ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
前往频道在 Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
显示更多637
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-1130 天
帖子存档
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ #መጋቢት ፰ (8) ቀን።
❤ እንኳን ብዙዎች ሰማዕታትን አሠቃይቶ ይገድል ለነበረው ለእንዴናው ገዥ #ለቅዱስ_አርያኖስ በሰማዕታቱ ጸሎት አምኖ እርሱም ራሱ በንጉሡ በዲዮቅልጥያኖስ ፊት የጌታችን አምላክነት መስክሮ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና ለእስክንድርያ ዐሥራ አንደኛ ሊቀ ጳጳስ ለቅዱስ አባት #ለአባ_ዮልዮስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #መኰንን_ቅዱስ_አርያኖስ፦ ይህም እንዲህ ነው የከበሩ ፊልሞንና አብላንዮስ በእርሱ እጅ በሰማዕትነት ከሞቱ በኋላ እርሱም በሥቃይ ውስጥ ሳለ ከአማንያን አንዱ ከቅዱሳን ከደማቸው ወስደህ ዓይንህን ብትቀባ በዳንክ ነበር አለው። ያን ጊዜም ከደማቸው ወስዶ ዐይኑን ቀባ ወዲያው ድኖ ፈጥኖ አየ።
❤ ከዚህም በኋላ በቅዱሳን ላይ በአደረገው ክፉ ሥራ ሁሉ በድንቁርናውም ምሕረት የሌለው ሥቃይ ስለ አሠቃያቸው ታላቅ ጸጸት ተጸጽቶ አዘነ ተነሥቶም ጣዖታትን ሰበረ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምኖ ምእመናንን ማሠቃየቱንም ተወ።
❤ ዲዮቅልጥያኖስም ወሬውን በሰማ ጊዜ ጭፍሮቹን ልኮ ወደርሱ አስመጣው "በምን ምክንያት አማልክትን ማምለክ እንደ ተወ" ጠየቀው። እርሱም "በቅዱሳን ሰማዕታት እጅ እግዚአብሔር የሚሠራቸውን አስደናቂዎች ተአምራት ሊነግረው ጀመረ ሕዋሳታቸውን እንዴት እንደ ሚቆራጡአቸው በየአይነቱ በሆነ ሥቃይም ሲያሠቃዩዋቸው ያለምንም ጉዳት ጤነኞች ሁነው ተመልሰ እንደሚነሡ" ነገረው። ዲዮቅልጥያኖስም የተአምራትን ነገር ስለ ነገረው ተቆጣ ጽኑ የሆነ ሥቃይንም እንዲያሠቃዩት አዘዘ። ሁለተኛም ከጉድጓድ እንዲጨምሩትና እስኪሞትም የጉድጓዱን አፍ እንዲዘጉ አዘዘ እንዲሁም አደረጉ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መልአኩን ልኮ ከጉድጓዱ አውጥቶ በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ መኝታ ላይ አቆመው። ንጉሡም በነቃ ጊዜ አይቶ ደነገጠ፣ ፈራ "ማንህ አንተ" አለው።እርሱም "እኔ የእዴናው ገዥ አርያኖስ ነኝ" ብሎ መለሰለት ንጉሡም ደንግጦ እየተንቀጠቀጠ በማቅ ጠቅልለው ከባሕር እንዲያሰጥሙት አዘዘ። በባሕሩም ውስጥ ነፍሱን በጌታችን እጅ መጋቢት8 ሰጠ።
❤ እንዲህም ሆነ ቅዱስ አርያኖስ ዘመዶቹንና አገልጋዮቹን ሲሰናበታቸው እንዲህ ብሎ ነገራቸው "ለሥጋዬ እርሱ እንደሚያስብና ወደአገሬ ወደእንዴናው እንደሚመልሰው በሌሊት ራእይ እግዚአብሔር አስረድቶኛልና እንተም በእስክንድርያ ወደብ ሥጋዬን ጠብቁ" አላቸው። በአሰጠሙትም ጊዜ ጌታችን ዓሣ አንበሪን አዘዘ አንበሬውም ተሸክሞ ወስዶ በእስክንድርያ ወደብ አውጥቶ በየብስ ላይ አኖረው። አሽከሮቹ ከዚያ እየጠበቁት ነበር። ወደ አገሩ ወደ እንዴናው አድርሰው ከቅዱሳን ሰማዕታት ከፊልሞና ከአብላንዮስ ከሥጋቸው ጋር በአንድነት አኖሩት። የቅዱስ አርያኖስ በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ዮልዮስ፦ ይህም አባት አስቀድሞ በእስክንድርያ ቄስ ሆኖ ነበር። እርሱም በአለበት ዘመን በግብጽ አገር እንደርሱ ያለ የሌለ አዋቂ ብልህ የሆነ ምሁር ነበር። የክብር ባለቤት በሆነ በእግዚአብሔርም ፈቃድ በእስክንድርያ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ ብዙዎች ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ።
❤ የሹመቱም ዘመን በሰላም የሰፈነበት ነበር በቀናች ሃይማኖትም ይጸኑ ዘንድ ሕግና ሥርዓትንም ሁሉ እንዲጠብቁ ሕዝቡን ሁል ጊዜ ይመክራቸውና ያስተምራቸዋል።
❤ በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ዐሥር ዓመት ከኖረ በኋላ መጋቢት 8 በሰላም በፍቅር ዐረፈ። በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 8 ስንክሳር።
❤ "#ሰላም_ለአርያኖስ_አማልክቲሁ_ኀዲጎ። ዘተለወ ፍጹመ ለእግዚአብሔር ሕጎ። ዲዮቅልጥያኖስ ምዑክ ቢጸ አራዊት በዛውጎ። እምድኅረ ደፈኖ አፈ ግብ መሪጎ። መልዕልተ ምስካቡ ንጹፍ ተረክበ ዐሪጎ"። #ሊቁ_አርከ ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_8።
❤ የተባረከው ሐዋርያ ቅዱስ ማትያስም የአማልክቱን አዳራሾች ሁሉ ያፈርሱ ዘንድ በውስጥ ከሚደርጉት ክፉ ተግባር የተነሣ ከእርሱ ምንም እንዳይገናኙ ከባሕር ይጥሏቸው ዘንድም ይህን አዘዛቸው። ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ስምም ቤተ ክርስቲያን ሠራላቸው። በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስምም አጠመቃቸው። የአገሩን ሰዎችም ወንዶችንም፣ ሴቶችንም፣ ሕፃናቱንም አንድ በሆነ በማይከፈል በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው።
❤ ከጥምቀት በኋላ ቤተ ክርስቲያኒቱን አከበረላቸው (ባረከላቸው)። በይቅርታና በሕይወት ትምህርትም ገሠጻቸው። የወንጌልን ሕግም አስተማራቸው፤ ከእርሱም ተለየ። ሁሉም በሰላም ሸኙት። እርሱ ትክክለኛውን ዕውቀትና ቅን የሆነች መንገድን አስተማሯቸዋልና። በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የማመን ዕውቀትን በማስተማርም ከስህተት አድኗቸዋልና።
❤ ካስተማረና የምስራችን ከነገረ በኋላም መልካም እንቅልፍን ተኛ። ከይሁዳ አገሮች ፍዕላዎን በምትባል አገርም በጌታችን በአምላካችን በእግዚአብሔር ጸጋ መጋቢት ስምንት ቀን ዐረፈ። ምስጋናና ክብር ለእርሱ ይሁን ። ከሐዋርያው ቅዱስ ማትያስ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎቱ ይማረን!። አሜን ምንጭ፦ ገድለ ሐዋርያትና የመጋቢት 8 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ "#ሰላም_ለማትያስ_ዘተኀረየ_ወተፈቅረ። ህይንተ ይህዳ ይተኌለቊ ምስለ ሐዋርያት ኅቡረ። ከዊኖ #ማትያስ በላእለ እኩያን ኄረ። ሥጋ ወልደ አምላክ ሴሰዮሙ ወደሞ ክብረ። ተውላጠ ሴሰይዎ ሎቱ ከመ ላሕም ሣዕረ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_8።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እግዚአብሔር ያበርህ ሊተ ያድኅነኒ ምንትኑ ያፈርሀኒ። እግዚአብሔር ምእመና ለሕይወትየ ምንትኑ ያደነግፀኒ። ሶበ ይቀርቡኒ እኩያን ይብልዑኒ ሥጋየ"። መዝ 26፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 18፥35-ፍ.ሜ።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወጽአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ 18፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 2፥1-17 ይሁዳ 1፥17-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 1፥15-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥1-16። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የሐዋርያው የቅዱስ ማትያስ የዕረፍት በዓልና የጾም ወራት። በሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፰ (8) ቀን።
❤ እንኳን #ከዐሥራ_ሁለቱ_ሐዋርያት ለአንዱ በአስቆርቱ ይሁዳ ፈንታ ለተሾመው #ለቅዱስ_ማትያስ_ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ማትያስ፦ ይህ ሐዋርያ የአስቆሮቱ ይሁዳ የሰማይና የምድር ንጉሥ በሚሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሕማም ሰይጣንና ሠራዊቱ ያፍሩ ዘንድ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ እንዲህ ሆነ፤ ይሁዳ ግን ከፍጥረቱ ሁሉ ተለይቶ ምስኪንና ጐስቋላ ነበር። ጌታውን ክፋ ለሆኑ አይሁድ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ ሄደና ራሱን አጠፋ። ክብሩንም አጣ፤ ከሐዋርያት ዙፋንም ተጣለ። ስለእርሱም ማትያስን ሾመው። ቅዱስ ማትያስም ያስተምር ዘንድ ወደ ደማስቆ ወጣ። ዕጣም እንዲያስተምር ደርሶታልና። ቅዱስ ወንጌልንም አስተማራቸው።
❤ ይህም ሰውን ወደሚበሉ ሰዎች አገር ወንጌልን ይሰብክላቸው ዘንድ በሔደ ጊዜ ወዲያውኑ ይዘው ዐይኖቹን አውልቀው አሠሩት ምግባቸው የመጻተኛ ሰው በድን ስለሆነ ልማዳቸውም እንዲህ ነው። መጻተኛ ሰው ሲይዙ ዐይኖቹን አውልቀው በእሥር ቤት ያኖሩታል። የያዙበትንም ቀን ይጽፋሉ ሠላሳ ቀንም እስቲፈጸም ሣር ያበሉታል ከዚያ በኋላም አውጥተው አርደው ይበሉታል።
❤ ሐዋርያ ቅዱስ ማትያስም ታሥሮ ሳለ ሠላሳው ቀን ሳይፈጸም በጌታችን ትእዛዝ ሐዋርያው ቅዱስ እንድርያስ ወደርሱ ደረሰ የአገሩ ሰዎች የሚሠሩትን ክፋ ሥራ አይቶ አደነቀ እጅግም አዘነ እሥረኞችንም ሁሉ አውጥቶ የአገር ሰዎች ወደማያገኙአቸው ቦታ አኖራቸው። እነርሱ ግን ሁለቱ ሐዋርያት ቅዱሳን እንድርያስና ማትያስ ተገለጡላቸው የአገሩም ሰዎች ያዙአቸው በአንገታቸውም ገመድ አስገብተው እስከ ሦስት ቀን በአገሩ ጥጋጥግ ጐተቷቸው ሐዋርያት ስለዚያች አገር ሰዎች ስለድኅነታቸው ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ ያንጊዜ ከወህኒ ቤቱ ምሰሶ ሥር ውኃን አፈለቁ ውኃውም ከፍ ከፍ ብሎ በአገር ውስጥ እስከሚአጥለቀልቅና ወደ ሰዎች አንገት እስከ ደረሰ አየበዛ ሔደ። በተጨነቁና የሕይወታቸውን ተስፋ በቆረጡ ጊዜ ወደ ሐዋርያት መጡ በፊታቸውም ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ አለቀሱ ሐዋርያትም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመኑ እናንተም ትድናላችሁ አሉአቸው እሊያ ሁሉም በክብር ባለቤት በጌታችን አመኑ።
❤ ሐዋርያትም አሰተማሩአቸው ገሠጹአቸውም የአንድነትን የሦስትነትን የመድኃኒታችን ሰው የመሆኑን ምስጢር ገለጡላቸው ደግሞም ይህን የአራዊት ጠባይ ጌታችን ከእነርሱ ያርቅ ዘንድ ጸለዩላቸው ከዚህ በኋላ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቋቸው ያ የአውሬ ጠባይ ከእርሳቸው ርቆ ሰው የሚመገበውን የሚመገቡ የዋሆች ቅኖች ሆኑ። ኤጲስቆጶሳትን፣ ቀሳውስትና ዲያቆናትንም ሾሙላቸው በቀናች ሃይማኖትም እያጸኑዋቸውና እያስተማሩዋቸው ሠላሳ ቀኖች ያህል ከእርሳቸው ጋር ኖሩ ከዚህም ወጥተው ሔዱ። የአገር ሰዎች ግን በሌላ ጊዜ ወደ እነርሱ እንዲመለሱላቸው ሐዋርያትን ለመኑዋቸው።
❤ ከዚያም ሐዋርያው ቅዱስ ማትያስ ወደ ደማስቆ አገር በገባ ጊዜም "በኃጢአታቸው የወደቁትን እውነተኛ እግዚአብሔር የማያውቁትን ሰነፍ ሰዎች ሆይ አምላካችሁ ሌላ ሰው ሠራሽ ነው። ሰዎች ሁሉ እንደ እናንተ የወደቁ እንዲሆኑም ትሻላችሁ? በደማስቆ የምትኖሩ ሰዎች ሆይ ትምህርቴን ስሙ አማልክትን ማምለክም ተው። ስህተትን ክፋ መሥራትንም ከእናንተ አስወግዱ። ወደ ፈጣሪያችሁ ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ። ከእኔ ትምህርት የተነሣም ተመለሱ። እኔም ወደ እግዚአብሔር አቀርባችኋለሁ። እርሱ ለመንግሥቱ የተዘጋጃችሁ ያደርጋችኋል። የመላእክትን ሥርዓት አስተምራችሁ ዘንድም ወደ እኔ ተመለሱ። እስከ ዘለዓለሙ ድረስ ሕያዋን ትሆኑ ዘንድም የሕይወት ኅብስት እንዲሰጣችሁ ወደ እኔ ተመለሱ። የሰው ሥራ የሆኑ አማልክትንም እንቢ በሏቸው። የእውነተኛው አምላክ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ትሆኑ ዘንድም ከሰይጣናዊ ምክንያት ራቁ። ኢየሱስ ክርስቶስ የሰማይና የምድር ገዢ ነው፤ የወረደው፣ ያለወንድ ዘር በድንግል ማርያም ማኅፀን ያደረው የእግዚአብሔር ቃል ቀዳማዊ ነው፤ የአዳምን ዘር በክብሩ በገናናነቱ የማይታይ ሰይጣንን ከማምለክ ያድነው ዘንድም መከራን ተቀበለ፤ እንደ ሥጋዊ ልጅም በምድር አባት ያለው አይደለም፤ እርሱም ያለመለየት ከአባቱ ጋር አለ፤ እርሱ ሁሉንም በጥበቡ ያረጋጋል፤ ከመሬት አፈርን የወሰደና አዳምን ከአፈር የፈጠረውም እርሱ ነው፤ የመጀመርያው አባትም እርሱ ነው፤ ይህ አምላክም ፍጥረታት ሁሉ ነፍስ በእጁ ናት፤ እርሱ ይወዳቸዋል፣ መመለሳቸውም በቀናች ሃይማኖት በምታምር ሕሊና ነው፤ እርሱ አባቱና መንፈስ ቅዱስ አንድ ናቸው፤ሦስትም ናቸው፤ አንድ መለኮት አንድ ሥልጣን" አላቸው።
❤ በመጀመሪያ የማዝዛችሁም "ከርኵሰት ሁሉ ትርቁ ዘንድ ነው፤ እግዚአብሔር ንጽሕናችሁን እንዲመለከትና ሰማያዊትና መንፈሳዊት በሆነች በረከት እንዲባርካችሁ፣ በፍርድ ቀንም እንዲምራችሁ ከሴት ጋር አንድ መሆንን (መገናኘትን) አታብዙ" አላቸው።
❤ የአገሩ ሰዎችም ይህን ነገር ከእርሱ በሰሙ ጊዜ በምክንያቱና በክፉ ሥራው ሰይጣን በልባቸው አደረ። እርስ በእርሳቸውም "በእውነትም ይህ ሰው በአገሩ ከሚዞሩ ከዐሥራ ሁለቱ ጠንቋዮች ወገን ነው፤ ሴቶችን ከባሎቻቸው ይለያሉ ምን እንደምታደርጉት አስቡ" ተባባሉ። እነርሱም ተሰበሰቡ። ሐዋርያውንም ያዙትና አሰሩት። በብረት አልጋም አስቀመጡት። ሥጋው እስከ ሚሸት ድረስም በታቹ እሳት አነደዱበት እያንዳንዳቸውም ተመለከቱ። ቁመቱ ከአልጋው ዐሥራ አምስት ክንድ ሆኖ የእሳቱ ነበልባል ከፍ ባለ ጊዜም አደነቁ።
❤ በአደባባይ የቆሙና የተሰበሰቡ ሰዎችም "ይህ ሰው ጠንቋይ ቢሆን ኖሮ እነሆ በጠፋ ነበር" ተባባሉ። ከሦስት ቀን በኋላም ክፉ ተገባራቸው ይገለጣል። ሦስት ቀን ከሆነ በኋላም ቅዱስ ማትያስን ያስቀመጡበት የብረት አልጋ ካለበት ቦታ በደረሱ ጊዜ በእሳት ሳይቃጠል በሕይወትም አገኙት፤ ዓይኖቹም የተገለጡ ነበሩ፤ በጤናም አገኙት፤ ምንም ዓይነት ጥፋት አላገኘውም፤ በእርሱ ላይ ምንም ዓይነት የእሳት ሽታ አልነበረም፤ ልብሱም አልተቃጠለም።
❤ የአገሩየአገሩ ሰዎች ለተባለረከው ሐዋርያ የእግዚአብሔር ይህን ይቅርታ በተመለከቱ ጊዜ ከአገሩ ሰዎች ብዙዎቹ በእግዚአብሔር አመኑ። ይህ አምላካቸው ነውም አሉ። ሰባት ቀንም ስምንት ቀንም አለፈ። ቅዱሱ ግን በአልጋው ተኝቶ ነበር። የአገሩ ሰዎችም ሁሉ ይመለከቱት ነበር። በዚህም ከአገሩ ሰዎች ብዙዎች በትክክለኛዋ ሃይማኖት አመኑ። በተባረከው ሐዋርያ በቅዱስ ማትያስ ትምህርትም አመኑ። በትምህርቱ ያላመኑም ነበሩ። እሳቱም ሃያ አራት ቀን ይንቦገቦግ ነበር።
❤ ሐዋርያው ስሙን የሚጠራው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በቀንና በሌሊት ሁሉ ምንም እንዳይነካው ከክፉ ነገር ያድነው ነበር።በእርሱ ስም መከራን ተቀብሏልና። ከዚህ በኋላም ከእሳቱ አወጡት። ሥጋውም ሕያው(ጤነኛ) ነበር። ፊቱም እንደ ሕፃናት ፊት ነበር። ሁሉም ወደ እርሱ ይመለከቱ ነበር። እርሱ በእሳት ውስጥ አልነበረም። "ከራሱ ፀጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ ድረስ ጤነኛ ነውና" አሉ። በዚያችን ሰዓትም የአገሩ ሰዎች ብዙዎች አመኑ። በአገሩ ያሉትም ሁሉ ጮኹ "በቅዱስ ስሙየሚያምኑበትን ሁሉ ከአዳናቸው ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ከቅዱስ ማትያስ አምላክ ከእግዚአብሔር በስተቀር በሰማይም በምድርም ሌላ አምላክ የለም" አሉ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ #መጋቢት ፯ (7) ቀን።
❤ እንኳን ሰማዕትነት ሲቀበል በጨርቅ ዐይኑን ሊሸፍኑ ሲል "ይህ ሞትን ለሚፈሩ ነው እኔ ግን #በክብር_ባለቤት_በጌታዬ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ስም ሞትን አልፈራም" ብሎ አንገቱ በመሰየፍ ሰማዕትነት ለተቀበለ #ለቅዱስ_ቴዎዶጦስ ለዕረፍቱ በዓልና ለከበሩ #ለቅዱሳን_ፊልሞን_አብላንዮስ ሰማዕትነት ለተቀበሉት ለዕረፍታቸው በዓል መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ ከጻድቅ ንጉሥ #ከቅዱስ 9_ቴዎድሮስ ከዕረፍቱ መታሰቢያ ረደኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ቴዎዶጦስ፦ እርሱም ከገላትያ አገር የሆነ በምክርና በተግሣጽ አምልኮተ እግዚአብሔርንም በማጽናት ያደገ ነው። ወደ ከሀዲ መኰንንም ሒደው የክርስቲያን ወገን እንደሆነ ነገር ሠሩበት መኰንኑም አሥረው እንዲያመጡት አዘዘ። ቅዱስም ይህን በሰማ ጊዜ ሳይዙት ወደ መኰንኑ ሔዶ መኰንኑንና የረከሱ ጣዖቶቹን ረገመ ዘለፋቸውም መኰንኑ እሱን በማስፈራራት ሁኖ የሥቃይ መሣሪያዎችን ሁሉ አሳየው ለጣዖት እንዲሠዋ በመሸንገል አስገደደው ቅዱሱም ስለ ድንቁርናው ረገመው ዘለፈውም። ከዚህ በኋላ የውስጥ ዕቃው እስከሚታይ ሰቅለው ጐኖቹን ይሠነጣጥቁ ዘንድ መኰንኑ አዘዘ።
❤ ከዚያም ወደ ወህኒ ቤት ይጨምሩት ዘንድ ደግሞ አውጥተው በዕንጨት እንዲሰቅሉት ቊስሎቹንም እንዲአድሱ ጐኖቹንም እንዲሠነጣጥቁ አዘዘ። እርሱ ግን መኰንኑ የሚያመጣውን ሥቃይ እንደ ኢምንት አደረገው በክብር ባለቤት በጌታችን ክርሰቶስ በፍቅሩ ፍላጻነት ልቡ ተነጽፏልና ዓይኖቹም ወደላይ ይመለከቱ ነበር። መኰንኑም ብርታቱን በአየ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ።
❤ ቅዱስ ቴዎዶጦስ የራሱን መቆረጥ ሰምቶ እጅግ ደስ እያለው ወጣ። ወደ እግዚአብሔርም ሲጸልይና ሲማልድ እንዲህ አለ "የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርሰቶስ ሆይ አመሰግናለሁ ከተከታተለኝ ክፉ ነገር ሁሉ አድነኸኛልና በጠላትነት የተነሡብኝም ወደ ገሃነም አወረድካቸው እኔንም ከሞት በር ከፍ ከፍ አደረግኸኝ"። ይህንንም ብሎ በሰገደ ጊዜ ወታደሩም የቅዱሱን ዐይን ይሸፍን ዘንድ መሸፈኛ አመጣ። ቅዱሱም "ይህ ሞትን ለሚፈሩ ነው እኔ ግን በክብር ባለቤት በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሞትን አልፈራም" አለ። ወታደሩም ሰይፍን መዝዞ የከበረች ራሱን መጋቢት 7 ቆረጠ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበለ። የቅዱስ ቴዎዶጦስ በረከቱም በላያችን ትደር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ለቅዱሳን_ፊልሞንና_አብላንዮስ፦ ይህ ፊልሞንም በእንዴናው ገዥ በሆነ በአርያኖስ ፊት በአዝማሪነት ይጫወት ነበር። ከአዝማሪው አብላንዮስ ጋራ እርስበርሳቸው ወዳጆች ሆኑ ለክብር ባለቤት ክርስቶስም ስለ ስሙ ምስክሮች ሊሆኑ ተስማሙ።
❤ አዝማሪው ፊልሞንም ልብሱን ወስዶ ለአብላንዮስ ሰጠው እርሱም የአብላንዮስን ልብስ ለብሶ ወደ መኰንኑ ወደ አርያኖስ ገብቶ በፊቱ ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ። መኰንኑም ተመልክቶ አዝማሪው አብላንዮስ እንደሆነ አሰበ በፍላጻም እንዲነድፋት አዘዘ ያንጊዜም አዝማሪው ፊልሞን መሆኑን አውቆ እጅግ ተቆጣ። ደግሞ አብላንዮስን እንዲነድፉት አዘዘ ሁለቱንም ነድፉቸው አንዲት ፍላጻም ወደ መኰንኑ ተመልሳ ዓይኑን አወጣቻት እጅግም አሠቃየችው።
❤ የከበሩ ፊልሞንና አብላንዮስ ግን ገድላቸውን መጋቢት7 ፈጽመው የሕይወት አክሊልን ተቀበሉ። የቅዱሳን ፊልሞንና አብላንዮስ በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 7 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ "#ሰላም_ለአብላንዮስ_ክርስቲያናዊ እምንዕሱ። #ለፊልሞን_ጸጋ_እንተ_ወሀበ_በልብሱ። በበሊሕ ሐፅ እምድኅረ ተመትረ ማዕሱ። መታሬ ሥጋሁ ሶበ ቀበላ ለፈውሱ። ምክንያተ ሚጠት ኮነቶ ለዕልው እምርኵሱ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት ፯ (7)
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ ከዘጠኙ ንዑስ በዐላት አንዱ ለሆነው ለዐቢይ ጾም አምስተኛ ሳምንት #ለደብረ_ዘይት እግዚአብሔር በሰላም በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የደብረ_ዘይት_መዝሙር፦ "እንዘ ይነብር #እግዚእነ_ውስተ_ደብረ_ዘይት ወይቤሎሙ #ለአርዲኢሁ_ዑቁኬ_ኢያስሕቱክሙ ወንበሩ ድልዋኒክሙ ብዙኃን ይመጽኡ በስምየ እንዘ ይብሉ #አነ_ውእቱ_ክርስቶስ ወዘአዝለፈ ትዕግሥቶ ውእቱ ይድኅን #ወአመ_ምጽአቱሰ_ለወልደ_እጓለ_እመሕያው ይትከወስ ኵሉ ኀይለ ሰማያት ወምድር አሜሃ ይበክዩ ኵሎሙ ኀጥአነ ምድር። #ወይወርድ_እግዚእነ እምሰማይ ዲበ ምድር በትእዛዙ ወበቃሉ #ወበአዕላፍ_መላእክቲሁ በንፍሐተ ቀርን #ዘእምኀበ_እግዚአብሔር_ይምሐረነ_አብ በይእቲ ሰዓት እሞተ ኃጢአት እስመ ገባሬ ሕይወት ውእቱ #እግዚአ_ለሰንበት። ትርጉም፦ #ጌታችን_በደብረ_ዘይት_ተራራ ላይ ተቀምጦ ሳለ #ለደቀ_መዛሙርቱ_ማንም_እንዳያስታችሁ_ተጠንቀቁ፤ ተዘጋጅታችሁም ኑሩ፤ #ብዙዎች_እኔ_ክርስቶስ_ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉ፤ እስከ መጨረሻው የጸና እርሱ ይድናል። የሰው ልጅ በሚመጣበት ጊዜ የሰማያትና የምድር ኃይላት ሁሉ ይናወጣሉ። ያን ጊዜ በምድር ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ ያለቅሳሉ አላቸው። #ጌታችንም_ከባሕርይ_አባቱ_ከእግዚአብሔር_አብ ዘንድ በመለከት ድምጽ #ከአእላፍ_መላእክት ጋር #በግርማ_መለኮቱ ከሰማይ ወደ ምድር ይወርዳል። በዚች ዕለት ሞትን ከሚያስከትል ኃጢአት #አብ_ይማረን_የሕይወት_ባለቤት_የሰንበትም_ጌታ_ነውና። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።
❤ "#ደብረ_ዘይት"
❤ ትርጉሙ፦ ደበረ ዘይት ትርጉሙ የወይራ መብቀያ፣ በወይራ ደን የተሸፈነ ተራራ ማለት ነው። ወይም "ደብር" ማለት "ተራራ" ማለት ሲሆን "ዘይት" ማለት ደግሞ "ወይራ" ማለት ነው። በተገናኝ "ደብረ ዘይት" ማለት የወይራ ዛፍ የሞላበት፣ የበዛበት፣ የወይራ ተራራ ማለት ይሆናል።
❤ ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ የሚገኝ ቦታ የሚገኝ ተራራ ሲሆን በመካከል የቄድሮን ሸለቆ ብቻ ነው ያለው። ከግርጌው ጌቴ ሴማኒ የተባለው የአትክልት ስፍራ ይገኛል። የጸሎተ ሐሙስ ማታ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተያዘበትና በኋላም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሥጋዋ ያረፈበት ወይም የድንግል መካነ መቃብር በዚህ ተራራ ግርጌ ይገኛል። ቤተ ፋጌ እና ቢታንያ በኮረብታው ጫፍ እና በምስራቅ ዳገታ ላይ ይገኛሉ።
❤ ይህ ተራራ በመጽሐፍ ቅዱስ የሚገኙ ብዙ ድርጊቶች የተደረጉበት ቦታ ነው። ጌታችን ስለ ቤተ መቅደሱ መፍረስ፣ ስለ ዓለም ፍጻሜና ስለ ዳግም ምጽአት በዚህ ተራራ ላይ በትንቢት መልክ ተናገረ (ማቴ 24፥3)። በዚሁ ተራራ ላይ ወደ ሰማይ ዐረገ (ሉቃ 24፥50)። በዚሁ ተራራ ላይ ቀን በከታማና በገጠር ሲያስተምር ውሎ ሌሊት የሚያድርበት የኤሌዎን ዋሻ ይገኛል።
በኋለኛው ምጽአቱ በዚሁ ቦታ እንደሚገለጥ ትንቢት ተነግሯል።(ዘካ 14፥3-5)።
❤ ስያሜው፦ የዐቢይ ጾም እኩሌታ ላይ ያለው ሰንበት በዚህ ተራራ ተጠርቷል። ይህንን ዕለት የቤተ ክርስቲያናችን ሊቅ ቅዱስ ያሬድ የዳግም ምጽአት አድርጎ መዝሙሩን ጽፏል። በዚህ ተራራ ላይ «እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው። ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት» (ማቴ.24፥3)። ተብሎ እንደተጻፈው
ለደቀ መዛሙርቱ የደግም ምጻቱን፣ የዓለምን ፈጻሜ፣ የትንሣኤ ሙታንን፣ ትምህርት በሰፊው ስላስተማረ በዓሉ በተራራው ስም ተሰይሟል።
❤ አመጣጡስ እንዴት ነው?
❤ ጌታ ይህንን ዓለም ለማሳለፍ ለሁሉም እንደ ሥራው ለመክፈል በግርማ መለኮቱ በክበበ ትስብዕቱ ይመጣል፡፡ ጊዜው ዘመነ ዮሐንስ ወርኃ መጋቢት ዕለተ እሑድ መንፈቀ ሌሊት እንደሆነ ሊቃውንት ተናግረዋል፡፡
ምነው "የሚያውቀው የለም ይል የለምን" ቢሉ እውነት ነው የሚያውቀው የለም ብዙ የዮሐንስ ዘመን ብዙ የመጋቢት ወር ብዙ የእሑድ ዕለት የበዙ ሌሊቶች አሉና ለይቶ የሚያውቅ የለም ለማለት ነው፡፡
❤ ሞት ለማንም አይቀርምና ሁሉም ይሞታል፡፡ ዘፍ 3፥19 በዕለተ ምጽአትም ቅዱስ ገብርኤል ስምንቱን ነፋሳተ መዓት ከየመዛግብታቸው ያወጣቸዋል፡፡ ዛፍን ነቅለው ድንጊያውን ፈንቅለው ምድርን እንደብራና ይዳምጧታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ነጋሪቱን ይመታል 1ኛ መቃብ 9፥8 ነጋሪት የተባለው በቁሙ ነጋሪት የሚመታ ሆኖ ሳይሆን አዋጁን የምትክ ንቃ የሚል አዋጅ የሚናገር ይታወጃልና ነጋሪት ይመታል አለ።
❤ ስለዚህ ቅዱስ እግዚኣብሔር ቅዱስ "ዘያነቅሖሙ ለሙታን" ሲል በዱር በገደል በባህር በየብስ በመቃብር ውስጥ ያሉት በአውሬ ሆድ ውስጥ ያሉ ሁሉ ይሰበሰባሉ፡፡ በሁለተኛው ነጋሪት ሲመታ አጥንትና ሥጋ አንድ ሆነው ፍጹም እንደ ዕለት በድን ይሆናሉ፡፡
ሦስተኛው ነጋሪቱን መትቶ "ቅዱስ እግዚኣብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ህያው ዘኢይመውት" "ንቃሕ መዋቲ ዘትነውም" ባለ ጊዜ መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ደጉ ደግነቱን ክፉውም ክፋቱን ይዞ ይነሳል፡፡
❤ ወንዱ የ30 ዓመት ሴቲቱ የ15 ዓመት ሆነው ጻድቃን ብርሃን ለብሰው ብርሃን ተጎናጽፈው ከፀሐይ 7 እጅ አብርተው ማቴ 13፥43 ኃጥአን ጨለማ ለብሰው ፍጹም ዲያብሎስን መስለው ይነሳሉ፡፡ ጻድቃን ስለሠሩት መልካም ሥራ ኑ የኣባቴ ብሩካን ብሎ መንግሥተ ሰማያትን ያወርሳቸዋል፡፡ ኃጥኣንን ስለክፋ ሥራቸው /ከኔ ሂዱ/ ብሎ ገሃነም ይሰዳቸዋል፡፡ ጻድቃን ደስ ይላቸዋል ኃጥአን ግን ያዝናሉ ዋይ ዋይ እያሉ ደረት ይደቃሉ እንባቸውን ያፈሳሉ፡፡ የማይጠቅም ልቅሶ የማይረባ ኃዘን ነው ሰቅለው የገደሉትም አይሁድ ክብሩን 0ይተው ላይጠቀሙ ይጸጸታሉ፡፡
❤ በዳግም ምጽአቱ ጊዜ አምላከ ቅዱሳን ልዑል እግዚአብሔር ከቅዱሳኑና ከሰማዕታቱ ጋር ለመቆም ያብቃን አሜን። ምንጭ፦ አምኃ ሥላሴ (መኩሪያ ተስፋዬ) ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ።
✝️ ✝️ ✝️
❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "እግዚአብሔርሰ ገሀደ ይመጽእ። ወአምላክነሂ ኢያረምም"። እሳት ይነድድ ቅድሜሁ። መዝ 49፥3። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ተሰ 4፥13-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 3፥7-15 እና የሐዋ ሥራ 24፥1-22። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 24፥1-36። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ አትናቴዎስ ቅዳሴ ነው። መልካም የደብረ ዘይት በዓልና የጾም ወራት። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፭ (5) ቀን።
❤ እንኳን #የስሟ_ትርጓሜ_ሰላምና_መወደድ ለሆነ ለከበረች #ለቅድስት_አውዶክሲያ ሰማዕትነት ለተቀበለችበት ለዕረፍቷ በዓልና በአስቄጥስ ገዳም #በአባ_ዮሐንስ_ደብር_አበ_ምኔት ለነበረው ለክቡር ቅዱስ መናኝና ገድለኛ ለሆነ #ለአባ_ሰራባሞን ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታበው፦ #ከአባ_ግርማኖስ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅድስት_አውዶክሲያ፦ የስሟ ትርጓሜ ሰላምና መወደድ ማለት ነው። ይህችም የተወደደች ቅድስት በሊባኖስ ተራራዎች አቅራቢያ በበስራ አውራጃ ወገን ነበረች። እርሷም በሮም ንጉሥ በጢባርዮስ ዘመነ መንግሥት ነበረች። የአባቷም ስም ዮናስ የእናቷም ስም ጠባቢት ይባላል። የቀደመው ኑሮዋ በዝሙትና በርኵሰት ነበር። ብዙዎችን አሳስታ ከእርሷ ጋራ በኃጢአት ትጥላቸው ዘንድ ፊቷን ታሳምር ነበር። መልኳንም ታስጌጥ ነበር። በዚህ በረከሰ ሥራም ብዙ ገንዘብ ሰበሰበች።
❤ በኢየሩሳሌምም የሚኖር ስሙ አባ ግርማኖስ የሚባል አንድ ጻድቅ መነኰስ ዝናዋን ሰምቶ ወደ ርሷ መግባት በለመዱ ሰዎች አምሳል ሆኖ ወደርሷ ገባ። ገብቶም ከርሷ በቤት ውስጥ ተቀመጠ ፈጽሞ በሚያስፈሩ ቃሎች ሊመክራትና ሊገሥጻት ጀመረ በገሀነምም ትሉ የሚያንቀላፋ እሳቱ የማይጠፋ ጨለማው የሚዳሠሠ የሚመስል በየአይነቱ የሚአስፈራ ሥቃይ መኖሩን አሳሰባት። እርሷም "ከሞቱ በኋላ የሰዎች በድኖች አፈርም ከሆኑ ተነሥተው ይሠቃያሉን?" ብላ መለሰችለት። እርሱም "አዎን" አላት። እርሷም "ለዚህ ለምትነግረኝ ነገር ምልክቱ ምንድነው እግዚአብሔር ለሙሴ በሰጠው ኦሪት አልተጻፈ አባቶቻችንም ይህን አላመኑም" አለችው። እርሱም "በፍርድ ቀን ሙታን እንደሚነሡ ስለ ኃጥአንም ሥቃይ ስለጻድቃንም ተድላ ደስታ በኦሪት መጽሐፍና በሐዲስ ኪዳን መጽሐፍ ተጽፎ እንዳለ" ገለጠላት።
❤ ትምህርቱና ተግሣጹ በልቧ አደረ ፍርድ ቀንም ሙታን እንደሚነሡ አመነች እንዲህም አለችው "ከዚህ ከረከሰ ሥራ ብመለስ እግዚአብሔር ይቀበለኛልን?" አለችው። አባ ግርማኖስም "ወደ ዓለም እንደመጣና ተሰቅሎ ደሙን በማፍሰስ ኃጢአታችንን እንዳራቀልን በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካመንሽ ስለዚህ የነጻችና የጸናች ንስሓ ይሆንልሻል የክርስትና ጥምቀትንም ተጠመቂ እግዚአብሔርም ይቀበልሻል አስቀድመሽ ከሠራሽው ኃጢአት ምንም ምን አያስብብሽም ከእናትሽ ማሕፀን እንደተወለድሽበት ቀን ትሆኛለሽ እንጂ። የክብር ባለቤት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቀናች ሃይማኖት ደጆችም ይከፈቱልሻል" አላት።
❤ ያንጊዜም የክርስትና ጥምቀትን ያጠምቃት ዘንድ ለመነችው እርሱም ወደ በአልበክ ኤጲስቆጶስ ወስዶ አደረሳት እርሷም በኤጲስቆጶሱ ፊት ልዩ ሦስትነት በመድኃኒታችን ክርስቶስም ሰው በመሆኑና ሙቶ በመነሣቱ አመነች። ኤጲስቆጶሱም ተነሥቶ በውኃው ላይ ጸልዮ አጠመቃት እግዚአብሔርም ዐይነ ልቡናዋን ገልጦላት ብሩህ መልአክ ወደ ውኃው ሲስባት ሌሎች መላእክትም ስለእርሷ ፈጽመሸ ደስ ሲላቸው ተመለከተች።
❤ ከዚህም በኋላ ገጻቸው የሚያስደነግጥ ጥቋቊሮችን አየች ከእርሷቸው አንዱ መልኩ የከፋ ሲጐትታት እርሱም በርሷ ላይ ይቆጣ ነበር። ይህንንም ራእይ በአየች ጊዜ የክርስትና ሃይማኖት ፍቅር በልቧ ተጨመረ ኃጢአት በመሥራት የሰበሰበችውን ገንዘቧን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች ሰጠች ከደናግል ገዳማትም ወደ አንዱ ገብታ ፍጹም የሆኑ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለች። ከአጋንንት ጋራ ተዋጋች። ሰይጣንም አስቀድሞ ከእርሷ ጋር ሲያመነዝሩ ከነበሩ በአንዱ ሰው ልብ አደረ ወደ መኰንኑ ሔዶ ነገር ሠራባት መኰንኑም ወደርሱ እንዲያቀርቧት አዘዘ። በደረሰችም ጊዜ ከደጅ ቆመች በሞተው በመኰንኑ ልጅ ገብታም ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጸለይ ማለች የሞተውን የአገረ ገዥውንም ልጅ ከሞት አስነሣችው። መኰንኑም ይህን ድንቅ ተአምር በአየ ጊዜ እጅግ አደነቀ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በእርሷ ምክንያት ፍጹም የጸና እምነትን አመነ።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ሰረባሞን፦ ይህም ቅዱስ በአስቄጥስ ገዳም በአባ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከልጅነቱ ጀምሮ መነኰሰ ቅዱሳን አረጋውያንንም እያገለገለና ሠላሳ ሁለት ዓመት ያህልም ብዙ ተጋድሎን እየተጋደለ ኖረ። ከዚህ በኋላ በዚሁ በአባ ዮሐንስ ገዳም አበ ምኔት ሁኖ ተሾመ። የተጋድሎውንም ሥራ አበዛ ከመነኰሰበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዐረፈበት ጊዜ ድረስ ሁል ጊዜ ይጸልይና ይጾም ነበር።
❤ በካህናት አለቃ ሹመት ሃያ ዓመት ከኖረ በኋላ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ራሱን እሥረኛ አደረገ። እኒህም ዐሥራ አምስት ዓመታት እስቲፈጸም ከቶ ከሰው ማንንም አላየም ከቅዳሜና ከእሑድ ሰንበት በቀር አይበላም አይጠጣም ነበር።
❤ ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በሕልም ታየው። ይህን መስቀል ያዝ ብሎ የእሳት መስቀል ሰጠው። ቅዱሱም "እሳትን መያዝ እንዴት ይቻለኛል" ብሎ መለሰለት። መልአኩም "አትፍራ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ክርስቶስ በአንተ ላይ ለእሳት ሥልጣንን አልሰጣትም" ብሎ መለሰለት። የጸናች እጁንም ዘርግቶ ያንን መስቀል ከመልአኩ እጅ ተቀበለው። ሁለተኛም መልአኩ እንዲህ አለው "በርታ ሥጋውንና ደሙንም ተቀበል። እስከ ዐሥርም ቀን ድረስ መጥቼ እወስድሃለሁ"።
❤ ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ለቅዱሳን አረጋውያን ነግሮ ተሰናበታቸው እነርሱም አለቀሱ በእግዚአብሔር ፊት እንዲአሳስብላቸው ለመኑት እርሱም ደግሞ በጸሎቶቻቸው ሁል ጊዜ እንዲአስቡት ለመናቸው። ከዚህም በኋላ ሥጋውና ደሙን ተቀበለ። ቅዱሳን አረጋውያንም ከእርሱ ጋር እያሉ መጋቢት 5 ቀን በሰላም አረፈ። እንደሚገባም በዝማሬና በብዙ ጸሎት ማኅሌት ገንዘው በጻድቃን መቃብር ቀበሩት። እግዚአብሔር በአባ ሰረባሞን በጸሎቱ ለዘላለሙ ይማረን አሜን።
❤ ከእርሱ በኋላም ስለ እርሱ ስሙ ዲዮግኖስ የሚባል ሌላ አገረ ገዥ ተሾመ የዚችንም ድንግል ዜናዋን ሰምቶ ወደርሱ አስመጣት። እርሷም በአደባባይ ውስጥ አንድ ዐይና የሆነ ጐልማሳ አየች ጸለየችና በመስቀል ምልክት በዐይኑ ላይ አማተበች ያንዜም ዐይኑ ተገለጦ አየ። ያደረገችውን ይህን ድንቅ ሥራ አይቶ ድንግሊቱን ወደ ቦታዋ መለሳት።
❤ ከእርሱም በኋላ ደግሞ ሌላ ስሙ በከኒቶስ የሚባል አገረ ገዥ ተሾመ እርሱም ዝናዋን ሰምቶ ይቺን ቅድስት አውዶክስያን ወደርሱ አስመጣት ሊያሠቃት ፈልጎ። እርሷም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቲያን ዕድሏን ከሰማዕታት ጋራ ይሰጣት ዘንድ ለመነችው እግዚአብሔርም ልመናዋን ተቀበለ። ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ መኰንኑ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነትን አክሊል ተቀበለች የቅድስት አውዶክስያ ጸሎቷና በረከቷ ለዘላለሙ ከእኛ ጋር ይኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 5 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለአውዶክስያ_ከመ_ትፍዲ_ፍዳ። በመጥባሕት በሊሕ እስከ መተሩ ክሣዳ። እስመ ተሊወ ጽድቅ አብደረት በኀዲገ እኩይ ልማዳ። ነጸረት ለተጠምቆ ኀበ ቀላየ ማይ ያወርዳ። እንዘ ይስሕባ #መልአክ_ቀዊሞ በዐውዳ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_5።
ወደየበዓታቸው ተመልሰው ሄዱ፡፡
❤ በመጨረሻም ከዚህ ዓለም የሚለዩበት በቀረበ ጊዜ እንሆ የክበር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እነሆ ተገለጠላቸው። ስማቸውን ለሚጠራና መታሰቢያቸውን ለሚያደርግ እስከ ዐሥራ አምስት ትውልድ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጣቸው። ዐሥራ ሁለት አክሊል ሰጣቸው። ቅዱስ ሚካኤል ሦስት አክሊሎች፣ ቅዱስ ገብርኤል ሦስት አክሊሎች፣ ቅዱስ ሱራፊ ሦስት አክሊሎችና ቅዱስ ኪሩብ ሦስት አክሊሎችን አቀዳጇቸው። የዕድሜያቸውም ዘመናት አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ሲሆን መጋቢት5 በሰላም በፍቅር ዐረፉ። ጌታችንም ነፍሳቸውን ተቀቡሎ አቅፎም ሳማት በመላእክትና በቅዱሳን ሁሉ ምስጋና አሳረጋት። ከአባትችን ከአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ የመጋቢት 5 ስንክሳርና ገድለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወትከይድ አንበሳ ወከይሴ። እስመ ብየ ተወከለ አድኅኖ። ወእከድኖ እስመ አእመረ ስምየ"። መዝ 90፥12-14። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 21፥33-ፍ.ም።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር። እግዚኦ አነ ገብረከ። ገብረከ ወልደ ዓመትከ"። መዝ 115፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 14፥1-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 4፥1-12 እና የሐዋ ሥራ 17፥19-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 6፥19-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዠ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የዕረፍት በዓልና ወራት ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ አባታችንም የኢትዮጵያን ሰዎች ኃጢአታቸውን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ ተወርውረው ወደ ባሕሩ በመግባት ተዘቅዝቀው መጸለይ ጀመሩ፡፡ "ከባሕር እንዳልወጣ፣ በእግሬም እንዳልቆም በሕያው ስምህ ምያለሁ" ብለው አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ቆዩ፡፡በ40ኛ ቀናቸው የታዘዘ መልአክ መጥቶ "ስምህን የጠራ መታሰቢያህን ያደረገውን እምርልሃለሁ ብሎሃ" አላቸው፡፡ አባታችንም መልአኩን "መላ ኢትዮጵያን ካልማረ ከዚህ ባሕር አልወጣም" አሉት፡፡ መልአኩም ከእሳቸው ተለይቶ ከሄደ በኋላ አባታችን በዚያ ባሕር ውስጥ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ሲጸልዩ ኖሩ፡፡
❤ አባታችንም በባሕሩ ውስጥ ተዘቅዝቀው መቶ ዓመት ሲጸልዩ ከኖሩ በኋላ ደማቸው ፈሶ አለቀና ውኃው ደም መሰለ፡፡ ሥጋቸውም አልቆ አጥንቶቻው እንደበረዶ ሆኑ፡፡ ሰባት ሺህ እልፍ ሦስት መቶ የሚሆኑ አጋንንትም ከአራቱም አቅጣጫ እየመጡ ሰውነታቸውን በፍላፃዎቻቸው ይወጓቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ወደ አባታችን መጥቶ ከባሕሩ ዳር በመቆም "ወዳጄ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! መላ ኢትዮጵያን ምሬልሃለሁና ተነሥ ከባሕሩ ውጣ" አላቸው፡፡ አባታችንም አጥንታቸው እንደመርፌ ቀዳዳ ተበሳስቶ ፈጽመው ደክመው ነበርና ጌታችን በክቡራን እጆቹ ሁለንተናቸውን ቢዳስሳቸው እንደቀድሞው ደህና ሆኑ፡፡ጌታችንም ከባረካቸው በኋላ ወደ ምድረ ከብድ እንዲሄዱ ነገራቸው፡፡
❤ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ምድረ ከብድ እንደደረሱ እንደ ዓምድ ተተክለው ሰባት ዓመት ቆመው ጸለዩ፡፡በዚህም ጊዜ ሰይጣን በቁራ ተመስሎ መጥቶ ሁለት ዐይኖቻቸውን አንቁሮ አጠፋቸው ነገር ግን አባታችን ጸሎታቸውን ሳያቋርጡ ሁለት ሳምንት በጸሎት ቆዩ፡፡ ከ2 ሳምንት በኋላ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል መጥተው በዐይኖቻቸው ላይ እፍ ብለው ብርሃናቸውን ከመለሱላቸው በኋላ አባታችንን "ከሰማይ ፍጹም ኃይል ይሰጥሃልና ጠላቶችህን ትበቀል ዘንድ ወደ ዝቋላ ሂድ" ብለዋቸው ዐረጉ፡፡
❤ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስም እንደታዘዙት ወደ ዝቋላ እየሄዱ ሳለ በመንገድ ላይ ከዛፍ ሥር ያረፉ ሦስት ሽማግሌዎችን አገኙ፡፡ አባታችንም ባዩአቸው ጊዜ ለመሰወር ቢያስቡም ሽማግሌዎቹ ግን ይመጡ ዘንድ ጠሯቸውና "በእግዚአብሔር ዙፋን ተማጽነናል ሦስታችንንም በጀርባህ አዝለህ አንድ አንድ ምዕራፍ ሸኘን" አሏቸው፡፡ አባታችንም ሽማግሌዎቹን በቀረቧቸው ሰዓት ሽበት የከበባቸው የደከሙ ሽማግሌዎች ሆነው አገኟቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን አንደኛውን ሽማግሌ አዝለው ከአንድ ምዕራፍ አደረሷቸው፡፡ ያም ሽማግሌ "ከዚህ አሳርፈኝ፣ አንተ ደክመሃል የማትበላ የማትጠጣ ነህና" አሏቸው፡፡አባታችንም "አባ የት ያውቁኛል?" አሏቸው፡፡ሽማግሌውም "አሁን ደግሞ ሄደህ ጓደኞቼን አምጣልኝ" አሏቸው፡፡ አባታችንም የቀሩት ሁለቱ ሽማግሌዎች ካሉበት ደርሰው ሁለቱንም በየተራ እያዘሉ የመጀመሪያውን ካደረሱበት ቦታ አደረሷቸው፡፡ከዚህም በኋላ እነዚያን ሽማግሌዎች "አባቶቼ ሆይ! ከየት ነው የመጣችሁት?" አሏቸው፡፡ ሦስቱም ሰዎች ተነሥተው ቆሙና ለአባታችን በአንድነት በሦስትነት ተገለጡላቸው፡፡ አንድ ሲሆኑ ሦስት ሦስት ሲሆኑ አንድ ሆኑ፡፡ ሥሉስ ቅዱስ ለአብርሃም በመምሬ አድባር ሥር በአንድነት በሦስትነት እንደተገለጡለት ሁሉ አሁንም ለአባታችን ለገብረ መንፈስ ቅዱስ በአንድነት በሦስትነት ተገለጡላቸው፡፡ በጀርባቸውም አዘሏቸው፡፡ የእግዚአብሔርንም ክብር ስላዩ አባታችን ፊታቸው እንደፀሐይ አበራ፡፡ ቅዱሳን መላእክት ወርደው እንደሻሽ ተነጥፈው ሲያመሰግኑ ሰማይና ምድር ተነዋውጠው ተራሮች ኮረብቶች ዓለቶች ተሰነጣጠቁ፡፡ በዚያችም ሰዓት ታላቅ ፍርሃት ሆነ፡፡ አባታችንም ዙሪያቸውን በከበባቸው በምሥጢራት ጎርፍ ተውጠው ተንቀጥቅጠው በግንባራቸው ወደቁና እንደ በድን ሆኑ፡፡በራእይ ውስጥም ሆነው እነዚያ ሽማግሌዎች አባታችንን እስከ ሰባተኛው ሰማይ እንዳደረሷቸው ተመለከቱ፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን እንደ ቅዱስ ጴጥሮስን እንደቀሰቀሳቸው አባታችንንም ቀሰቀሳቸውና "ወደ ዝቋላ ውረድ መቶ ዓመት ሙሉ አጥንትህን ሥጋህን እየነደፉ የተዋጉህን አጋንንት ታጠፋቸው ዘንድ፡፡ እነሆ እኔ እንደወሰድኩህ ባለማወቃቸው በትዕቢት ላይ ናቸውና "በባሕር ውስጥ አለ" ይሉሃል፡፡ ሰባቱ ሊቃነ መላእክት ይረዱሃል፤ መባርቅትም በፊት በኋላ ይከተሉሃል" አላቸው፡፡
ያንጊዜም አባታችን በመብረቅ ላይ ሆነው እነዚያ አጋንንት ወዳሉበት ወረዱ፡፡ አጋንንቱንም ደመናት ከበቡአቸው፣ መላእክትም በእሳት ሰይፍ መተሩአቸው፣ በመብረቅ አጨዷቸው፤ አመድ ሆነው በነፋስ በተኗቸው፡፡ የእነዚያም አጋንንት ቁጥራቸው ሰባ ሺህ እልፍ ከአንድ ሺህ ነበር፡፡ ሁሉም በአንድ ጊዜ አልቀዋልና ከእነርሱ ሸሽቶ ያመለጠም አልነበረም፡፡ ሰባቱ ሊቃነ መላእክትም ወደ ሰማይ ዐረጉ፡፡ አባታችንም አንበሶችና ነብሮች፣ ድብና ዘንዶ ወዳሉበት ምድረ ከብድ ተመለሱ፡፡
❤ አባታችንም ወደ ምድረ ከብድ ከተመለሱ በኋላ መንፈስ ቅዱስ የጠራቸው ሦስት ቅዱሳን ሁሉም በየአንበሶቻቸው ላይ ተቀምጠው ወደ ምድረ ከብድ መጡ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን የዋልድባው አቡነ ሳሙኤል፣ የአዘሎው አቡነ አንበስ እና ከላዕላይ ግብፅ ተነሥቶ የመጣው አቡነ ብንያም ናቸው፡፡ ነገር ግን አባታችን እነዚህን ቅዱሳን ስለተሰወሯቸው ቅዱሳኑ እስከ ሰባት ቀን ድረስ በምህላ ሰነበቱ፡፡ የአባታችን የሚያስፈሩ አንበሶች ወጥተው የቅዱሳኑን አንበሶቻቸውን ገድለው ደማቸውን አፍስሰው ሥጋቸውን በሉ፡፡ ሦስቱም ቅዱሳን በዚህ ፈጽመው ደንግጠው ሳለ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ 60 ነብሮችንና 60 አንበሶችን አስከትለው ተገለጡላቸውና "ሰላም ለእናንተ ይሁን የእግዚአብሔር ቅዱሳኑ አትፍሩ" አሏቸው፡፡ ቅዱሳኑም "አባታችን ሆይ! ጸሎትህ ቅድስት እንደሆነች ባወቅን ጊዜ በእግዚአብሔር ፈቃድ እንባረክ ዘንድ ወደ አንተ መጣን፡፡ ነገር ግን ባላገኘንህ ጊዜ እስከ ሰባት ቀን አለቀስን" አሏቸው፡፡ ዳግመኛም "የእርስዎም አንበሶች መጥተው አንበሶቻችንን በሉብን" አሏቸው፡፡ አባታችንም አንበሶቻውን "እስከ ዕለተ ሞቴ ድረስ በእግሬ ከረገጥኩት ምድር በቀር እግዚአብሔር ያላዘዛችሁን ለምን በላችሁ? አሁንም የበላችሁትን ትፉ" አሏቸው፡፡ እነዚያም አንበሶች አፋቸውን ከፈቱና የበሉትን የአንበሶቹን ሥጋቸውን አጥንታቸውን ከደም ጋር ተፉ፤ በሆዳቸውም የቀረ የለም፡፡ አባታችንም ወዲያው ወደ ምሥራቅ ዞረው እግዚአብሔር ካመሰገኑ በኋላ "አቤቱ አልዓዛርን ከሞት ያስነሣኸው አንተ ነህና አሁንም እነዚህን አናብስት ከሞት አስነሣቸው፤ ለባሮችህም የድካማቸውን ማረፊያ ይሆኑላቸው ዘንድ የሰጠሃቸውን አትከልክላቸው… " እያሉ ጸለዩ፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ብለው ጸሎታቸውን ከጨረሱ በኋላ የአንበሶቹን ሥጋቸውን በመስቀል ምልክት ባርከ "በጌታዬ በፈጣሪዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ተነሡ"አሏቸው፡፡ አንበሶቹም እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥነው ተነሡና እንደቀድሞው ሆኑ፡፡ ለአባታችንም እጅ ነሥተውና ሰግደው የእግሩን ትቢያ ላሱ፡፡ አባታችንም ወደ ጌቶቻቸው መለሳቸው፡፡
❤ እነዚህም ሦስቱ ቅዱሳን በአባታችን ላይ አድሮ ድንቅ ነገርን የሚሠራ እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ የዋልድባው አቡነ ሳሙኤልም አባታችንን "አባት ሆይ በዚህች ቀን ድንቅ ሥራን አየን፣ አርአያህ የእግዚአብሔርን መልአክ አርአያ ይመስላል፣ ቅድስናህ ፍጹም ነው፣ የጸሎትህ ኃይል ሙታንን ያስነሣል፣ የተበሉ አንበሶችን ከአንበሶች ሆድ አወጣህ" አሏቸው፡፡ቅዱሳኑም ሥራቸውን እያደነቁ በልተው ጠጥተው ጠገቡ፡፡ በማግሥቱም አባታችን ቅዱሳኑን "በሰላም ሂዱ" ብለው መርቀው ሸኟቸውና የእግዚአብሔር ሥራ እያደነቁ
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ #መጋቢት ፭ (5) ቀን።
❤ እንኳን #ተአምራታቸውና_ትሩፋታቸው እንደ ሰማይ ከዋክብት ለበዛ የእግዚአብሔር ማደርያ ተጋዳይ ለሆኑ #በዝቋላ_ተራራ_ባለው_ባሕር_ውስጥ_100 ዓመታት ተዘቅዝቀው #ለኢትዮጵያ_ሰዎች ምሕረትን ለለመኑት #ለታላቁ_አባት_ለአቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ፦ ትውልድ አገራቸው ደቡባዊ ግብፅ ከቆላው ልዩ ስሙ ከንሒሳ አካባቢ ነው፡፡አባታቸው ስም ቅዱስ ስምዖን እናታቸው ስም ቅድስት አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ ወላጆቻቸው በእግዚአብሔር ፊት ደጋጎች የነበሩ ቢሆኑም አቅሌስያ መካን ሆና ልጅ በማጣቷ እያለቀሰች 30 ዘመን ኖራለች፡፡
❤ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብታ እናታቸው ቅድስት አቅሌስያ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ሥዕል ካለበት ፊት ለፊት በመቆም እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣት ዘንድ አልቅሳ ስትለምን ያንጊዜ ከሥዕሉ ቃል ወጥቶ "ክቡሩ ከሰማይ ከምድር ከፍ ከፍ የሚል፣ ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር በክብር የሚተካከል ክህነቱ እንደ መልከጼዴቅ ንጽሕናው እንደ እንደ ነቢይ ኤልያስ፣ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ የሆነ በክብር ከነቢያትና ከሐዋርያት ጋር የሚተካከል ልጅ ትወልጃለሽ" አሏት። ይኸውም ለአንቺ ብቻ አይደለም ለዓለሙ ሁሉ ነው እንጂ። ያን ጊዜ ከሦስቱ አንዱ ተነሥቶ በእጁ ባርኮ በሰላም ወደ ቤትሽ ግቢ አሏት"። እርሷም ደስ እያላት ወደ ቤቷ ገባች፡፡
❤ ቅድስት አቅሌስያም በመጋቢት 29 ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ እንደወለደች መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ "የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን" አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ተነሥቶ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ ዳግመኛም "ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን" አለ፡፡
❤ ከ3 ዓመት በኋላም እግዚአብሔር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን እንዲህ ብሎ አዘዘው፡- "ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ተቀበል፣ ብዙ ገዳማውያን ወዳሉበት ገዳም ውሰድና ከበራቸው አስቀምጠው፣ አበ ምኔቱንም ዘመደ ብርሃንን ከበር አንሥተህ ካንተ ዘንድ አኑረው ስለ ልብሱ ስለ ምግቡ አታስብ ሕፃኑ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ነውና ምግቡም መንፈሳዊ ነው ይኸውም ከእግዚአብሔር የሚወጣ ቃል ነው፣ ሰው በእንጀራ ብቻ እንደማይኖር ዕወቅ በለው" በማለት አዘዘው፡፡ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም እንደታዘዘው ከሰማይ ወርዶ ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ወስዶ በክንፎቹ አቅፎ ስሞ እስከ ሰባቱ ሰማይ አውጥቶ በሥሉቅ ቅዱስ ፊት አቅርቦት አስባረከው፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩን "ወደ እናቴ ወደ ማርያም ውሰደውና ትባርከው" አለውና ወስዶት እመቤታችንም ባረከችው፡፡ ዳግመኛም ከአዳም ጀምሮ ኄሮድስ በግፍ እስካስፈጃቸው ሕፃናት ያሉት ሁሉም ቅዱሳን ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ጻድቃን፣ ሰማዕታት፣ ደናግልና መነኰሳት ሁሉም እንዲባርኩት አደረገው መልሶ ከእግዚአብሔር ፊት አቆመው፡፡ መድኅን ጌታም ሕፃን ገብረ መንፈስ ቅዱስን "በመንግሥቴ ከእኔ ጋር ትነግሣለህና ደስ ይበልህ፣ በርታ የሚደርስብህን ሁሉ ታገሥ ብዙ ነፍሳት በአንተ ምክንያት ይድናሉ፣ ሰላሜ ከአንተ ጋር ይሆናል" አለው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደውና ሕፃኑን ከበር ላይ አስቀምጦ እርሱ ወደ ውስጥ ገብቶ እግዚአብሔር እንዳዘዘው ሁሉን ነገረው፡፡
❤ አባ ዘመደ ብርሃንም ሕፃኑን አስገብቶ በእንክብካቤ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማረ አሳደገው፡፡ ሕፃኑም ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ተቀብሎ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተመላ ሆነ፡፡ ፍጹም የእግዚአብሔር ጸጋ አድሮበታልና ሥራው ሁሉ በዕውቀት የተመላና የተቃና ሆነ፡፡ አባ ዘመድ ብርሃንም በሕፃኑ ላይ ያደረበትን ጸጋ እያየ እጅግ ደስ ይለው ስለነበር እንደ ቅዱስ እንጦንስ አስኬማን ሰጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡
❤ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዳግመኛ ተገልጦላቸው ወደ ሰማይ አሳረጋቸውና ከእግዚአብሔር ፊት አቆማቸው፡፡ ያን ጊዜም ጌታችን ክቡራን የሆኑ እጆቹን ዘርግቶ ከባረካቸው በኋላ "በጸሎትህ ከሲኦል የምታወጣቸው ብዙ ነፍሳት አሉ፤ ድውያንንም ትፈውሳለህ፤ ከእንግዲህ ወዲህ ከሰው ተለይተህ ወደ ጫካ ገብተህ ከአንበሶችና ከነብሮች ጋር ኑር" አላቸው ቁጥራቸውም ስልሳ ነብርና ስልሳ አንበሶች፡፡አባታችንም ጌታችንን "የሰጠኸኝ እነዚህ አንበሶችና ነብሮች ምን ይመገባሉ?" አሉት፡፡ ጌታችንም "የረገጥከውን መሬት ይልሳሉ በዚያም ይጠግባሉ፡፡ ወደ እኔም እስክትመጣ ድረስ ይኸው ምግብ ይሆናቸዋል" አላቸው፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ይህንን በሰሙ ጊዜ ደስ አላቸው፡፡ ጌታችንም መልአኩን ወደ ቀደመ ቦታቸው ይመልሳቸው ዘንድ አዘዘው፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከራሳቸው እስከ እግራቸው ድረስ ጠጉር በቀለላቸው፡፡ የጠጉራቸውም ርዝመቱ አንድ ክንድ ከስንዝር ነው፡፡ አባታችንም በታላቅ ተጋድሎ ሲኖሩ በጸጋ ላይ ጸጋ ተጨመረላቸው፡፡ከዕለታት በአንድ ቀን የፈወሳቸው ሕሙማን ብዛታቸው እልፍ ሆነ፡፡ የሀገሩ ሰዎችም ሥራቸውን ስላወቁባቸው አዘኑ፡፡ "ውዳሴ ከንቱ እንዳይሆንብኝ ተነሥቼ ሰው ወደማያውቀኝ አገር እሄዳለሁ" ብለው ተነሥተው ሄዱ፡፡ሕዝቡም አባታችን እንደተሰወሩ ባወቁ ጊዜ በሀዘን አለቀሱ፡፡
❤ ከዚህም በኋላ አባታችን ወደ ጫካ ገብተው ብቻቸውን የበጋውን ሐሩር የክረምቱን ቁር ታግሰው ምንም ልብስ ሳይለብሱ ራቁታቸውን ሆነው በተጋድሎ ኖሩ፡፡ ከጽኑው ተጋድሎአቸውና ከጫካው ቅዝቃዜ የተነሣ ሰውነታቸው አልቆ ከአጥንታቸው ጋር ተጣበቀ፡፡ ፍራፍሬም ሆነ ምንም ነገር አይመገቡም ውኃም ፈጽሞ አይጠጡም ነበር፡፡ አባታችን በምድረ በዳ እንደሰው ሳይሆን እንደመላእክት ኖሩ፡፡ ቅዱሳን መልእክትም ዘወትር ይጎበኟቸው ነበር፤ ስለምግባቸውም ሰማያዊ ኅብስት አምጥተው ይሰጧቸዋል ነገር ግን አባታችን ያንን ኅብስት አይመገቡትም ይልቁንም ጽዋውን ባሸቱት ጊዜ እንዲሁ ይጠግባሉ ይረካሉ፡፡
❤ ዕድአቸው 300 ዓመት በሆነ ጊዜ ጌታችን "ወደ ኢትዮጵያ ሂድ በዚያም ከደይን የምታወጣቸው ነፍሳት አሉ" አላቸው፡፡ አባታችንም "አምላኬ ሆይ ወደዚያች አገር ማን ያደርሰኛል?" አሉት፡፡ እግዚአብሔርም "እኔ በሥልጣኔ አደርስሃለሁ" ካላቸው በኋላ ከእርሳቸው ተሰወረ፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን ስድሳ አንበሶችና ስድሳ ነብሮች እየተከተሏቸው ወደ አገራችን ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም ከእነዚሁ ተከታዮቻቸው ጋር በነፋስ ሠረገላ ጭኖ ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ዳግመኛም "ደብር ቅዱስ" ወደሚባለው ወደ ዝቋላ ወሰዳቸው፡፡ አባታችንም በውኃው ዳር ቆመው ምሥራቁን፣ ምዕራቡን፣ ሰሜኑን፣ ደቡቡን በመለከቱ ጊዜ የኢትዮጵያ ሰዎች ኃጢአታቸው በፊታቸው የተገለጠ ሆነ፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመሥታወት እንደሚያይ የኃጥአንም ሥራቸው በአባታችን ፊት እንዲሁ የተገለጠ ነውና፡፡
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፬ (4) ቀን።
❤ እንኳን #ስለ_ፋሲካ_በዓል የአይሁድ ተሳታፊዎች ስለ ሚባሉ ክፉዎች ሰዎች #በአምር_ደሴት_የዐሥራ_ስምንት_ኤጲስቆጶሳት አንድነት ስብሰባ ለተደረገበትና ለከበረና ለተመሰገነ ከጵንፍልያ አውራጃ ብርግያ በትምባል ከተማ ለሆነ ለመኰንን #ለቅዱስ_ሐኑልዮስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የአሞር_ደሴት_የአንድነት_ስብሰባ፦ እነሱ የከበረ የፋሲካን በዓል በኔሳን ወር ማለት በሚያዝያ ዐሥራ አራት ቀን ከአይሁድ ጋር ያከብሩ ነበርና። ሰኞ ቢሆን ማክሰኞም ቢሆን ወይም ረቡዕ ወይም ሐሙስ ወይም በዓርብ ቀን ወይም በቅዳሜ ሰንበት ከአይሁድ ጋር ያከብሩ ነበርና የደሴታቸውም ኤጲስቆጶስ አወገዛቸው ግን አልተመለሱም።
❤ ስለዚህም ወደ ሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ድምትራጥዮስ ወደ አንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ ሰራባሞን ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ ድሜጥሮስ ወደ ኢየሩሳሌሙ ኤጲስቆጶስ ወደ ሲማኮስ መልእክትን ላከ። የእነዚህንም ሰዎች ስሕተታቸውን ነገራቸው። አራቱም ሊቃነ ጳጳሳት ከእርሱ እየአንዳንዳቸው የከበረ የፋሲካ በዓልን በእሑድ ቀን ካልሆነ በቀር ከአይሁድ በዓልም በኋላ ካልሆነ በቀር አታድርጉ የሚል መልእክትን ላኩ። ይህንም ትእዛዝ የሚተላለፈውን ከምዕመናን እንዲለይ አወገዘ።
❤ በዚህም ጉባኤ ዐሥራ ስምንት ኤጲስቆጶሳት ተሰበሰቡ። እነዚያንም ሕግ ለዋጮች አቅርበው የሊቀነ ጳጳሳቱን መልእክቶቻቸውን በፊታቸው አነበቡ ከእነርሱም በከፋች ምክራቸው የተመለሱ አሉ። በስሕተቻቸውም ጸንተው የቀሩ አሉ። ረግመውና አውግዘውም ከምዕመናን ለዩአቸው።
❤ አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያትም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተነሣባት ዕለት ፋሲካን ያለ እሑድ ቀን የሚያከብር እርሱ በበዓላቸው ከአይሁድ ጋር ተሳታፊ ነውና ከምዕመናን ይለይ ብለው እንዳዘዙ እንዲሁ የፋሲካ በዓል በዕለተ እሑድ እንዲከበርና ሕጉም ጸንቶና ተወስኖ እንዲኖር ተሠራ። እግዚአብሔር ከሰይጣን ስሕተት ይጠብቀን። በተጋድሎአቸውና በትሩፋታቸው ደስ ባሰኙት በቅዱሳን ጸሎትም ከወጥመዶቹና ከሽንገላውም ያድነን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ሐኑልዮስ፦ ይህንንም ቅዱስ ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ስለ መውደዱና እርሱንም ስለ ማምለኩ ከዲዮቅልጥያኖስ ተልኮ የመጣ ብርይንኮስ መኰንን ያዘው። በመኰንኑም ፊት በቆመ ጊዜ ምስጋና ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት ከፍ ከፍ ባለ ቃላት አብራርቶ ገለጠ። ብዙ ምስጋናዎችንም ለእግዚአብሔር አቀረበ የረከሱ ጣዖታትንም ረገማቸው።
❤ መኰንኑም በዕንጨት መስቀል ላይ ይሰቅሉት ዘንድ አዘዘ ስለ ከበረ ስሙም ምስክር ይሆን ዘንድ ስለ አደለው ምስጋና ይግባውና ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገነው። ከዚያም ምስጋና ይግባውና በእግዚአብሔር እጅ ነፍሱን መጋቢት4 ሰጠ። የቅዱስ ሐኑልዮስ ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ጋር ለዘላለም ይኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 4 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለክሙ_አሐተኔ_ጉቡአን። ኤጲስቆጶሳት ዐሥር ዘተውሳክክሙ ሳምን። አመ ፲ ወ ፬ ለወርኃ ኔሳን። በፋሲካ ኦሪት ኢይግበሩ ፋሲካ ወንጌል ብርሃን። ከመ ትምትርዎሙ ለዕልዋን በበሊሕ ልሳን። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_4።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ጸላእኩ ማኅበረ እኩያን። ወኢይነብር ምስለ ጽልሕዋን። ወአሐፅብ በንጹሕ እደውየ"። መዝ 25፥5-6። የሚነበቡት መልዕክታት ፊሊ 3፥1-ፍ.ም፣ 2ኛ ዮሐ 1፥1-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 20፥1-7። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 22፥1-24። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፬ (4) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊቷ_ጻድቅ በዝዋይ ደብረ ጽዮን ሐይቅ ውስጥ ገብታ ለአምስት ዓመት ለጸለየች ለታላቋ እናት #ለቅድስት_ሐይመተ_ሥላሴ ለዕረፍቷ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅድስት_ሐይመተ_ሥላሴ፦ የትውልድ ሀገሯ ጎጃም ደብረ ጽላሎ ነው፡፡ ብዙ እናቶች በጣና ደሴት ውስጥ እየገቡ እንደጸለዩ ሁሉ እሷም ወደ ዝዋይ ሄዳ በዝዋይ ደብረ ጽዮን ሐይቅ ውስጥ ገብታ አምስት ዓመት ከባሕሩ ላይ የጸለየች ቅድስት እናት ናት፡፡ በታዘዘ መልአክ መሪነት ከሐይቁ ውስጥ ከወጣች በኋላ በገዳሙ ውስጥ ዐሥራ ዘጠኝ ዓመት ቆማ ጸልያለች፡፡
❤ በመልአኩ መሪነት ወደ ቡልጋ ሄዳ በዚያም ዐሥራ አምስት ዓመት በታላቅ ተጋድሎ ኖራለች፡፡ ሰውነቷም እጅግ ከስቶ ሥጋዋ አልቆ ይታይ ነበር፡፡ በመጨረሻም መልአኩ ተገልጦ ጊዜ ዕረፍቷን ከነገራት በኋላ ወዲያው መጋቢት 4 ቀን በሰላም ስታርፍ ሦስት አክሊላት ወርደውላታል፡፡ ቅድስት ሐይመተ ሥላሴን ስንክሳሩም "የጽድቅ ኮከብ" እያለ ይጠቅሳታል፡፡ ቅዱስ ገድሏ በደብረ በግዕ ይገኛል፡፡ ከእናታችን ቅድስት ሐይመተ ሥላሴን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
