ch
Feedback
KAWGMS

KAWGMS

前往频道在 Telegram

Kegn. Andarge W/Giorgis Memorial School Official Telegram Channel

显示更多
2 398
订阅者
+124 小时
无数据7
-2930
帖子存档
KAWGMS
2 398
ከፍተኛ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ጉዳዩ፤ በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ማትሪክ ተፈታኝ ተማሪዎቻችን መሀከል የሚዘዋወር አደገኛ/የተሳሳተ/ ሀሳብ ስለቀረበላቸው፣ ትክክለኛ መረጃ በመስጠት ስለመታደግ ይሆናል፤   በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ማትሪክ በኦንላይን ተፈታኝ ተማሪዎች ዘንድ እየተሰራጨ ያለውን፣ ‹‹በኦንላይን (CBT) የፈተና ኮምፒዩተር ላይ የአንድን ተማሪ መልስ ሴቭ አድርጎ፣ በሌላ ተማሪ አካውንት ገብቶ መፈተን ይቻላል›› የሚለው ወሬ ለከፍተኛ አደጋ እራስን የሚያጋልጥ ነው። ይህ ድርጊት በኮምፒዩተር ወንጀል አዋጅ አንቀፅ 11 መሠረት በሕግ የሚያስቀጣ፣ እንዲሁም የፈተና ውጤትን ሙሉ በሙሉ የሚያሰርዝ ከባድ ጥፋት ነው።   ዘመናዊው የኮምፒዩተር ፈተና ማስፈተኛ አፕሊኬሽን (CBT) ማጭበርበሮችን በቀላሉ የሚከታተልባቸው 4 ዋና ዋና የቴክኖሎጂ መንገዶች፦   1)  ዲጂታል አሻራ (Digital Footprint)፦ ሲስተሙ የተፈተነበትን ኮምፒዩተር ልዩ መለያ (MAC Address) እና የራውተሩን IP አድራሻ ይመዘግባል። ሁለት የተለያዩ አካውንቶች በአንድ ኮምፒዩተር ላይ ከተጠቀሙ በቀላሉ ይለያል። 2)  የጊዜ ስታምፕ እና የሥራ እንቅስቃሴ ሎግ፦ ፈተናው የተጀመረበትን፣ የተጠናቀቀበትንና የተላከበትን ሰዓት በትክክል ይመዘግባል። ተማሪዎች ባልተለመደ ፍጥነት ወይም ተመሳሳይ የጊዜ ቅደም ተከተል (Pattern) ሲያጠናቅቁ ሲስተሙ ጥቆማ ይሰጣል። 3)  ባዮሜትሪክስ እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)፦ የኮምፒዩተሩ ዌብካሜራ የፊት ገጽታን በማንበብ ተፈታኙ በትክክል የተመዘገበው ተማሪ መሆኑን እና በፈተናው ወቅት ከስክሪኑ ፊት መኖሩን በAI ረዳትነት ያረጋግጣል። 4)  የመልስ አመላለስ ትንተና፦ ኩረጃን የሚከላከሉ አልጎሪዝሞች የመልሶችን መመሳሰል እና ያልተለመዱ የምላሽ ጊዜዎችን በመለየት የኩረጃ ምልክት (Flag) ያሳያሉ።   ይህ ዓይነቱ ማጭበርበር በወንጀል የሚያስጠይቅ፣ ውጤትን የሚያሰርዝ እና በተማሪዎች ስነ-ልቦና ላይ አሉታዊ ጫና የሚፈጥር በመሆኑ፣ ተማሪዎች በራሳቸው ጥረት ብቻ አጥንተው እንዲፈተኑ ትምህርት ቤቱ አጥብቆ ያሳስባል።   ወላጆችም ልጆቻቸው በራሳቸው ተማምነው እንዲሰሩ እና እንዲያልፉ ተደጋጋሚ ምክርና ማሳሰቢያ እንድሰጡ ጥሪ እናቀርባለን።   ትምህርት ቤቱ፣

KAWGMS
2 398
የስብሰባ ጥሪ ስለመሠረዝ ውድ የ12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች የ2018 ዓም አገር አቀፍ ፈተና (በተለምዶ ማትሪክ) ግንቦት 3 ቀን ይጀምራል የተባለው ወደ ሰኔ ወር መዛወሩ ትናንት ይፋ ተደርጓል። ት/ቤታችንም የፈተና ጣቢያ አንዲሆን የተወሰነው  ቀርቷል። በመሆኑም ተማሪዎቻችን ፈተናውን የሚፈተኑት በአቅራቢያችን በሚገኝ ሱመያ ት/ቤት መሆኑም ተረጋግጧል። ነገር ግን ት/ቤታችን 58 ኮምፒዩተሮች ማቅረብ እንዳለበት ታዟል። ስለዚህ ወላጆች ልጆቻችሁ በለመዷቸው/የራሳቸው/ ላፕቶፖች ቢፈተኑ ተጠቃሚ ይሆናሉ። መብራት እንኳን ቢቋረጥ በላፕቶፕ ከተፈተኑ ያለእንከን ፈተናውን መጨረስ ይችላሉበዴስክቶፕ ከተፈተኑ ግን ጀነሬተር እስኪነሳ እንዲሁም ኮምፒዩተሮቹ እስኪጀምሩ ድረስ የሚባክነው ጊዜ ተፈታኞቹ ላይ የሚያስከትለው ሳይኮሎጂካል ጫና ስለሚኖር ውጤታቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያስከትላል። ስለዚህ ወላጆች በራሳቸው ላፕቶፕ እንዲፈተኑ ተባበሯቸውም አበረታቷቸውም።            በተረፈ  ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ  8 ቀን ከቀኑ በ 11:00 ሰዓት ት/ቤቱ የጠራው ስብሰባ መሠረዙን እናሳውቃለን።                                          ት/ቤቱ

KAWGMS
2 398
የስብሰባ ጥሪ ውድ የ12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች የ2018 ዓም አገር አቀፍ ፈተና (በተለምዶ ማትሪክ) ግንቦት 3 ቀን እንደሚጀምር ታውቋል። ት/ቤታችንም የፈተና ጣቢያ መሆኑ ተነግሮናል። በመሆኑም የቀረው ጊዜ በጣም አጭር ስለሆነ በዚህ ፈተና እና ዝግጅት ዙሪያ ተቀራርቦ መወያየት አስፈላጊ በመሆኑ ሐሙስ ሚያዝያ  8 ቀን ከቀኑ በ 11:30 ሰዓት ት/ቤቱ ቤተ-መፃሕፍት እንድትገኙ በአክብሮት ጠርተናችኋል። አደራ ተገኙ፣ ጊዜ የለም !!                                          ት/ቤቱ

KAWGMS
2 398
12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸው የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎችን ይፋ ሆኑ። (መጋቢት 24/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ
12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸው የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎችን ይፋ ሆኑ። (መጋቢት 24/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸውን የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎችን ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሠረት ፈተና የሚሰጥባቸው የትምህርት አይነቶች በተፈጥሮ ሳይንስ እንግሊዝኛ ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪና ፊዝክስ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ እንግሊዝኛ ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው። ፈተናው በየትምህርት ዓይነቱ ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች የሚሸፍን ይሆናል። የዝግጅት አግባቡም 9ኛ ክፍል ላይ የቀድሞውና የአዲሱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘት ላይ ያተኩራል። ከ10ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ያለው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ይሆናል። የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ሆኖ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን የሚሸፍን መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

KAWGMS
2 398
ለ ቀአወጊመ ተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች ሠላም ለሁላችሁም፤ ለመቄዶንያ አረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን ገንዘብ የማሰባሰብ ዘመቻ ከያዝነው መጋቢት ወር ጀምሮ በዘመቻ በሰፊው በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል። በቀኛ አንዳርጌ ወ/ጊዮርጊስ ት/ቤት በኩልም የማሰባሰብ ሥራ ለመጀመር በወ/ሮ ሙሉሰው ሙንዬ እና አቶ መስፍን ኃይሉ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000753353139 ለዚሁ ዓላማ አካውንት የተከፈተ እና በራሪ ወረቀቶች የተላኩላችሁ መሆኑ ይታወሳል፤  ሆኖም ሁኔታዎች ተጣርተው ት/ቤቱ በይፋ እስኪያሳውቃችሁ ድረስ ላልተወሰነ ጊዜ ማንኛውንም መጠን ያለው ገንዘብ በዚህ ሂሳብ ቁጥር እንዳታስገቡ ት/ቤቱ ያሳስባል።                                              ት/ቤቱ

KAWGMS
2 398
photo content

KAWGMS
2 398
የስብሰባ ጥሪ ስለመሰረዝ ውድ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ወላጆች፣ የአንደኛ ሴሜስተር ትምህርትን አስመልክቶ በመማር ማስተማር ሂደት፣ በተማሪዎች የፈተና ውጤት፣ በዲሲፕሊን ግድፈት እና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ ት/ቤታችን ከወላጆች ጋር ተገናኝቶ ለመመካከር ለእሁድ ጥር 3 ቀን 2018 ዓም በ 3:00 ሰዓት በትቤቱ አዳራሽ ስብሰባ መጠራቱ ይታወሳል፣ ይሁን እንጂ አዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ከጥር 4 እስከ 6  የማትሪክ ሞዴል ፈተና እንዲፈተኑ በአ.አ ት/ ቢሮ ታህሳስ 30 ቀን ስለታዘዘ ቅዳሜና እሁድ ለፈተና ዝግጅት የሚውሉ ቀናት በመሆናቸው ምክንያት እሁድ ጥር 3 ቀን ተጠርቶ የነበረው ስብሰባ መሰረዙን ከይቅርታ ጋር እናሳውቃለን።                                            ት/ቤቱ

KAWGMS
2 398
የስብሰባ ጥሪ ውድ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ወላጆች፣ የዘንድሮ አንደኛ ሴሜስተር ትምህርትን አስመልክቶ በመማር ማስተማር ሂደት፣ በተማሪዎች የፈተና ውጤት፣ በዲሲፕሊን ግድፈት እና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ ት/ቤታችን ከወላጆች ጋር ተገናኝቶ መመካከር አስፈላጊ እና ተጠባቂ በመሆኑ እሁድ ጥር 3 ቀን 2018 ዓም በ 3:00 ሰዓት በትቤቱ አዳራሽ እንድትገኙ በአክብሮት ተጠርታችኋል።                                            ት/ቤቱ

KAWGMS
2 398
ውድ የ12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች፣ መንግስት የ2018 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና (ማትሪክ) ተፈታኝ ተማሪዎች የፋይዳ ቁጥር የግድ ሊኖራቸው ይገባል ባለው መሠረት የፋይዳ ቁጥራቸው (National ID FIN number) ለሰኞ ታህሳስ 13 ቀን 2018 ዓም ተማሪዎቹ ይዘው እንዲመጡ አስታውሱልን። አደራ! አደራ! አደራ! ቀአወጊመ   ት/ቤት

KAWGMS
2 398
ለ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ወላጆች፣ ሰኞ ህዳር 29 ቀን 2018 ዓም በአገር አቀፍ ደረጃ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ታስቦ ይውላል። መንግስት የዕለቱን አከባበር አስመልክቶ መመርያ ያወጣ ሲሆን በዚህ ቀን ተማሪዎች ጠዋት ሲማሩ ውለው ከምሳ በኋላ በጥያቄ እና መልስ ውድድር ሲያሳልፉ መምህራንም በፓናል ውይይት ቀኑን አስበው ይውላሉ። ከዚህ ውጪ ሌላ ዝግጅት ወይም የዴይ አከባበር ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ማድረግ የማይፈቀድ መሆኑን መመሪያው ይገልፃል። ይህ በእንዲህ እያለ በቀአወጊመ ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች አነሳሽነት ሌሎቹንም ተማሪዎች በአካተተ መልክ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ በሌላ ቀን ከልቸር ዴይ በሚል ስያሜ ለማክበር ልብስ መግዣ ወይም በትምህርት ቀን ከት/ቤት ቀርተው ሌላ ቦታ ለማከበር ወይም ቀኑን ለማክበር ባሰቡት ቀን መኪና ለመከራየት ገንዘብ በማሰባሰብ ላይ መሆናቸውን ደርሰንበታል። በመሆኑም  ተማሪዎች ት/ቤት ግቢ ውስጥ እናከብራለን ሲሉ እኛ ደግሞ አይቻልም ብለን ስንከለክል አለመግባባት እንዳይፈጠር ወላጆች ከወዲሁ አንድም የተከለከለ ድርጊት መሆኑን እንድታስረዱልን እና ከት/ቤት በማንኛውም ቀን እንዳይቀሩ ተከታትላችሁ እንድትልኩ፣ ሁለትም ገንዘብ ባለመስጠት እንድትተባበሩን ከአደራ ጭምር እናሳስባለን።                                                 ት/ቤቱ

KAWGMS
2 398
ውድ የ ቀኛ አንዳርጌ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በሙሉ፣ ሰኞ ህዳር 15 ቀን የ1ኛ ወሰነ ትምህርት አጋማሽ ፈተና እንደሚሰጥ የተነገራችሁና የፈተና ፕሮግራምም የተለጠፈላችሁ መሆኑ ይታወሳል። ነገር ግን በአንዳንድ የትምህርት ዓይነቶች በጊዜ መጣበብ ምክንያት ተማሪዎች ያልተማሩት ፓርት ፈተና ላይ ስለወጣ ተምረው እንዲፈተኑት ታስቦ ፈተናው የሚጀመርበት ቀን ወደ እሮብ እንዲሸጋሸግ ተወስኗል። በመሆኑም ሰኞ እና ማክሰኞ መደበኛ ትምህርት ስለሚኖር ሁላችሁም ደብተሮቻችሁን ይዛችሁ ት/ቤት እንድትመጡ ይሁን ወላጆችም መልዕክቱን እንድታስተላልፉልን እናሳስባለን።                                              ት/ቤቱ

KAWGMS
2 398
የስብሰባ ጥሪ ለ12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዛሬ በሠሩት ጥፋት ዙሪያ ተወያይቶ መፍትሔ ለመፈለግ እንዲቻል አስቸኳይ ስብሰባ ከወላጆች ጋር ለማድረግ ነገ ረብዑ ህዳር 10፣ 201
የስብሰባ ጥሪ ለ12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዛሬ በሠሩት ጥፋት ዙሪያ ተወያይቶ መፍትሔ ለመፈለግ እንዲቻል አስቸኳይ ስብሰባ ከወላጆች ጋር ለማድረግ ነገ ረብዑ ህዳር 10፣ 2018 ዓም 4:00 ሰዓት ላይ ተጠርቷል። በዚህ ስብሰባ ላይ ያልተገኘ ወላጅ ተማሪ ልጁን ከት/ቤት እስከማገድ የሚደርስ እርምጃ እንደምንወስድ በቅድሚያ እናስታውቃለን።                                           ት/ቤቱ

KAWGMS
2 398
photo content

KAWGMS
2 398
የስብሰባ ጥሪ ለ12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዛሬ በሠሩት ጥፋት ዙሪያ ተወያይቶ መፍትሔ ለመፈለግ እንዲቻል አስቸኳይ ስብሰባ ከወላጆች ጋር ለማድረግ ነገ ረብዑ ህዳር 10፣ 2018 ዓም 4:00 ሰዓት ላይ ተጠርቷል። በዚህ ስብሰባ ላይ ያልተገኘ ወላጅ ተማሪ ልጁን ከት/ቤት እስከማገድ የሚደርስ እርምጃ እንደምንወስድ በቅድሚያ እናስታውቃለን።                                           ት/ቤቱ

KAWGMS
2 398
ውድ ወላጆች፣ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓም ት/ቤት በቡድን ላለመምጣት ተነጋግረው የቀሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ስም ዝርዝር፤                              ከ12C ክፍል ትናንት ያልመጡ ተማሪዎች፦                                                                                                                            1. አብርሃም ሚሊዮን                   2. አሜን በፍቃዱ                3. ባምላክ ፀጋ               4. ዳግም ጥላሁን         5. ዳግማዊት ሰለሞን 6. ዳናይት አበራ                          7. ኢዮሲያስ ሳሙኤል           8. እዩኤል አሳምነው      9. እዩኤል እሱእንዳለ      10. ፍቅር ወንድሜነህ  11. ሃምሌት ተፈሪ                      12. ሂልዳና ኤልያስ               13. ጆርዳን ካሳ            14. ካሌብ አስፋው        15. ካውሰር መሀመድ  16. ሚኪ አሰፋ                          17. ኑሃሚን አባይነህ             18. ረድኤት ካሳሁን      19. ሮቤነስ ተክሌ           20. ሮብሰን ንጉሴ  21. ሳባ አብርሃም                      22. ሳሚያ መሃመድ             23. ያፌት በለጠ  ከ12C ክፍል የቀሩ 23 ሲሆን ተማሪዎች 2 ተማሪዎች ብቻ 12C ክፍል ገብተው ሲማሩ ውለው  ተመልሰዋል፡፡ የዛሬ አመት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓም የአመቱ መድኃኒያለም የሚነግሥበት ቀን ነው ብለው በቡድን ከት/ቤት መቅረታቸው ይታወቃል። የትናንቱስ ከት/ቤት መቅረት ከዚሁ ቀን ጋ የተያያዘ ይሆን? ወላጆች በደንብ አስቡበት! የጋራ መፍትሔ በጊዜ ልንፈልግለት ይገባል። በዚህ እና በሌላም ትምህርት ነክ ጉዳዮች ለመነጋገር ማክሰኞ ህዳር 02 ቀን 2018 ዓም ከ11 እስከ 12 ሰዓት የ11ኛ እና 12 ክፍል ተማሪ ወላጆች በት/ቤቱ አዳራሽ ስብሰባ ስለሚኖረን አደራ እንዳትቀሩ፡፡                                                                                                           ቀኛ/ አንዳርጌ ት/ቤት

KAWGMS
2 398
ውድ ወላጆች፣ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓም በቡድን ት/ቤት ላለመምጣት ተነጋግረው የቀሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ስም ዝርዝር፤                        ከ12A ክፍል፦              1. አብርሃም ውብሸት        2. አማኑኤል ሀይሉ         3. አማኑኤል ረታ           4. አርሴማ አማኑኤል                 5. በፀሎት አሳየኸኝ       6. ቢታንያ ተስፋዬነው        7. ብሌን ሄኖክ               8. ኤፍራታ ፍቅሩ          9. ኢማን ካሬጅ                      10. ሀውለት አብደላ     11. ሄርሜላ ይድነቃቸው    12. ቃልኪዳን ዳዊት       13. ማርቲና ገ/ወልድ      14. ሜላት ፍቃዱ                   15. መና በላቸው         16. መርሃን አረብ             17. ናሆም በቀለ            18. ነጋ አዳሙ               19. ኑራያን ኢምራን                20. ጥበቡ ሰለሞን       21. ፂዮን ኤርሚያስ           22. ያኔት ባህሩ             23. የአብስራ ሰይፉ        24. የሮሰን ዘሪሁን                 25. ዮሐንስ ይልማ        26. ዮናታን ዮሐንስ            27. ዮሴፍ አፈወርቅ                                                                                   ከ12A ክፍል የቀሩ ሲሆን 12 ተማሪዎች ብቻ 12A ክፍል ገብተው ሲማሩ ውለው  ተመልሰዋል፡፡ የዛሬ አመት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓም የአመቱ መድኃኒያለም የሚነግሥበት ቀን ነው ብለው በቡድን ከት/ቤት መቅረታቸው ይታወቃል። የትናንቱስ ከት/ቤት መቅረት ከዚሁ ቀን ጋ የተያያዘ ይሆን? ወላጆች በደንብ አስቡበት! የጋራ መፍትሔ በጊዜ ልንፈልግለት ይገባል። በዚህ እና በሌላም ትምህርት ነክ ጉዳዮች ለመነጋገር ማክሰኞ ህዳር 02 ቀን 2018 ዓም ከ11 እስከ 12 ሰዓት የ11ኛ እና 12 ክፍል ተማሪ ወላጆች በት/ቤቱ አዳራሽ ስብሰባ ስለሚኖረን አደራ እንዳትቀሩ፡፡                                                           ቀኛ/ አንዳርጌ ት/ቤት ከ12B ክፍል ትናንት ያልመጡ ተማሪዎች፦  1.  አቤኔዘር ሰለሞን             2.አቢጊያ መላክ               3. አዱገነት መስፍን    4. አሜን ጀምስ          5. አስማ አዱለቲፍ  6. በረከት ይሁን                            7. ብሌን ፀበሉ                  8. ኢባዋክ ክብሩ                 9. ኤልዳና ሀይሉ        10. ፍራኦል ደሳለኝ 11. ግርማ ደሳለኝ                        12. ሄመን በሀይሉ             13. ማህሌት ሳሙኤል        14. ማህሌት ደመቀ      15. ናኦድ ተክሌ   16. ነስራ ረሺድ                           17. ኖላዊ ሰለሞን              18. ሳምራዊት ሀ/ስላሴ      19. ሳሙኤል ንጋቱ       20. ሳሮን ክፍሉ   21. ሳያት አቡዬ                       22. ሶፎንያስ አንለይ           23. ፂዮን መኮንን               24. አርሴማ ንጉሴ        25. ወንጌላዊትሺናወል 26. ዮሐንስ ተሻለ                         27. ዮናታን ይታየው          28. ዛብሎን ነጋሳ  ከ12B ክፍል የቀሩ 28 ሲሆን ተማሪዎች 12 ተማሪዎች ብቻ 12B ክፍል ገብተው ሲማሩ ውለው  ተመልሰዋል፡፡ የዛሬ አመት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓም የአመቱ መድኃኒያለም የሚነግሥበት ቀን ነው ብለው በቡድን ከት/ቤት መቅረታቸው ይታወቃል። የትናንቱስ ከት/ቤት መቅረት ከዚሁ ቀን ጋ የተያያዘ ይሆን? ወላጆች በደንብ አስቡበት! የጋራ መፍትሔ በጊዜ ልንፈልግለት ይገባል። በዚህ እና በሌላም ትምህርት ነክ ጉዳዮች ለመነጋገር ማክሰኞ ህዳር 02 ቀን 2018 ዓም ከ11 እስከ 12 ሰዓት የ11ኛ እና 12 ክፍል ተማሪ ወላጆች በት/ቤቱ አዳራሽ ስብሰባ ስለሚኖረን አደራ እንዳትቀሩ፡፡                                                              ቀኛ/ አንዳርጌ ት/ቤት

KAWGMS
2 398
ውድ ወላጆች፣ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓም በቡድን ት/ቤት ላለመምጣት ተነጋግረው የቀሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ስም ዝርዝር፤                        ከ12A ክፍል፦              1. አብርሃም ውብሸት        2. አማኑኤል ሀይሉ         3. አማኑኤል ረታ           4. አርሴማ አማኑኤል                 5. በፀሎት አሳየኸኝ       6. ቢታንያ ተስፋዬነው        7. ብሌን ሄኖክ               8. ኤፍራታ ፍቅሩ          9. ኢማን ካሬጅ                      10. ሀውለት አብደላ     11. ሄርሜላ ይድነቃቸው    12. ቃልኪዳን ዳዊት       13. ማርቲና ገ/ወልድ      14. ሜላት ፍቃዱ                   15. መና በላቸው         16. መርሃን አረብ             17. ናሆም በቀለ            18. ነጋ አዳሙ               19. ኑራያን ኢምራን                20. ጥበቡ ሰለሞን       21. ፂዮን ኤርሚያስ           22. ያኔት ባህሩ             23. የአብስራ ሰይፉ        24. የሮሰን ዘሪሁን                 25. ዮሐንስ ይልማ        26. ዮናታን ዮሐንስ            27. ዮሴፍ አፈወርቅ                                                                                    ከ12A ክፍል የቀሩ ሲሆን 12 ተማሪዎች ብቻ 12A ክፍል ገብተው ሲማሩ ውለው  ተመልሰዋል፡፡ የዛሬ አመት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓም የአመቱ መድኃኒያለም የሚነግሥበት ቀን ነው ብለው በቡድን ከት/ቤት መቅረታቸው ይታወቃል። የትናንቱስ ከት/ቤት መቅረት ከዚሁ ቀን ጋ የተያያዘ ይሆን? ወላጆች በደንብ አስቡበት! የጋራ መፍትሔ በጊዜ ልንፈልግለት ይገባል። በዚህ እና በሌላም ትምህርት ነክ ጉዳዮች ለመነጋገር ማክሰኞ ህዳር 02 ቀን 2018 ዓም ከ11 እስከ 12 ሰዓት የ11ኛ እና 12 ክፍል ተማሪ ወላጆች በት/ቤቱ አዳራሽ ስብሰባ ስለሚኖረን አደራ እንዳትቀሩ፡፡                                                              ቀኛ/ አንዳርጌ ት/ቤት ከ12B ክፍል ትናንት ያልመጡ ተማሪዎች፦  1.  አቤኔዘር ሰለሞን             2.አቢጊያ መላክ               3. አዱገነት መስፍን    4. አሜን ጀምስ          5. አስማ አዱለቲፍ  6. በረከት ይሁን                            7. ብሌን ፀበሉ                  8. ኢባዋክ ክብሩ                 9. ኤልዳና ሀይሉ        10. ፍራኦል ደሳለኝ 11. ግርማ ደሳለኝ                        12. ሄመን በሀይሉ             13. ማህሌት ሳሙኤል        14. ማህሌት ደመቀ      15. ናኦድ ተክሌ   16. ነስራ ረሺድ                           17. ኖላዊ ሰለሞን              18. ሳምራዊት ሀ/ስላሴ      19. ሳሙኤል ንጋቱ       20. ሳሮን ክፍሉ   21. ሳያት አቡዬ                       22. ሶፎንያስ አንለይ           23. ፂዮን መኮንን               24. አርሴማ ንጉሴ        25. ወንጌላዊትሺናወል 26. ዮሐንስ ተሻለ                         27. ዮናታን ይታየው          28. ዛብሎን ነጋሳ  ከ12B ክፍል የቀሩ 28 ሲሆን ተማሪዎች 12 ተማሪዎች ብቻ 12B ክፍል ገብተው ሲማሩ ውለው  ተመልሰዋል፡፡ የዛሬ አመት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓም የአመቱ መድኃኒያለም የሚነግሥበት ቀን ነው ብለው በቡድን ከት/ቤት መቅረታቸው ይታወቃል። የትናንቱስ ከት/ቤት መቅረት ከዚሁ ቀን ጋ የተያያዘ ይሆን? ወላጆች በደንብ አስቡበት! የጋራ መፍትሔ በጊዜ ልንፈልግለት ይገባል። በዚህ እና በሌላም ትምህርት ነክ ጉዳዮች ለመነጋገር ማክሰኞ ህዳር 02 ቀን 2018 ዓም ከ11 እስከ 12 ሰዓት የ11ኛ እና 12 ክፍል ተማሪ ወላጆች በት/ቤቱ አዳራሽ ስብሰባ ስለሚኖረን አደራ እንዳትቀሩ፡፡                                                              ቀኛ/ አንዳርጌ ት/ቤት

KAWGMS
2 398
photo content

KAWGMS
2 398
photo content

KAWGMS
2 398
photo content