3 462
订阅者
-624 小时
-257 天
-8130 天
帖子存档
3 462
Repost from ፋአድ 𝐅𝐔𝐀𝐃 𝙰𝚋𝚞 𝚕𝚀𝚖𝚊𝚗𝚎
“በመጨረሻይቱም (አለም) እነርሱ የሚያረጋግጡ ከሆኑት (መሪ ነው)። (አል' በቀራህ፡ 4)
በዚህ የቁርኣን አንቀጽ የተፈለገው ሲቀጠሩት የነበረው ነገር እንደመጣቸው እርሱም የቂን (ሞት) እንደሆነ ይገልጻል፡፡))
ይህ አንቀጽ ፣ ዓቅለኛ ሆኖ ለአካለ መጠን ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ _ እስኪሞት ድረስ ዒባዳ ዋጅብ እንደሆነ ፣ ሱፍያዎች እንደሚሉት ከሞት በፊት ግዴታ የሚቆምበት “ሀል” የሚባል እንደሌለ ይጠቁማል፡፡
ይህ ፣ ድሮም ይሁን አሁን የሱፍያ ዲን ነው፡፡ ዒባዳን አስመልክቶ የሱፍያ አቋም ይህ ነው፡፡ ከሱፍያዎች ኪታብ የነቀልነው ጥቂቱን ብቻ ነው… እኔ በጥናቴ ላይ ትኩረት ያደረኩት የዒባዳውን እና በዒባዳ ላይ ያላቸውን አቋም ብቻ ነው፡፡ ሌሎችም ልክበተውሂድ ፣ በሩሡሎች መልእክተኛነት ፣ በሸሪዓው እና በቀደር ዙሪያ አቋም እንዳላቸው ሁሉ ባልተጠቀሱ የቀሩ ጉዳዮችም የተለዩ አቋሞች ያሏቸው ሲሆን ይህን
ለማብራራት ተከታታይና በጣም ሰፋ ያሉ ማብራሪያዎች ይሻል በዚህ እርስ ግን ለቅምሻ ያክል የስኳሁኑ ይበቃናል
ሀቅን በሀቅነቱ እንዲያሳየን እና መከተልንም እንዲለግሰን ፤ ባጢልንም በባጢልነት እንዲያሳየን እና መራቅን እንዲቸረን ፤ ከመራን በኋላ ልቦቻችንንም እንዳያጠምብን
አላህን እለምነዋለሁ፡፡
#ክፍል1 https://t.me/AbulQmane/2148
ክፍል2 https://t.me/AbulQmane/2149
ክፍል3 https://t.me/AbulQmane/2150
ክፍል4 https://t.me/AbulQmane/2172
ክፍል5 https://t.me/AbulQmane/2176
ክፍል6 https://t.me/AbulQmane/2219
3 462
Repost from ፋአድ 𝐅𝐔𝐀𝐃 𝙰𝚋𝚞 𝚕𝚀𝚖𝚊𝚗𝚎
🔺ሱፊያዎች በዲንና በዒባዳ መሰረቶቸ ላይ ያአላቸው ስህቱ አቋም #ክፍል6
~~~
وموقف الصوفية من أصول العبادة والدين
ስድስተኛ፡- ባጢል (ስህተት) ከሆነው የሱፍያ ዲን መካከል ፡ አንድ ሰው ከሸሪዓዊ ሀላፊነት የሚወጣበት ደረጃ አለ ማለታቸው ነው
ይህ የተሶውፍ አመለካከት ድንበር አልፎ የጥመትን ጫፍ የመድረሱ ውጤት ነው፡፡ የተሶውፍ መሰረቱ ኢብን አልጀውዝይ እንደተናገረው ነበር፡-ወራዳ የሆነን ስነምግባር ታግሎ መመለስ፣ ነፍስን አሰልጥኖ ወደጥሩ ስነምግባርመውሰድ፡፡ ዙህድ ፣ ችሎታ ፣ ትዕግስት ፣ ኢኽላስ እና እውነተኛነት፡፡))
በተጨማሪ የሚከተለውን ተናግሯል፡- ((የመጀመሪያዎቹ (ሱፍዮች) ባህሪ ይህ ነበር ፤ አንዳንድ ነገሮችን ኢብሊስ እነርሱን ከዚያም ተከታዮቻቸውን ቀላቀለባቸው፡፡ አንድ ክፍለ ዘመን ባለፈ ቁጥር በሁለተኛው ክፍለ ዘመን (ሰይጣን) ወደኋላ ላሉት የበለጠ የተመቻቸ እስኪሆንለት ድረስ በሰዎች ላይ ዲናቸውን ይቀላቅልባቸዋል፡፡ ዋናው የመቀላቀል መሰረቱ ከእውቀት ማገዱ ፣ ተፈላጊው አላማ እውቀት ሳይሆን ተግባር ነው ብሎ ማሳየቱ ነው፡፡ የሰይጣን ዋና አላማ የእውቀትን መብራት በእነርሱ ላይ ካጠፋ በኋላ በጨለማ እንዲደናበሩ ማድረግ ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ዱንያን በአጠቃላይመተው አስፈላጊ እንደሆነ ያሳያቸዋል፡፡ አካላቸውን የሚያስተካክሉበትን ዱንያ እንዲተው ያደርጋቸዋል፡፡ ገንዘብን ከጊንጥ ጋር ያመሳስሉታል … ነፍስን ከአቅም በላይእንድትሸከም ያደርጓታል፡፡ ጭራሽ ከአልጋ ላይ መጋደምን አያስፈልግም እስከማለት ይደርሳሉ … ከእነርሱ መካከል እውቀት ካለመኖሩ የተነሳ ሳያውቅ በረሡል ላይበተዋሹ ሐዲሶች ለመተግበር ይሞክራል፡፡ ከዚያም ሰዎች መራብ ፣ መደህየት እንዳለባቸው በወስዋስ (በብዥታ) ላይ የሚቀሰቅሱ መጽሐፎችን የጻፉ ሰዎች መጡ፡፡ ልክ እንደ ሀሪስ አልሙሀሲቢ ማለት ነው፡፡
ሌላው ደግሞ መጣ የሱፍያን መዝሀብ ማጣራት ጀመረ ፣ እነርሱ የሚለዩበትን ባህሪዎች ነጥሎ አስቀመጠ፡፡ የሱፍያ ባህሪ በማጨብጨብ ፣ በመወዛወዝ ፣ በዜማ የተለየ እንደሆነ ግልጽ አደረገ፡፡ አሁንም ነገሩ በዚህ አላቆመም እየጨመረ ሄደ፡፡ መሻይኾቻቸው …. ከዑለማ ራቁ እነርሱ ያሉበትን “ኢልመል ባጢን”(ስውር እውቀት)በማለት ሰየሙ ፣ የሸሪዓውን እውቀት ደግሞ “ኢልመ ዟሂር” (ግልጽ እውቀት) በማለት ሰየሙ፡፡ ከእነርሱ መካከል ከረሐብ የተነሳ ብዥታ ውስጥ የወደቀውን ፣ በቃ ይህ ግለሰብ የአላህ ከፍተኛ ወዳጅ እንደሆነ አድርገው ቆጠሩ…እነዚህ ሰዎች በክህደትና በቢድዓ መካከል ሆኑ፡፡ ከዚያም ጦሪቃዎች በርካታ ሆኑ (1) ፣ ዓቂዳቸውም በዚህ ምክንያት ተበላሸ፡፡ ከእነርሱ መካከል የ “ሁሉል” ዓቂዳ ያለው አለ፡፡ ከእነርሱ መካከል የኢቲሃድ ዓቂዳ ያለው አለ፡፡ ኢብሊስ በቢድዓ የእውቀት አይነቶች እንዲዋዥቁ ከማድረግ አልተወገደም …)) (
📕ተልቢስ አል'ኢብሊስ 157-158)
ሸይኹል ኢስላም ብን ተይሚያ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ጥያቄ ተጠየቁ፡-
((አንዳንድ ሰዎች አሉ ነፍስን በማለማመድ የዘወተሩ ፣ ከዚያም እራሳቸውን ጀውሐር (በራሳቸው የተብቃቁ) ነን ብለው ያሰቡ ፤ “… ፣ ትዕዛዝ ክልከላ የተራው ማህበረሰብ መንገድ ነው ፣ እነርሱም ጀውሐር ደረጃ ቢደርሱ ሁሉም ነገር ከእነርሱ ላይይነሳላቸው ነበር፡፡ ነብይነት ተራውን ማህበረሰብ በህግ ለመዳኘት እና ስርዓት የማስያዝ ጥበብ ነው፡፡ እኛ ደግሞ ከተራው ማህበረሰብ አይደለንም፡፡ በተክሊፍ (በህግ) ጓዳ የምንገባ አይደለንም፡፡ እኛ ጀውሀር ሆነናል ጥበብን አውቀናል ይላሉ፡፡”
መልስ፡- ይህ ንግግር ከአይሁድና ነሷራ ንግግር የከፋ ትልቅና ከባድ ክህደት እንደሆነ ከኢማን እና ዒልም ባለቤቶች ዘንድ ጥርጥር የለውም፡፡ አይሁድና ነሷራ በተወሰኑ ኪታቦች አመኑ በከፊሉ ካዱ፡፡ እነዚህ ከሐዲ ከመሆናቸው ጋር ለአላህ ትዕዛዝን ፣ ክልከላን ፣ ዛቻ ፣ ቀጠሮ እንዳለ ያምናሉ ይህም የተሰረዘረውን የተቀየረውን አይሁድነትን እና ነሷራነትን አጥብቀው እስከያዙ ድረስ ነው፡፡ከእነርሱ አማኞች ውስጥ ሙናፊቆቻቸው ማለትም ፈላስፎቻቸው ከዚህ ኡመት ሙናፊቆች በጣም የከፉ ናቸው፡፡ ምክንያቱም ክህደትን ይፋ አድርገው ፣ ኒፋቅን ድብቅ አደረጉ፡፡ ኢማንን ይፋ አድርጎ ንፍቅናን ከደበቀው የከፋ ሆነ፡፡
የተፈለገው አላማ ፣ በተሰረዘው ጥቅል ህግ አጥብቀው ከያዙት ነሷራ እና አይሁድ በአጠቃላይ ትዕዛዝ ክልከላ ከእኔ ላይ ወድቆልኛል ከሚለው ሱፍያ የተሻለ ነው ። እነዚህ ከማንኛውም መጽሓፍ ፣ ሸሪዓዎች እና ሚለሎች ሁሉ አፈንግጠዋል፡፡ ምክንያቱም ለአላህ መታዘዝና መከልከል የሚባል ነገር ከእነርሱ ዘንድ የለም፡፡ እንደውም ከዚህ በፊት ከኢብራሂም ቅሪት መጽሓፍትን አጥብቀው ከያዙት የአረብ ሙሽሪኮችም ይከፋሉ፡፡ እነዚህ ሙሽሪክ ከመሆናቸው ጋር እነርሱ የያዙት የተወሰነ ሐቅ አለ፡፡ እነዚህ ግን ፣ ከሐቅ የወጡ ናቸው ፤ ከሐቅ አንድም የያዙት የለም፡፡ እነርሱ ፣ ትዕዛዝንም ክልክልንም ሙሉ በሙሉ ዝግ አድርገዋል፡፡))
በመቀጠል እንዲህ ይላል፡- ((ከእነርሱ መካከል በሚከተለው ቁርኣን ማስረጃ የሚያደርግ አለ፡-
وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡
Surah: Al-Hijr, Ayat: 99
የዚህ ትርጉሙ፡ “ጌታህን ተገዛ እውቀት እና ግንዛቤ እስክትደርስ” ማለት ነው ይላሉ፡፡ ከዚህ ደረጃ ከደረስክ ዒባዳ ከአንተ ላይ ይነሳልሃል፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ፡ “የሆነ ባህሪ ላይ እስክትደርስ ድረስ ስራ” ይላሉ፡፡ የሱፍያ ባህሪ ላይ ከደረስክ ዒባዳ ከአንተ ላይ ይነሳልሃል፡፡ እውቀትና ግንዛቤ ላይ ከደረሱ ፈርድ ይተዋሉ ፤ ሀራም ይሰራሉ፡፡ ይህ ከዚህ በፊት እንዳስቀደምነው ግልጽ የሆነ ክህደት ነው፡፡በእነርሱ ላይ እንጅ ለእነርሱ ማስረጃ ሆኖ የሚያገለግል አይደለም፡፡
ሀሰን አልበስርይ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
" إن الله لم يجعل لعمل المؤمنين أجلا دون الموت"
“ለሙእሚን ከሞት በፊት (ስራን የሚያቆምበት) የጊዜ (ገደብ) አላህ አላደረገም” ከዚያም የሚከተለውን ቁርኣን አነበበ፡-
وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡
“የቂን” ማለት ሞት እና ከሞት በኋላ መሆኑን ዑለሞች በአጠቃላይ ተስማምተዋል፡፡ ለዚህ ተመሳሳይ የሚከተለው ቁርኣን ማስረጃ ይሆናል፡፡
مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
وَلَمْ نَكُ نُطْعِمُ الْمِسْكِينَ
"ምስኪኖችንም አንመግብም ነበር።"
وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ الْخَائِضِينَ
"ከከንቱ ንግግርና ከሐሰት ጋር ከሚገቡ ሰዎች ጋር እንገባ ነበር።"
وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوْمِ الدِّينِ
"የፍርድ ቀንንም እናስተባብል ነበር።"
حَتَّىٰ أَتَانَا الْيَقِينُ
"እርግጠኛው ነገር (ሞት) እስከ መጣብን ድረስ።"
ሱረቱ አል ሙደሲር42-47
ይህን ቃል ሶላትንና ዘካን እንደተው ፣ በትንሳኤ ቀን መዋሸታቸውን ፣ ሞት እስኪመጣቸው ድረስ ከሚዘባርቁት ጋር መዘባረቃቸውን የተናገሩት በጀሀነም ውስጥ ሆነው ነው፡፡ እነርሱ በዚህ ባህሪ ላይ ሆነው በዱንያ ላይ አማኝ ያልነበሩ መሆናቸው የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ አላህ በሚከተለው ቃል ከተናገረላቸው ሰዎችም አይደለም፡፡
وَبِالْآخِرَةِ هُمْ يُوقِنُونَ
3 462
ሰኔና ሰኞ አንድ ቀን ከዋለ ገዥው ይወርዳል እኛ ወደ ስልጣን እንመጣለን የሚለው የህልም እንጀራ የሆነ የደብተራዎች ጥንቆላ ነው ።
ሰኔ ሰኞም ገባ ማክሰኞ ሮብም ገባ እሁድ ከምንም ነገርጋ ግንኙነት የለውም ።
3 462
መለወጥ በማትችለው ነገር ላይ ለምን ትናገራለህ?
አንዳድ ነገራቶች አንተ በመናገርህ ከመስተካከሉ ይልቅ ሰዎች ቂም እና ቁርሾ እንድይዙ ሊያደርግ ይችል ይሆናል። ይህ ደግሞ “ ለእውነት” የሚከፈል ዋጋ እንጂ ሌላ አይደለም። “ ሰሚ የለምና የያዝከው እውነትም ቢሆን አታውራ ” የሚለው መርህ ከብዙ ሸሪዓዊ አስተምህሮዎች ጋር የሚቃረን ሆኖ ይስተዋለል።
وَمَا عَلَيْنَا إِلَّا الْبَلَاغُ الْمُبِينُ
(Yasin 17)
እንዲል ቁርዓኑ ከዳኢ ሚጠበቀው ዋናው ነገር እውነትን ማድረስ ሲሆን ውሳኔው ደግሞ ለአድማጩ መተው ነው። የ አንድ ዳዒ ውጤታማነትም ቢሆን ሚታየው ዳእዋው ላይ በመፅናቱ እንጂ ሰዎችን በማሳመኑ አይደለም።
عرضت علي الأمم فرأيت........ والنبي ومعه الرجل والرجلان، والنبي وليس معه أحد........
ነብዩ (ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሰላም) በዚህ ሀዲስ ላይ በቀጣዩ ዓለም ነብይ ሆኖ ሁለት ተከታይ ብቻ ያለው ነብይ ሆኖ አንድም ተከታይ ቢሆን የሌለው እንደሚኖር አስቀምጠዋል።
ነቢይ ሆኖ ተካታዮች በዚህ ደረጃ ካነሱ ወይም ጭራሹን ከሌሉ እነዚህን ነብያት Successful አይደሉም ማለት ይቻላል? በጭራሽ ምክንያቱም የስኬት መመዘኛ እና መስፈርያው ተከታይና አጨብጫቢ በማፍራት ሳይሆን በዳእዋው ላይ ፀንቶ በመታገል ብቻ የሚለካ ነው።
ስለዚህ እውነት በመናገር ዙርያ “ምንም ላታመጣ አታውራ" አይባልም። ነቢያቶች እውነትን ያወሩ የነበሩት ጣቶቻቸውን ጆሮዋቻቸው ወስጥ ይከቱ በነበሩ ማሕበረሰብ ላይ መሆኑን ልብ ሊባል ይገባል።
የሀገራችን ቢሕልም ቢሆን “እውነትን ተናግረህ የመሸበት ማደር" አይደል የሚለው? ብዙኃኑ ሰዎች እንዳይደብራቸው ወይም ቂም እንዳይቋጥሩ ተብሎ የሚድበሰበስ እውነት የለም።
አፋችን መናገር ፣ ጣታችን መፃፍ እስከቻለ እና ጉዳዩ ከኢስላም ጋር እስከተያያዘ መዕሩፋን መዕሩፍ ሙንከሩን ሙንከር ልንለው የተገባ ነው።!
3 462
Repost from ሐላል ድጅታል ኔትወርክ (Halal Digital Network -HDN) 🇪🇹
+1
ይህ ከላይ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ወንድማችን ከድር ቃሲም የ30አመት ወጣት እና ትንሽ የአእምሮ ህምተኛ ሲሆን ። ሸገር ሲቲ አንፎ / 105 አካባቢ የሚኖር ሲሆን በቀን 15/8/2018 ከቀኑ 10:00 አካባቢ ከወጣ እስካሁን አልተመለሰም። እናም እናት አባት በጣም በጭቀት ላይ ናቸው እና ያያቹት ወይንም የገኛቹት ከታች በምናስቀምጠው ስልክ ደውላቹ እንድታሳውቁን በአላህ ስም እነለምናቹዋለን። ሰ.ቁጥር 0902673985/0913590793/ 0918179110 ሙሳ ቃሲም
3 462
•••
መስጂዶች ቀዝቀዝ አሉ
የሰላት ሰፎች ብዛት ቀነሱ،
ቁርአኖች ወደ መደርደርያቸው ተመለሱ !
ሆኖም ግን አሁንም ሀያቷን ሁሉ ረመዳን ያደረቀች ንፁህ የሆነች ጀመዐ በነበረችበት ቀርታለች ا...
እቺ ጀመዐ
ቁርአናቸው አቧራ ማይነካባቸውና የማያኮርፉ...
ወደ መስጂዲ የሚያደርጉት እርምጃም ሁሌም የማያታክታቸው ናቸው ...
ለነዚህ ሰዎች ረመዳን በጥንካሬያቸው ላይ ጥንካሬን ነው የጨመረላቸው
አላህ ከእዚህ ጎራ ያደርገን ...
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
