ch
Feedback
EOTC BOOK PDF FREE/(የኢ/ኦ/ተ-መጽሐፍት )

EOTC BOOK PDF FREE/(የኢ/ኦ/ተ-መጽሐፍት )

前往频道在 Telegram

ይኽን መጽሐፍ ብላ! ሕዝ.3:1 ꧁-------------------------꧂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክርስትናን የሚሰብኩ የቅዱሳት መጽሐፍት ማሕደር!! በ #PDF Free "መጽሐፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።" ማቴ 22፥29 የመጽሐፍ ቅዱስ አርዕስቶችና አንድምታዎች ፣ የአባቶች የሊቃውንት መጽሐፍት ይገኙበታል። ኑ ༒

显示更多
655
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ሕይወቱና_ትምህርቱ_1.pdf2.05 MB

Repost from Adebabay Media
ከመንፈሳዊ ሰው የተገኘ መንፈሳዊ መጽሐፍ፦ "ዓምደ ሃይማኖት" ******* በ1980ዎቹ ስለ ሃይማኖቱ በየመንገዱ ይጠየቅ ለነበረው ክርስቲያን የእምነቱ ማስረገጫ፣ ለተጠየቀው ምላሹ፣ ለአርቶዶክስነቱ መ
+1
ከመንፈሳዊ ሰው የተገኘ መንፈሳዊ መጽሐፍ፦ "ዓምደ ሃይማኖት" ******* በ1980ዎቹ ስለ ሃይማኖቱ በየመንገዱ ይጠየቅ ለነበረው ክርስቲያን የእምነቱ ማስረገጫ፣ ለተጠየቀው ምላሹ፣ ለአርቶዶክስነቱ መጽሐፍዊነት ማጣቀሻ ምንጩ፣ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ተበትኖ ቃለ እግዚኣብሔርን ለሚያስተምረው ዋነኛ መሣሪያው ይህች መጽሐፍ ነበረች። ስለ ኦርቶዶክስ እምነት ለማወቅ ለሚፈልጉ ሌሎችም ዓይን ገላጭ መጽሐፍ ነበረች። ከ29 ዓመት በኋላ ድጋሚ ተሻሽላ ለሕትመት ስትበቃ ለተማሩባትም ላስተማሩባትም ጥሩ ማስታወሻ ትሆናለች። አዲሱ ትውልድም ከቀደምቶቹ ታሪክ ይቋደስባታል። ስለ መጽሐፉ በዝርዝር ከመናገር በፊት ስለ ጸሐፊው መናገር ይቀድማል። ከመንፈሳዊ ሰው የተገኘ መንፈሳዊ መጽሐፍ ነው ያልኩት ብዙ ሊያስብል ይችላል። ደራሲው በዚህ ዘመን የወንጌል ብርሃንን ቀድመው ከለኮሱት ዋነኞቻችን አንዱ ነው። መንፈሳዊ ዕውቀት ከርጋታና ከማስተዋል ጋራ የተሰጠው፣ ያለ ማንጎራጎርና ስሞታ ሃይማኖቱን በንጽሕና የሚኖር፣ ለበደሉትና የብረት እጃቸውን ላሳረፉበት ያለ ምንም በቀል ወዳጅነታቸውን ያልገፋ፣ ከተማ ተወልዶ አድጎ፣ ከታላላቅ አባቶች ተምሮ ነገር ግን በየመድረኩ ልታይ ልታይ የማይል፤ ተናገር ካልተባለ ለመናገር የማይፈጥን፣ በአፈ ጮሌዎች መካከል ተቀምጦ አላዋቂ መስሎ መታየትን ያልተጸየፈ፤ ወደ ክህነት ዓለም ከገባም በኋላ በአባታዊ ጸጋውና በከባቴ አበሳነቱ ለብዙ ምዕመናን የልብ እረፍት የሆነ፤ እውነተኛ ካህን፤ መንፈሳዊ አባት፤ ለእኔ ደግሞ ወንድምና ጓደኛ፦ መልአከ አርያም ቀሲስ ብርሃኑ ጎበና ነው። ይህች መጽሐፍ ዓምደ ስምዕ፣ ዓምደ ታሪክ፣ ዓምደ ሕይወት ትሁንልህ። ረዥም ዕድሜ ከጤና ጋራ እመኝልኻለሁ። (ከቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ)

እንደ ወይነ ቃና ዓምደ ሃይማኖት እንደገና መልአከ አርያም ቀሲስ ብርሃኑ ጎበና ጭልምልም ባለበት ሠዓት የብርሃን ፋና ይዘው ብቅ ካሉት የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች አንዱ ነው። [አንተ ማለቴን
እንደ ወይነ ቃና ዓምደ ሃይማኖት እንደገና መልአከ አርያም ቀሲስ ብርሃኑ ጎበና ጭልምልም ባለበት ሠዓት የብርሃን ፋና ይዘው ብቅ ካሉት የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች አንዱ ነው። [አንተ ማለቴን ይቅር በሉልኝ] የሐመር መጽሔት የመጀመሪያው ዋና አዘጋጅ መኾኑን ብዙ ሰው አያውቅ ይኾናል። ብዙ ውጣ ውረድ የነበረበትን የቦረዳ ዋሻን ድንቅ ግኝት ከቦታው ድረስ ወርዶ ዘግቦ በመጀመሪያዋ ሐመር እና በተከታታይ እትሞች አስነብቧል። ብሬ የታይታ ጾር የራቀለት ገና ከማለዳው ነው። ሥራው ከሚገልጠው በቀር ለመታየት አንገቱን ሲያሰግግ አታገኙትም። በኬሚስትሪ ሜጀር ከዐራት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ ተመርቆ በሙያው በመምህርነትም በEast Africa Holdings Company በኬሚስትነትም ብዙ ሠርቷል። ይኹን እንጅ በጣም ፈታኝ በነበረው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ያለዕረፍት ለፍቷል። በበሳል የነገረ ሃይማኖት ትምህርቱ ይታወቃል። በጊዜው በሐራጥቃዊያን ይነሡ ለነበሩ ጥያቄዎች በየዐውደ ምሕረቱ የተብራራ መልስ እየሰጠ የቀረቡትን አጽንቷል፣ የጠፉትን መልሷል። በዐዲስ አበባ እና በክፍለ ሀገር ጉባኤ በተዘጋጀ ቁጥር ይምጡልን ከሚባሉት ግንባር ቀደም ተጋባዦች የብሬ ስም አይጠፋም። የዐዲስ አበባ ዐውደ ምሕረቶች አፍ አውጥተው ይመሠክሩታል።

Amlak Zebeama Book by Dn. Yohannes Lisanework.pdf2.70 MB

ዐብይ ፆም.pdf0.69 KB

Asres Yenesew - Teqami Mikir (1953).pdf3.48 MB

ከዓለም አቀፍ ጉባኤያት ውሳኔዎች ጋር የማይጋጭ እስከሆነ ድረስ ከቅዱሳን አበው አባበሎች ጋር ቅራኔ ሳይኖረው ሲቀር ብቻ ነው፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ይጠብቃል፡፡ ለምሳሌ ውዝግቦችን በመፍታት እና በሁሉም ቦታ ተመሳሳይ የሆነ አገልግሎትና ሥርዓት እንዲኖር ያግዛል (ዮሐ 15፤1-29) በአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን የሆነውን የቤተ ክርስቲያን ካልሆነው መለኪያ (Standard) በመሆን ያገለግላል፡፡ 7.ትውፊት፡- በሰዋስዋዊ ዘይቤው ሲፈታ፥ ትወፊት ማለት ስጦታ፣ ልማድ፣ ትምህርት፣ ወግ፣ ታሪክ፣ ሃይማኖት፣ ሥርዓት፣ ከጥንት ከአበው ሲያያዝ ሲወርድ፥ ቃል በቃል ሲነገር የመጣ ማለት ነው /አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፣ ገጽ፣ 397/፡፡ በግሪክ(በጽርዕ) “ፓራዶሲስ” ይባላል፤ አንድን ነገር እጅ በእጅ ለሌላ ሰው ማስረከብን ወይም ማቀበልንም ያመለክታል፡፡ ዕብራውያን ደግሞ “ማሳር - ማቀበል” እና “ቂብል - መቀበል” የሚሉ ቃላትን ይጠቀማሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ለቃሉ የሚከተለውን ትርጕም ሰጥታዋለች፡፡ ትውፊት ማለት እግዚአብሔር ለሰው ልጆች በጠቅላላ በአበው፣ በነቢያት፣ በሐዋርያት፣ በጳጳሳት፣ በሊቃውንት፣ በካህናት በኵል የሚያስተላልፈው ሕያው (ሕይወትን የሚሰጥ) ቃል ማለት ነው፡፡ ይኽ ሕያው ቃል ቀደምት አበው ከእግዚአብሔር የተቀበሉትና ለቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፉት፥ ቤተ ክርስቲያንም በየጊዜው እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የምትጠቀምበት ሕያው ትምህርት ነው፡፡ እንደ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ፥ እግዚአብሔር ከፍጥረት መዠመሪያ አንሥቶ በጽሑፍም ያለ ጽሑፍም የገለጠውን እውነት የምናገኘው በቅዱስ ትውፊት ውስጥ ነው፡፡ በመኾኑም የተጻፈውና ያልተጻፈው ቅዱስ ትውፊት ለድኅነታችን የሚኾን የእግዚአብሔርን መገለጥ የያዘ ስለኾነ አስፈላጊ ነው፡፡ ትውፊት ሲባል ስላለፈ ነገር ብቻ የሚናገር፥ ነገር ግን በአኹኑ ሰዓት ምንም ሕይወት እንደሌለው ተደርጐ የሚታሰብ አይደለም፡፡ አኹንም ሕይወት ያለው ብቻ ሳይኾን ሕይወትንም የሚሰጥ ነው፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍ ቅዱስ የቅዱስ ትውፊት አንድ አካል ነው(የተጻፈ ትውፊት ነው)፡፡ ነገር ግን ስላለፈው ነገር ብቻ የሚናገር አይደለም፡፡ አኹንም ሕይወትን የሚሰጥ ነው፡፡ ስለዚኽ ትውፊትን መቀበል ያለፈውን ነገር የመጠበቅ ጕዳይ ብቻ አይደለም ማለት ነው፤ የሕይወት ጕዳይ እንጂ፡፡ በሌላ አነጋገር የምንጠብቀው የሕይወት ጕዳይ እንደኾነ ስለሚገባን ነው ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር በዚኹ ቅዱስ ትውፊት ሲናገር ስላለፈው ነገር ብቻ ሳይኾን ሰለአኹኑም ስለሚመጣውም ዘለዓለማዊ ሕይወት ነው፡፡ ትውፊትን ቅዱስ ብለን መጥራታችንም የመንፈስ ቅዱስ ጥበቃ ስለማይለየው፥ አንድም ከክርስቶስና ክርስቶስ አድሮባቸው ከሚኖር ከቅዱሳን የተገኘ ስለሆነ ነው፡፡ እንደ ምዕራቡ ቤተ ክርስቲያን (ካቶሊክ) ትርጕም ቅዱስ ትውፊት ማለት ያልተጻፈ ነገር እና በቃል ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍን ብቻ የያዘ ነው፡፡ በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ግን ከላይ እንደገለጥነው ቅዱስ ትውፊት የተጻፈውም ያልተጻፈውም ኹሉ የሚያካትት ነው፡፡ በመኾኑም (ቅዱስ ትውፊት) በውስጡ መጽሐፍ ቅዱስን፣ የአንዲቱ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖትን፣ የሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትንና ቀኖናትን፣ የሦስቱን ዓለም አቀፍ የቤተ ክርስቲያን ጉባኤያትን (ጕባኤ ኒቅያ፣ ጕባኤ ቁስጥንጥንያ፣ ጕባኤ ኤፌሶን) እና ትእዛዛትን፣ መጻሕፍተ ቅዳሴያትን፣ ገድለ ቅዱሳንን፣ ቅዱሳት ሥዕላትን፣ የቤተ ክርስቲያን አመራርና የሥርዓተ አምልኮ አፈጻጸምን፣ ክርስቲያናዊ የአለባበስ፥ የአነጋገር እንዲኹም የአመጋገብ ሥርዓትን ሌላውንም ኹሉ ያካተተ ነው፡፡ ትውፊትን ቁሳዊ፣ ቃላዊና ርእያዊ ብለን በ3 ልንከፍለው እንችላለን፡፡ ርእያዊ፡- ይህም ማለት በመጻሕፍትና በቃል ባይገለጥም በማየት የወረስነውን ያመለክታል፡፡ ለምሳሌ በ2ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ የነበረው ቅዱስ ሄሬኔዎስ፥ ፍሎሪነስ ለተባለ ጓደኛው ሲጽፍለት፡- ‹‹ ነፍስ እስከማውቅና በሕይወቴ እስኪዋሐደኝ ድረስ በሕፃንነቴ የተማርኩትን አኹን ከምማረው በላይ ወለል ብሎ ይታየኛል፡፡ ቅዱስ ፖሊካርፐስ (የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀመዝሙር ነው) ሲቀመጥበት የነበረውን ቦታ፣ የትምህርት አሰጣጡ ዘዴ፣ እንዴት ይገባና ይወጣ እንደነበር፣ ክርስቲያናዊ ሕይወቱና የሰውነቱ መልክዕ፣ ለምእመናን ያስተማረውን ትምህርት፣ ከወንጌላዊ ዮሐንስና ከሌሎች ጌታችንን በዓይን ካዩት ደቀ መዛሙርት ጋር ስለነበረው ትውውቅ፣ ትምህርታቸውን እንዴት ያስታውሰው እንደነበር፣ ስለ ጌታ ከእነርሱ ምን እንደሰማ፣ ጌታችን ያደረጋቸውን ተአምራትና ያስተማረውን ትምህርት ይኽንና ይኽን የመሰለ ኹሉ ቅዱስ ፖሊካርፐስ ከቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች እንደምን እንደተቀበለና ለእኛ እንዴት እንዳስተላለፈልን ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር አዋሕዶም እንዴት እንዳስተማረን አስታውሳለኁ፡፡ የእግዚአብሔር ቸርነት ረድቶኝ፥ በሕፃንነት አዕምሮዬ እነዚኽን ነገሮች ለመስማትና በወረቀት ሳይኾን በልቤ ጽላት እጽፋቸው ዘንድ ደግሞም ዘወትር አስባቸው ዘንድ እጅግ እጓጓ ነበር ›› በማለት ከቀደሙት አበው ስለተቀበለውና በኑሮ፣ በሕይወት ስለሚገለጡ፥ ግን ደግሞ ያልተጻፉ ትውፊቶች እንዳሉ አብራርቶ የተናገረበት አኳኋንም የትውፊትን ምንነት ፍንትው አድርጐ የሚተረጉምልን ነው / /፡፡›› ቃላዊ፡- ይህ ዓይነቱ ደግሞ በንግግር ከአባቶች ሲተላለፍ የመጣውና እኛ ደግሞ በመስማት የምንቀበለውን ያመለክታል (2ኛ ተሰ 2፤15)፡፡ ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም ‹‹የትኞቹ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት የትኞቹ የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት እንደሆኑ ከቤተክርስቲያን ጠቅቀህ ተማር ›› ብሏል፡፡ ይህም የሚያስረዳን መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ የመጻሕፍቱን ብዛት ቀኖና ሲሠራለት እውነተኞቹን መጻሕፍት ከሐሰተኞቹ ለመለየት አባቶች የተጠቀሙት ቅዱስ ትውፊትን መሆኑን ነው፡፡ ለምሳሌ ቅዱስ ሄሬኔዎስ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ አምስት መጻሕፍትን እንደ ጻፈ እነዚህንም መጻሕፍት የሰበሰበው ደቀ መዝሙሩ ቅዱስ ፖሊካርፐስ እንደሆነ ጽፏል፡፡ ስለዚህም ቅዱሳን አባቶች ከዚህ ትውፊት በመነሣት 5ቱን የቅዱስ ዮሐንስን መጻሕፍት በሐዲስ ኪዳን ቀኖና(የመጻሕፍት ዝርዝር) ውስጥ አካተው በሐሰት በእርሱ (በቅዱስ ዮሐንስ) ስም ከተጻፉ መጻሕፍት ለይተዋል፡፡ በተለያዩ መናፍቃን በቅዱሳን ስም የሚጠሩ ከ50 በላይ የሚሆኑ ወንጌላት ተጽፈው ነበር፤ አባቶችም ከእነዚህ የሐሰት ወንጌላት ለይተው እውነተኞቹን 4 ብቻ በቀኖና አስቀምጠዋል፡፡ ለዚህም ነው ሊቁ አርጌንስ ‹‹በትውፊት ወንጌላት 4 እንደሆኑ እናስተውላለን›› ያለው፡፡ ቁሳዊ፡- ከላይ ከገለጥናቸው በተለየ በሚዳሰስ በሚጨበት ነገር የተላለፉልን የቤተ ክርስቲያን ሀብቶች ናቸው፡፡ ለምሳሌ አብያተ ክርስቲያናት፣ ንዋያተ ቅድሳት፣ ቅዱሳት መጻሕፍት፣ . . . ወዘተ ያካትታል፡፡ 8.የክርስቲያናዊ ትውፊት ማረጋገጫዎች ቤተ ክርስቲያን እንዲሁ ማንኛውንም ትውፊት ክርስቲያናዊ ነው በማለት አትቀበልም፡፡ አንድን ትውፊት እውነተኛ መሆኑን የምታረጋግጥበት የራሷ የሆነ መለኪያ አላት፡፡ እነዚህም ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የማይጣረስ እስከሆነ ድረስ፡- ምንም እንኳን መጽሐፍ ቅዱስ የትውፊት አንዱ አካል ቢሆንም የመጀመሪያውን ስፍራ ይይዛል፡፡ ይህም ካልተጻፈው ቅዱስ ትውፊት ይልቅ በቀላሉ ለስሕተት የማይጋለጥ በመኾኑ ው፡፡ ምክንያቱም በቀኖና አንዴ ተወስኖ (ምን ያህል መጻሕፍት እንዳሉና ይዘታቸው) የቀረበ ነውና፡፡ በዚኽም ያልተጻፈው ቅዱስ ትውፊት የሚመዘንበት ሚዛን ነው፡፡ ከመሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጋር የማይጋጭ እስከሆነ ድረስ

#Ethiopia ሦስቱ የእምነት መመሪያዎች 1.ዶግማ ምንድነው 2.ቀኖና ምንድነው 3.የቀኖና ቤተ ክርስቲያን መገለጫዎች 4. ቀኖና በመጽሐፍ ቅዱስ 5.የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ምንጮች 6.የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥቅሞች 7.ትውፊት ምንድነው 1.ዶግማ ምንድነው ዶግማ ፡- ዶከይን ከሚለው የግሪክ (የጽርእ) ቃል የተገኘ ሲሆን በጥሬው አመለካከት፣ አስተሳሰብ፣ አዋጅ ማለት ቢኾንም በምሥጢራዊ ማለትም እንደ ቤተ ክርስቲያን አተረጓገም ግን የማይለወጥ፣ የማይቀየር፣ የማይሻሻል፣ የማያረጅ መሠረተ እምነት ማለት ነው፡፡ በመኾኑም ዶግማ የተደነገገ ሳይኾን የተገለጠ ነው፡፡ መገኛውም እግዚአብሔር ነው፡፡ ከሰው ሊፈጠር አይችልም፡፡ ከእግዚአብሔር የተሰጠ እውነት ነው፡፡ በማኝኛውም አካል (በሲኖዶስም ጭምር)፣ በየትኛውም ዘመን፣ በየትኛውም ኹኔታ (በሞትም በሕይወትም) የማይለወጥ ማንነት አለው፡፡ ዶግማ የቤተ ክርስቲያን መሠረታዊ ትምህርተ ሃይማኖት ነው ብለናል፡፡ ስለ ቅድስት ሥላሴ፣ ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ ፣ ስለ ምሥጢረ ጥምቀት፣ ስለ ምሥጢረ ቁርባን፣ ስለ ቤተ ክርስቲያንና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ክብረ ድንግል ማርያምና ክብረ ቅዱሳን የምንማረው ነው እንጂ ማናችንም ልናሻሽለው አንችልም፡፡ እንኳንስ አንድ ግለሰብ ይቅርና ሲኖዶስም ቢኾን አለመለወጡን፣ አለመፋለሱን መርምሮ ሃይማኖታችን ይህ ነው በማለት ያሳውቃል እንጂ መጨመር ወይም መቀነስ አይችልም፡፡ ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ፡- ‹‹ነገር ግን (ሐሳባችንን ቀይረን) እኛ ብንኾን ወይም ከሰማይ መልአክ ከሰበክንላችኁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን የሚሰብክላችኁ የተረገመ ይኹን›› ያለውም ስለዚኹ ነው /ገላ.1፡8/፡፡ 2.ቀኖና ምንድነው ቀኖና(Canon) ፡- ማለት ሕግ፣ ሥርዓት፣ ደንብ፣ ፍርድ፣ ቅጣት፣ መጠን፣ ልክ ማለት ነው፡፡ በግሪኩ ካኖን ሲባል በዕብራይስጡ ቃኒህ ይሉታል፡፡ ይኸውም አንድን ነገር ለመለካት፣ ለመመዘን፣ ትክክል መኾኑንና አለመኾኑን ለመለየት፣ መጠኑን ለማወቅ የሚያገለግል መለኪያ ወይም መስፈርት ነው፡፡ ቀኖና በዋናነት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ማለት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ቀኖና የሚለውን ቃል ስትጠቀም የመጻሕፍቶቿን ዝርዝር፣ የሥርዓተ አምልኮቷን አፈጻጸም፣ የምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን አፈጻጸም፣ የአንድ ክርስቲያን ሥነ ምግባር ምን መምሰል እንዳለበት የሚገልጠውን ሥርዓት፣ ሕግና ደንብን ያመለክታል፡፡ የጌታ ትእዛዛት በሙሉ ዶግማ ነው፡፡ ጾም፣ ጸሎት፣ ጥምቀት፣ ቁርባን፣ ንስሐ፣ ከወንድም ጋር መታረቅ…ወዘተ ዶግማ ነው፡፡ ቀኖና የሚኾነው ዝርዝር አፈጻጸሙ ላይ ሲኾን ነው፡፡ ቀኖና “እምነታችንን እንዴት እንፈጽም?” ለሚለው ጥያቄ መልስ የሚሰጥ ዝርዝር አፈጻጸም ነው፡፡ 3.የቀኖና ቤተ ክርስቲያን መገለጫዎች ሥልጣን ባለው አካል (በቅዱሳን ጳጳሳት ጉባኤ) የሚደነገግ፣ የሚተገበር፣ ነው፡፡ ሲደነገግም በግለሰቦች የግል ፍላጐት ወይም ፈቃድ የሚደነገግ አይደለም፡፡ ሃይማኖታዊ ይዘት አለው፡፡ ምክንያቱም ዓላማው ሰውን ሁሉ ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር ማፍለስ ስለሆነ ቄሣራዊ ይዘት የለውም፡፡ ቢኖርም እንኳን አንድ ክርስቲያን በዚህ ምድር የሚኖረው ቆይታ ከሰማያዊ ሕይወቱ ጋር ሳይጣረስበት እንዴት መኖር እንዳለበት የሚያስረዳ ነው፡፡ የሰው ልጅ ከሚችለው በላይ ሸክምን አይጭንም፤ “ሸክሜ ቀሊል ነው” እንዲል /ማቴ.11፡29/፡፡ የሸላሚነትና የቀጪነት ሥልጣን አለው፡፡ ቄሣራዊ ሕግ የሸላሚነት ይዘት የለውም፡፡ በቤተ ክርስቲያን ቀኖና ግን ለምሳሌ ተጋድሎአቸውን በድል ያጠናቀቁት ክርስቲያኖች ቀን ተለይቶላቸው፣ ታቦት ተቀርጾላቸው በምእመናን ዘንድ ክብርን እስከ ማግኘት ይደርሳሉ፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድ ደግሞ የዘለዓለም አክሊል ዘውድ አለው፡፡ የአምልኮ ይዘት አለው፡፡ በውስጡ ጾም፣ ጸሎት፣ ምጽዋት እና የመሳሰሉትን ኹሉ ያካትታል፡፡ የመመዘን ጠባይ አለው፡፡ ለምሳሌ የቃየን መሥዋዕት ያልሰመረችው መሥዋዕት ስላላቀረበ ሳይኾን በሕጉ መሠረት አሰስ ገሰስ ኾኖ ስለተገኘ ነው /ዘፍ.4/፡፡ በአንድ ጊዜ በአንድ ቦታ የተደነገገ አይደለም፡፡ ሰዎችን ደስ ለማሰኘት አይወጣም፤ የሚወጣው እግዚአብሔር ደስ ለማሰኘት ብቻ ነው፡፡ “ለዓለም ከሚመች ከንቱ ልፍለፋ ራቅ” እንዲል ለዓለም የሚመች ቀኖና አይወጣም፡፡ ቀኖና የሚወጣው የምእመናን መንፈሳዊ ሕይወት እንዲያድግና ምእመናን በሚኖሩበት ማኅበረ ሰብእ ውስጥ አርአያ እንዲኾኑ ነው፡፡ አንጻራዊ ጽድቅ ስለሌለ አንጻራዊ ቀኖናም የለም፡፡ ጥቁሩን ጥቁር ነጩንም ነጭ የሚል እንጂ የተድበሰበሰ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን አታወጣም፡፡ 4.ቀኖና በመጽሐፍ ቅዱስ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን በሥርዓትና በቀኖና ትመራ ዘንድ አዝዘዋል፡፡ ‹‹ያለ ሥርዓት ከሚሄድ ወንድም ሁሉ ትለዩ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛችኋለን፡፡›› (2ኛተሰ 3፤6) ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ለሥርዓት ዘብ መቆም እንደሚገባ ሲያመለክቱ ‹‹ወንድሞች ሆይ ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን ገስጹአቸው፡፡›› ብለዋል (2ኛ ተሰ 5፤14፣ 1ኛ ቆሮ 14፤40)፡፡ ከአይሁድ ወደ ክርስትና የመጡ ወገኖች ከአሕዛብ ወደ ክርስትና የገቡትን የሙሴን ሥርዓት ካልፈጸማችሁ (ግዝረትን፣ የመንጻት ጥምቀትን . . .) አትድኑም በማለት በቤተ ክርስቲያን ውዝግብ አስነሥተው ስለነበር ሐዋርያት ችግሩን ለመፍታት በኢየሩሳሌም የመጀመርያውን ጉባኤ (ሲኖዶስ) አድርገዋል፡፡ በችግሩም ዙርያ ከተነጋገሩ በኋላ 3 ቀኖናዎችን ደንግገዋል፡፡ እነዚህም በሐዋ. ሥራ 15፤29 ላይ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም ኤጲስ ቆጶሳትና ዲያቆናት ለአገልግሎቱና ለሥልጣኑ ማሟላት ያለባቸውን መሥፈርቶች ዘርዝረዋል፡፡ መሥፈርቶቹም ቀኖና (ሥርዓት) እንደሆኑ እንረዳለን (1ኛ ጢሞ 3፤2-13)፡፡ 5.የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ምንጮች የሐዋርያት ሲኖዶስ፡- እነዚህ ቤተ ክርስቲያን የሥርዓት መጻሕፍት ብላ በምትቀበላቸው ውስጥ የሚገኙ ሲሆኑ ስለ ቅዳሴ፣ ወደ ምሥራቅ ዞሮ ስለመጸለይ፣ በሰንበት፣ ረቡዕ፣ ዓርብና እና በተለያዩ በዓላት የሚጸለዩ ጸሎቶች፣ ስለ ሥርዓተ ክህነት፣ እንዲሁም ስለ አንድ ምእመን ክርስቲያናዊ ሥነምግባር . . . ወዘተ የሚገልጡ ቀኖናዎች ናቸው፡፡ ዓለም አቀፋዊ ጉባኤያት፡- እነዚህም በ3ቱ ጉባኤያት ማለትም በጉባኤ ኒቂያ፣ በጉባኤ ቊስጥንጥንያ፣ በጉባኤ ኤፌሶን ላይ የተወሰኑ የተለያዩ ሥርዓቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ቀኖናት በሁሉም የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ተቀባይነትና ተፈጻሚነት ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ብሔራውያን ጉባኤያት (የውስጥ ጉባኤያት)፡- እነዚህ ደግሞ ዓለም አቀፋዊ ሳይሆኑ በየሀገሩ ወይም በየአካባቢው በሚደረጉ ሲኖዶሶች የተወሰኑ ቀኖናዎች ናቸው፡፡ ለምሳሌ የዕንቆራ ጉባኤ፣ የቅርጣግና ጉባኤ፣ የሎዶቅያ ጉባኤ፣ የጋንግራ ጉባኤ፣ . . . ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያው 3ኛ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ዘመን ምእመናን በጾም ወቅት ዓሣ እንዳይመገቡ ተወስኗል፡፡ እነዚህ ቀኖናት በዚያ ሀገር ወይም አካባቢ ውስጥ ብቻ ተፈጻሚነት ሊኖራቸው ይችላል፡፡ የአበው ውሳኔ፡- የተለያዩ ቅዱሳን አበው በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው የወሰኗቸው ቀኖናዎች ናቸው፡፡ ለምሳሌ እንደ ቅዱስ አቡሊደስ (በምሕጻረ ቃል “በደስ” ይባላል)፣ የቅዱስ ባስልዮስ በጋብቻ በክህነትና በምንኵስና ላይ የሠራቸው ቀኖናዎችን (“ባስ”)፣ . . . የመሳሰሉት ናቸው፡፡ 6.የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥቅሞች የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ሥርዓት እንዲኖረው ያደርጋል፡፡

VPN ( Virtual private network) አንደኛው ጥቅሙ ለምሳሌ አንድ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ ኢንተርኔት ተጠቃሚ VPN በሚያገናኝበት ጊዜ ከኢትዮጵያ ውጭ ባሉ ሀገሮች ከአንደኛው ሀገር ሰርቨር ጋር ይገናኛል፡፡ ያ ሆነ ማለት ደግሞ ኢትዮጵያ ላይ የተዘጉ ወይም access ለማድረግ የማይቻሉ የኢንተርኔት መረቦችን( like facebook, telegram) እንዲጠቀም ይረዳዋል፡፡ ለስልክ ለምሳሌ SUPER VPN , THUNDER VPN የመሳሰሉትን ከPLAYSTORE ላይ እንዲሁም ለላፕቶት ኮምፒውተር PSIPHON VPN አይነት አውርዳቹ ተጠቀሙ፡፡ Birhan Mezgeb

ሳንቀደም እንቅደም። ለኦርቶዶክሳውያን ሁሉ ይህንን ሊንክ ላኩላቸውና እንሰብሰብ። አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ጫና የማይፈጥር የሩሲያው ቴሌግራም ነው። ከሌሎች ማኅበራዊ ሚዲያዎች ቀድመን ቴሌግራምን የመረጥነውም ለዚህ ነው። በፍጥነት እንተሳሰብ እንተሳሰር። የጠላትን ወጥመድ ሴራውን ከሥር ከሥር እናፍርስ። የሚከተለው ሊንክ ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ይዳረስ ዘንድ ሊንኩን ለጓደኞቻችን ፎርዋርድ እናድርግ። https://t.me/+oQKWtq5vrzk1YWY0 https://t.me/onesinod

#one_eot_church ከሰኞ ጥር ፳፱ እስከ አርብ የካቲት ፫ / ፳፻፲፭ ዓ/ም በጾመ ነነዌ እና ተጨማሪ ሁለት ቀናት ምሕላ እና ጸሎት እንዲደረግ የአንድነት ገዳም ኅብረት መክረዋል:: It is o
+4
#one_eot_church ከሰኞ ጥር ፳፱ እስከ አርብ የካቲት ፫ / ፳፻፲፭ ዓ/ም በጾመ ነነዌ እና ተጨማሪ ሁለት ቀናት ምሕላ እና ጸሎት እንዲደረግ የአንድነት ገዳም ኅብረት መክረዋል:: It is ordered and suggested to fast and pray from Monday Feb 6 till Friday Feb 10, 2023, by the Monastic Union Association.

መልዕክተ ገዳማት pdf.pdf12.56 MB

የአባቶቻችን መልዕክት!

የመንፈስ ነፃነት.pdf17.23 MB

ስለ ቅዱስ ጋብቻ ዲን ብርሃኑ አድማስ.pdf0.23 KB

Screenshot 2021-02-12 at 7.01.18 PM.pdf17.23 MB