ch
Feedback
የኢ/ኦ/ተዋህዶ የቅዱሳን ስእል አድኖ

የኢ/ኦ/ተዋህዶ የቅዱሳን ስእል አድኖ

前往频道在 Telegram
696
订阅者
+124 小时
+77 天
+3830 天
帖子存档
​​✧ ታቦር አበራ ✧ ታቦር አበራ ምድርን ከደናት ያደመና እንቅልፍ የለንም ታላቅ ነጎድጕድ ሆኗልና አነቃን ለምስጋና     ሙሴም የቀደመው ሰዉ  ኤልያስ ኃይለኛው ተገኝተዋል በታቦር ምስክርህ ሆነው እኛም ከገናናው ክብር ያባቱን ቃል ሰምተናል በረዶ ሆኗል ልብሱ እፁብ እፁብ ብለናል        ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ ቃል ገብተህልኝ ነበር ልታሳየኝ ክብርህን ንገስ ከሞት ገስግሰህ አይቸሃለሁ አሁን የሳት ፈረሶች አሉህ ታዋጊው የኔ ጌታ አርሙኒየም ደስ አለው ስሳራን ስለመታ         ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ እጠብቅሃለሁኝ በምታልፍበት ቆሜ መብራቶቼን አብርቼ ነጩን ልብስ ተሸልሜ የዳዊት ልጆይ ግባ ኢየሱስ ወደቤቴ ብልኤል እልሀለሁ ድናለች ሰውነቴ         ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ ሁሉንም ብታከብር ሁሉንም ብትምረው ማነው ቸርነትህን የሚከለክለው ጠዋትም የተጠራ አምሽቶ የገባው ሆነዋል ባለዋጋ ከበዛው ስጦታው         ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ የረዳኸው ይናገራል ያሰበከው በሕይወቱ አቤነዘር እያለ ይዘምር ባንደበቱ በደስታየም ቀን አለህ አይሃለሁ ከጎኔ ከነጋር አ ልቅሰሃ አሳዝኖህ ሀዘኔ  ✥•┈•●◉

✧ በደብረ ታቦር ✧ በደብረ ታቦር (፪) ለሙሴ ወኤልያስ ታያቸው ምሥጢር ዮሐንስ ያዕቆብ ጴጥሮስም ባሉበት ሙሴና ኤልያስ በተጋበዙበት አምላካዊ ክብሩን ኢየሱስ ገለጠ በፊታቸው ድንገት መልኩ ተለወጠ       ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ ሙሴና ኤልያስ የታደሉ ናቸው ብርሃነ መለኮት ማየት መቻላቸው ከሕያዋን ዓለም ወደዚህ በመምጣት ከሔዱ በኋላ ጥለውት ንቀውት           ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ ቀኑ በመድረሱ ሳይጎድል ከቁጥሩ የሚገለጽበት አምላካዊ ክብሩ ክብሩን ተመልካቾች እንዲሆኑ ጠራ እነ ኤልያስን ከነ ጴጥሮስ ጋራ  ✥•┈•●◉ ናሁ ሰማን-ዜማ ◉●•┈•✥ ╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮     ✞ @Nahuseman256✞     ✞ @Nahuseman256 ✞         ╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯

+1
ደብረ መቅደሱ ✧ ደብረ መቅደሱ ለእግዚአብሔር ማርያም ሰላም ሰላም ለላሕይኪ አዳም ናዝሬት ሰላም ዘአህጉር እም ደብረ ታቦር ሰላም ሰላም ለላሕይከ አዳም ትርጕም፡- የእግዚአብሔር የቅድስናው ተራራ ማርያም ሰላም ለአንቺ ይኹን ለደም ግባትሽ ምስጋና ይገባል የአህጉር እናት የምትኾኚ ናዝሬት ሰላምታ ይገባሻል አንተ የታቦር ተራራ ሰላምታ ይገባኻል ለውበትኸም ሰላምታ ይገባል ለነሐሴ 13 ወይም በደብረ ታቦር ጊዜ የሚዘመር  ✥•┈•●◉ ናሁ ሰማን-ዜማ ◉●•┈•✥ ╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮     ✞ @Nahuseman256✞     ✞ @Nahuseman256 ✞         ╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯

እንደ ፀሐይ      እንደ ፀሐይ ፊቱ ሲያበራ      ዓይናችን ካየ ታቦር ተራራ      በታቦር መሆን ለእኛ መልካም ነው      ስለጠገብን ክብሩን አይተነው የአምላክ ልጅ አምላክ ንጉሥ ነው እርሱ ሌላ አያስመኝም ፍቅሩን ሲቀምሱ (ሁሌ ከእርሱ ጋር መሆን ደስይላል እንዳለፈ ወንዝ ችግር ያስረሳል)(2)      ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ ገናናነቱ ክብሩ ተገልጦ የግርማው ሙቀት ሰንሰለት ቆርጦ (ከዓለም መንጋጋ እኛን ተናጥቋል ሞትን ዘልፎልን ህያው አርጎናል)(2)      ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ ከቶ አይደለንም እኛማ የእኛ በዋጋ ገዝቶን መልካሙ እረኛ (ተከፍቶልናል የምህረት በሩ ፍቅር የሳበው ስቦን በፍቅሩ)(2)    ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ የተሰሎንቄ አሸንክታቧ እንዳይማርከን ያ ወጥመድ ልቋ (ክብሩ ይውረሰን ሌላ አይግዛን ልባችን ታቦር ይሁነው ዙፋን)(2) ዘማሪት አዜብ ከበደ  ✥•┈•●◉ ናሁ ሰማን-ዜማ ◉●•┈•✥ ╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮     ✞ @Nahuseman256✞     ✞ @Nahuseman256 ✞         ╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯

ደብረ ታቦርደብረ ታቦር ተሞላ በግርማው ብርሃን ከበበው አሸብርቋል ረጅሙ ተራራ ክብሩ ሲያበራ ክብሩ ሲያበራ..... ጴጥሮስና ያዕቆብ ደግሞ ዮሐንስን ዩዟቸው ተጓዘ የወረጣቸውን በፊታቸው ሳለ ድንገት ተለወጠ ኢየሱስ ሲያበረ ልባቸው ቀለጠ ክብሩ ሲያበራ.... ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ታዯቸው ጴጥሮስ በተመስጦ ዳስ እንስራ አላቸው ፍቅሩን የቀመሰ አይመኝም ሌላ ክርስቶስ ነውና እውነተኛ ተድላ ክብሩ ሲያበራ.... በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነውና ስለመዳናችሁ ስሙት በጽሞና ብሎ ሲመሰክር የሰማይ ንጉሱ ከኢየሱስ በቀር አላዩም ሲነሱ  ✥•┈•●◉ ናሁ ሰማን-ዜማ ◉●•┈•✥ ╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮     ✞ @Nahuseman256✞     ✞ @Nahuseman256 ✞         ╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯

ሀሁ ብዬ .mp37.36 MB

✧ ሀሁ ብዬ ፊደል ✧ ሀሁ ብዬ ፊደል የቆጠርኩብሽ በአቦጊዳ አፌን የፈታውብሽ በመልእክት መንፈሴ ተደሰተ በዳዊቱ ብዙ ነው በረከቱ (2) ተዋህዶ ኧኸ ሀይማኖቴ የእውቀት ምንጭ ኧኸ መሰረቴ አለኝ ትዝታ ከዛፉ ስር 2 የኛ የኔታ ዱላ በትር 2 ሀሁ ብዬ ስጮህ         ሀ ድምፄን እያሰማው      ሁ አንዷን ቃል ስገድፋት    ሂ የኔታን አስቆጣው        ሃ ሀ ማለት እግዚህ ነው   ሄ እያሉ ሲቀኙ               ህ የኔታን አንደበት           ሆ ማር ይንጠፍጠፍበት   ሆ አዝ አቦጊዳ ብዬ መልእክተን ሳልወጣ 2 የኔታ ደከሙ እንቅልፋቸው መጣ 2 ፊደል ገበታዬን            ሀ ግዕዝ ጥያት ከመሬት            ሁ ካዕብ አቧራዬን ማቡነን          ሂ  ሣልስ ያዝኩኝ መላፋት           ሃ ራብዕ ሲነቁ የኔታ                  ሄ ኃምስ ብለው ከቀደሙ           ህ ሳድስ ልምጯን አነሱ             ሆ ሳብዕ ቁጣ ቃል አሰሙ          ሀ ግዕዝ አዝ ተማሪ እና ውሻ ሁል ጊዜ አይስማሙ 2 እስከ እድሜ ልካቸው አሉ እንደ ተዳሙ 2 አቆፋዳ አንግቦ            ሀ ገመሎውን ለብሶ         ሁ በእንተ ስሟ ሲል          ሂ ድምፁን አለስልሶ        ሃ አንዲት እፍኝ ጥሬ        ሄ የቁራሽ እንጀራ           ህ ውሻ ሲያባርረው         ሆ አይ ያለው መከራ        ሆ አዝ አለኝ ትዝታ ቅኔ ቤት 2 በእንተ ስሟ ለማርያም ማለት 2 የዜማው መለኪያ         ሀ ጭረት ምልክቱ            ሁ እዝልና ግዕዙ               ሂ ቅናቱ ድፋቱ                 ሃ ጣቢዘር ጥሬዘር          ሄ ደግሞም ቅኔ ቤት       ህ አገባብ ሚስጥሩ         ሆ ሰባት ስምንት ቤት       ሆ አዝ አለኝ ትዝታ ከመቅደሱ 2 ሌሊቱን ሙሉ ማወደሱ 2 መፃሃፍን ዘርግቶ         ሀ ከጉባኤ ውሎ             ሁ መሪ ዜማ አጥንቶ        ሂ ስምአኒ ብሎ              ሃ ተፈስሂ እያልን             ሄ እሱን ስደረድር           ህ ሳዜመው ይነጋል        ሆ ቅኔ ስደረድር             ሆ አዝ አለኝ ትዝታ ከጎጆዬ 2 ተሰቅላ አቆፋዳዬ 2 ሀሁ ብዬ ፊደል የቆጠርኩብሽ በአቦጊዳ አፌን የፈታውብሽ በመልእክተ መንፈሴ ተደሰተ በዳዊቱ ብዙ ነው በረከቱ   ✥•┈•●◉ ናሁ ሰማን-ዜማ ◉●•┈•✥ ╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮     ✞ @Nahuseman256✞     ✞ @Nahuseman256 ✞         ╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯

በክብር_ተገለጠ_በታቦር_Bekbr_Tegelette_Betabor_ደብረ_ታቦር_.mp35.67 MB

✧ በክብር ተገለጠ በታቦር ✧ በክብር በክብር ተገለጠ በታቦር /2/ በተራራው ላይ አበራ እንደ ፀሀይ /2/ ድምፅህን ሰማና በብሩህ ደመና×2 የቡሄው ብርሀን ለኛ በራልን×2 ግርማህን አይቶ    ሆ ማነው ያልፈራ       ሆ ከፀሀይ ልቆ            ሆ እርሱ ሲያበራ        ሆ የሙሴ አምላክ     ሆ የነ ኤልያስ             ሆ በፍጥረታቱ           ሆ የምትወደስ          ሆ በክብር በክብር ተገለጠ በታቦር /2/   ድምፅህን ሰማና በብሩህ ደመና ×2   የቡሄው ብርሀን ለኛ በራልን ×2 ብሩህ ደመና              ሆ ሲጋርደን                    ሆ መንፈስ ቅዱስም        ሆ አረጋጋን                     ሆ አባቱም አለ              ሆ ከሰማያት                  ሆ አንድያ ልጄን            ሆ እርሱን ስሙት         ሆ በክብር በክብር ተገለጠ በታቦር /2/ በተራራው ላይ አበራ እንደ ፀሀይ /2/          ቃሉንም ሰምተናል ህይወት አጊኝተናል×2    ለነፍሳቹ ጌታ አቅርቡ እልልታ×2 ብሩህ ደመና              ሆ ሲጋርደን                    ሆ መንፈስ ቅዱስም        ሆ አረጋጋን                     ሆ አባቱም አለ                ሆ ከሰማያት                    ሆ አንድያ ልጄን              ሆ እርሱን ስሙት            ሆ በክብር በክብር ተገለጠ በታቦር /2/ በተራራው ላይ አበራ እንደ ፀሀይ /2/ ታቦር አበራ            ሆ አርሞንየም           ሆ ክብሩ ሲገለጥ       ሆ መድኀኔአለም        ሆ የሁሉ ንጉስ           ሆ የፍጥረት ጌታ        ሆ መልኩ ተለየ           ሆ ከታቦር ከፍታ          ሆ በክብር በክብር ተገለጠ በታቦር /2/ በተራራው ላይ አበራ እንደ ፀሀይ /2/  ጴጥሮስም አለ    ሆ ዳስን እንስራ        ሆ እዚ እንድንኖር     ሆ ከጌታ ጋራ            ሆ አምላክነቱን         ሆ ክብሩን ስላየ       ሆ ከዓለም ጉያ        ሆ እራሱን ለየ          ሆ    እንሆ ለስሙ ምስጋናን አሰሙ×2    የቡሄው ብርሀን ለኛ በራልን×2 አመት አውደአመት ድገምና አመት ድገምና ያባብዬን ቤት  ድገምና አመት ይባረክ በእውነት  ድገምና አመት የማምዬን ቤት ድገምና አመት ይትረፍረፍ በእውነነት ድገምና አመት     ክበር በእልልታ ×2 የሁሉ ጌታ /2/     ንገስ ዘለዐለም ×2 መድኅኔአለም /2/     ይኸው ምስጋና ×2 ንጉስ ነህና /2/ ከታቦር ከፍታ ተገለጠ ጌታ ከታቦር ተራራ እንደ ፀሀይ በራ የሰላም የደስታ ይሁን አውደ አመቱ በጤና ያድርሰን ደግሞ ለአመቱ    ያድርሰን ×2 ደግሞ ለአመቱ /2/   ✥•┈•●◉ ናሁ ሰማን-ዜማ ◉●•┈•✥ ╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮     ✞ @Nahuseman256✞     ✞ @Nahuseman256 ✞         ╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯

እመቤታችን_በቀኝ_ቆማለች_መዝሙረ_ዳዊት_በቴሌግራም.mp34.78 MB

✧ ሃሌ-ሉያ አንተ ✧ ሃሌሉያ አንተ ሰው ሆይ /2/ ቡሄ መድረሱን ሰምተሃል ወይ ሀሌሉያ አንተ ሰው ሆይ መስማቱንማ ሰምቼ ነበር ሀሌሉያ አንተ ሰው ሆይ ከዚያ ቢያደርሰኝ ልዑል እግዚአብሔር ሃሌሉያ አንተ ሰው ሆይ እናቴ ሆይ.......... ሆ ይህን ባየሻ ........ሆ በቁርማ ዳቦ .......ሆ ሲጥለኝ ውሻ........ሆ ደጓ ጫማዋን ......ሆ አውልቃዋለች........ሆ ውሃ ሲጠማ..........ሆ አጠጥታዋለች........ሆ የስዋ ውዳሴ ........ሆ ሆኖኛል ውይን ......ሆ ዘሬም ብዘምር ......ሆ እኖራለሁኝ ............ሆ ዘምር በለው ተነሳ በገናን አንሳ (4) በእምነት እንውጣ .ሆ ከተራራው ላይ......ሆ ይታይ ብርሃኑ........ሆ ክብሩ ኤልሻዳይ....ሆ ሙሴን እንጠይቅ...ሆ የጥንቱን ነገር .......ሆ ምን እንደሚለው ...ሆ ጌታን ሲያናግር......ሆ ድምጹን እንስማ ....ሆ እንደ ትሁትነቱ.......ሆ እንቀበለው ..........ሆ እኛም በትሩን .......ሆ ዘምር በለው ተነሳ በገናን አንሳ (2) ተቁኙለት በልልታ ላዳኙ ጌታ(2) ተራራውማ ...............ሆ ነውና አምሳል.............ሆ ለቤተ ክርስቲያን.........ሆ መንበረ ልዑል............ሆ ወጥተን እንጠይቅ .....ሆ ኤልያስን...................ሆ እንድንዳስሰው...........ሆ ጸጓር ክንዱን...........ሆ ሰማይ ብትለጉም........ሆ ባህር ብትከፍል...    ....ሆ እሳት ብታወርድ..    ...ሆ ጠላትም ቢርድ    ......ሆ በሰረገላ .    .............ሆ የተነጠከው..............ሆ ይህ ሁሉ ክብር.... .....ሆ በማን ስልጣን ነው.....ሆ ለሁላችን መልካም ነው በዚህ መኖር(4) የእመብርሃን .........ሆ የምዬ ልጅ............ሆ ተጥሎ ላይቀር .....ሆ ተረስቶ ደጅ...........ሆ ሰአሊ ለነ .............ሆ ባለበት አፉ...........ሆ የጭንቁን እለት .....ሆ ተሰብሮ ሰልፉ  ......ሆ እንዳባቶቹ ... .........ሆ ቅኔን ተቀኘ...... .......ሆ ድንግል ስትረዳው....ሆ አይኑ ስላየ.... ..........ሆ ተፈስሂ ደብረ ታቦር(2) ተፈስሂ አርሙኒየም (2) ባንቺ ላይ ታየ እግዚአብሔር ተፈስሂ አርሙንየም ሙሴ ስላለ ...........ሆ መና ያውርዳል........ሆ ቅዱስ ኤልያስ........ሆ ስጋ ያመጣል..........ሆ ዮሃንስንም.............ሆ ጌታ ይወዳል..........ሆ መድኃኒታችን.........ሆ ፈውስ ይሆነናል......ሆ በዚህ እንድንኖር ....ሆ ዳሱን ጥለናል ........ሆ ዘምር በለው ተነሳ በገናን አንሳ (4) አባቴም ቤት..........ሆ አለኝ ለከት.............ሆ እናቴም ቤት ..........ሆ አለኝ ለከት...,.........ሆ ፍልሰታ ስትሆን.......ሆ የቆምኩባት............ሆ በድብረ ታቦር .........ሆ ያጌጥኩባት...........ሆ ዘምር በለው ተነሳ በገናን አንሳ(2) ተቀኙለት  በልልታ ላዳኙ ጌታ(2) አመት አውዳመት "ድገምና" አመት "ድገምና" ያባብዬን ቤት "ድገምና" አመት "ድገምና" ይግባ በረከት "ድገምና" አመት "ድገምና" የማምዬ ቤት "ድገምና"  አመት "ድገምና" ይትረፍረፍ በእውነት "ድገምና" አመት "ድገምና" ነሩ በሀይማኖት ጽኑ በጸሎት  በተዋህዶ ቤት(4) የሰማይ ሰራዊት በእምነት ያድርጋችሁ "" "' አማኑኤል በጸጋ በእምነት ያኑራችሁ "  " ከስጋ ወደሙ በእምነት ያድላችሁ  "  " ዘርን እንደ አብርሃም በእምነት ያድላችሁ "  " ይባረክ በእግዚአብሔር በእምነት ዘመናችሁ  "  " /2/ እድሜና ጤናውን በእምነት ያድላችሁ "  "  /2/             ✥•┈•●◉ ናሁ ሰማን-ዜማ ◉●•┈•✥ ╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮     ✞ @Nahuseman256✞     ✞ @Nahuseman256 ✞         ╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯

ቡሄ በሉ.mp311.93 MB

✧ ሃሌ-ሉያ አንተ ✧ ሃሌሉያ አንተ ሰው ሆይ /2/ ቡሄ መድረሱን ሰምተሃል ወይ ሀሌሉያ አንተ ሰው ሆይ መስማቱንማ ሰምቼ ነበር ሀሌሉያ አንተ ሰው ሆይ ከዚያ ቢያደርሰኝ ልዑል እግዚአብሔር ሃሌሉያ አንተ ሰው ሆይ እናቴ ሆይ.......... ሆ ይህን ባየሻ ........ሆ በቁርማ ዳቦ .......ሆ ሲጥለኝ ውሻ........ሆ ደጓ ጫማዋን ......ሆ አውልቃዋለች........ሆ ውሃ ሲጠማ..........ሆ አጠጥታዋለች........ሆ የስዋ ውዳሴ ........ሆ ሆኖኛል ውይን ......ሆ ዘሬም ብዘምር ......ሆ እኖራለሁኝ ............ሆ ዘምር በለው ተነሳ በገናን አንሳ (4) በእምነት እንውጣ .ሆ ከተራራው ላይ......ሆ ይታይ ብርሃኑ........ሆ ክብሩ ኤልሻዳይ....ሆ ሙሴን እንጠይቅ...ሆ የጥንቱን ነገር .......ሆ ምን እንደሚለው ...ሆ ጌታን ሲያናግር......ሆ ድምጹን እንስማ ....ሆ እንደ ትሁትነቱ.......ሆ እንቀበለው ..........ሆ እኛም በትሩን .......ሆ ዘምር በለው ተነሳ በገናን አንሳ (2) ተቁኙለት በልልታ ላዳኙ ጌታ(2) ተራራውማ ...............ሆ ነውና አምሳል.............ሆ ለቤተ ክርስቲያን.........ሆ መንበረ ልዑል............ሆ ወጥተን እንጠይቅ .....ሆ ኤልያስን...................ሆ እንድንዳስሰው...........ሆ ጸጓር ክንዱን...........ሆ ሰማይ ብትለጉም........ሆ ባህር ብትከፍል...    ....ሆ እሳት ብታወርድ..    ...ሆ ጠላትም ቢርድ    ......ሆ በሰረገላ .    .............ሆ የተነጠከው..............ሆ ይህ ሁሉ ክብር.... .....ሆ በማን ስልጣን ነው.....ሆ ለሁላችን መልካም ነው በዚህ መኖር(4) የእመብርሃን .........ሆ የምዬ ልጅ............ሆ ተጥሎ ላይቀር .....ሆ ተረስቶ ደጅ...........ሆ ሰአሊ ለነ .............ሆ ባለበት አፉ...........ሆ የጭንቁን እለት .....ሆ ተሰብሮ ሰልፉ  ......ሆ እንዳባቶቹ ... .........ሆ ቅኔን ተቀኘ...... .......ሆ ድንግል ስትረዳው....ሆ አይኑ ስላየ.... ..........ሆ ተፈስሂ ደብረ ታቦር(2) ተፈስሂ አርሙኒየም (2) ባንቺ ላይ ታየ እግዚአብሔር ተፈስሂ አርሙንየም ሙሴ ስላለ ...........ሆ መና ያውርዳል........ሆ ቅዱስ ኤልያስ........ሆ ስጋ ያመጣል..........ሆ ዮሃንስንም.............ሆ ጌታ ይወዳል..........ሆ መድኃኒታችን.........ሆ ፈውስ ይሆነናል......ሆ በዚህ እንድንኖር ....ሆ ዳሱን ጥለናል ........ሆ ዘምር በለው ተነሳ በገናን አንሳ (4) አባቴም ቤት..........ሆ አለኝ ለከት.............ሆ እናቴም ቤት ..........ሆ አለኝ ለከት...,.........ሆ ፍልሰታ ስትሆን.......ሆ የቆምኩባት............ሆ በድብረ ታቦር .........ሆ ያጌጥኩባት...........ሆ ዘምር በለው ተነሳ በገናን አንሳ(2) ተቀኙለት  በልልታ ላዳኙ ጌታ(2) አመት አውዳመት "ድገምና" አመት "ድገምና" ያባብዬን ቤት "ድገምና" አመት "ድገምና" ይግባ በረከት "ድገምና" አመት "ድገምና" የማምዬ ቤት "ድገምና"  አመት "ድገምና" ይትረፍረፍ በእውነት "ድገምና" አመት "ድገምና" ነሩ በሀይማኖት ጽኑ በጸሎት  በተዋህዶ ቤት(4) የሰማይ ሰራዊት በእምነት ያድርጋችሁ "" "' አማኑኤል በጸጋ በእምነት ያኑራችሁ "  " ከስጋ ወደሙ በእምነት ያድላችሁ  "  " ዘርን እንደ አብርሃም በእምነት ያድላችሁ "  " ይባረክ በእግዚአብሔር በእምነት ዘመናችሁ  "  " /2/ እድሜና ጤናውን በእምነት ያድላችሁ "  "  /2/             ✥•┈•●◉ ናሁ ሰማን-ዜማ ◉●•┈•✥ ╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮     ✞ @Nahuseman256✞     ✞ @Nahuseman256 ✞         ╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯

​​​​ፍልሰታ ምን ማለት ነው? ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም ለዚህ ጥያቄ የሚከተለውን ምላሽ ሰጥተዋል፤ "ፍልሰታ ማለት ፈለሰ /ተሰደደ/ ከሚለው ግስ የወጣ ነው።" ‹ፍልሰት› ማለት ደግሞ የተለያየ ትርጕም ቢሰጠውም ‹ፍልሰታ  ለማርያም› ተብሎ ሲገለጽ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው  ወደ ማያልፈው ዓለም ከመቃብር የወጣችበት (የተነሣችበት) ቀን ማለት ነው፡፡ ወይም ደግሞ ከሥጋዊው ዓለም ወደ መንፈሳዊው ዓለም የተሸጋገረችበት ማለት ነው፡፡›› ቀሲስ ስንታየሁ አባተም በተመሳሳይ መልኩ ስለ ፍልሰታ እንዲህ በማለት ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡  ‹ፍልሰታ ለማርያም› የሚለው የግእዝ  ቃል ሲኾን ‹ፍልሰታ› ማለት ደግሞ ‹ፈለሰ› ከሚል ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ‹ፍልሰት› ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መሔድን (መፍለስን) ያመለክታል፡፡ እመቤታችን ካረፈች በኋላ የሥጋዋን መፍለስ አስመልክቶ ሐዋርያት የእመቤታችን ሥጋ የት እንደ ተቀበረ አላወቁም ነበርና እግዚአብሔር የእመቤታችንን ሥጋ እንዲገልጥላቸው የጾሙት ጾም ነው፡፡ ሐዋርያት ሁለት ሱባዔ ጾመው የእመቤታችንን ሥጋዋን ሰጥቷቸው  ትንሣኤዋንና ዕርገቷን በማየት በረከት ያገኙበት ጾም ነው፡፡ ስለኾነም ምእመናን ፍልሰታ ለማርያምን ከልጅ እስከ አዋቂው በጾም በጸሎትና በመቍረብ በጋራ በፍቅር፣ በሰላም ያሳልፉታል፡፡››  ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም ካሣ እንዳብራሩት ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን እንዲጠብቃት ከተደረገ በኋላ ሐዋርያት ‹‹የእመቤታችን ነገር እንዴት ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ‹‹እመቤታችንማ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ናት›› ብሎ ነገራቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሐዋርያት እመቤታችን ከመቃብር መነሣቷንና ማረጓን ማየት አለብን፤ እንዴት ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ እንቀራለን ብለው በመንፈሳዊ ቅናት በመነሣሣት ነሐሴ አንድ ቀን በዕለተ ሰኞ ሁለት ሰባት ሱባዔ ያዙ፡፡ በዐሥራ አራተኛው ቀን ጌታችን የእመቤታችንን ሥጋ አንሥቶ ሰጣቸውና በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡ እመቤታችን በ፷፬ ዓመቷ ጥር ፳፩ ቀን ዐርፋ ነሐሴ ፲፬ ቀን ተቀብራለች፡፡ ይኹንና ሐዋርያት ቢቀብሯትም ትንሣኤዋንና ዕርገቷን አላዩም ነበር፡፡ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያየው ሲቀብሯት ያላየው ሐዋርያው ቶማስ ነው፡፡ ቶማስ እንዲያስተምር ሕንድ አገር ዕጣ ደርሶት አስተምሮ በደመና ሲመለስ ነሐሴ ፲፮ ቀን እመቤታችን ስታርግ ሕዋ ላይ ተገናኙ በማለት ሊቀ ማእምራን ደጉ ያስረዳሉ፡፡ እንደ እርሳቸው አገላለጽ ምእመናን ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን ዕረፍት፣ ትንሣኤና ዕርገቷ የሚዘከርበት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ የኾነ ጾም ነው፡፡ በየዓመቱ ሕፃን አዋቂው ሳይቀር የእመቤታችን ፍቅር አድሮባቸው ጾሙን ይጾማሉ፣ ያስቀድሳሉ፤ ይቈርባሉ፡፡ የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው? የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው? ለሚለው ጥያቄ ሊቀ ማእምራን ደጉ ምላሽ ሲሰጡም "ኢትዮጵያ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዐስራት ሀገር በመሆኗ እና ሕዝበ ክርስትያኑ ለእመቤታችን ልዩ ፍቅር ስላላቸው መሬት ላይ እየተኙ፣ ጥሬ እየበሉ በሰላም በፍቅር ይጾሙታል፡፡  ምእመናን ፍልሰታን ከሌሎች አጽዋማት በተለየ መልኩ መሬት ላይ እየተኙ ይጾሙታል፡፡ ይህ ደግሞ የእመቤታችን ፍቅር ስለሳባቸው ነው ፍቅር›› በማለት ያብራራሉ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ! 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur

እንኳን አደረሳችሁ! ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል *-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-* ዑራኤል የሚለው ስም `ዑር' እና 'ኤል' ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። ዑራኤል ማለት ትርጉሙ “የብርሃን ጌታ”፣ ”የአምላክ ብርሃን" ማለት ነው። ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነዉ። በመሆኑም መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ፣ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። መጽ/ሄኖክ 6÷2 ምሥጢረ ሰማይና እውቀትንም ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት የፀሀይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል። መጽ/ሄኖክ 28÷13 ቅዱስ_ዑራኤል_(ሱርያል)/ዑርኤል/ በመላእክት_ከተማ_በራማ_ካሉት_ሦስት ነገዶች ውስጥ አንዱ ነገድ ሥልጣናት ይባላል በሥልጣናት ላይ ከተሾሙ ሊቀና መላእክት ውስጥ አንዱ ሊቅን መላእክት ቅዱስ ሱርያል ይባላል ሱርያል የሚለውን ስም በአንዳንድ ድርስናት ካልሆነ በስተቀር እምብዛም አይታውቅም ትርጉሙም ፦፦ዐለቴ እግዚአብሔር ነው ፦፦ማለት ነው ሱርያል የቅዱስ ዑራኤል ሌላ ስሙ ነው ዑራኤል ማለት እግዚአብሔር_ብርሃን ነው ማለት ነው በቤተ ክርስቲያን በስፍት የሚታውቅው ስም ዑራኤል የሚለው ስም ነው።/ድርሳን ዑራኤል 1991 ገጽ 14/ • ቅድስት ድንግል ማርያምን፣ ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ የመራ፤ • ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ በተሰቀለ ጊዜ፣ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ፣ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨ፤ •እውቀት ለተሰዎረባቸው ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን ያጠጣ፤ • አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመልአኩ አማላጅነት ብዙ ድርሰት የደረሱት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ጽዋ ሕይወትን ስላጠጣቸው ነው፣ • በቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ የተመሰረቱ ገዳማት በቅዱስ ዑራኤል መሪነት ነው፤ የመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል በዓላት በዓመት 3 ናቸው። • ጥር 22 በዓለ ሲመቱ፣ • መጋቢት 27 የጌታ ደሙን ለዓለም የረጨበት፣ • ሐምሌ 21 እና 22 ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበት። በጸሎቱ ለተማጸነ ከአምላኩ በረከትን ምህረትን የሚያሰጥ አዛኝ እሩህሩህ መልአክ ነው። የቅዱስ ዑራኤል አማላጂነት አይለየን፤ ሁላችንንም ይጠብቀን፡፡ @ortodoxtewahedoo

ሐምሌ ፳፩ ቀን 💠ድንግል እመቤታችን እና ቅዱስ ዑራኤል💠 በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት በዚህች ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዑራኤል:- 1⃣ ድንግል ማርያም በአካለ
ሐምሌ ፳፩ ቀን 💠ድንግል እመቤታችን እና ቅዱስ ዑራኤል💠 በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት በዚህች ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዑራኤል:- 1⃣ ድንግል ማርያም በአካለ ሥጋ እያለች ወደ ሰማይ አሳርጓታል ፤ በሠረገላ ብርሃን ጭኖ በክንፎቹም ተሸክሞ አስቀድሞ ገነትን ቀጥሎም ሲዖልን አስጐብኝቷታል። በዚህም ምክንያት እመ ብርሃን ስለ ኃጥአን የምታለቅስ የምትለምንና የምትማልድ ሆናለች ለምናም አልቀረች የምሕረት ቃል ኪዳን ተቀብላለች። 2⃣ ቅዱሱ መልአክ እመ ብርሃንን በስደቷ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መርቶ አምጥቷታል ፤ በክንፉ ተሸክሞ በአራቱም አቅጣጫ አዙሮ አሳይቶ አሥራት እንድትቀበል አድርጓል። 3⃣ ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ ደሙን በጽዋዕ አድርጐ በኢትዮጵያ ወንዞች ላይ አፍስሷል። 4⃣ ለብዙ ቅዱሳን (አባ ጊዮርጊስን ጨምሮ) ጽዋዐ ልቡናን አጠጥቷል። "ዑራኤል የተባለ መልዐክ ሊረዳኝ መጣ"            መ/ዕዝ.ሱቱ ፪፥፩ ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮    @yamazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯

ጾመ ፍልሠታ እየደረሰች ነው ፡ የዘንድሮን እንዴት ለማሳለፍ አስበዋል?
ጾመ ፍልሠታ እየደረሰች ነው ፡ የዘንድሮን እንዴት ለማሳለፍ አስበዋል?

​​እንኳን ለቅዱስ ዑራኤል አመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳቹ አደረሰን! መልዐኩ ቅዱስ ዑራኤልና አገልግሎቱ በጥቂቱ ✍ ዑራኤል የሚለው ስም "ዑር"እና ኤል ከሚለው ሁለት ቃላት የተመሰረተ ነው ። ትርጉሙም ብርሃነ ጌታ አምላክ ብርሃን ነው። ማለት ነው። ✍ ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ መብረቅና ነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው።በመሆኑም መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበቁ ነጓድጓድ ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። (መጽሐፈ ሄኖክ ፮፥፪) ✍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከእየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ እየመራ፤ ከእስራኤል ወደ ግብጽ ከዚያም ከእመቤታችን ጋር በሀገራችን ኢትዮጵያ እየመራ ያመጣት መልአክ ነው። ✍ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለበት ጊዜ፥ክቡር ደሙ በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃን ነሳንስ የረጨው እሱ ነው። ✍ ለነብዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ልቦና ያጠጣው፥ጥበብን ማስተዋልን የሰጠው የጠፉ መጽሓፍት በቃሉ አስታውሶ እንደገና ያጻፈው የረዳው መልአክ ነው።(ዕዝ፲፫፥፴፱) ✍ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ትዕዛዝ ብዙ ድርሰት የደረሱት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ጽዋ ህይወት ስላጠጣቸው ነው። ✍ በዓላቱም በዓመት 3ናቸው። ፩...ጥር። 22 በዓለ ሲመቱ፤ ፪....መጋቢት 27 የጌታችንን ደም በዓለም የረጨበት፤ ፫...ሐምሌ 21 እና 22 ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ። ✍ በጸሎቱ የተማጸነ ከእግዚአብሔር አምላክ በረከትን ፣ምህረትን የሚያሰጥ አዛኝ ጠባቂ ና የዋህ መልአክ ነው።በተለይም ህጻናትን የሚጠብቅ የሚለምኑትን ሁሉ የሚሰማ ፥ኃጢአተኞች ካሉበት ቦታ እኔን ላከኝ እያለ አምላኩን የሚማጸን አዛኝ የዋህ መልአክ ነው። ✍ ይህ አለም በአማላጅነቱ አምኖ በእምነት ጸበሉን ቢጠጣ ፥ዝክሩንም ቢዘክር ከክፉ በሽታው እንደሚድን፤ እንደሚፈውሰው ቃል ኪዳን ተሰጥቶታል ። ✍ ቅዱሳን መላዕክት እግዚአብሔርን በሚፈሩ ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራሉ ከመከራም ያድኑዋቸዋል።(መዝ ፴፫÷፯) የአባታችን የጠባቂያችን የአማላጃችን የመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል ቃል ኪዳን አይለየን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur

+1
​​​​ ✞ ባሕራንኒ ይቤ ✞
ባሕራንኒ ይቤ (፮) ባሕራንኒ ይቤ ኦ ዘነገደ ባህር (፪)    ርዒክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቱ ዘይብል(፪) ባህራንኒ ይቤ (፮)
የሞቱን ደብዳቤ - - -  ባሕራንኒ    ሚካኤል አጥፍቶ - - -   ባሕራንኒ    ባሕራንን አዳነው - - -   ባሕራንኒ    በሠርግ ተክቶ - - - ባሕራንኒ  ሠዳዴ ሳጥናኤል - - -  ባሕራንኒ    ሊቀ መላእክት - - -    ባሕራንኒ    እኛንም አድነን - - -   ባሕራንኒ        ከሲኦል እሳት - - - ባሕራንኒ    
አዝ= = = = = ከሊቀ ነብያት - - - ባሕራንኒ     ከነሙሴ ጋራ - - - ባሕራንኒ ሕዘበ እሥራኤልን - - - ባሕራንኒ ሚካኤል ሲመራ - - - ባሕራንኒ   ቀን ደመና ጥሎ - - -  ባሕራንኒ   ሌሊት እያበራ - - -  ባሕራንኒ     ተሻገሩ ኤርትራን - - - ባሕራንኒ   ሁሉም በየተራ - - -  ባሕራንኒ
             መዝሙር            ጸሐፌ ትዕዛዝ        ዲያቆን ታዴዎስ ግርማ