ch
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

前往频道在 Telegram
805
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
-130 天
帖子存档
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች በሱባኤ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ጥናት ዛሬ እንቀጥላለን። የዛሬው ጥናት ምዕራፍ 13 ይሆናል። ተዘጋጁ። ዛሬ ማታ 3:30 እንገናኝ።

ለሞጆ ሱባኤ ሴንተር የመጨረሻ የምዝገባ ቀን የሚሆነው ቅዳሜ ነሐሴ 13 ስለሆነ ከዛ በኃላ የሚመጣውን ስለማንቀበል ከወዲሁ የሚጠበቅባችሁን እንድትጨርሱ እናሳስባለን። ማስታወሻ መያዧ ደብተር እና መፅሐፍ ቅዱስ መያዝ ግዴታ ነው። ብትችሉ ጉዳዮቻችሁን ቀድማችሁ ጨርሳችሁ በመምጣት ስልካችሁን ማጥፍት ከቻላችሁ ጥሩ የሱባኤ ግዜ እንዲኖራችሁ ይረዳችኋል።

ቀጣይ የሚመጣው 2016 ዓ.ም ሊሆን ያለውን ሊመጣ ያለውን አናውቀውም። ግን አንድ ነገር ከወዲሁ ማወቅ እንችላለን ምንም ያልባከኑ ልንጠቀምባው ፈቃደኛ የሆኑ ቀናቶች ሳምንታቶች እና ወራቶች አልፎም ሙ
ቀጣይ የሚመጣው 2016 ዓ.ም ሊሆን ያለውን ሊመጣ ያለውን አናውቀውም። ግን አንድ ነገር ከወዲሁ ማወቅ እንችላለን ምንም ያልባከኑ ልንጠቀምባው ፈቃደኛ የሆኑ ቀናቶች ሳምንታቶች እና ወራቶች አልፎም ሙሉ አንድ ዓመት ይጠብቁናል። እነዚህ ግዜያቶች በራሳቸው ከሌሎች ዓመታቶች የተለየ ነገር አይሰጡንም ወይም ደግሞ 2016 ከ 2015 የሚለየው በአቆጣጠር ለውጥ ብቻ ነው። ግን አንድ ነገር ማድረግ ዕድል አለን ዓመታችን ፍሬያማና ስኬታማ እንዲሆን እኛ መ ዋ ጀ ት ከቻልን ዘመኑን መዋጀት እንችላለን። እንዴት ዘመኑን አንዋጃለን? 1 ዘመኑን በእግዚአብሔር ቃል በማየት 2 በአእምሮ በመታደስ 3 ግልፅ የሆነ ራዕይ በመያዝ 4 ውስጣችን ያለውን እግዚአብሔር የሰጠንን በመረዳት እንደ ክርስቲያን ዓመቱ ያመጣልኝን የምቀበል ሳይሆን በዓመቱ ላይ እንዴት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መኖር እንደሚገባኝ በመዘጋጀት ዓመቱ ለእኔ እንደተሰጠኝ በመረዳት ስኬታማ ዓመት ለማሳለፍ መዘጋጀት ትልቅ መረዳት ነው። እኔ ለዘመኑ የተሰጠሁ ሳልሆን ዘመኑ ለኔ የተሰጠኝ ነኝ!!! በሞጆ ሱባኤ ሴንተር በእነዚህ ሀሳቦች ላይ እንደ እግዚአብሔር ቃል በደንብ እንማማርበታለን እንወያይበታለን ለቀጣዩ ዓመት የሚሆን ኃይል ይዘን እንወጣለን።

#ደረሰ_ደረሰ በጉጉት የምንጠብቀው ዓመታዊ የሱባኤ ፕሮግራም ከነሐሴ 17-20 በሞጆ ሱባኤ ሴንተር #እነሆ_አዲስ_ነገር_አደርጋለሁ_እርሱም_አሁን_ይበቅላል!!! 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿�
#ደረሰ_ደረሰ በጉጉት የምንጠብቀው ዓመታዊ የሱባኤ ፕሮግራም ከነሐሴ 17-20 በሞጆ ሱባኤ ሴንተር #እነሆ_አዲስ_ነገር_አደርጋለሁ_እርሱም_አሁን_ይበቅላል!!! 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ዘንድሮ በሚኖረን የሱባኤ ግዜ ይህን ዓመት እንዴት እንዳሳለፍን በእግዚአብሔር ቃል ራሳችንን የምንፈትሽበት ለቀጣዩ ዓመት ስንቅ ይዘን ታጥቀን የምንወጣበት ልዩ ግዜ ይኖረናል። #የምንማማርበትና_የምንወያይበት_ርዕሶች 1 በፍቅር መመላለስ 2 በታደሰ አእምሮ ያለ ሕይወት 3 ዘመኑን መዋጀት(እንዴት ዘመናችንን እንዋጅ?) 4 በጥበብ መመላለስ 5 በሕብረት መታደስ 6 የምስጋና ኃይል 7 ፍሬያማ ንስሐ 8 በመንፈስ መሞላት 9 የፀጋን ኃይል መረዳት

ነሐሴ.jpg1.19 MB

#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_መነቃቃት_ሰሚናር ዘወትር እሁድ ከቀኑ 7:30 አስከ 9:00 ሰዓት ቦታ ጎተራ ዶንቦስኮ ቤተ ፀሎት መፅሐፍ ቅዱስ ለመማር ፍላጎት ላላችሁ ልዩ እድል ነው

#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_መነቃቃት_ሰሚናር ሐምሌ 30 ይጀምራል ዘወትር እሁድ ከቀኑ 7:30 አስከ 9:00 ሰዓት ቦታ ጎተራ ዶንቦስኮ ቤተ ፀሎት መፅሐፍ ቅዱስ ለመማር ፍላጎት ላላችሁ ልዩ እድል ነው።
#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_መነቃቃት_ሰሚናር ሐምሌ 30 ይጀምራል ዘወትር እሁድ ከቀኑ 7:30 አስከ 9:00 ሰዓት ቦታ ጎተራ ዶንቦስኮ ቤተ ፀሎት መፅሐፍ ቅዱስ ለመማር ፍላጎት ላላችሁ ልዩ እድል ነው

“የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤” — ኤፌሶን 5፥9-10

#ምዝገባ #ተጀመረ ሞጆ ሱባኤ ሴንተር ከ ነሐሴ 17 እስከ 20 የአዲስ ዓመት ልዩ ዝግጅት ሱባኤ “እነሆ፥ አዲስ ነገርን አደርጋለሁ፤ እርሱም አሁን ይበቅላል፥ እናንተም አታውቁትምን? በምድረ በዳም መንገድን በበረሀም ወንዞችን አደርጋለሁ።” — ኢሳይያስ 43፥19 #የሚኖሩን #ፕሮግራሞች ቅዳሴ : የእግዚአብሔር ቃል ትምህርት : በቃሉ ውይይት : ዝማሬ (አምልኮ) የቅዱስ ቁርባን ስግደት (አዶሬሽን) : ንስሐ: የግል የፀጥታ ግዜ ይኖረናል። ቀድመው ለሚመዘገቡ ከአዲስ አበባ ለሚነሱ 22 ሰዎች የደርሶ መልስ ትራንስፖርት ማህበሩ ይሸፍናል። በሴንተሩ ለሚኖር ቆይታ ሙሉ ወጪ ዶርም 1650 ብር አዲሱ ፎቅ ላይ መጠቀም ለሚፈልጉ 2250 ይሆናል። 0911958019

ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ሳምንታዊው መደበኛ የእሁድ ፕሮግራማችን (በ16/11/15) በፊሶን የመዝሙር ኮንሰርት ምክንያት የማይካሄድ በመሆኑ ሁላችንም ኮንሰርቱ ላይ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆን ስንል በትህትና እንጠይቃለን።

ኢሳይያስ 43 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁸ የፊተኛውን ነገር አታስተውሉ፥ የጥንቱንም ነገር አታስቡ። ¹⁹ እነሆ፥ አዲስ ነገርን አደርጋለሁ፤ እርሱም አሁን ይበቅላል፥ እናንተም አታውቁትምን? በምድረ በዳም መንገድን በበረሀም ወንዞችን አደርጋለሁ። ²⁰-²¹ ምስጋናዬን እንዲናገሩ ለእኔ የፈጠርሁት ሕዝብ፥ የመረጥሁትን ሕዝቤን አጠጣ ዘንድ በምድረ በዳ ውኃን በበረሀም ወንዞችን ሰጥቻለሁና የምድረ በዳ አራዊት፥ ቀበሮችና ሰጎኖች፥ ያከብሩኛል። #ሰላም ቅዱሳን የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንዴት ናችሁ? ከነገ ሰኞ ጀምሮ ለቀጣዮቹ #21 ቀናት የፆም ፀሎት ፕሮግራም ይኖረናል። ሁላችሁም በዚህ ፕሮግራም ላይ እንድትሳተፉ አደራ እንላለን። በድካም ውስጥ ላለን ሁሉ ልዩ የሆነ ጉብኝትና ኃይል የምንቀበልበት ልዩ የሆነ ግዜ ይኖረናል። ቦታ ቅዱስ ሚካኤል ቻፕል ሰዓት ከ 11 እሰከ 1:30

ኢሳይያስ 43 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁸ የፊተኛውን ነገር አታስተውሉ፥ የጥንቱንም ነገር አታስቡ። ¹⁹ እነሆ፥ አዲስ ነገርን አደርጋለሁ፤ እርሱም አሁን ይበቅላል፥ እናንተም አታውቁትምን? በምድረ በዳም መንገድን በበረሀም ወንዞችን አደርጋለሁ። ²⁰-²¹ ምስጋናዬን እንዲናገሩ ለእኔ የፈጠርሁት ሕዝብ፥ የመረጥሁትን ሕዝቤን አጠጣ ዘንድ በምድረ በዳ ውኃን በበረሀም ወንዞችን ሰጥቻለሁና የምድረ በዳ አራዊት፥ ቀበሮችና ሰጎኖች፥ ያከብሩኛል። #ሰላም ቅዱሳን የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንዴት ናችሁ? ከነገ ሰኞ ጀምሮ ለቀጣዮቹ #21 ቀናት የፆም ፀሎት ፕሮግራም ይኖረናል። ሁላችሁም በዚህ ፕሮግራም ላይ እንድትሳተፉ አደራ እንላለን። በድካም ውስጥ ላለን ሁሉ ልዩ የሆነ ጉብኝትና ኃይል የምንቀበልበት ልዩ የሆነ ግዜ ይኖረናል። ቦታ ቅዱስ ሚካኤል ቻፕል ሰዓት ከ 11 እሰከ 1:30