ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 369 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 633,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 187

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 369 名订阅者。

根据 19 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -46,过去 24 小时变化为 37,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.37%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.87% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 438 次浏览,首日通常累积 1 210 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 22

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 20 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 369
订阅者
+3724 小时
+367
-4630
帖子存档
#ጾመ_ሐዋርያት  ‹‹ይኽ ጾም በአላዋቂዎችን እና በቤተክርስቲያን ጠላቶች የሽማሌዎች ጾም እየተባለ ምዕመናን እንዳይጾሙት ብዙ ተለፍቷል..›› በየዓመቱ በዕለተ ሰኑይ የሚዠምሩ ሶስት አጽዋማት ብቻ አሉ ፡፡ ከእነርሱ መሀከል አንዱ ጾመ ሐዋርያት ነው ፡፡ ቅበላው በዕለተ እሑድ ይሆንና ጾሙ ሰኞ ይውላል ፡፡ የ2016 ዓ.ም ጾመ ሐዋርያት ሰኔ 17 ይገባል ፡፡ ይህ ጾም እራሱ ጌታቸን ኢየሱስ ክርቶስ ትንቢት የተናገረለት ጾም ነው፡፡ ይኽ ታላቅ ጾም የዛሬ 1902 ዓመት በፊት በራሳቸው  በቅዱሳን ሐዋርያት የተጀመረ ጾም ነው ፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መሀከልም አንዱ ነው ፡፡ ፈሪሳውያ ጌታችንን ደቀ መዛሙርትህ አይጾሙም ብለው በጠየቁት ጊዜ እርሱም ‹‹ ሚዜዎች ሙሽራ ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን ? ነገር ግን መሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል ፤ በዚያ ጊዜም ይጾማሉ ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ   የሚያኖር የለም ፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና ፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል ፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም ፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል የወይን ጠጁም ይፈሳል ፡፡አቁማዳው ይጠፋል ፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ ፡፡›› ማቴ 9 ፥ 14-17  አላቸው ፡፡ይኽ ቃለ እራሱ  ጌታችን መድኀኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ስለ ጾመ ሐዋርያት የተናገረው ትንቢት ነው ፡፡ ‹‹#መሽራው_ከተወሰደ በኃላ››  ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኃላ ማለት ሲኾን ይኽን ጾም ከዕረገት በኋላ የምንዠምረው ፤ ይኽን ምሳሌ በማድረግ ነው ፡፡ ዐሥር ቀን ዘግይቶ መዠመሩም የሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበትና  ነው ፡፡ የዚኽን ማብራርያ በቀጣይ ጽሑፋችን እንመለስበታልን፡፡ ይኽ ጾም በአላዋቂዎችን እና በቤተክርስቲያን ጠላቶች የሽማሌዎች ጾም እየተባለ ምዕመናን እንዳይጾሙት ብዙ ተለፍቷል ልናውቅ የሚገባው ነገር ግን ሐዋርያት ዓለምን ዞረው ከማስተማራቸው በፊት ይህን ጾም  ጾመዋል ፡፡ በዚህም ጌታችን የተናረው ተንቢት ተፈጽሟል፡፡  ከሰባቱ አጽዋማትን አንዱ ነው ፡፡ በዚህ  ምክንያት ይህን ጾም ታላቅ እና ልዩ ያስብለዋል ፡፡ ይኽንን አውቀን ሁላችንም በሕግ በሥርዓት ልንጾመው ይገባል ፡፡   #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram...  https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot  .YouTube    https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w                    www.finotehiwotsundayschool.com ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት .

10. ድሬዳዋ ቅዱስ ሚካኤል ጭሮ አሰበ ተፈሪ ቅዱስ ሚካኤል (ድሬዳዋ፥ አሰበ ተፈሪ) ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል አርባ ምንጭ ላከ ኢየሱስና ሚካኤል ዲላ ቅዱስ ሚካኤል 15. አሰላ ደብረ ሰላም ቅድስ ሚካኤል ጂጂጋ ቅዱስ ሚካኤል ሚዛን ቴፒ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል ቦንጋ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ኢሉባቦር ሌንቃ ቅዱስ ሚካኤል 20. እነሞርና ኤነር ወረዳ ቅዱስ ሚካኤል (ጉራጌ ሀ/ስብከት) አሰቦት ደብረ ወገግ ቅዱስ ሚካኤል (ምሥ. ሀረርጌ ሀ/ስብከት) ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ኩክ የለሽ ዛሪያ ቅዱስ ሚካኤል ጅሩ ሞቶሎኒ ቅዱስ ሚካኤል (ጅሩ አርሴማ ውስጥ) 25. መንዝ ይገም ቅዱስ ሚካኤል መሐል ሜዳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል የሲጠር ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል (መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ) ወንጪት ቅዱስ ሚካኤል (በነብር የሚጠበቅ) ሸዋሮቢት ጫሬ ቅዱስ ሚካኤል 30. ወልዲያ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ኮምቦልቻ ቅዱስ ሚካኤል ደሴ ጢጣ ደብረ ሲና ቅዱስ ሚካኤል ራያ ቆቦ ቅዱስ ሚካኤል ደብረ ማርቆስ ዋሻው ቅዱስ ሚካኤል 35. ደብረ ማርቆስ አጠገብ ብዕርና ቅዱስ ሚካኤል ደምበጫ ቅዱስ ሚካኤል መርዓዊ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል ባሕር ዳር ድባንቄ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል አዘዞ አይራ ቅዱስ ሚካኤል 40. ዛራ ቅዱስ ሚካኤል (ባሕር ዳር አጠገብ ሐሙሲት) ጉመር ደብረ ኅሩያን ቅዱስ ሚካኤል ካምባ ቅዱስ ሚካኤል ሳንቃ ወይራ ቅዱስ ሚካኤል ዳስ ዓምባ ቅዱስ ሚካኤል 45. ላሐ ቅዱስ ሚካኤል 46. ጊራራ ቅዱስ ሚካኤል 47. መለኮዛ ቅዱስ ሚካኤል 48. ዋይሎ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #ከኢትዮጵያ_ውጭ_የሚከብርባቸው_ #፪ #ጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ላስ ቬጋስ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ወቅዱስ ዑራኤል ወቅድስት ማርያም ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት፥ አሜሪካ፥ ላስቬጋስ (USA, 2575 Westwind Rd. Las Vegas, NV 89146)፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → አሜሪካ ላስ ቬጋስ፡፡ ፪. ላስ ቬጋስ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል እና አቡነ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ፤ (USA, 2575 Westwind Rd. Las Vegas, NV 89146) (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ገዳማት ካሉ አሳውቁን) አድራሻ፤ ዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት፥ አሜሪካ፥ ላስቬጋስ (USA, 5985 S Lindell Rd, Las Vegas, NV 89118)፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → አሜሪካ ላስ ቬጋስ፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ገዳማት ካሉ አሳውቁን) / #ክብረ_በዓላት #Feasts / / #ገዳማትና_አድባራት #Monasteries_and_Churches /

አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ልኳንዳ፥ ፈጥኖ ደራሽ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → ኮልፌ አጣና ተራ → ልኳንዳ → (በስተግራ ባለው አስፓልት በእግር 5 ደቂቃ ፈጥኖ ደራሽ ማሰልጠኛ)፡፡ ፴፬. ቃሌ ተራራ ደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተ ማርያም ወቅድስት ልደታ ወቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻው፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ፥ ካኦ ጄጄ ዱቄት ፋብሪካ፥ ቃሌ ተራራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → አስኮ፤ ፴፭. ማኅደረ መለኮት ወይብላ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ የሺ ደበሌ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → የሺ ደበሌ፡፡ ፴፮. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ፡፡ ፴፯. ኮተቤ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና አቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ፥ ካራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ኮተቤ (ካራ) ፴፰. ረጲ መካነ ጎልጎታ መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ካራ ቆሬ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → አለም ባንክ → ካራቆሬ (ረጲ)፡፡ ፴፱. ፉሪ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጋራ ኦዳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጋራ ኦዳ፡፡ ፵. ሐመረ ወርቅ ማርያምና አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ወርቁ ሰፈር፡፡ ፵፩. ቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → ሰፈረ ገነት፡፡ ፵፪. ቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አባ ሳሙኤል ዘዋልድባና ቅዱስ አማኑኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቡልቡላ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ሳሪስ አቦ → ቡልቡላ መድኀኔ ዓለም (ኮንዶሚኒየም)→ ወደ ላይ በአስፓልቱ የ5 ደቂቃ የእግር መንግድ፡፡ ወይም፤ ከቦሌ መድኃኔ ዓለም → ቡልቡላ (በአዲሱ መንገድ) ፵፫. ደብረ ዐባይ ቅድስት አርሴማ ወቅዱስ ሚካኤል ወመርቆሬዎስ ወአቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አለም ባንክ፥ ግራር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ጦር ኄሎች → አለም ባንክ → ግራር፡፡ ፵፬. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ፥ ጋራው መድኃኔዓለም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → አቃቂ፡፡ ፵፭. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሣሎ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ሣሎ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ጥንታውያን #፲፱ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #እየላ_ቅዱስ_ሚካኤል፤ (#የ3 #ሺህ_ዓመታት_ባለታሪክ፤ ከታቦተ ጽዮን ጋራ በ980 ከክ.ል.በ. ታቦቱ የመጣ፤ መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ፤ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መጥቶ የባረከው) ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → ግዳን (እየላ)፡፡ ፪. ሰሜን ትግራይ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል፤ (መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ) አድራሻው፤ ሰሜን ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ሰሜን ትግራይ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፫. ጎሐ ጽዮን ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተሠራ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፬. ሸኖ ጎልባ ደብረ ሣሕል ቅዱስ ሚካኤል ደብር፤ (በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ሰኖ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ሸኖ፡፡ ፭. መላሃይዘንጊ ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ8ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፮. ላስታ ላሊበላ ቤተ ሚካኤል፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን በቅዱስ ላሊበላ የታነፀ፥ ከ11ዱ የላስታ ላሊበላ ፍልፍል ሕንጻዎች አንዱ) አድራሻው፤ ላስታ ሀገረ ስብከት፥ ላሊበላ ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ፡፡ ፯. ገርዓልታ ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል፤ አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ገርዓልታ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መቀለ → ገርዓልታ፡፡ ፰. ሚካኤል ዓምባ፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ውቅሮ፥ (በመቀለና በአዲግራት መሃል)፥ አጽቢ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ውቅሮ → አጽቢ፤ ፱. ባሕር ዳር ሽምብጥ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ13ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13 ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር ከተማ → ሆስፒታል በሚል ታክሲ (ዲፖ ጋር)፡፡ ፲. እስቴ አበርጉት ቅዱስ ሚካኤል ፤ (በአፄ ዓምደ ጽዮን ዘመነ መንግስት በልጃቸው በአቡነ ፊልሞና የተሠራ ታሪካዊ ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ እስቴ ወረዳ፥ ደስኳ አጋማች ቀበሌ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → እስቴ፡፡ ፲፩. በሮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል፤ በ16ኛው መ/ክ/ዘመን መጨረሻ የተመሠረተ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ሳይንት ወረዳ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → አማራ ሳይንት፡፡ ወይም፤ ከጎጃም በመርጠሉ ማርያም → አማራ ሳይንት ፲፪. ጎንደር ፊት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ በአፄ ፋሲለደስ ዘመነ መንግሥት ተመሠረተ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፫. ጎንደር አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፬. ተንታ ደብረ ብርሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ (ንጉሥ ሚካኤል በሚያስደንቅ ሁኔታ ያሠሩት) አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ አምባሰል፥ ተንታ ወረዳ፥ ጠዓት ቀበሌ፥ እሜገኝ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ፡፡ ፲፭. አጃና ቅዱስ ሚካኤል፤ (በቀስተ ደመና ጠበል አጥማቂው) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለት፥ አጃና፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ → አጃና፡፡ ፲፮. ቦንብ አርግፍ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ወሎ ሀ/ስብከት፤ የጁ ወልዲያ) ፲፯. ቦረዳ ቅዱስ ሚካኤል ፲፰. ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ ኢቲሳ) ፲፱. አንኮበር ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀ/ስብከት) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፵፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ 1.. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ ሚካኤል ጎሚስታው ሚካኤል (ትግራይ) እንዳ ቅዱስ ሚካኤል (ትግራይ) መቀለ ቅዱስ ሚካኤል 5. ጾረና ቅዱስ ሚካኤል (ኤርትራ) ዓለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ደብረ ዘይት /ቢሾፍቱ/ ደብረ አሚን ቅዱስ ሚካኤል ዱከም ቅዱስ ሚካኤል ናዝሬት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል

የሰኔ 12 የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል (በአ.አ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ ባሉ) ከሚከበርባቸው በርካታ ገዳማትና አድባራት 114ቱን እንጠቁምዎ፡፡ ሰኔ ፲፪ የቅዱስ ሚካኤል እና የቅዱስ ላሊበላን በዓል በየት ሊያከብሩ ዐስበዋል? #ቅዱስ_ሚካኤል_አፎምያንና_ባሕራንን_ያዳነበት_እለእስክንድሮስ_ቅዳሴ_ቤቱን_ያከበረበትና_የቅዱስ_ላሊበላ_ዕረፍቱ_ነው፡፡ #ኅዳር_፲፪ #በዓለ_ሢመቱ_ወመጋቤ_መርሖቱ_ለእስራኤል_፡፡ #በመላው_ዓለም_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፻፲፫ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ገዳማት ካሉ አሳውቁን) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_ #፵፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡፡ ፩. የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (በኦሪት ዘመን መሥዋዕተ ኦሪት ይሰዋበት የነበረ፥ ዋሻ ቤተ ክርስቲያኑ በ4ኛው ክ/ዘመን በአብሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) (የቅዱስ ላሊበላም በዓለ ዕረፍት በማኅሌት በወረብ ጨምር ሳይቀር የሚከበርበት ነው) አድራሻው፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሾላ መገናኛ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4 ኪሎ) → ሾላ መገናኛ፤ ፪. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (ራስ ካሳ ሚካኤል) (ጭቁኑ) /የቅዱስ ላሊበላ ታቦትም አብሮ ይከብራል/፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ራስ ካሳ ታክሲ፤ ከ4ኪሎ(ከ6 ኪሎ) → ፈረንሳይ፡፡ ፫. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (አዲሱ ሚካኤል) አድራሻ፤ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፥ መርካቶ አውቶቡስ ተራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4ኪሎ) → መርካቶ አውቶቡስ ተራ፡፡ ፬. አፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (ወህኒ ቤት) (ከርቸሌ) አድራሻ፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፥ ቡልጋርያ (ከርቸሌ) (አፍሪካ ኅብረት)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ቄራ፡፡ ፭. ኮተቤ (ሲኤምሲ) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ /ሳጠራው/ (ቀድሞ ኮተቤ አሁን ሲኤምሲ) አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ካራ አሎ ፥ አባዶ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሲኤምሲ፡፡ ፮. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ፡፡ ፯. ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ላፍቶ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ላፍቶ፡፡ ፰. ቤተል ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቤተል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃሎች → አየር ጤና፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → አለም ባንክ/ኤር ጤና/፡፡ ፱. ኤረር በር መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ጎሮ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ፒያሳ) → ጎሮ፡፡ ፲. መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ቀጨኔ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ)(ከአዲሱ ገበያ) → ቀጨኔ፡፡ ፲፩. አያት ጨፌ ኢያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ1980ዓ.ም ጽላቱ ከነ ድርሳናቱ ተቀብሮ የተገኘበት) አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9፥ ጎሮ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ጎሮ፡፡ ፲፪. ካራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል፥ 24ቱ ካህናተ ሰማይና ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → አባዶ ፲፫. ቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቦሌ ሚካኤል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቦሌ ሚካኤል፡፡ ፲፬. የካ አባዶ ገ/አ/ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → አባዶ ፲፭. ምሥራቀ ፀሐይ ዳንሴ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 10 ከጉራራ ከፍ ብሎ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ → ጉራራ፡፡ ፲፮. ወረገኑ ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሩዋንዳ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ቦሌ) → ወረገኑ፡፡ ፲፯. ቃሊቲ ሰፈረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡ ፲፰. ንቡ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሃራብሳ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉ ዲምቱ → ንቡ ሚካኤል፡፡ ፲፱. ጀሞ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #እንዲሁም_በአዲስ_አበባ_በአንድነት_ተሠሩ_በሚከተሉት_አብያተ_ክርስቲያናት_ይከበራል፤ ፳. ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ጎላ (ኢምግሬሽን ጀርባ)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል (ኢምግሬሽን)፡፡ ፳፩. ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ዮሴፍ፥ ደጃዝማች መርዕድ መንገድ፥ ቀለበት መንገድ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ከላጋር (ከፒያሣ) (ከ4 ኪሎ) (ከቦሌ)(ከመገናኛ) → ቃሊቲ መናኸሪያ /በቀለበት መንገድ/ ወይም፤ ከሳሪስ አቦ → ቦሌ /በቀለበት መንገድ/ ፳፪. ጀሞ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ ፳፫. ቃሊቲ ደብረ ቊስቋም ማርያምና ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡ ፳፬. ኮተቤ ማኅደረ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሎቄ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሎቄ፡፡ ፳፭. ፉሪ መካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ፥ ፉሪ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ለቡ፡፡ ፳፮. ቂሊንጦ መካነ ፍስሐ ቅዱስ ሚካኤልና በዓታ ለማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቂሊንጦ ዐደባባይ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቂሊንጦ፡፡ ፳፯. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ ኬላ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቱሉዲምቱ፡፡ #እንዲሁም_በድርብነት_በሚከተሉት_አብያተ_ክርስቲያናት_ይከበራል፤ ፳፰. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ወቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ 6 ኪሎ ዐደባባይ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ → 6 ኪሎ (ማርቆስ)፡፡ ፳፱. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቦሌ በሚል ታክሲ → መስቀል ዐደባባይ፡፡ ፴. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኃኒት መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ልደታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጦር ኃይሎች በሚለው ታክሲ → ልደታ፡፡ ፴፩. ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አረዳ ክፍለ ከተማ፥ ሰባራ ባቡር፥ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል አጠገብ (አርበኞች መንገድ)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → በዊንጌት አስኮ /ሩፋኤል ፊንሐስ/ ታክሲ → ዮሐንስ፡፡ ፴፪. ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ዊንጌት፥ ጠሮ፥ አራት መንታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → ዊንጌት → ጠሮ፡፡ ፴፫. ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም፤

ሰላም ለልደትኪ እማኀፀነ ድክምት ሥጋ ድኅረ ኀለፋ ውርዙት ወድኅረ ትክቶ ኃደጋ ማርያም ሥመሪ ወጸሐቂ እንበለ ንትጋ ፤ ለማየ ንጽሕኪ ትረስዩኒ ፈለጋ፤ እስመ ንጽሕ   ይሁብ ምገሰ ወጸጋ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤      የተዘጋጀ ::   #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram...  https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com  YouTube    https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram (https://t.me/finotehiwot1927) ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት .

ꔰ ꔰꔰእንኳን ለእመቤታችን 2031ኛ ዓመት በዓለ ልደት አደረሳችሁꔰ ꔰꔰ ꔰ  #ልደታ_ለማርያም  ꔰ ꔰ #ልደቷ_መጽሐፍ_ቅዱስ_ላይ_ከሌለ_ተቀባይነት_እንዴት_ይኖረዋል? ꔰ ሰላም ለልደትኪ እማኀፀነ ድክምት ሥጋ ድኅረ ኀለፋ ውርዙት ወድኅረ ትክቶ ኃደጋ ፠ #የግንቦት_ልደታ_ለማርያም_ክብረ_በዓልና_የእመቤታችን_በዓላት በቀደመዉ ዘመን በዘመነ ብሉይ ‹‹የቤተ መቅደስ መታደስ በዓል›› ይከበር እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል፡፡ ይህ በዓል እስከ ጌታችን ዘመንም ይከበር ነበር፡፡ /ዮሐ. 10፥22/ በሐዲስ ኪዳን እውነተኛ የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤተ መቅደስ ለሆነችዉ እመቤታችን በስሟ በዓል ሊደረግላት ይገባል፤ ‹‹የጻድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል›› እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝ. 111፥7በተአምረ ማርያም ላይ በዝርዝር እንደተቀመጠዉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 33ት በዓላት አሏት፡፡ ከእነዚህ በዓላት ሁሉ አስበልጣ የምትወደዉ በዓለ ልደቷን እንደሆነ በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ከዐረብኛ ወደ ግእዝ በተተረጎመዉ እመቤታችን በተለያዩ ሀገራት ያደረገቻችዉን ገቢረ ተአምራት በኢትዮጵያ ከተፈጸሙት ጋር አካቶ የያዘው ተአምረ ማርያም በዝርዝር ያስረዳል፡፡ ፠ #ልደቷ_መጽሐፍ_ቅዱስ_ላይ_ከሌለ_ተቀባይነት_እንዴት_ይኖረዋል?       በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተካተቱና ምሉዕነት የሌላቸዉ ታሪኮች በአዋልደ መጻሕፍት እንደሚሟሉ ራሱ መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል ለምሳሌ ስለ ቅዱስ ዳዊት የሚናገረዉ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ‹‹የንጉሡም የዳዊት የፊተኛዉና የኋለኛዉ ነገር በነቢዩ በናታን ታሪክ እንዲሁም በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ላይ ተጽፏል›› ይላል፡፡ 1ኛ ዜና 29፥29 ፠ #የእመቤታችን_የልደቷ_ታሪክ የእመቤታችን ወላጆች በአብዛኛዉ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ‹‹ሐና››ና ኢያቄም/ዮአኪን በሚለዉ ስም የሚጠሩ ሲሆን ሐና በቤተልሔም ተወልዳ እንዳደገች ታሪክ ያስረዳል፡፡ በናዝሬት ገሊላ ለመሥዋዕት የሚሆኑ በጎች የሚያቀርብ እንዲሁም እረኛ የነበረዉን ኢያቄምንም አግብታለች፡፡ ቅድስት ሐና ወደ ቤተ መቅደስ ስትሔድ እርግብን አይታ ታለቅስ ነበር፡፡ ከብዙ ልመና በኋላ ቅድስት ድንግል ማርያምን ግንቦት አንድ ቀን በደብረ ሊባኖስ ወልደዋል፡፡ ስለ ሐና መካንነት ወደ ቤተ መቅደስ ሄደዉ መባዕ ሲያቀርቡ ካህኑ ያልተቀበላቸዉ መሆኑን በብስራተ መልአክ ልጅ እንደሚወልዱ እንደተነገራቸዉ በእኛ ቤተ ክርስቲያን የሚተረከዉና በሌሎች ኦርቶዶክሳዊያን አብያተ ክርስቲያናት የሚነገረዉ ታሪክ ተመሳሳይ ነዉ፡፡ ፠ #እመቤታችን_የት_ተወለደች? እመቤታችን ስለተወለደችበት ስፍራ በዓለም የተለያዩ ሐሳቦች ይስተጋባሉ፡፡ ሌላዉ ቀርቶ በዶግማ አንድነት ባላቸዉ አኃት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ በእንዲህ ዓይነት ታሪክ ነክ ጉዳዮች ላይ ልዩነት መኖራቸዉ የተለመደ ክስተት ነዉ፡፡ የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ሐሳቦች የሚያነሱ ሲሆን፤ አንደኛዉ ‹‹ድንግል ማርያም ብስራተ መልአክ በሰማችበት ናዝሬት ተወልዳለች›› የሚል ነዉ፡፡ ሁለተኛዉ ሐሳብ ደግሞ ‹‹ከሦስተኛዉ ክ/ዘመን ወዲህ የማርያም መግቢያ ተብሎ በሚታወቀዉ ከኢየሩሳሌም የቅድስት ሐና የክሩሲድ ቤ/ክ በታች ነዉ የተወለደችዉ የሚል ነዉ፡፡ የግብጽ ስንክሳር የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ በናዝሬት ነዉ ይላል፡፡ የኢትዮጵያ ስንክሳር ግን በቀደምትነታቸዉ ተጠብቀዉ የቆዩ ከመሆናቸዉ አንጻር ተአማኒነታቸዉ የጎላ መሆኑን ያሳያል፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለዉ ተራራማ ሀገር ነዉ፡፡ ሊባኖስ ከገሊላ በስተ ሰሜንና ከፊንቄ በስተምስራቅ ይገኛል፡፡ ‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ›› መኃ. 4፥7 የሚለዉ ቃለ ትንቢት ምሥጢርም የአመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸዉ የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃዉንት ያስረዳሉ፡፡ ፠ #የልደታ_ለማርያም_በዓል_መቸ_ነዉ? እንደተወለደችበት ሥፍራ የእመቤታችን የልደት ቀን እንዲሁ አወዛጋቢ ነዉ፡፡ በ6ኛዉ ና7ኛዉ መቶ/ክ/ዘመን ነዉ የሚሉ የተለያዩ ሃሳቦች የተጻፉ ሲሆን Encyclopaedic of Christian antiquities ደግሞ በ431 ዓ/ም ከተካሄደዉና ንስጥሮስ ከተወገዘበት ከጉባኤ ኤፌሶን በኋላ ነዉ ይላል፡፡ በዓለም ቅዱሳንን የሚያከብሩ አብያተ ክርስቲያናት የቅዱሳንን በዓለ እረፍታቸዉን የሚያከብሩ ሲሆን ልደታቸዉ የሚከበረዉም በሦስተኛ ደረጃ የመጥምቀ መለኮት ቅ/ ዮሐንስ፤ በሁለተኛ ደረጃ የእመቤታችን ቅ/ድንግል ማርያም ልደት ነዉ፡፡ በአንደኛ ደረጃ ለስም አጠራሩ ክብር ይግባዉና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ነዉ፡፡ የአመቤታችን ልደት በምዕራባዊያን አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ኬ.ክ በመጋገር፡ የአመቤታችን ትንሽ ሀዉልት በማቆም ዐስር ሻማዎችን በማብራት ያከብራሉ፡፡ #የድንግል_ማርያም_ልደት_ለምን_ይከበራል? * ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ልደት በመልአኩ ቅ/ገብርኤል አንደበት‹‹በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል›› በማለት ተነግሯል (ሉቃ 1-14)፤ ምክንያቱም ቅ/ዮሐንስ የጌታ መንገድ ጠራጊ፥ የአዋጅ ነጋሪ በመሆኑ ነዉ፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ መወለድ ለብዙዎች ደስታ ምክንያት ከሆነ፤ የድንግል ማርያም ልደትማ ምንኛ የሚያስደስት ይሆን!?፡፡ስለሆነም ከጌታ ቀን ቀጥሎ የምንደሰትበት ትልቁ ቀን የእርሷ የልደት ቀን ነዉ፡፡ * የቀርጤሱ ቅ/እንድርያስ ስለ ከበረ ልደቷ እንዲህ ብሏል ‹‹ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌዉ በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነዉ፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነዉ፡፡››ብሏል * እመቤታችን  ለፀሐዩ መምጣት የተዘረጋች ሰማይ፤ በቅድመ አያቶቿ በነ ቴክታና ጰጥሪቃ ሕልም እንደታየችዉ በሌሊት የምታበራ ጨረቃ፤ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰዉ ልጅ ሁሉ ደስታ ነዉ፡፡ * ነቢያት በብዙ ሕብረ አምሳል የተናገሩላት ‹‹መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራራዎች ናቸዉ››፤ ‹‹ከእሴይ ስር በትር ትወጣለች አበባዋም ከግንዱ ይወጣል››፤ ‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ነይ››፤ …. ብለዉ የተናገሩላት ቅ/ድ/ማርያም ልደቷ የትንቢታቸዉ ፍፃሜ ነዉና ታላቅ ደስታቸዉ ደስታችንም ነዉ፡፡ (መዝ. 86፥1፣ ኢሳ. 11፥1፣ መኃ. 4፥7)ጂነአ * በዓለም ላይ የብዙ ታዋቂ ሰዎች ልደት ከሞቱም በኋላም ጭምር በታላቅ ድምቀት ይከበራል፤ ታዋቂ ያልሆኑ ሰዎች ልደትም እንዲሁ ይታሰባል፡፡ ለሰዉ ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ግን ምንኛ ሊከበር ይገባዉ ይሆን! ፠ #የግንቦት_ልደታ_በዓል_አከባበር ሐናና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር  እመቤታችንን ወለዱ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ ‹‹ንፍሮና ጥራጥሬ›› ነበር፡፡ ይኼንን ትዉፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ ሆኖም ግን በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መሃል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳውያት በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ የእመቤታችን በዓል ነዉ፡፡ አንዳንዶች በድፍረት ለአድባር ለዉጋር ነዉ ፣ቆሌዉን ለመለመን ነዉ፣ እያሉ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ፈንድሻ የሚጥሉ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቂቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ፣  እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸዉ፡፡