እሺ በቃ ልክ
ነክ" አለችና ስልኩን ዘጋችው።
፨ዲና መዘጋጀት ጀመረች። ጊዲዮን ብዙ ጊዜ ሊገላት እንደዛተባት
ስለነገራት ግን ደሞ ዲና "የእኔ ሞት የምወዳቸውን ከአዳነ 99
ጊዜ እሞታለው" ብላ እራሷን አሳምናለች። ዲና ወዲያው ሉክ እና
እስኪብረቶ አውጥታ መፃፍ ጀመረች። ለአዳም ፣ለሄዋን ፣ለቦስ እና
ለሰራተኞቹ። ጌዲዮን ጋረ ሄዳ የምትተርፍ አልመስላትም በህይወት
መጥታ እነሱን የምታገኛቸው አልመስላትም ባወጣችው ሉክ ሙሉ
ፆፈችላቸው። ስትጨርስ ከቤቱ በር ልትወጣ ስትል ዘበኛው
ከክፍሉ ወጥቶ "ምነው በእዚህ ሰአት ዲና በሰላም ነው የት
ልትሄጂ ነው" አላት። ዲና "ጓደኛዬ ችግር ገጥሞት ነው ቤተ
ክርስቲያን ላገኛት ልሄድ ነው" ብላ ወጣችና የውጩን በር
ዘጋችው። ፊቷ ልክ ባይሆግም ዘበኛው ግን በነገረችው ምክንያት
እንዲ የሆነች ነው የመሰለው። ዝም ብሎ ፊቱን ለመታጠብ ሄደ።
ዲና ከበር እንደወጣች ባገኘችው የጊዲዮን መኪና ገባች። ነጠላ
ለብሳ በነጠላዋ ተሸፋፍና ነበር።
፨ከመኪናው ኋላ ገባች ሹፌሩ ያለ ማቋረጥ እየነዳ እያከነፈ
ወሰዳት ዲና በጣም ፈራች። ቀስ ብላ ስልኳን አብረታ የመልክት
መፃፊያ ላይ የአዳምን፣ለቦስ እና የሄዋንን ስልክ አወጣችው
በአንዴ ለሳስቱም እንዲ ብላ መልክት ላከችላቸው። "ይህንን
መልክት ስታዩ በጭራሽ እንዳትደነግጡ እስከ ማታ ካልመጣው
እና ካልደወልኩኝ መኝታ ቤቴ ጠረጴዛ መሳቢያ ውስጥ
ያስቀመጥኩትን ደብዳቤ አለ አንብቡት እወዳችዋለው። ይህንን
መልክት እንዳያችሁት በጭራሽ መኝታ ቤቴ እንዳትገቡ ምክንያቱም
ካያችውት ሞቴን እንዳፋጠናችሁት ቁጠሩት እወዳችዋለው" የሚል
መልክት ላከች። ሹፌሩ እየነዳ ስለነበረ አላያትም። ሄዋን
፣አዳምእና ቦስም ተኝተው መልክቱን አላዩትም። ዲና በጠዋት
ውሀ እረጭታ ስታስነሳቸው እንጂ አስደንጋጭ መልክት
በስልካቸው ስትልክ አይተው አያቁም።
ይቀጥል...
@hayitiye
😘አለሜ ነሽ😘
✍️ እድል
🔥ክፍል 37
"""""
"""""
"""""
"""""
ኡፋፋፋፋፋ አለች እና
መኝታ ቤቷ ገብታ ስለ ባለ ላዳው እያስበች አልጋዋ ላይ ብታርፍም
እንቅልፍ በአይኗ አልዞር አላት በጣም ጨነቃት በጣም።
ስልኳ ጠራ አነሳችው ጌዲዮን ነበረ። ባላት ነገረ ደንግጣ
መንቀጥቀጥ ጀመረች.....
፨ ጊዲዮን በሞገዳዊ ድምፁ "የዛሬ ውሎሽን ወደድሽው?"
አላት።ዲና ተከትሎኝ አይቶኝ ነው ብላ ደነገጠች ። "ምን?" አለች።
"ዛሬ ከሄዋን ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ያሳለፋችውት ቀን እንዴት
ነበር?"። አላት። ዲናም "ያስጨነቀክ አትምሰል አንተ እርጉም
ሁለተኛ ስልኬ ላይ እንዳደውል" አለችው። ጊዲዮን ሳቁን ለቀቀው
ሳቁን ሲጨርስ "ስሚ አንቺ ስሙኒ ስልክሽ ላይ መደወል ከፈለኩኝ
እደውላለው ተግባባን ፍቃዱ የኔ እንጂ ያንቺ አደለም" አለ።ዲና ተናዳ "እኔ ደሞ ስልኬ ላይ ስትደውል የመዝጋት
መብት አለኝ" አለችና ጆሮው ላይ ስልኩን ዘጋችው። ጌዲዮን
ተናደደ በሽቀ በድጋሜ ደወለ አታነሳም አትፈታተኝኝ የሚል የፁሁፍ
በመልክት ላከላት ስልኩን ብሎክ አረገችው። ሲደውል አልሰራለትም
ጌዲዮን አረረ፤ ተከነ።
፨ዲና ለባለ ላዳው ደውላ ያላትን እንደፈፀመች ነገረችው። ባለ
ላዳው "ጥሩ በጣም ጥሩ" አላት።ዲና ከ ባለ ላዳው ጋራ
ካወራቻቸው እና ከተስማሙበት አንዱ ጌዲዮንን እንደታናድደው
እና በተቻላት አቅም ትኩረቱን ሙሉ ለሙሉ እሷ ጋራ እንዲያረግ
ነበር። ባለ ላዳው ለዲና ጊዲዮን በድጋሜ በሌላ ስልክ
ከደወለላት አንስታ እንድታላግጥበት ነገራት እና ተሰናበታት ። ዲና
ስልኩን ዘጋችው። ወዲያው የማታውቀው ስልክ ተደወለላት
"ጌዲዮን" አለችና የፍረሀት ፈገግታ አሳየች። ሄሎ አለች።
፨ጊዲዮን ነበረ "አንቺ አጭር ጠብቄኝ አሳይሻለው" አላት።ዲና
ከት ብላ ስቃ "የት ልጠብቅህ እእእ አንተ አውሬ የማትረባ"
አለችው። ጊዲዮን በንዴት ቀንድ አወጣ
በተንቀጠቀጠ ድምፅ "ስሚ አንቺ ዋጋሽን ነው የምስጥሽ" አላት።
ዲናም "ኧረ ባክህ እየፈራው ነው አታስፈራራኝ" ብላ ስቃ ስልኩን
ጆሮው ላይ ዘግታ ይህኛውንም ስልክ ቁጥር ብሎክ አረገችው።
፨ ዲና ሄዋን ስትስቅ ሰማቻት "ተነስተው ነው እንዴ?" ብላ
ከመኝታ ቤቷ ወጣች። ቦስና ሄዋን የኮሜዲ ፌልም እያዩ ነው።
ዲና "እናንተ ምንድነው አትጠሩኝም እንዴ" አለች። ቦስ
"ከምንቀሰቅስሽ ብለን ነው" አላት። "አዳምስ" የት ነው አለች
ዲና። ሄዋን "ዶክተር ሄዋን የምትባለዋን ታካሚ ሊያሳዩት
ጠርተውት ነው" ብላ ዝርዝሩን ነገረቻት። ዲና "እሺ ጥሩ" አለች
እና ቁጭ አለች።
፨ "አዳምን ጌዲዮን በእኔ ተናዶ የሆነ ነገረ ቢያረገውስ" ብላ
አልተጨነቀችም ምክንያቱም ባለ ላዳው ሁሉንም
እንደሚጠብቃቸው ስለነገራት እና ስላመነችው። ዲናም ፊልሙን
እያየች መሳቅ ጀመረች። ለአንድ ስአት ያክል ከቆዩ በኋላ ስአቱ
አመሻሽ1:20 ሆነ። ፡ሄዋን "ኧረ ለአዲ ደውይ እስቲ ዲዬ"
አለቻተ። ዲና "እሺ" ብላ በፍጥነት ስልኳን አንስታ ደወለች።ጠርቶ
ሊጨርስ ሲል አዳም ስልኩን አነሳው። ሄሎ "አዳምዬ" አለችው።
አዳም ለቅሶ በዘጋው ድምፅ "ወዬ" አላት። ዲና ተደናግጣ "ምን
ሆነክ ነው" አለችው።"አትጠይቂኝ ዲናዬ አትጠይቂኝ በር ላይ ነኝ
በቃ መጣው" ብሎ ስልኩን ዘጋው።
፨ሄዋን በዲና የፊት መቀየር ተገርማ እና ደንግጣ "ምን ተፈጠረ"
አለቻት። ዲና "እኔ እጃ እስቲ መጥቻለው በር ላይ ነኝ ብሎኛል
ምን እንደተፈጠረ ከእሱ እንሰማለን ግን ደምፁ ልክ
አደለም"አለች። ሄዋን ከተቀመጠችበት በፍጥነት ብድግ ብላ ወደ
በር ወጣች። አዳም ፍዝዝ ብሎ ሲመጣ በር ላይ ተገጣጠሙ
"አዲ ምን ሆንክብኝ ውዴ" አለችው ጉንጮቹን በሁለት መዳፏ ይዛ
አይን አይኑን እያየች። "እኔ ደና ነኝ አትጨናነቂ" አለና እጃን ይዞ
ወደቤት ገባ።
፨ ቦስና ዲና ሲያዩት ተደናገጡ ቦስ "ምን ሆነካል ወዳጄ" አለው
ዲናም ቦስን ተከትላ "ምነው ችግር አለ እንዴ? አዳምዬ"
አለችው። ሄዋን ጉትታ ሶፋው ላይ አስቀመጠችው። አዳም ሁለት
መዳፏቹን አይኖቹ ላይ አሳርፎ ሰው ሲሞት በአይኔ አየው። "ዛሬ ዛሬ
ዛሬ ዛሬ በጣም ካዘንኩባቸው ቀኖች ዋናው ነው" አለ። ሁሉም
ከቆሙበት መሬት ሶፋው ላይ ተቀመጡ። ሄዋን አጠገብ ተቀምጣ
እጁን ያዘችው። አዳም እያለቀስ ወሬውን ቀጠለ። "ዶክተር ስለ
ሄዋን ሲያወሩ ስምቼ ነበር። የካንሰር በሽታ ስለያዛት አትተርፍም
ሲሉ የኔ ሄዋን መስልላኝ እራሴን ስቼ ነበረ።ከዛም ከወደኩበት
እስክነቃ ጠብቀው '''ያንተ ሄዋን ሳትሆን ሊላ ሄዋን ናት''' አሉኝ።
የመዳን ትንሽ ተስፋ አላትም ሲሉ ነበረ።ከዛ ዶክተርን ሄዋን
የምትባለዋን ታካሚ ላያት እፈልጋለው ብያቸው ነበረ። ዛሬ ተኝቼ
ስልክ ደወሉልኝ እና '''ሄዋንን ማየት ከፈልክ አሁን ና''' አሉኝ።
እኔም እሺ ብዬ ሄድኩ ሄዋንን አገኘዋት በፊቷ ላይ ምንም ፀጉር
የለም በሽታው አርግፎታል። ዝም ብዬ አየዋት የሆነ ቦታ
የማውቃት መሰለኝ"።
፨ ኡፋፋፋ ካለ በኋላ ወሬውን ቀጠለ "ለማስታወስ ብዙ ከፈጀብኝ
በኋላ አስታወስኳት ማደጊያ ቤት እያለው እሷን አውቃት እንደ
ነበር ታወስኝ አብሮ አደጌ ነበረች። ከስታና ገርጥታ ማንነቷ
ጠፍቶል ስታየኝ እሷም አወቀችኝ መሰለኝ ፈገግ ብላ አአአአአ አ
ዳ ም ብላ ፈገግ እንዳለች ማቃስት እና እግሮቿን ማላፋት
ጀመረች። ከዛም በቃ አፏን ከፍታ አይኗን አፍጥጣ ቀረች።
ደነገጥኩኝ በጣም ደነገጥኩኝ ዶክተሩ አይንና አፏን አሰተካከላት
ልቤ ተስበረ። አለቀስኩ በጣም አለቀስኩ ግን በቃ ልመልሳት
አልቻልኩ"።
፨ የለቅሶ ሲጋ ወሬውን አቋረጠው እና ወደ ወሬው ተመለሰ "እዛ
ሀኪም ቤትም እግሬ ለመቆም አልቻለም እየሮጥኩኝ መኪናዬን
አስነሽቼ ወጣው። ፈጣሪን ለምን እስካሁን በጤና እያለች
ሳታገናኘን እስትንፋሷ ሊወጣ ሲል አገናኘከኝ ብዬ ጮኽኩበት ግን
አልስማኝም በዙሪያዬ ያሉ ስዎች ሲጎዱ ለምን ተመልካች አዳረገኝ
አልገባኝም" አለና። ተንሰቀሰቀ ሁሉም አለቀሱ ማንም ማንንም
አላባበለም። በአጠቃላይ የሄዋን ለቅሶ እነ አዳም ቤት መሰለ።
፨ ስራተኖቹም የአዳምን ንግግረ እየስሙ ስለነበር አለቀሱ።
ረዥም ስአት አለቀሱ። ሁሉም በእየተቀመጡበት ተኙ ሰራተኞቹ
ሁሉንም ጋቢ ደረቡላቸው። በነጋታው የሄዋን የቀብር ስነስረአት ላይ
ሁሉም ተገኝተው ቀበሯት።
፨ "ጊዜ መሄዱን አያቋረጥም እኛም በእሱ ፍጥነት መጓዛችን ግድ
ነው" አለ አዳም ። ቦስም ከአዳም ቀጠል አድርጎ "አሁን ማን
ያምናል እስቲ ያን ሁሉ ጊዜ አልፎ ዛሬ አሁን የሄዋን የምርቃት ቀን
ነው ቢባል" አለ አይነት ጊዜ ሄዋን በአንድ አመት የዩንቨርስቲ
ቆይታዋ በ6 ወር እና በእየ መሀሉ ለበአል ብትመጣም ናፍቆቱ
አንገላቷቸው ነበር። ዲናና ባለ ታክሲው ጊዲዮንን ማብሸቁን
ተያይዘውታል።
ሄዋን ዛሬ የምርቃት ቀኖ እንደመሆኑ አዳም በትዛዝ ባሰፋላት
ቀሚስ አሽብርቃለች ዲናም እንደዛው ቦስና አዳምም ሙሽራ
መስለዋል። ኬብሮን የሜካፕ ስራዋን ለሁሉም ተጠባባቸዋች።
የሚያውቋቸው ስዎች በሙሉ ተገኝተዋል የምርቃት ስነስርዓቱ
አዳራሽ በአስመራቂ ቤተስቦች በአስመራቂ እና በተመራቂ ባለ
ስልጣናት መምህራን ተሞልቷል።
፨ሁሉም ደስተኞች ናቸው። በጣም ደስተኞች። ቦስ ዲና በስልክ
ከባለ ላዳው ጋረ ስታወራ ቅናቱን ተያይዞታል። ሁሌም "ማነው?"
ይላል "መቼም ሴት አትሆንምም። ይላል ግን ዛሬ የቃል ኪዳን
ቀበት ሊያረግላት ወስኖ ቀለበት ይዟል።ቦስ አዳምን "አብረን
ጉልባን
ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ነው፡፡
በጸሎተ ሐሙስ በቤት ውስጥ ከሚፈጸሙ ተግባራት አንዱ ጉልባን ማዘጋጀት ነው፡፡ ጉልባን እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ሲወጡ በችኮላ መጓዛቸውን የምናስታውስበት ከእስራኤላውያን የመጣ ትውፊታዊ ሥርዓት ነው፡፡
በአገራችን ኢትዮጵያ አብዛኞቹ የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ይህ ሥርዓት ዛሬም በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዘንድ ይከበራል፡፡
ጉልባን እስራኤላውያን ከባርነት በወጡ ጊዜ አቡክተው፣ ጋግረው መብላት አለመቻላቸውን ያስታውሰናል፡፡ በወቅቱ ያልቦካውን ሊጥ እየጋገሩ ቂጣ መመገብ ፤ ንፍሮ ቀቅለው ስንቅ መያዝ የመንገድ ተግባራቸው ነበርና፡፡
ይህን ታሪክ ለማሰብም በሰሙነ ሕማማት በተለይም በጸሎተ ሐሙስ ቂጣና ጉልባን ይዘጋጃል፡፡ በጸሎተ ሐሙስ የሚዘጋጀው ጉልባንና ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል፡፡ ይኸውም ጨው ውኃ እንደሚያስጠማ ዅሉ፣ ጌታችንም በመከራው ወቅት ውኃ መጠማቱን ለማስታወስ ነው፡፡
Join Join Join
@Hayitiye 🦋
🌿🌿🌿🌼🌼🌼🌿🌿🌿🌼🌼🌼
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
"ጌታዬ እጠበኝ"
እግሮቼ የዛሉ ብዙ የተጓዝኩኝ
በቀኝ በግራ ስል መድረሻ ያጣሁኝ
ከጠባቧ መንገድ መርጬ ሰፊውን
በሰፊው ጎዳና ላይ እታች ስኳትን
ንጽሐ ሰውነቴን በበደል ያቆሸኩ
ንጽሐ ልቦናዬን በክፋት ያሳደፍኩ
በኃጥያት ቀንበር ሸክሜ ያጎበጠኝ
ውስጤ ክፋት ሞልቶት ጉልበቴ የከዳኝ
በነፍስ በስጋዬም እጅግ ደካማ ነኝ
ምህረትን የምሻ ተግባር የጎደለኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ልክ እንደ መጻጉ እንደ ምስኪኑ ሰው
ባህር ውስጥ ሚከተው ዘመድ እንደሌለው
መዳንን ትሻለክ ብለክ የጠየከው
በባህር ውስጥ ሚከት የለኝም መልካም ሰው
ብሎ እንደመለሰው
አይደለሁም እኔ አልጋ ላይ የቀረው
አካሌ የከዳኝ የቆምኩ የመሰለኝ
አልጋህን ተሸክመህ ሂድም እንዳትለኝ
በኃጢያት በሽታ መታመሜን ማላምን
መድኅኒት እንዳላገኝ ህመሜን ምሸሽግ በሽተኛ ሰው ነኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንደ ባለሽቶዋ መግደላዊት ማርያም
አንተ ባረፍክበት ማንም ባይጠራትም
ከእግሮችህ ስር ወድቃ ሽቶዋን አፍስሳ
በእንባዋ አጥባ በፀጉራ አብሳ
ከኃጢያት እስራት ስትፈልግ መላቀቅ
በንሰሃ ልንቦናዋ ምህረትን ስጠይቅ
እንደ ሰዎች ሳይሆን ልቧን ተመልክተክ
ዳግም እንዳበድዪ ብለህ እንደማርካትክ
አይደለሁም እኔ ከእግር ስር የምወድቅ
ሽቶን የማላፈስ እንባዬም ነው ደረቅ
ለታይታ የምኖር ሰዎች ምን ይሉኛል ምል
በኃጥያት ቆሽሼ ንጹህ ሰው ስመስል
የምህረት ቀኔን በከንቱ ማሳልፍ
ልበ ደንዳና ነኝ ምግባሬም የሰንፍ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ቀድመህ እንደነገርከው ለሐዋርያው ጴጥሮስ
ሥስቴ እንደሚክድህ ፍርሃት በልቡ ሲነግስ
አላቀውም ብሎ ዶሮ እስኪጮህ ድረስ
የንሰሃው ዶሮ ለጸጸት ሲያነቃው
ፊትህን አዙረህ በትዝብት ስታየው
መበደሉን ገብቶት ህሊናውን ሊወቅስ
የንሰሀን እንባ ከአይኖቹ ቢያፈስ
ምህረትን ሲሻ መጸጸቱን አይተክ
በደሉን እረስተክ ንስሀውን ተቀበልክ
እኔ ግን ደካማው በጊዜዬ ያልነቃው
ኃጥያቴን እያወኩ ንስሃ ያልገባው
የንሰሃው ዶሮ ሰልሶ ቢጮህም
ፊትህም ወደኔ በምህረት ቢዞርም
ኅሊናዬ ገብቶት ልቤ አልደነገጠም
የንስሃም እንባም ከዐይኖቼ አሎጣም
።።።።።።።።።።።።።።።፡።፡።።።።።።።
እናም ጌታዬ ሆይ እኔ ምለምንክ
በኃጥያት ላደፍኩኝ እንዲሆነኝ ምህረትክ
በበደል ዳክሬ ቆሽሻለውና
ሆሳዕና ጌታ ፈጥነህ ወደኔና
ደንዳናውን ልቤን እንድታለሰልሰው
የልቤን መዝጊያ በር በፍቅርህ ስበረው
በኃጥያት ሸክም የዛለ አካሌን
ጉልበቴ ሆነከኝ ልስበረው ቀንበሬን
እንደ መጻጉ አልጋን ባልሸከም
የኃጥያት እግሬ ነጽቶ በንጽሐ እድቆም
ከኃጥያት ልንፃ በፍቅርህ እጠበኝ
ከበረዶም ይልቅ በምህረትህ አንፃኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
#መልካም ቀን
ለመቀላቀል 👉
@Hayitiye
🍂☝አንድ ሰው ነበረ 😒🍂🍂
ሲያሻው መጥቶ ከኔ እዉቅና የፈጠረ
ከመንገዴ ቆሞ አይኔን በእሱ ያጠረ
አላስኬድም ያለኝ አንድ ሰው ነበረ
እናም ልቤ ፈርቶ ብዙ ተፈተነ
ከሱ የነበረው ከእኔ ተወጠነ
ግና...
ግና ረፍዶ ነበር
ከኔ የሰፈረው በንዴት ሲቀዬር
ሲያሻው ጥሎኝ ሊሄድ ልቤን ሲያንገራግር
ዉስጡን ደበቀና ፊቱን ከእኔ ሲያዞር
የእኔን ጉስቁልና ንቆ ሲንጠባረር
ዋጀሁት ዘመንን ትዝ አለኝ ሲጀመር
እንዲህ ያደረገኝ አሁንም ያዬለኝ
ሁሉንም አስጥሎ ከአለም ያስመነነኝ
ነበረ የምለው አሁንና ነገን ጥሎ የማይጥለኝ
ሀዘን ሲቃ ደስታ እያቀናበረ
ነገንም የሚኖር ላይቀር እየቀረ
ትናንትም ዛሬንም ነገንም የኖረ
አንድ ሰው ነበረ....
ተስፋን ያሳዘለኝ በፊት በኋላዬ
ቀላቅሎ ስሜቴን ልቤን ያሰቃዬ
እጅ እግሬን አሳስሮ ልክ እንደ ግዛቱ
ሲያሻው የሚፈታኝ ሚያስረኝ እንደ ከንቱ
ትናንትም ዛሬንም ነገም እየጣረ
ዉስጤን አደንዝዞ ምንም ያልቀየረ
ጠብቂ ... እያለ ነገ እየቀጠረ
መኖሬን በእሱ ዉስጥ ገሎ የቀበረ
አንድ ሰው ነበረ...
✍ እድል 🌹@Marsilas_23
@Hayitiye
ባላት ነገር ተስማማች።
፨ስራቸውን ለመጀመር ዝግጁ ሲሆን በድጋሜ እንደሚጠራት እና
ማንም ስለ ሁለታችን ግንኑነት ማወቅ እንደሊለበት ተሳስታ እንኳን
ካወራች ነገሩ ብልሽትሽቱ እንደሚወጣ ስለ ትብብሯ እና ስለ
መልካም ስራዋ ደጋግሞ የምስጋና ቃል አዝንቦላት እቤቷ አድረሷት
ትንሽ ስልክም ስጥቷት አዲስ ነገር ካለ በሰጣት ስልክ
እንድትደውል ነግሯት ተለያዩ።
፨ዲና 30 ደቂቃዎችን አስቆጥራ ቤት ተመለሰች ሁሉም እንደተኙ
ነው እና ዘበኛውም የግቢ ፅዳት ላይ ነው።በቀስታ ቤት ገባች።
ሁሉም ሀገር ሰላም ብለው ተኝተዋል። ኡፋፋፋፋፋ አለች እና
መኝታ ቤቷ ገብታ ስለ ባለ ላዳው እያስበች አልጋዋ ላይ ብታርፍም
እንቅልፍ በአይኗ አልዞር አላት በጣም ጨነቃት በጣም።
ስልኳ ጠራ አነሳችው ጌዲዮን ነበረ። ባላት ነገረ ደንግጣ
መንቀጥቀጥ ጀመረች።
ይቀጥላል...
@Hayitiye
@Hayitiye
አደረሳቸው። ዘበኛው እንዲከፍትላቸው ክላክስ አሰሙ።
ከፈተላቸው። ሄዋን መስኮቱን ዝቅ አድርጋ ስላም አንተ ስውዬ
አለክልኝ አለችው። ዘበኛው ግራ ገባው ምክንያቱም ሄዋን
ትውስታዋን ከማጣቷ በፊት ነበር እንዲህ የምትለው ዘበኛውን
የቀልድ ለማናደድ ነው ምክንያቱም አንተ ሰውዬ ስትለው
ስለሚናደድ። ከመኪና ወርደው ወደ ቤት ለመግባት አንኳኩ ሁሉም
ስራተኞች ተክተልትለው ወጡ። ሄዋን እንዳየቻቸው የእኔ ውዶች ኑ
እስቲ እቀፋኝ ኑ እናንተን በመርሳቴ መቼም እራሴን ይቅር
አልለውም አለች። ሁሉም ሄዋን እንዳስታወሰች ከንግግሯ
ተረድተው እልልታቸውን አቀለጡት ዘበኛው ምን ተገኘ ብሎ ሮጦ
መጣ።ምንድነው አለ አንደኛዋ ሰራተኛ ሄዋኔ አስታወስች አለች
ከዛማ በቃ ሁሉም በደስታ አበዱ የደስታ እብደት ዲና ቦስ አዳም
ሄዋን ስራተኞቹ ምግብ በጋራ በሉ ተሳሳቁ ተቀላለዱ ተሳሳቁ ቤቱ
ፌሽታ በፌሽታ ሆነ የሳቅ ቤት የደስታ ቤት ሆነ።
፨አመሻሽ ላይ ሁሉም የደስታ እንቅልፍ አሽለቡ። ጠዋት ሄዋን
ከዲና ቀድማ ተነስታ ሳሎን መዝሙር ከፍታ እየሰማች ነበር። ዲና
ሄዋንን ስታያት በጣም ደስ አላት። "እህቴ እንዴት አደርሽ?"
አለቻት። ሄዋንም "አምላክ ይመስገን ነይ እዚህ ቁጭ በይ ወይስ
ውሀ ልትርጫቸው ነው?"። አለቻት ዲና "እንዴ እሱን
ታስታውሻለሽ እንዴ?" አለች። ሄዋን "እንዴ አዎ" ብላ ሳቀች። ሳቋ
ቦስና አዳምን ቀስቀሳቸው ሁለቱም ከክፍላቸው ወጥተው "ምን
ተገኘ ምን ሆናቹ" እያሉ መጡ። ዲና "ኧረ ምንም እንዲሁ ነው
ነገሩ የሚያስቅ ነገር ሆኖ አደለም እንዲው ልጅቷ ሳቅ
የሚቀድማት ስለሆነች እንጂ" አለቻቸው።
፨ሄዋን "መጀመሪያ እንዴት አደራቹ አይባልም?እንዴ? ሰዎች
አለች። በጩከት አነጋገር። ቦስም ፈገግ ብሎ "መቼ ፋታ
ስጠሽን?" አላት።ሄዋን በድጋሜ መብረቃዊ ሳቆን ለቀቀችው
አዳም "እሺ ለማንኛውም ደና አደራቹ?" አለ። ሶስቱም
እንደተመካከረ ሰው "ይመስገን እንዴት አደርክ?" አሉት። ሄዋን
አሁንም ሳቀች። ዲና "ሆሆ በሉ ምንም አትናገሩ ስዎች እኔ
በሳቀች ቁጥር እንደ አዲስ ቆሌዬ እየተገፈፈ ነው"። አለችና
ሶፋው ላይ ቁጭ አለች። ሄዋን በድጋሜ በስሱ ሳቀች። ዲና እነ
ቦስን "በሉ እናንተ ወረኞች እህቴ የሱናሜ ጦርነት፤ መድፍ እና
መትርየስ ቢጮህ አሰሙም ነበር በሉ ሂዱ ልብስ ቀይሩ" አለች።
አዳም ቦስና ሄዋን በህብረት ሳቁ ስራተኞችም "እንዴት አደራቹ?"
ብለው በእጆቻቸው አንደኛዋ የቁርስ ሰሀን ሌላኛዋ ብርጭቆ እና
ስኒ ይዘው መጡና የምግብ ጠረጴዛው ላይ እያስቀመጡ "በሉ
ቁርስ ደርሷል ተዘጋጁ" አሏቸው ከዛም ሁሉም ወደየ መኝታ
ቤታቸው ሄደው ተጣጥበው እና ልብስ ቀይረው መጡ።
፨ሁሉም በአንድ ላይ ተሰብስበው ቁርሳቸውን በሉ በደስታ እና
በፍቅር በልተው ሲጨርሱ ቲቪ እያዩ እያወሩ ሰአቱ የምሳ ሰአት
ደረስ ሁሉም ምሳ መብላት አላሰኘንም ብለው ሳይበሉ ቀሩ። ሄዋን
እንቅልፌ መጣ ብላ ተኛች ከቆይታ በኋላ ቦስም እንቅልፌ መጣ
ብሎ ተከተላት። ስራተኖችም ወደእየ ስራቸው ተመለሱ። አዳም
እና ዲና ቀሩ አዳም "ዲናዬ በቃ እኛም ወደ መኝታ ቤታችን
ገብተን እንረፍ " አለና ተነስቶ ወደ መኝታ ቤቱ ሄደ። ዲናም
ሄደች። አዳም ሊተኛ ሲል የሄዋንን የቁስል ፋሻ አለመቀየሩን
አስታውሶ ወደ ሄዋን ክፍል ሄደ ሲያንኳኳ ሄዋን ተኝታ ነበር። እና
በሩን ሲከፍተው አልሰማችም ቀስ ብሎ ሄዶ ከክፍሉ የቁስል
ማጠብያዎችን ይዞ መጣ። የሄዋን አልጋ ጫፍ ላይ ቁጭ ብሎ
በቀስታ ሄዋኔ፤ ሄዋንዬ፤ የኔ ስስት ፤ተነሽ አንዴ ቁስልሽን ላፅዳልሽ
አላት። ሄዋን ፈገግ ብላ ተነስታ ተመቻችታ ተቀምጣ እጇን
ስጠችው።አዳምም ፈገግ ብሎ እያያት እጇን ሳማት እና "አንቺ
ምኔ እንደሆንሽ ታውቄያለሽ?" አላት ሄዋን "እ ንገረኝ እስቲ ምንክ
ነኝ?" አለችው። አዳም የእጇን ፋሻ በቀስታ አንስታ ቁስሏን
እያፀዳላት "አለሜ ነሽ አንቺ አንቺ ማለት ለእኔ አለሜ ነሽ ሄዋኔ
አለም ላይ ብዙ ሀዘን ብዙ ደስታ ጥቂት ሀዘን ጥቂት ፌሽታ በየጊዜው የምናሳልፍበት ብዙ ነገር የምናይበት መድረክ ነው ግን
ደሞ አለም ታሳሳናለች ምክንያቱም ህይወት ነው አንቺም ለእኔ
እንደዛው ነሽ።" አላት ሄዋን በስስት አይን አትኩራ እያየችው "አንተ
ደሞ ለእኔ እስትንፋሴ ነክ ትንፋሻችን ሲቋረጥ ሁሉም ነገር ቀጥ
ይላል ከእዛን በኋላ ህይወት የለም አንተም ለእኔ እንደዛ ነክ።
በህይወቴ ያለክ ትርጉም ይህ ነው" አለችው። አዳም ፋሻውን
ጠቅልሎ ጨረስ። ሄዋን አዳምን አቀፈችው እሱም አቀፋት።
፨ሄዋን ፈገግ ብላ "ና እዚህ ላይ ውጣ" አለችው አልጋው ላይ
እንዲወጣ እየተጠጋችለት "እሺ" ብሎ አልጋው ላይ ወጣ።ከዛ
ተቃቅፈው ተኑ። ዲና መኝታ ቤቷ ገብታ አልተኛችም የቀን
ውሏቸውን በምትፅፍበት ደብተር የሄዋንን ከትውስታ መንቃትን እና
ደስተኝነታቸውን የታሪኩ መደምደሚያ ለማረግ ወስና ፃፋ
ጨረስችው። መፅሀፉን ለማሳተም እና ለማስገምገም ወሰነች።
፨ጓደኛዋ ጋር ደወለች። ሩት ትባላለች ደራሲ ናት "ሄሎ"
አለች።"ሄሎ ሩት?""አለች ዲና።ሩትም "አቤት ዲና አንቺ
አልሞትሽም እንዴ?" አለችና ሳቀች። ዲናም ስቃ "ባክሽ ዝም በይ
ሙቺ እሺ" አለች እና ስለ ደህንነታቸው አጥብቀው ከተጠያየቁ
በኋላ ዲና "እኔ እምልሽ እሩትዬ የመጀመሪያ መፅሀፍሽን
ስታሳትሚ የገመገመልሽ ሰውዬ" አለቻች እሩትም "ሊቁ ጻውሎስ
ናቸዋ ምነው ለምን ፈግሽው?" አለቻት "አይ ምንም የሆነ ጓደኛዬ
ፈልጓቸው ነው" አለቻት "እ እንደዛ ነው በቃ እሺ" ብላ አድራሻና
ስልካቸውን ሰጠቻት። ዲና አመስግናት እና የምትኖርበት ድሬደዋ
እንዴት እንደሆነች ጠይቃት ጓደኛዋም ጥሩ እንደሆነ ነግራት።
ተለያዩ።
፨ ዲና ወዲያው ስልኩን እንደዘጋችው ስልክ ተደወለላት
ኮልታፋው ሰውዬ ነበር። "ሄሎ አሁኑኑ ነይ በር ላይ ነኝ" ብሎ
ስለኩን ዘጋው። ዲና ከመኝታ ክፍሏ ተሯሩጣ ወጥታ የግቢው በረ
ላይ ደረስች። ዘበኛው አበባዎችን እየኮተኮተ አላያትም ፈጠን ብላ
ወጣች። ስትወጣ ማንም የለም ካለ ላዳ መኪና በቀር መስታወቱን
ዝቅ አርጎ "ነነነነይ ግቢ" አላት። ዲና ፈጠን ብላ ገባች።ጥቂት
ዝም ከተባባሉ በኋላ መኪናውን አስነስቶ ነዳው ዲና ደንግጣ
"ወዴት ነው?" አለች። "አይዞሽ ብዙ አላቆይሽም" አለና መኪና
ማደሪያ ቦታ ወሰዳት እና መኪናውን አቁሞ "ስሚ አሁን የምልሽን
አዳዳዳዳምጪኝኝኝ " አለና ፈገግ ብሎ ሳይተባተብ "እኔ እንደሆንኩ
እንድታምኒ ነው እንጂ ተብታባ አደለሁም ሰው እንዳያውቀኝ ነው"
አለ። ዲና ደንግጣ "እሺ ምን ፈለክ እንዴት ነው ለምወዳቸውን
ሰዎች ካሉበት መከራ የማወጣቸው" አለችው።
፨ ባለ ላዳው "የሚያስፈልገውን ሁሉ ልከፍይ ዝግጁ ነሽ?" አላት
ዲና ያለ ማቅማማት "አዎ በደንብ ነዋ" አለች።ባለ ላዳው "ጥሩ
በጣም ጥሩ እየውልሽ እኔ የጠበቃ ኤርሚያስ ጓደኛ ነኝ ወንድሜ
ነው ማለት ይቻላል። እና እኔ የወንድሜን እና የዘሮቼን ገዳይ
በቀል መወጣት እፍልጋለው። አንቺም የምትወጃቸውን ስዎች
ስቃይ ለማቆረጥ ትፍልጊያለሽ ስለእዚህ ምን እናደርግ መሰለሽ"
ብሎ እቅዱን ነገራት። ዲና በጣም ብትፈራም ስለ እርሷ
ልትጨነቅ እና ልፈራ እንደማይገባት ለእራሷ ነግራ አሳመነችው
😘አለሜ ነሽ😘
✍ እድል
🔥ክፍል36
""""
""""
""""
""""
ከሄዋን ክፍል ውስጥ የመስታወት ስብርባሪ ድምፅ ተሰማ....ሁሉም በድንጋጤ እየተርበደበዱ ድምፁ ወደተሰማበት እየከነፉ በረሩ...አዳም የሚያየውን ማመን አቃተው የልብ ትርታው ለተወሰኑ ሰከንዶች መምታቷን አቆመች አለሙ በደም ተጨማልቃ ከመስኮቱ በተቃራና ተዘርራለች...ከሰውነቷ የሚፈሰው ትኩስ ደም ወለሉ ላይ ተዝረክርኳል....አዳም ከድንዛዜው እንደምንም ለመላቀቅ እየሞከረ ሄዋን ብሎ ጮኽ....ዲናም የምታየውን ማመን አልቻለችም መሬት ላይ ተዘርራ የምታያት ከደቂቃዎች በፊት ተነጋግረው የነበረችው ፍልቅልቋ ድምጿ ከጣራ በላይ የሚሰማው ደመ ግቡዋ ሄዋን አልመስልሽ አለቻት ገረጣችባት...ቦስም ቢሆን በድንጋጤ ክው ቢልም እንደዲናና አዳም ደርቆ አልቀረም ሄዋንን አፋፍሶ ወደ ሆስፒታል ይዟት ነጎደ...... "ነርስ ከዚህ በሁዋላ የሄዋን በህይወት የመኖር እድሏ በከፍተኛ ደረጃ የተመናመነ ነው...ህመሙን ማሸነፍ አልቻለችም ይባስ ብሎ ይሄም ተጨመረባት....ሄዋን ከዚህ በሁዋላ በሂወት የምትቆየው ለጥቂት ጊዚያት ነው ግፉ ቢል የአንድ ሳምንት ጊዜ ነው" አሉ ዶክተሩ ፊታቸው ላይ የሚነበበውን የሀዘን ስሜት መደበቅ አቅቷቸው....."ዶክተር ይሄን ኬዝ ልክ እንደቅርብ ሰዎ ይዘው ልዩ ክትትል ሲያደርጉላት እንደነበረ አውቃለሁ መቼም ለዶክተር ታካሚው ሳይሽር ስቀር የሚፈጥረውን ስሜት አይደለም በሞያው ላይ ያለውት እኔ ቀርቶ ስለሞያው ምንም የማያውቀውም ሰው የሚረዳው ነው...ለማንኛውም ፈጣሪ ጥንካሬው ያችሮት"አለች ነርሷ ከዶክተሩ የህክምናውን ፋይል ተቀብላ መድሀኒቶችንንና የህክምና ፋይል የምታስቀምጥበት የምትገፋው ጋሪ ላይ እየመለሰች...."አሜን ነርስ"ብለው ሲጠራ የነበረውን ስልካቸውን አንስተው ወደ አንዱ ጥግ ሄዱ...
ወደ ዶክተሩ ሲሄድ የነበረው አዳም ንግግራቸው ጆሮው ላይ ተንቆረቆረ... የሚሰማውን ማመን አልቻለም ነገረ አለሙ ጨለመበት ደጋግሞ የአለሙ መሞትን በአይነ ህሊናው ሳለው መንታ መንታ ሆነው ከአይኑ ሲፈሱ የነበሩት እንቧዎቹን ለመጠራረግ ፉታ ሳያገኝ ነገረ እይታው በጭለማ ተቀየረ ወድያዋ ወደ መሬት ተዘረረ...
፨አዳም ሲወድቅ የሰሙት ዶክተር ስልካቸውን ጥለው ፈጥነው
ወደ በሩ ሄዱ። አዳም ወድቆል ሮጥ ብለው ከክፈላቸው ውሀ
አምጥተው ፊቱን እረጩት። ከዛ ፊቱን መታ መታ ሲያረጉት
ደቂቃዎች ተቆጥረው ነቃ ። ፍዝዝዝ እንዳለ በጭልምልም
አስተያየት ዶክተርን እያያቸው። "ዶክተር ምንድነው ያሉት ? ሄዋኔ
ልትሞትብኝ ነው? አለ። ዶክተር ወዲያው አዳም በስልክ ያወሩትን
ነገር በመስማቱ እንዲህ እንደሆነ አወቁ። "አይ አይ የተሳሳተ
መረጃ ነው የሰማከው አዳም እባክህ ተረጋጋ" አሉት።
፨ አዳም እንባውን እያጎረፈ "ተዉ ተዉ ዶክተር እባካቹ
አታፅናኑኝ፤ ልዘንና ልበድበት፤ አብጄ ምንም አላስታውስ አለና
ጮከ። ዶክተር "እውነት ነው የነገርኩክ አዳም እኔ በጭራሽ
አልዋሸውክም እንደዚህ አትሁን እያወራው የነበረው ስለ ሊላኛዋ
ታካሚ ነው። ሄዋን የምትባል ሊላ ታካሚ አለች። ከፈለክ ላሳይክ
እችላለው" አሉት። አዳም እያለቀስ "አትዋሹኝ እባኮት"
አለ።ዶክተር "እውነት አልኩክ እኮ ና ላሳይክ ከፈለክ" አሉት።
፨አዳም የዶክተርን ክንድ አጥብቆ ይዞ "እና ለምንድን ነው ታዲያ
የጠሩኝ?" አላቸው። ዶክተር ፈገግ ብለው "እንኳን ደስ አለክ
ለማለት እና ሄዋን ስትወድቅ እጆን የመስታወቱ ስንጣቄው
ስለቆረጣት ቁስሏ ኢንፌክሽን እንዳይፈጥር መዳኒት ገዝቼልላታው
፤እንዳባትክ እየኝ አዳም የተቻለኝን ሁሉ አረግላችዋለው" አሉት።
አዳም አሁን ደህና ሆነ ከዛም እራሱን ታዘበ "የሰው ነገር ግን
ሲገርም በዙሪያችን ያሉትን ስዎች ከሁሉም አስበልጠን ማየታችን"
አለ።በውስጡ ከዛ "እሺ አሳዩኝ" አላቻው።
፨ ዶክተር የቢሮ መቀመጫ ወንበራቸው ላይ ተቀመጡና አዳም
የእንግዳ( የታካሚ) ወንበር መቀመጫ ጋር እንዲቀመጥ
በእጃቸው ጠቆሙት።አዳም በአይኑ እሺታውን ገልፆላቸው
ተቀመጠ። ዶክተርም ሁለት ፈሳሽ የሽሮፕ ይዘት ያላቸው መዳኒቶች
ከመሳቢያው አውጥቶ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጡ። ተለቅ ያለውን
ወደ እሱ በአውራ ጣታቸው ገፋ እያረጉ "ይሄ የቁስሉ ማጠቢያ
ነው፤በቀስታ በጥጥ ታፀዳዋለክ አሉት።በመቀጠል ሁለተኛውን እና
በጣም ትንሽ ይዘት ያለውን ብልቃጥ በተመሳሳይ መንገድ
በአውራ ጣታቸው ገፋ አርገው "ይህንን ደሞ
ትቀባላታለክ።በጥንቃቄ በእየ 6 ሰአቱ" አሉት። "እሺ ጥሩ በጣም
አመሰግናለው" አላቸው። "እሺ አዳም በል ብዙ ያዝኩክ አደል
መሄድ ትችላለክ" አሉት። አዳም "እሺ ዶክተር አመሰግናለው"።
አለ ዶክተር የአዳምን እጅ ለመጨበጥ እየዘረጉ ከእዚህ በኋላ
አባትክ ነኝ ፤አባቴ ብለክ ልትጠራኝ ትችላለክ አንተም ልጄ ነክ
ልጄ ብዬ እጠራካለው" አሉት። አዳም በደስታ ወንበሩን በፍጥነት
ዞሮ ወደ ዶክተር ሄዶ አቀፋቸው። ዶክተርም አቀፉቸው
አመሰገናቸው "አመሰግናለው አባቴ ብሎ ፈገግ" አለ።
፨ዶክተርም ጮክ ብለው ሳቁ አዳምም ሳቀ።ከዛም ዶክተር "በቃ
አሁን ሄዋንን ይዘካት መሄድ ትችላለክ" አሉት። እሺ በቃ "ግን ነገ
ስመጣ ሌላኛዋን ሄዋን ያሳዩኛል" አላቸው ዶክተርም "እሺ በል
እንካ" ብለው መዳኒቱን ሰጡት ። በመቀጠል ተስማምተው
ተስናበቱ ዶክተርም ወደ ስራቸው አዳምም ወደ አለሙ ህይወቱ
ሄዋን ተመለሰ። ሄዋን ጋር ሲደርስ ሄዋንን እና ቦስን አገኛቸው።
"ዲናስ" አለ አዳም። ቦስም "ወጥታለች ስልክ ልታወራ" አለ።
በበሸቀ ድምፅ ወዲያው ዲና መጣች። አዳም "አሁን ሁላችሁንም
አንድ ነገር ልንገራቹ። ዛሬ አሁን ሄዋንን ወደ ቤት ይዘናት መሄድ
እንችላለን ዶክተር የሄዋን መውደቅ ጥቅም እንጂ ጉዳት
አላስከተለባትም አሉኝ። ስለዚህ በቃ እንሂድ ይህንን መዳኒት
ለቁስሏ ገዝተው ሰጡኝ እና ደሞ ልክ እንደ አባትክ እየኝ አባቴ
በለኝ አሉኝ" አላቸው። ዲና "ውይይይ በጣም አሪፍ ሰው ናቸው"
አለች። ሁሉም "ልክ ነሽ በጣም" በማለት ንግግሯን ደገፏት።
፨ከዛም አዳም በሉ እንዘጋጅ ዲናዬ አንቺ እቃውን አስተካክይ
ወዳጄ አንተ ደሞ መኪናውን አሙቀው ሄዋኔ የእኔ ፍቅር አንቺ
እስከዛ እርፍት አርጊ እኔ ሂሳብ ዘግቼ መጣው። በእዛውም ቤት
ደውለው እንዲዘጋጁ ልንገራቸው አለ። ዲና አንተ ዝም ብለክ
ሂሳብ ዝጋ እኔ ለእነሱ ምን እንደሚያረጉ እነግራቸዋለው አለችው።
አዳም እሺ ዲናዬ ወዳጄ ና እኛ አብረን እንውጣ አለው። ቦስ እሺ
ብሎ ተከተሎት ወጣ። ከወጡ እና ከክፍሉ እራቅ ካሉ በኋላ አዳም
ቦስን ወዳጄ ምን ሆነካል ልክ አደለክም ምነው በሰላም ነው
አለው።ቦስ ረዥም ትንፋሽ ከወሰደ በኋላ ዲናዬ ሰሞኑን ደና
አደለችም ግን ደሞ ስልክ ስታወራ እቀናለው አለው። አዳም
የቦስን እጅ ይዞ ጓዴ አታስብ መቅናት የለብክም ዲና እኮ
አፍቅራክ እንጂ ተገዳ ህይወት ሳይሆን ፍቅር ይዟት ነው ካንተ ጋር
የሆነችው ስለእዚህ አትስጋ አለው። ቦስም ልክ ነክ በቃ እኔ
መኪና ሄጄ ላሙቅ አንተም ጉዳይክን ፈፅም ብሎት ሄደ።
ከደቂቃዎች በኋላ ሁሉም አልቆ ቦስ መኪናውን እያከነፈ እቤት
ልበልሽ ?" አላት። ሄዋን ወዲያው "አለሜ" ብላ ቃሉን እርግጥ
አርጋ ደገመችው። ከኮማ የነቃች ስሞን አለሜ ብሎ የጠራትን
አስታወሰች።
፨አዳም ይህንን አላስተዋለም እንጂ ትንፍሽ አይልም ነበር።
ይልቅም በውስጡ ያሰበውን ያንን ሀሳቡን ይነግራት ነበር።ሄዋን
ዝም አለች። አዳምም ዝም ብሎ ወደ ጨዋታው ተቀላቀለ። ቦስ
ዲናን ፈዞ ያያታል እሱም እንደነ አዳም እና ሄዋን ዲናን አቅፎ
እሳት እየሞቀ በጋራ ጋቢ መልበስ ፈለገ።
፨ዲና ቡናውን አፈልታ ጨረስች። ከዛም ልታነሳሳው ስትል
አንደኛዋ ስራተኛ "ተይው እኔ አነሳዋለው" አለቻት።ዲና "እሺ አንቺ
ካነሳሽውማ" ብላ ቦስ ጋር ሄደች። ቦስ ጋቢውን በጋራ እንዲለብሱ
አመቻችቶ ተቀመጡ። ሁሉም በጋራ ማውራትና መሳሳቅ ጀመሩ።
እዚህው ፓርኩ ላይ እንቆይ ብላ ዲና ባመጣችው ሀሳብ
ተስማሙ።
፨ ሌላኛዋ ሰራተኛ ተነስታ ሻይ አፈልታ በኩባያ ፔረሙዝ ሻይ እና
ወተት አመጣችላቸው ሁሉም የመረጠውን ይዞ ጨዋታቸው እስከ
ምሽቱ 6:45 ቆየ። ዲና ድህረ-ገፅ ላይ ስላየቻቸው ቀልዶች
እየነገረቻቸው ስታስቃቸው ቆዩ በተጨማሪም ቦስ ዲናን
በሚቀጥለው አመት ጥር ላይ እንደሚያገባት ተናገሩ አያይዞም
ፍቃድ ጠየቃትና ተስማሙ።
፨ ከእሩቅ አደለም ከቅርብ ላያቸው እንኳንስ በህይወታቸው ከባድ
ነገር እያሳለፉ ያሉ ቀርቶ ለአንድ ቀንም ቢሆን መጥፎ ነገር ያሳለፉ
አይመስሉም ወይም ደሞ ክፉውን አልፈው ደስታን እያጣጣሙም
ይመስላል ። በመጨርሻ ሁሉም ስለደከመው ዘበኛው እሳቱን
አጥፍቶ ሁሉም ወደየ አልጋቸው ሄደው ተኑ።
፨ የጓሮ ቤት ዶሮ 12 ሰአት መሆኑን ለማብስር ፤"እስይ ደስ
ይበላቹ አምላካቹ የዛሬ ሰው እንድትሆኑ ፈቅዶላችዋል ፤ እኔም ልክ
እንደ እናንተ ነግቶልኛል። ምስጋኔዬን በጩከት ገልጫለው
፤እናንተም ተነሰታቹ ፈጣሪን አመስግኑ የሚለውን መልክት
ለማስተላለፍ ጫኸ።
፨ዲና ተነሳች 12 ስአት ከሆነ በኋላ እንቅልፍ ባይኖ አይዞርም ኧር
እንደውም ከዶሮውን ጩከት ቀደማ ነው የተነሳችው። ተነስታ
አንድ ነገር እየፃፈች ነው ይህንን ነገር ማድረግ ከጀመረች 6 ወር
ከ 15 ቀን ሆኖታል። የምትፅፈው ስለ አዳም እና ሄዋን ታሪክ ነው።
አዳም ስለነገሯት ታሪኮች እና እሷ ሳይካትሪስት እንደመሆኗ
የምታስበውን በሌላ መንገድ ደሞ ሳይካትሪስት ባትሆን እና እንደ
ሳይካትሪስት ሳይሆን በሙያው ውስጥ እንደሌለ ሰው ስታስበው
የሚስማትን ስሜት እሷ በመማር ያላመጣችውን የሰውን ፀባይ
ማወቁን ብቻ አዳምን የታዘበችበት እና ያየችበት መንገድን
አስፍራለች።ይህንን መፅሀፍ መምህሬ ብላ ሰይማዋለች።
ግን ይህንን ከእሷ በቀር ማንም አያውቅም የቀን ተቀን ውሏቸውን
በሚገባ እና ሳቢ በሆነ መልኩ አስፍረዋለች። ዲና 1:15 ሲሆን
ሁሉንም ለመቀስቀስ ከመኝታ ቤቷ ወጣች።
፨ከዛም ካሜራዋን እንደተለመደው አመቻችታ ዝግጁ ሆነች። ዛሬ
ዲና ፈርታለች። "ምን አልባት የቀጠረኝ ስውዬ የጌዲዮን ሰው
ቢሆንስ? እና አዳም እንደነገረኝ ጊዲዮን ስው ለመጉዳት ሲያስብ
መጀመሪያ በዙሪያቸው ያሉትን ስዎች እንደሚጎዳ አዳም የነገራት
ትዝ አላት
፨ሮጥ ብላ መኝታ ቤቷ ገብታ ልሙጥ ሉክ አውጥታ ለአዳም
ለሄዋንና ለቦስ የሚሆን ደብዳቤ ለ15 ደቂቃዎች ፃፋ ስትጨርስ
ካሜራዋን አብርታ ሄዋን ጋራ ሄደች።አልተኛችም ሄዋን አሟት ፊቷ
ገርጥቶ ነበር።ሄዋን ትራሷን ተደግፋ ተቀምጣ ነበር። ዲና ስታያት
በጣም ደነገጠች።
፨"እህቴ ምን ሆንሽ?"አለቻት ሄዋን ግን መልስ አልስጠቻትም ዲና
ተነስታ አዳም እና ቦስን በጩከት ጠራቻቸው። ሁለቱም በእሩጫ
መጡ። "ምነው አሉ?" ሄዋን መኝታ ቤት በር ላይ ደርሰው።
ዲና"ሄዋን አሞታል ፊቷ በጣም ያስፈራል"አለች። አዳም ዲናን
ከበሩ ዞር አድረጎት ገባ። ቦስም ተከተለው። ስራተኞቹም በፍጥነት
ሮጠው መጡ።ሄዋን እንድታወራ ብዙ ሞከሩ እሷ ግን ትንፋሽም
አላወጣችም።ዲና ለዶክተር ልደውል አለች። አዳም ግን ወደ
ህክምና ቦታ እንውሰዳት አለ። ቦስ በበኩሉ ትንሽ እንድትረጋጋ ቤት
እርፍት ብታረግ እና ከባሰባት ደሞ ወደ ህክምና እንውሰዳት
"ምኗን አመማት ብለን እንወስዳታለን?"አሉ ዲና በመጨርሻ አንድ
ሀሳብ አመጣች።"ለዶክተር ሉሊት ደውለን እሷ ሳይካትሬስትም
ስለሆነች በቀላሉ ሄዋንን ትረዳታለች"አለች። ሁሉም አዎ ጥሩ
ጥሩ ነው አሉ።ዲና ወዲያው ደወች። ዶክተሬት ወዲያው
አነሳችው። ዲና ስላምታ አስቀድማ የተፈጠረውን ለዶክተር ሉሊት
ነገረቻት። ዶክተር ሉሊት በፍጥነት እንደምትመጣ እርፍት ላይ
ስለሆነች ሙሉውን ጊዜ ከሄዋን ጋራ እንደምታሳልፍ ነገረቻት። ዲና
የዶክተር ሉሊትን እርጋታ ሰምታ ግራ ተጋባች።"እሺ በቃ ነይ
ቶሎ" አለቻት ዶክተሪት "እሺ እንዲህ ያለ ነገር ለእንደ ሄዋን አይነት
ሰዎች ጥሩ ነገር ነው" አለችና ስልኩን ዘጋችው። ዲና አዳምና
ቦስን ወደ በረንዳ ይዛቸው ወጥታ ዶክተሪት ያለችውን ነገርቻቸው።
፨ ከ 1 ስአት በኋላ ዶክተሪት መጣች።ሁሉንም አስወጥታ ሄዋንን
መኝታ ቤቷ አስቀረቻት።ሁሉም ሳሎን መንጎራደድ ጀመሩ።ዶክተሪት
ከቆይታ በኋላ ወደ ሳሎን ዶክተሪት መጣች።ሁሉም ምን ተፈጠረ?
ምን ሆና ነው? አልዋት። ዶክተሪት እንዲረጋጉ እና ለማስታወስ
የሚረዳት የምትውጠው መዳኒት ስላልተስማማት እንደሆነ
በተጨማሪም ደሞ ብዙ ስዎች እንዲህ አይነት ሁኔታ ላይ ያሉትን
ሰዎች በህክምና ስራዋ እንደምታቃቸው ነገረቻቸው።
፨ይህንን እያወሩ ሳለ ከ ሄዋን ክፍል መስታወት ሲሰበር ሰሙ
ሁሉም እሩጠው ሄዱ። እናም ባዩት ነገር ተደናገጡ። አዳም
ሄዋዋዋዋዋንንንንንንን ብሎ ጮከ።
ይቀጥላል
@Hayitiye
😘አለሜ ነሽ😘
✍️ እድል
🔥ክፍል 35
""""
""""
""""
""""
፨ ዲና እና ዶክተር ምን እንደሚያረጉ እና እንደሚያስቡ ግራ
ገባቸው። ዝም ብለው ደንዝዘው ተቀመጡ። ዲና በፍርሀት
መንቀጥቀጥ ጀመረች። መኪናው እየጋለበ ወደ እነሱ እየመጣ
ነው። በድንገት ከ አጠገብ ያሉ ትንንሽ መኪኖች የትልቁን መኪና
ጎማ በተኩስ አስተነፈሱት። ያኔ መኪናው ቀጥ ብሎ ቆመ።
፨ዲናና ዶክተር የሚፈጠርውን ነገር በዝምታ ከድንጋጤ ጋር ማየት
ቀጥለዋል። ትልቁ መኪና ውስጥ ያለውን አሽከርካሪ ከትንሹ
መኪና የወጡት ሁለት ፊታቸው በእስካርቭ የተሽፈኑ ስዎች
እየጎተቱ አስወጥተው አንበረከኳቸው። ያሉበት ቦታ መሀልኛው
አስፓልት ሲሆን ዳር እና ዳሩ ጫካ ነው። መኪናም ሆነ ስው
አልያም እንስሳ በአጋጣሚ ካልሆነ ዝር አይሉም።
፨ ሹፌሩን ጎትተው ጫካው ውስጥ ካስገብት በኋላ አንደኛው
እስካርቭ ጠምጣሚ ከደቂቃቆች በኋላ ወደ ዲናና ዶክተር
በዝግታ መጣ። የዶክተር እና የዲና የልብ ምት በእጥፍ ጨመር።
ሰውየው ይበልጥ ተጠጋቸው። እራሳቸውን ሊስቱ ትንሽ ብቻ
ቀራቸው። መኪናቸው በር ላይ ቆመ። በዲና በኩል አንኳኳ ቀስ
ብላ እጇ እየተንቀጠቀጠ መስታወቱን ዝቅ አረገችው።
፨ ፈጠን እያለ በኮልታፋ ድምፅ አአአአአንንንንብብብበበበሽ
ተተተረረጂ ብሎ የሆነ እጥፋጥፋ ያለ ወረቀት ሰጣት። ዲና እጇን
በቀስታ ወደ እጁ ልካ ተቀበለችው። ሰውየው ወዲያው ሮጥ ብሎ
ሶስትኛ እርድፋ ላይ ያለችውን መኪና አስነስቶ ከትልቁ መኪና ፊት
አርገው። ከዛም ወደ ዲና በማየት እለፉ የሚል ምልክት
አሳያችው። እንደምንም እራሷን አረጋግታ መኪናውን በተከፈተላት
መንገድ በፍጥነት ነዳችው በፍጥነት ነዳችው
ከዶክተር ጋራ ምንም ቃል አላወሩም። በስተመጨረሻ ዶክተር
መኪናቸውን ካቆሙበት ቦታ ደረሱ።
፨ዲና መኪናውን አቁማ ወረቀቱን ከፈተችው እንዲ ይላል። "ሰላም
ለእናንተ ይሁን ወይዘሪት ዲና እና ዶክተር ለአዳምና ለሄዋን
ደህንነት እንደምትጨነቁ አውቃለው። ስለ እዚህ ነገር በስፊው
ለመነጋገር ነገ ከስአት 7:30 ላይ ከስፈራቹ እራቅ ብሎ በሚገኘው
ሪልስቴት እናወራለን"።ይላል ዲና አንብባ ስትጨርስ ለዶክተር
ሰጠቻቸው። እሳቸውም አነቡት።ዶክተር ዝም አሉ በመሀከላቸው
ረዥም ዝምታ ሰፈነ።
፨በመጨርሻ ዶክተር "እሺ ጥሩ እኔ ለሁለቱም ፍቅር የተቻለኝን
ለመክፈል ዝግጁ ነኝ" አሉ። ዲና "እኔም እንደ እርሶ ነኝ። በቃ ነገ
እንገናኝ" አለች።ዶክተር ተስናብተዋት ሄዱ።
፨ዲና መኪናዋ ውስጥ ሆና ብዙ አሰበች እና በጣም ደስ
አላት።"የእራሴን ህይወትም ሰጥቼ ፍቅራቸውን አድናለው" አለች።
ውስጧን ስላም ተስማት ደስ አላት። በጭራሽ
አልተከፋችም እንደውም ደስ አላት። የአዳም እና የሄዋን ገፋ ሲል
ደሞ የቦስን ህይወት ማትርፍ እንደምትች ለውስጧ ነግራው
የተፈጠረባትን ሁሉ እረስታ ወደ ቤት መኪናዋን ነዳችው።
፨ከ ግማሽ ሰአት በኋላ እቤት ደርሳ የቤቱን የውጭ በር ዘበኛው
እንዲከፍትላት ክላክስ ስታረግ ሁሉም ወደ በር ወጡ። ለጥቂት
ስአታት ብትለያቸውም ዘላለማዊ መስሎ ነበር የታያቸው። ምንም
ቢስቁና ቢጫወቱ ውስጣቸው ነበረች። መኪናዋን ጊቢ አቁማ
በረንዳው ላይ ስትደርስ ሁሉም ስብስብ ብለው በናፍቆት እይታ
ተመለከቷት ሄዋን ሮጣ አቀፈቻት ዲና "ምንድነው ነገሩ እንዲ
እንደምናፍቅሽ አላስተዋልኩም ነበር" አለችና የቀኝ ጉንጯን በደንብ
አርጋ ሳመቻት። ከዛ ሁሉም በእየ ተራ እያቀፈች ሳመቻቸው።
፨ሁሉም ተያይዘው ወደ ቤት ገቡ ። "ዲናዬ ምነው አስጨነቅሽን
እኮ በተለይ ቦስ ሊያብድልሽ ነበር"።አለች ሄዋን። ዲና ወደ ቦስ
ሄዳ አጠገብ ተጠምጣ አቀፈችው። እና ግንባሩን ሳመችው። ሄዋን
እና አዳም ተያይተው ሳቁ። ዲና "ምን ያስቃችዋል እዩት እስቲ
በእኔ ናፍቆት እንዴት እንደገረጣ" አለችና የቦስን አገጭ
በመጠቀም ፊቱን አዞረችው። ከዛ አይኑን እያየችው "አይዞክ
ከእንግዲ ጥዬክ አልሄድም ነገ ብቻ ነው ለተወሰነ ሰአት
የምሄደው ጓደኛዬን እቃ አጋዝቻት እመጣለው" ስትለው። ቦስ
"ኡፍፍፍፍ ምንድነው ቆይ ነገሩ እሺ ቶሎ ነይ እባክሽ" አላት።
፨አዳም "ኦኦ ወዳጄ አይዞን ቶሎ ትመጣለች" ሲለው ሄዋን አዎ ዘና
በል ደሞ ከአሁን እስከ ነገ ጊዜ አለክ መነጫነጭክን ትተክ
ናፍቆትክን ተወጣ" አለች። ከቦስ በስተቀር እርሷን ዲናን ጨምሮ
ሁሉም በጣም ሳቁ። ዲና "እሺ ስዎች በቃ ኩሽና ሄጄ የብና ቁርስ
እንዲያዘጋጁ ልንገራቸው" አለች።
፨ቦስ "እነሱን ተያቸው እኔና አንቺ ሄደን እንግዛ" አላት። ሁሉም ቦስ
ከዲና ጋራ ለብቻው ጊዜ ማሳለፍ እንደሚፈልግ ስለገባው "እሺ"
አለችና ዲና ተነስተው ወጡ በረንዳ ፤የግቢ በር፤ አልፈው ውጭ
ወጡ። በዝምታ ሄደው ትንሽ እንደቆዩ ቦስ ዲናን ጥምጥም ብሎ
አቀፋት።
ዲና ግራ ገባት። በጣም እንደከፋው ተረዳች። እሷም እቅፍ
አረገችው። መንገድ ላይ ሁሉም እያያቸው አላፊ አግዳሚው
እያያቸው ነው። ላያቸው ሰው ስንብት ላይ ያሉ ይመስላሉ። "ይህን
ያክል ናፍቄሀለው" አለች ዲና። ቦስ "በጣም በጣም ለምን
እንደሆነ ባላውቅም በሰላም የምትመለሽ እራሱ ስላልመሰኝም
ልቤ ተጨንቆ ነበር" አለት። ዲና "ውይይይ ቦስዬ ይህው መጣው
አደል በቃ አትጨነቅብኝ" አለችው።
ቦስ "እሱማ አዎ" አለና አቅፎት በአቅራቢያቸው ካለው ኮክቴል
ቤት ለቡና ቁርስ የሚሆኑ የተለያዩ ጣፋጭ ምግቦች ገዝተው
እንደተቃቀፉ ቤት ደርሱ። ከዛም ዲና ፓርኩ ላይ ብና አፈላች
ዘበኛውም ፓርካቸው መሀል በተዘጋጀው የእሳት ማቀጣጠያ እሳት
አቀጣጠለ። ሁሉም እሳቱን ከበውት ጨዋታቸውን አደሩት።
ለመቀመጫቸው እንዲሆን በተዘጋጀው የተነጠፈ ምንጣፍ ላይ
ሄዋንና አዳም ለሁለት አንድ ጋቢ ለብስው ተቀምጠዋል።
፨ያን ሰአት ሄዋን "ምን አለበት አዳም የኔ ቢሆን ፤ ፈጣሪዬ
እባክህን አዳምን የኔ የብቻዬ አርገው" እያለች በአዳም እቅፍ
ውስጥ ሆና ለፈጣሪ ምልጃና ፀሎቷን ታደርሳለች። አዳም በበኩሉ
"ሄዋኔ ምነው ትውስታዋ በተመለሰ ይህ ነገር ቢያበቃ፤ ይህ
የውስጤ ቁስል ቢፈወስ ፤ እሷንም ከጭንቀት ብትወጣ"እያለ
ምኞቱን በእቅፉ ለሸሸጋት ሄዋን ምኞቱን ለአምላኩ ሰደደ።
፨ሄዋን ብዙ ጊዜ "ምንክ ነኝ?" ስትለው ሁሌም "ፍቅረኛሽ" ቢላት
ትመኛኛለች። ሄዋን አንድ ነገር አሳስቧታል። "ምን አልባት አዳም
ዘመዴ ቢሆንስ የሚል" አዳምን ለመጠየቅ ከእራሷ ጋር
ከተከራከረች በኋላ ወደ ጆሮ ጠጋ ብላ "አንድ ጥያቄ ልጠይቅክ?"
አለችው። አዳም እሺ አላት ግን ፈርቷል ጥያቄዋን አለመመለሱ
ሁሌም ውስጡን ያመዋል ሄዋን ስታወራ ብትጮክም። ዘበኛው
፣ስራተኞቹ ፣ ዲና እና አልፎ አልፎ ቦስ የደመቀ ጨዋታ ስለያዙ
አልስሟትም።
፨ሄዋን በለሰለሰ ድምፅ "የምታፈቅራት ሴት አለች?" አለችው።
"የለችኝም ምን ይስራልኛል ፤ ፍቅር የሚባል ነገርን አስቤ
አላውቅም" ብሎ ሊዋሻት አልፈለገም እንዲ ካላት ልቡ
ይስባበራል እሷን የሚያፈቅራትን አለሙን በቁሟ እንደገደላት ነው
የሚያስበው።
፨ አዳም ጥቄት ዝም ብሎ "አዎ " አላት። ሄዋን እንደመናደድ
እያረጋት "ማን ናት?" አለችው። አዳም ፈገግ ብሎ "አለሜ ናት
፤ህይወቴ ሁሉ ነገሬ፤ ስለሆነች ምኔ ናት ብዬ ልንገርሽ ማን ናትስ
ህይወቷ አሁን ላይ ብታውቅ ምን አልባት በትንሹ ልታስታውስ
ትችል ይሆናል። ግን በድጋሜ ትረሳለች በድጋሜ ከረሳች ደሞ
መቼም አታስታውስም" የሚለው ንግግር አዳም በሀሳብዋ ተዋጠ።
አዳም አለችው ሄዋን። ደንገጥ ብሎ "ወዬ" አላት። "ምን ሆነካል
ችግር አለ?" አለችው። "አይ አይ አታስቢ ምንም ችግር የለም"
አላት።
፨ ሄዋን "እንዲ ስትሆን አልወድም ካንተ በበለጠ እኔ
እጨነቃለው" አለችው። አዳም ይህንን ከሄዋን ስለስማ በጣም
ተደስተ። "እሺ አልጨነቅም በቃ ታሪኩን ልንገርሽ?" አላት። "እሺ
ደስ ይለኛል ቀጥል" አለችው።
፨አዳም ያኔ ወዳሳለፉት ጊዜ በሀሳብ ተጓዘ። ያንን ጊዜ እያሳለፈው
መስለው።ሄዋንም ፈገግታው ተጋብቶባት ፈገግ አለች።የእዛን ጊዜ
ፈገግታ በታከለበት መልኩ አንድ በአንድ ነገራት። ሄዋን በጣም
ተገርመች።
፨ አዳም ዲና ትዝ ብላው "እስቲ ልደውልላት" አለና ደወለላት
ስልኳ አይነሳም ዲና የስልኳን ድምፅ አጥፍታ ከዶክተር ጋር
እያወሩ ነው። በጣም ወደራቀና ስው ወደማያቸው ቦታ ሄደው።
ዲና የተፈጠርውን ለዶክተር ስትነግራቸው ዶክተር በጣም አዘኑ
ተበሳጩም። "አዳምን እንዴት ከእዚህ ጉድ እናውጣው?" ብለው
ተማከሩ ምንም አይነት ሀሳብ ሊመጣላቸው አልቻለም። ግን
ይህንን ነገር ለማንም ላለ መናገር እና በእየ ግላቸው አስበውበት
በቀጣይ ቀን ለመገናኘት ወስነው። በዲና መኪና ገብተው ወደ
መጡበት ጉዞ ጀመሩ።
፨የዶክተርን መኪና እዛው ከተገናኑበት ቦታ አቅራቢያ ባለው
የመኪና ማቆያ አስገብተዋታል። ዲና መኪናዋን ከማስነሳቷ በፊት
ስልኳን ድምፅ ላይ ለማድርግ ከለበሰችው ሊዘር ጃኬት
አወጣችው። አዳም ደጋግሞ ደውሎላት ነበር። አዳም ጋር
ደወለች። አዳም ቦስ ከእንቅልፋ ተነስቶ ስለነበር ከእሱና ከ ሄዋን
ጋር ያቆርጡትን ውድድር እያዩ ነው። ፈጠን ብሎ ስልኩን አነሳው።
ዲና "ሄሎ አዳምዬ" አለችው።አዳም ፈጠን ብሎ "ሄሎ እንዴት ነሽ"
አላት። ሄዋን ስልኩን ከአዳም መንጭቃ "እህቴ ኧር ናፈቅሽኝ"
አለቻት። ዲና "እየመጣው ነው" አለች። የማታውቀው ቁጥር
ዊቲንግ ሲገባ አየችው። "በቃ እየመጣው ነው ባሌን
ተንከባከቡት" ብላ ስልኩን ዘጋችው። ወዲያው ያንን የማይታውቅ
ስልክ አነሳችው "ሄሎ" አለች አይስማም ዘጋችው።ከዛ መኪናውን
ማሽከርከር ጀመርች በድጋሜ ጠራ ዶክተር አንሱት እና ላውድ
አርጉት አለች።ፈርታለች። ጋቢና የተቀመጡትን ዶክተር አነሱት።
ሄሎ አለ ጌዲዮን ነበር። "አሁን ከፊት ለፊትሽ የምልክልሽን በፀጋ
ተቀበይ ሞትሽ ቀርቧል" አላት። ዲና ቀና ስትል ግዙፍ መኪና ከፊቷ
እየከነፈ ሲመጣ ታያት ከጉኑ ሁለት መኪኖች በተመሳሳይ ፍጥነት
እየመጡ ነው። ዶክተር ደርቀው ቀሩ።ዲና መኪናዋን አቁማ ልክ
እንደ ዶክተር ደርቃ ቀርች።
ይቀጥላል
@Hayitiye 🦋
😘አለሜ ነሽ😘
✍️እድል
🔥ክፍል 34
"""
"""
"""
"""
፨ "ስላምምም የተከበሩ የአዳም ቀኝ እጅ እንደምን አለሽ.... እኔ
በጣም ደና ነኝ " አለ ጊዲዮን ነበር። ዲና "ምን ፈለክ አንተ
የማትርባ" አለችው። ጊዲዮን "ምንም እንዲው ናፍቀሽኝ ድምፅሽን
ለመስማት ነው። መቼም አልልሽም። ሁለት የምነግርሽ ነገሮች
አሉ። አንደኛው ልክ የዛሬ ሳምንት እኔ ጋር ትመጫለሽ"። አላት።
ዲና በበሸቀ ድምፅ "ለምን? አልመጣም በጭራሽ" አለች።
፨ጌዲዬን ርዥም ሳቅ ከተዝናኖት ጋር አዋዝቶ "እሱን ለአዳም
ብለሽ ታረጊዋለሽ ያ የማይረባ እስማኤል የተባለ ጠበቃ ስለ እኔ
የሞነጫጨረውን ፁሁፋ ታመጭልኛለሽ። ካለ በለዚያ እሱንና ያቺ
ሞናኒዛው ሄዋን ታይቶ በማይታወቅ ለጆሮ በሚዘገንን መልኩ
እደፋቸዋለው ሲላው ደሞ ያ ፍቅርኛሽን "። አላት።
፨ ዲና ደንግጣ የምትለው ጠፋባት ሲገላቸው እና ሲያሰቃያቸው
በሀሳቦ ቁልጭ ብሎ ታያት። ስልኩ ጆሮዋ ላይ ተዘጋ።የምትሆነው
ጠፋባት። ይህንን ጭንቀቷን ቤት ውስጥ ላሉት ሰዎች ማጋባት
ስላልፈለገች እራስዋን እንደምንም አረጋግታ ወደ ቤት ገባች። ቤት
ስትገባ ሁሉም ቁርሳቸውን ለመብላት የምግብ ጠረጴዛ ላይ
ተቀምጠዋል። ዲናን ሲያዋት ሁሉም "ነይ ተቀመጭ፣ ቆየሽ እኮ
ስንጠብቅሽ" እያሉ ተንጫጩ።
፨ዲና መከፋቷን ደብቃ ፈገግ ብላ "ጓደኛዬ ደውላልኝ እኮ ስለ ቦስ
እየነገርኳት ነበር። ለእዛ ነው ይህው መጣው በሉ ብሉ እጄን
ታጥቤ መጣው" አለችና ወደ መታጠቢያ ክፍል ሄደች። በሩን
ዘግታ በጣም ተንጎራደደች ጨነቃት ምን ላድርግ ብላ ከእርሷ ጋር
ተማከርች። በስተመጨርሻ የመጣላት የመጨርሻ አማራጭ
ለዶክተር መናገር ነው።
፨እጇን ታጥባ ትኩረት በማይስብ መልኩ ከፈገግታ ጋረ ወደእነሱ
ተመለሰች። ቁርሷን በላች ግን በጣም ስትፈዝ ሁሉም አይቷታል።
ግን ደሞ ሲስቁ አብራቸው ስትስቅ የከፋት አትመስልም። ዲና
"ሰዎች ዛሬ ጓደኛዬ ነይ ብላኛለች እሷ ጋር ደርሼ እመጣለው
ስመጣ ቆንጆ ቡና አፈላላችዋለው በቃ ልብሴን ልቀይር" ብላ ወደ
መኝታ ቤቷ ገባች። ሁሉም የዛሬ የዲና ሁኔታ ግራ አጋብቷቸዋል።
ግን ምንም አላሉም ምክንያቱም ሳቅና ጨዋታዋ አልጎደለም።
ሁሉም "እሺ ስትመጪ ቡናሽን እንጠብቃለን" አሉዋት ሌላ ምንም
አላሏትም የትኛዋ ጓደኛሽ ናትም አላሏትም። ዲና ወዲያው ልብሷን
ቀያይራ ሁሉንም ዞራ ስማቸው ሄደች።
፨ መኪናዋን አስነስታ ዘበኛው ተከትሎ በሩን ከፍቶላት ወጣች።
እራቅ እንዳለች ለዶክተር ደወለች። ከሁለት ጥሪ በኋላ አነሱት።
"ሰላም ዲና" አሏት። ዲና "ዶክተር እንዴት ኖት በጣምም
ላስፈላጊ ጉዳይ ፈልጌዎት ነበር አሁኑኑ ብንገናኝ ደስ ይለኛል"
አለች። ዶክተር "ምነው በስላም" አሉዋት። ዲና "አይ ዶክተር
ሰላም አደለም እባኮት እንገናኝ" አለቻቸው። እሳቸውም በግራ
መጋባት "እሺ ጥሩ ጥሩ የት እንገናኝ" አሉዋት።
፨ዲና "የሆነ የማይታወቅ ቦታ" አለቻቸው። ዶክተር ይበልጥ ግራ
ተጋቡ "እሺ ጥሩ ያለሽበት ጋር እመጣና ቦታውን እንወስናለን"
አሉዋት ዲና ያለችበትን ነግራቸው አሁኑኑ እመጣላው ጠብቂኝ
20 ደቂቃ ብቻ አሉዋት።ዲና "እሺ ጥሩ በቃ እጠብቆታለው"
አለችና ስልኩን ዘጋችው። ዲና ዶክተርን በጉጉት መጠባበቅ
ጀመርች።ሰአቱም አልደርስ አላት መኪናዋ ውስጥ 10 ደቂቃ
አስቆጠረች።፨ ቦስ ደወለ አነሳች። "ቦስዬ" አለችው። ቦስ "ወዬ
ዲናዬ ምነው በሰላም ነው?" አላት።"ኧረ ስላም ነው ቦስዬ ምነው
ለምን ጠየከኝ?" ስትለው። "አይ እንዲሁ ሳይሽ ጠዋትም ፊትሽ
ልክ አደለም በተለይ ስልክ አውርተሽ ከተመለሽ በኋላ ምን ሆንሽብኝ
እባክሽ በጣም ጨነቀኝ ንገሪኝ እስቲ" አላት። ድምፁ በጣም
እንደተጨነቀ ያስታውቃል። ዲና ምን እንደሆነች ብትነግረው እና
ጭንቀቷን ቢያጋራት ደስታዋ ነበር። ግን እንዲጨንቀው
አልፈለገችም። ቦስዬ ምንም አልሆንኩም አትጨነቅብኝ ውዴ
የሴቶች ግዴታ ላይ ስለሆንኩኝ ነው ድብርብር ያለኝ" አለችው።
ቦስ እየዋሸሽኝ ነው በርግጠኝነት ባለፈው ሳምንት አደል እንዴ
አንቺና ሄዋን የሴቶች ግዴታ ላይ ነን ብላቹ ተኝታቹ የዋላችውት"
አላት።
፨ዲና ቦስ ይህንን በማስተዋሉ በጣም ገረማት። ሳቅ ብላ "አይ
ውዴ ያኔ እንዲው ደብሮኝ ነበር ሂዊ እንጂ እኔ አልነበርኩም። በቃ
አታስብ እሺ ቶሎ እመጣለው" አለችው።
፨ በስልኩ ውስጥ የሄዋን ድምፅ ስትስቅ ተሰማት "ቦስዬ ሂዊ
ምን አግኝታ ነው እንዲ የምትስቀው?" አለችው። ቦስ "አይ
ከአዳም ጋር የኮሜዲ ውድድር እያዩ ነው" አላት። ወዲያው አዳም
ሲስቅም ተሰማት።"እሺ በቃ ደና ዋሉልኝ" ስትለው ቦስ "እሺ
አንቺም ስላም ዋይልን ትናፍቂኛለሽ እባክሽ ቶሎ ነይ" አላት። ዲና
"እሺ ችግር የለም እመጣለው" አለችው። አዳም "ና ወዳጄ
አመለጠክ" ሲል ተሰማት ሄዋን ተከትላ "ኧር ቶሎ" ና አለችው።
ዲና "በቃ እየጠሩክ ነው ስልኩን ዘግተክ ብትሄድ ይሻልካል እኔም
ትናፍቀኛለክ" አለችው።
፨ ቦስ "እሺ" ብሎ ስልኩን ዘግቶ ገባ። ሄዋና አዳም ሶፋ ላይ
ናቸው። አዳም ተቀምጦ ሄዋን ደሞ አዳም ታፋዎች ላይ ጋደም
ብላ ሶስት የሚያስቀምጠውን ሶፉ ይዘውታል። ቦስ ሄዶ ሌላኛው
ሶስት የሚያስቀምጠው ሶፋ ላይ ጥቃቅን የሳሎን ትራሶችን ደራርቦ
ጋደም ብሎ ውድድሩን ማየት ጀመር። ክፍት ብሎታል የዲና ነገር
አሰሳስቦታል የሰጠችው ምክንያት ፈፅሞ አልተዋጠለትም።
፨ ቲቪ እያየ ከነ ሄዋን ጋር መሳሳቅ ጀመር። ውድድሩ የሳቅ
መድረክ ስለሆነ አለመሳቅ አይልቻለም።ይህ ሁኔታ ለቦስ
እየተገረፉ መኮርኮር ሆኖበተበታል። የሚያስቅ ነገር አይቶ ማንም
አለመሳቅ አይችልም። የሚያስለቅስም ነገር አይቶ አለማልቀስም
ፈፅሞ አይቻልም ቦስ ከፍቶታል። መሳቁንም አልፈለገውም
"እንቅልፌ መጣ" ብሎ ሶፋው ላይ እንዳለ ጋደም አለ። ቦስ
ሳያስበው እንቅልፍ ወሰደው። ሄዋን ጋደም ካለችበት ተነስታ ቦስን
የሚለበስ ነገር አለበሰችው።
ከዛ ሄዋን አዳምን "ወደ በረንዳው እንሂድና እዛ እናውራ" ብላው
እሱም እሺ ብሉዋት ወጡ። ከዛ በረንዳው ላይ ቁጭ ብለው ሄዋን
"ስለ ጀመርክልኝ ታሪክ ንገረኝ" አለችውና መናገር ጀመረ። "ዛሬ
የምነግርሽ ልጁ ለልጅቷ ቀለበት ያስረላትን ጊዜ ነው"።አላት ሄዋን
"እሺ ደስ ይለኛል ከእዛ በፊት ግን አንድ ጥያቄ አለኝ ቆይ
ለምንድነው ሁሌ እጀ እና አንገተ ሙሉ ልብስ የምትለብሰው
በሙቀት ስአትም በብርድ ስአትም ልክ እንደ ቦስ ለምንድነው
ቲሽርት ቦዲ ምናምን የማታረገው" አለችው። አዳም ደንገጥ አለና
ፈገግ ብሎ "አይ የአየር አላርጂክ ስላለብኝ ነው"። አላት። "እና
መድሀኒት የለክም" አለችው። "አይ መዳኒትማ አለው እስቲ ቦስ
በቀጣይ ወር በረራ ስላለው ያመጣልኛል" አላት። "እንዴ የምን
በረራ አልገባኝም" ስትለው "ከዲና ጋር ለመሄድ አስቧል" አላት።
"ወዴት" አለችው "እሱን አላውቅም" አላት። አዳም ይህን ምክንያት
እንዴት እንደፈጠርው ገረመው። በእርግጥ "አንገተ ሙሉ እና እጀ
ሙሉ ልብስ የምለብስው አንቺ አንገቴ እና እጄ ላይ ያለውን
ንቅሳት እንዳታይብኝ ነው" ብሎ ቢነግራት ደስ ይለው ነበር። ግን
አይሆንም በጭራሽ የዶክተር ድምፅ ያቃጭልበታል "ስለ ወደፊት
#በሰሙነ_ሕማማት_የሚፈጸ_ሥርዓቶች
1, #ስግደት :-
በሰሙነ ሕማማት 41 ጊዜ ኪርያላይሶን 12 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት እየተዜመ እጅግ አብዝቶ ይሰገዳል።
2, #ጸሎት :-
በሰሙነ ሕማማት ከ24 ሰዓት ውስጥ 10 የጸሎትና የንባብ ሰዓታት ይገኛሉ እነዚህም ከጠዋቱ 1 ሰዓት; 3ሰዓት; 6ሰዓት; 9ሰዓት; 11ሰዓት እንዲሁም ከምሽቱ 1 ሰዓት; 3ሰዓት; 6ሰዓት; 9ሰዓት; 11ሰዓት ናቸው።
በእነዚህም ሰዓታት የጌታን ስቃይ ለማዘከር መዝሙረ ዳዊትና ግብረ ሕማማት ድርሳነ ማኅያዊ አብዝተው ይጸለያሉ።
3, #ጾም :-
በሰሙነ ሕማማት ብዙ አዝማደ መባልዕት / አዘውትረን የምንመገባቸው ምግቦች አይበሉም። በዚህም ሳምንት እስከ ምሽቱ #አንድ_ሰዓት እንድንጾም; ይኸውም ቆሎ;ዳቦ;ወኃና ጨው ብቻ እንደታዘዙ በግብረ ሕማማት ላይ ተጽፎ ይገኛል።
4, #አለመሳሳም :-
አይሁድ ጌታችንን ለመስቀል እየተንሾካሾኩ ስለተመካከሩና ይሁዳ ጌታችንን በመሳም አሳልፎ ስለሰጠው መሳሳም አይፈቀድም። መስቀልም በዘመነ ኦሪት የወንጀለኛ መቅጫ የእርግማን ምልክት ስለ ነበር ጌታችን በክቡር ደሙ ቀድሶ የድል አርማ እስኪያደርግልን ድረስ አንሳለመውም ገላ.3:13 ማቴ.10:38 ማቴ. 26:29
5. #አክፍሎት :-
እመቤታችን; ያዕቆብና ዮሐንስ የጌታችን ትንሳኤ ሳናይ እህልና ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሳኤው መቆየታቸውን በማሰብ የሚጾም ነው።
6, #ጉልባን :-
ከባቄላ ከስንዴ ከገብስ የሚዘጋጅ በጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ሲሆን ትውፊቱም የስቅለቱ ሐዘን መግለጫ ነው።
7, #ጥብጠባ :-
ይህ ምዕመናን በሰሙነ ሕማማት የፈጸሟቸውን ኃጢአቶች ለካህን እየተናዘዙ በወይራ ቅጠል ቸብቸብ እየተደረጉ ስግደት የሚቀበሉበት ነው። ይህም የጌታ ምሳሌ ነው።
8, #ቄጠማ :-
ጌታችን ብርሃነ ትንሳኤዉን እንደገለጠልን የምናስብበት ሲሆን የእሾህ አክሊል በመድፋቱ ምሳሌም በራሳችን ላይ እናስረዋለን።
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻም ወድካም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም።
#ሼር
Join @Hayitiye
