Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 380 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 588,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 193 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 380 名订阅者。
根据 10 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 43,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 23.36%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.42% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 592 次浏览,首日通常累积 1 449 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 23。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 11 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 380
订阅者
-324 小时
-27 天
+4330 天
帖子存档
#ኅዳር_፰ #ተዝካረ_አበው_(ኅዳር ፮-፰)
፠፠ በታላቁ ገዳም በዋልድባ/ዋሊ/ ብቻ ለሚደረገው የተዝካረ አበው (የዋልድባ አባቶች መታሰቢያ) አደረሳችሁ ፥ አደረሰን፨
በኢትዮጵያ በብቸኝነት ጌታችን በመሠረተው በዚህ ታላቅ ገዳም በዋልድባ ብቻ ከሚደረጉ ሥርዐቶች መካከል አንዱና ከቀድሞ አባቶች ሲወርድ ሲዋረድ ከመጣው መካከል፤ ከሰኔ ፳፩ ጀምሮ የወጣ ሳይገባ፥ የገባ ሳይወጣ (መርፌም ቢኾን ከሱባዔው በፊት ወደ ገዳሙ ካልገባ ሱባዔው እስኪያልቅ ጥቅም ላይ አይውልም)፨ የ158 ቀናት ሱባዔ ይደረጋል፤ ከ140 ቀናት በኋላ ከኅዳር ፮ - ፰ ተዝካረ አበው ይደረጋል፤ በሱባኤ የቆዩ አባቶች በማኅበር ደረጃ ይሰባሰባሉ፤ መልሰው ከኅዳር ፱ ጀምረው ደግሞ እስከ ኅዳር ፳፬ ወደ ሱባዔ ገብተው በ፳ወ፬ቱ ካህናተ ሰማይ ትልቁ ሱባዔ ያበቃል፤ ከኅዳር ፳፬ ጀምሮ ወደ ገዳም መግባት መውጣት ይፈቀዳል፨
በእነዚህ 158 የሱባኤ ቀናት (ከሰኔ ፳፩ - ኅዳር ፳፬ ድረስ)፤ ከቀባሪ በስተቀር ወደ ገዳሙ መግባትም አይቻልም፨
ሰላም ለዝክረ ስምክሙ ለዘይሴኒ እምወይን፤
ወእምነ ሐሊብ ጣዕሙ እንተ ይሠምዮ ልሣን፡፡
አበው ቀደምት ዘአብረንታንት ቅዱሳን፤
እለ ሕገክሙ ዘእንበለ ፍሬ ምኑን፤
ከመ ኢያብኡ እክለ በዛቲ መካን፡፡
፠፠ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ከአርጋብ ጸዓድዒድ ቅዱሳን አበው አንድነት፥ ከአቡነ ሳሙኤል ልጅነት፥ ከገዳመ ዋሊ ረድኤት በረከት ይክፈለን፨
/ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/
ይህንን ተዓምር ላልሰማ አሰሙ፨ ኅዳር ፯፤ (የአቡነ ገብረ እንድያስ በዓለ ዕረፍትና እንዲሁም የሊቀ ስማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅዳሴ ቤቱ ነው)፨
፠ ዕፁብ ድንቅ የኾነ ተዓምራትን የሚሠሩት (#እንጨቱ_ጸበላቸው_ውስጥ_ሲገባ_መቊጠሪያ_የሚያደርጉት፤ #በፎቶ_የምታዩት)፤
፠ በጠበላቸው ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተዓምራትን የሚያደርጉት
፠ ፻ ትውልድ የሚያስምሩት፤
፠ በደንጊያ ሠረገላነት የሚጓጓዙት፤
፠ ከ፯ቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ አንዱ የኾኑት፤ #አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_በዓለ_ዕረፍታቸው_ነው፨
ቦታቸውን ክርስቲያን የኾነ ኹሉ ሊያየው የሚገባ የተዓምራት ቦታ ነው፤
✤✣✤ #ጻድቁ_አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_ዘወለቃ_ወዘደብረ_ቆዘት_፤
✤አባታቸው ተንሥአ ክርስቶስ፥ እናታቸው አርሴማ ሲባሉ፥ የትውልድ ሀገራቸው ወሎ፥ ቦረና፥ ጋሥጫ ሲኾን፤ የቀድሞ ስማቸው ንፍታሊም ይባል ነበር።
✤ ለትምህርት ሲሄዱ መምህራቸው ብዙኃኑን የምታድን ጻድቅ ትሆናለህ ብለው ትንቢት የተናገሩላቸው ሲኾን፤ የመጻሕፍትን ትርጓሜ በደንብ ካስተማሯቸው በኋላ ንፍታሊም ይባል የነበረውን የቀድሞ ስማቸውን ለውጠው ገብረ እንድርያስ አሏቸው።
✤ ጻድቁ በአቡነ ከማ ገዳም ለረጅም ጊዜ በታላቅ ተጋድሎ አገልግለዋል፤
ብዙ አባቶች ሱባኤ በሚይዙበት በስኮሩ ሥላሴ ቤተክርስትያን ጸሎት ሲያደርጉ ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል በወርቅ ጽዋ ማየ ሕይወት አጠጥቷቸዋል።
✤ ጻድቁ አባታችን ሙታንን በማስነሳትና ድውያንን በመፈወስ ብዙ ተአምራትን ሲያደርጉ ኖረዋል።
✤ ጻድቁ ዐርብ ፥ ዐርብ የጌታችንን ቅዱስ ሥጋውን ና ክቡር ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም ይመላለሱ የነበረው በአየር ላይ ድንጋዩን እንደ ሰረገላ ፥ ዋርካውን እንደ ጥላ እየተጠቀሙበት ነበር። ይህ ሰረገላ የሆነው ድንጋይ በገዳማቸው ዛሬ ድረስ ይገኛል። (ፎቶውን ይመልከቱ)
✤ ጻድቁ አባታችን እግዚአብሔር ኀጥአንን እንዲምርላቸው ርቀት ወንዝ ከተሰኘው ቦታ በአንገታቸው ላይ በጣም ትልቅ ድንጋይ እየተሽከሙ ይጸልዩ ነበር። በዚህም ይጸልዩበት በነበረው ወንዝ ውስጥ በተአምራት መቊጠርያ የሚሰራ ጸበል ፈለቀላቸው፤ ጠበላቸው ውስጥም እንጨት ሲነከርበት እንጨቱ በተአምራት መቊጠርያ ሆኖ ይወጣል፤ ይኸውም መቊጠሪያ ለብዙ ሕመሞች መድኀኒት ነው፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ)
✤ ✤ ✤ አቡነ ገብረ እንድርያስና ሊቀ ሰማዕቱ ስለ ሃገራችን በተቀበሉት ቃል ኪዳን ሰላምና ጤና ያውርዱልን፤ ጠላታችንን ከሃገራችን ያባርሩልን፨
#ግጥም_በእንተ_ቅዱሳን_ወገዳማት_ዘወለቃ_
✤ እባካችሁ ዝም አትበሉን እናንት ገዳማት፤!
ዕድሜ ጠገቦቹ የዘመን አዝማናት፡፡
እነ አባ ያዕቆብ ፥ እነ ደብረ ጽጌ፤
እነ ቦሎ ዋሻ ፥ እነ ደብረ ሐይጌ፤
እነ ፍልፍሌ ጸዓዳ ፥ እነ ጅቦ ዋሻ፤
እነ ደብረ ቆዘት ፥ እነ ጊዮርጊስ ዋሻ፡፡
ታሪካችሁን ንገሩን እንያዝ ማሰታወሻ፤
ድንገት ብትጠፉብን እንዲሆን ማልቀሻ፡፡
ደብረ ቆዘት ጠርተን ገብረክረስቶስ አልን፤
የገዛዛን ታሪክ ለላሊበላ ሰጠን፤
ደበረ ከረቤ ብለን አባ ያዕቆብ አልን፤
የወለቃን ጉዳይ ለዘካርያስ ሰጠን፡፡
እነ ደብረ ሐይጌ እነ ጅቦ ዋሻ፤
የያጌ ጌጦች የታሪክ መናገሻ፤
የጎለሌው ዋሻ የተባለከው ፍልፍሌ፤
የቦሎ ቤቴክርስቲያን የጉርባው ቀበሌ፤
የጊዮርጊስ ዋሻ ነአኵቶ ድድምቱ፤
እስኪ ተናገሩ የታሪክ እውነቱ፡፡
ማን እንበላችሁ የመጠርያ ስማችሁ፤
እነማን ነበራችሁ የታለ ገድላችሁ?
ያሁኑ ስማችሁስ ማን ሰየመላችሁ?
* (በደቡብ ወሎ ወግዲ ወረዳ ለሚገኙ ከዘመናት ብዛት በመፈራረስ እና በመጥፋት ያሉ ታሪካቸው በአግባቡ ያልታወቁ 13 ጥንታዊያን ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት፡፡ 2001 ዓ.ም)
(ከቦታው ድረስ በመሄድ አባቶችን በመጠየቅ ለዘገበልን ወንድማችን አምላከ አቡነ ገብረ እንድርያስ በበረከት ይጎብኝልን)
/ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/
#ኅዳር_6፤ ደብረ ቊስቋም፤ #እመቤታችን_ከልጇ_ጋርስ_ደትን_የጀመረችበት_ዕለት_ነው፡፡
**ድንግል ማርያም ከልጇና ከአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ጋርለ3 ዓመታት ከ6 ወራት (ወይም ለ42 ወራት) (1275 ቀናት) ከተሰደደች በኋላ #ግንቦት_24_ደግሞ_በዓተ_ግብጽ_ (ወደ ግብጽ ወደ ደብረ ቊስቊም ገብታ ያረፈችበት ቀን ነው፡፡
ዖፍኒ ረከበት ላቲ ቤተ፤ ወፍም ቤቷን ሰራች፡፡ መዝ. ፹፫፥፫
ንጉሥ ተወልዷል መባሉን የሰማው ሔሮድስ 144,000 ሕጻናትን ሲፈጅ በቅዱስ ገብርኤል ትዕዛዝ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አንድ አምላክ ልጇን አዝላ፤ በአንዲት አህያ ላይ ተቀምጣ፤ ጥቂት ስንቅ ቋጥራ፤ ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ስደት ወጣች፡፡ ከገሊላ ተነሥታ በጭንቅ፣ በመከራ፣ በረሃብና በጥም፣ በሐዘንና በድካም፣ በእንባ ተጕዛ በዚህች ቀን ምድረ ግብፅ ገብታ በሥደት እጅግ ብዙ መከራ ተቀብላለች::
† የአምላክ እናቱ እሳትን አዝላ በብርድ ተንገላታለች::
† ለእኛ የሕይወት እንጀራን ተሸክማ እርሷ ተራበች::
† የሕይወትን ውሃ ተሸክማ ተጠማች::
† የሕይወት ልብስን ተሸክማ ተራቆተች::
† የሕይወት ፍስሐን ተሸክማ አዘነች::
† እመ አምላክ ተራበች፣ ተጠማች፣ ታረዘች፣ ደከመች፣አዘነች፣ አለቀሰች፣ እግሯ ደማ፣ ተንገላታች::
ለሚገባው ይሕ ሁሉ የተደረገው ለእኛ ድኅነት ነው:: በእውነት ይህንን እያወቀ ለድንግል ማርያም ክብር የማይሰጥ ሰይጣን ብቻ ነው:: አራዊት: ዕፀዋትና ድንጋዮች እንኳን ለአመላክ እናት ክብር ይሰጣሉ:: አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍና ቅድስት ሰሎሜ ደግሞ የክብር ክብር ይገባቸዋል:: ከአምላክ እናት ከድንግል ማርያምና ከቸር ልጇ ጋር መከራ መቀበልን መርጠዋልና::
#መድኃኔ_ዓለም_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ለምን_ተሰደደ? #ለምን_ስደቱን_ወደ_ግብፅና_ኢትዮዽያ_አደረገ?
1. ፠ትንቢቱን ይፈጽም ዘንድ:: በፈጣን ደመና ወደ ግብፅ እንደሚወርድ ተነግሯልና(ኢሳ 19፥1፣ ዕን. 3፥7)
2. ፠ምሳሌውን ለመፈጸም፤ የሥጋ አባቶቹ እነ አብርሃም፥ ያዕቆብ (እሥራኤል):፥ ኤርምያስ ወደዚያው ተሰደዋልና::
3. ከግብፅ ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ዘንድ:: (ኢሳ. 19፥1)
4. የግብፅና የኢትዮዽያ ገዳማትን ይቀድስ ዘንድ::
5. ሰው መሆኑ በአማን (በእውነት) እንጂ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ:: (ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበር:: ሔሮድስ ቢያገኘው ደግሞ ሊገድለው አይችልም:: ያለ ፈቃዱና ያለ ዕለተ ዐርብ ደሙ አይፈስምና::
6. ስደትን ለሰማዕታት ባርኮ ለመስጠት:: እና
7. የአዳምን ስደት በስደቱ ለመካስ ነው::
እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት (ወይም ለ42 ወራት) (1275 ቀናት) በስደት የቆየችባቸው ቦታዎች አሉ::
፠ በመጀመርያ ድንግል ማርያም ከርጕም ሔሮድስ ስትሸሽ መጀመሪያ የሔደችው ከገሊላ ወደ ሶርያ ደንበር (ደብረ ሊባኖስ) ነበር:: በዚያም የሸሸጋት ቅዱስ ጊጋር መስፍኑ በሔሮድስ ሲገደል ወደ ምድረ ግብጽ ወረደች፡፡
፠ በግብጽም ለብዙ ጊዜ ከአንዱ ወደ ሌላው ስትሸሽ ቆየች:: ‹‹እንዘ ከመ በግዕት ግድፍት አመ ሳኮይኪ ውስተ ምድረ በዳ፡፡›› እንዲል:: (እሴብሕ ጸጋኪ)
፠ ቀጥላም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ገብታ ደብረ ቢዘን ላይ (አሁን ኤርትራ ውስጥ ነው) ዐረፈች፤
፠ ከደብረ ቢዘን ደብረ ሐዊ፣ በደብረ ዳሞ፣ አኵሱም፣ ደብር ዐባይ፣ ዋልድባ አድርጋ እየባረከች ቆይታለች፤
፠ በዋልባም ቆይታቸው ልጇ ገዳሙን በኢትዮጵያ በብጨኝነት ራሱ የገደመውን ገዳም መሥርቶ እየባረከ ወደ ጣና ሄደዋል፡፡
፠ በጣና ገዳማትም፤ በተለይ በጣና ቂርቆስ ለ100 ቀናት ቆይታ ቀጥታ በጐጃም ወደ ሸዋ ሔዳ ደብረ ሊባኖስን ቀድሳለች::
፠ ቀጥላም እስከ ደብረ ወገግና ደብረ ሐዘሎ ደርሳለች፤ በእግሯ ያልደረሰችባቸውን የሀገራችን ክፍሎች በደመና ተጭና ዐይታ ባርካቸዋለች፡፡
፠ በደብረ ኤረር ተራራ ላይም ከልጇ ኢትዮጵያን በዐሥራትነት ተቀብላለች፡፡
ሔሮድስ መሞቱን መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል የነገራትም እዚሁ ኢትደዮዽያ ውስጥ መሆኑን ትውፊት ያሳያል::
እመቤታችን የሄሮድስን ሞት ከሰማች በኋላ ቊስቋም ከሚባል ተራራ ላይ ሆና ደስታዋን አብረዋት መከራን ከተቀበሉት ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር አከበረች፡፡ ከሃገራችን ሰዎች (ከሰብአ ኦፌር) የተቀበለችውን ስንቅና ስጦታ በ5 ግመሎች ጭና ከቅዱሳኑ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ኅዳር 6 ቀን ቊስቋም ውስጥ ገብተው ከድካም ዐርፈዋል፤ ሐሴትንም አድርገዋል::
#ግብጽ_ደብረ_ቊስቋም_፤
ከክርስቶስ ስደት 400 ዓመታት በኋላ በዚህች ቀን የግብጿ ደብረ ቊስቋም ታንጻ ተቀድሳለች፤ የቅዱሳን ማደሪያም ሆናለች፡፡ ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ፤ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ390ዎቹ አካባቢ ድንግል እናቱን፣ ቅዱሳን ሐዋርያትን፣ አእላፍ መላእክትን፣ ጻድቃን ሰማዕታትን፣ አስከትሎ ወረደ፡፡ የወቅቱ የግብጽ ፓትርያርክ ቅዱስ ቴዎፍሎስና ሊቁ ቅዱስ ቄርሎስ ቤተ ክርስቲያኑን አንጸው፤ ሕዝቡን ሰብስበው ይጠብቁት ነበርና ወርዶ ቀድሶላቸው ታላቅ ደስታ ኾኗል::
ይህቺ ቀን ለእኛ ለክርስቲያኖች ሁሉ እጅግ የደስታ ቀን ነውና ሐሴትን እናድርግ፤ የሰማይና የምድር ጌታ ለእኛ ሲል ካደረገው ስደቱ ኅዳር 6 ተመልሷልና:: ስደቷን አስበን ካዘንን: መመለሷን አስበን ደስ ልንሰኝ ይገባልና:: ‹‹አብርሒ አብርሒ ናዝሬት ሃገሩ፤ ንጉሥኪ በጽሐ ዘምስለ ማርያም መጾሩ›› ልንልም ይገባል፡፡
***ኅዳር 5 ለኅዳር 6 ከዋይዜማው ጀምሮ የሚባለውን ሙሉ ሥርዐተ ማኅሌትም እነሆ ብለናል፤ መልካም የማኅሌት ሌሊት ይሁንልን፡፡
/የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡/
፠ በኢትዮጵያ ደረጃ ኅዳር 6 የሚከበርባቸው ቦታዎች፤
ገዳመ ጽጌ ድንግል፤ ደቡብ ወሎ፤ ወግዲ፡፡
ደብረ ፀሐይ ጎንደር ቋስቋም ማርያም፤ ጎንደር ከተማ ከሆስፒታል አጠገብ፡፡
፠ በአዲስ አበባ ታቦተ ሕጉ የሚነግሥባቸው ቦታዎች፤
፠እንጦጦ መንበረ ንግሥት ቅድስት ቊስቋም ማርያም፡፡ (#365ት_ቀናት_ሙሉ_ዝክር_በማኅበረ_መድኀኔ_ዓለም_አዳራሽ_የሚዘከርባት_ቤ/ክ)
፠ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን፡፡ (የቤ/ክርስቲያኑ ዐጸድ እጅጉን ልብን የሚገዛና የሚማርክ)
፠ቃሊቲ ቊስቋም ማርያም ቤ/ክ፡፡
… ሌላም ካለ ጨምሩበት፤ ቢቻል ከፎቶ ጋር፡፡
/የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡/
ቅዱሱ አባ ዮሐኒም ከአራዊትና አባ አበይዶን ከመሰሉ አባቶች ጋር ኖረ፡፡ ከንጽሕናውም የተነሳ ቅዱሳን መላእክት ያነጋግሩት ነበር፤ በእንዲህ ያለ አኗኗር 12 ዓመታት ከኖረ በኋላ፤ ስም አጠራሩ በመላዋ ሃገሪቱ ሲሰማ ወላጅ እናቱ በሕይወት ነበረችና ሰማች፤ ልታየውም የወንድ ልብስ ለብሳ ወዳለበት ተራራ ገሰገሰች፡፡ ኅዳር 5 ቀን ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት እንደ ልማዱ ተራራ ላይ ወጥቶ ሳለ፤ ወደ ተራራው ደርሳ ስትጠራው ቅዱሱ ተመለከታት፤ አንተ ማነህ? አለ፤ እናቱም በክርስትና ስሟ አኔ ‹ዓመተ መንፈስ ቅዱስ ነኝ› አለችውና ወደ እርሱ ቀረበች፤ በቀረበች ጊዜም ሴት መኾኗን ተመለከተ፤ አባቱ አሞኒ የነገረውን (ሴት ስታይ ሩጥ ያለውን) ወዲያውኑ አስታውሶ፤ መጽሐፉንና የቀለም መጻፊያ ብዕሩን አንስቶ በሩጫ ወደ ገደሉ /በፎቶ ላይ ወደ ምታዩት እጅግ እጅግ በጣም ረጅም ገደል/ ተወረወረ፤ አባ አበይዶ እያየው በክንዶቹ ግራና ቀኝ ክንፍን አውጥቶ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከእርሱ ጋር ሁኖ መንፈስ ቅዱስ እየመራው ሞትን ሳይቀምስ ሔኖክና ኤልያስ ሌሎችም አባቶች ወዳሉበት ወደ ብሔረ ሕያዋን በ32 ዓመቱ ገባ፡፡ ደቀ መዝሙሩም አባ አበይዶም ኅዳር 4 በደብረ ዓሣ በሰላም አረፈ፡፡
*ወደ ገደል መወርወሩ፤ እንደ ሞትና መቃብር፡፡
*ክንፍ አውጥቶ ብሔረ ሕያዋን መግባቱ፤ እንደ ትንሣኤ ሙታን ነው፡፡
ለኢትዮጵያውያን ብሩክ ኮከብና ገባሬ ተአምር የሆነው አባ ዮሐኒ ይህ ኹሉ ተዓምራት የሚፈጸመው እመቤታችን (አበባ፥ ፍሬ) በወለደችው መድኀኔዓለም ክርስቶስ (ጽጌ) ነው፤ ይህንንም በማስመልከት የተለያዩ ሊቃውንት የተለያዩ ድርሰቶችን ደርሰዋል፤ ከእነዚህም መካከል አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰታቸው፥ አባታችን አርከ ሥሉስ በስንክሳር (በአርኬ) ድርሰታቸው፥ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በኆኅተ ቅዱሳን ድርሰታቸው፥ ቅዱስ ያሬድ በመጽሐፈ ድጓው የሚከተለውን ደርሰውላቸዋል፤
፩. #ስለ_አባ_ዮሐኒ_
፠ ሊቁ ቅዱስ ያሬድም በመጽሐፈ ድጓ ላይ የአባ ዮሐኒን ወደ ብሔረ ሕያዋን መሰወሩን በተመለከተ፤
‹‹አባ ዮሐኒ ጸገየ ሕይወተ፤
ፈረየ ሠላሳ ወስሳ ወምእተ፤
ብሔረ ሕያዋን ተመሥጠ ግብተ፤
ዘዐይን ኢርዕየ ነሥአ ዕሤተ፡፡
(አባ ዮሐኒ ሕይወትን አብቦ፤ ሠላሳ፥ ስሳንና፥ መቶን አፈራ፤ ወደ ሕያዋን ሀገር በድንገት ተነጥቆ ዐይን ያላየውን ዋጋ አገኘ)
፠ አባ አርከ ሥሉስ ቅዱስ በመጽሐፈ ስንክሳር አርኬው ላይ የአባ ዮሐኒን መሰወር በተመለከተ፤
‹‹ሰላም ዕብል ለዘኮነ ሱቱፈ፤
ምስለ እለ ገብሩ ሰብእ ብሔረ ሕያዋን ምዕራፈ፡፡
እምሥርዓተ መላእክት ዮሐኒ ምንትኒ ኢያትረፈ፤
ከመ ሕይወቶሙ ሕይወተ ተጸገወ ዘልፈ፤
ወከመ ክንፎሙ አብቈለ አክናፈ፡፡›› (አርኬ)
(ብሔረ ሕያዋንን ማረፊያን ካደረጉ ሰዎች ጋር ኅብረትን ያደረገ ለኾነ ሰላም እላለኊ፤ ዮሐኒ ከመላእክት ሥርዐት ምንም ምን አላስቀረም፤ እንደ ሕይወታቸው ሕይወትን ተቀበለ ፥ ተቸረ፤ እንደ ክንፋቸውም ክንፎችን አበቀለ)
፠ አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰቱ የአባ ዮሐኒን ታሪክና በጽጌና በፍሬ የተመሰሉ እናትና ልጇን አመሳትሮ እንዲህ ደርሶታል፤
‹‹ሶበ ዴገነኪ አርዌ በሊዓ ሕፃንኪ ዘኀለየ፤
በዘትሠርሪ ገዳመ ወታፈጥኒ ጐይየ፡፡
እንተ ጸገይኪ አክናፈ ከመ ዮሐኒ ጸገየ፤
ብእሲተ ሰማይ ማርያም ዘትለብሲ ፀሐየ፤
ተአምረኪ ጸሐፈ ዮሐንስ ዘርእየ:: /አባ ጽጌ ድንግል፣ ማሕሌተ ጽጌ/
፠ አባቶቻችን በወርኃ ጽጌ በመጽሐፈ ወረባቸው እንዲህ ብለውታል፤
ወረብ፤ ብእሲተ ሰማይ ማርያም ፀሐየ ዘትለብሲ፤
ተአምረኪ ጸሐፈ ዮሐንስ ዘርእየ/፪/ ተአምረኪ፡፡
ወረብ፤ አመ/፪/ ጸገይኪ አክናፈ ከመ ዮሐኒ
ተአምረኪ ጸሐፈ ዮሐንስ ዘርእየ/፪/ተአምረኪ፨
፠ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ የአባ ዮሐኒን ክብር እንዲህ ገልጾታል፤
‹‹ሰላም ለአባ ዮሐኒ ከመ ንህብ ዘተመሰለ፤
እምኲሎሙ ቅዱሳን ዘአስተጋብአ ገድለ፡፡››
(እንደ ንህብ የተመሰለ ኾኖ ከቅዱሳን ኹሉ ገድልን የሰበሰበ ለኾነ ለአባ ዮሐኒ ሰላምታ ይገባል)
፪. #ስለ_አባ_አበይዶ_
፠ አባ አርከ ሥሉስ በመጽሐ ስንክሳር አርኬው ላይ የዚኽን ዓለም ሥራ ትቶ የአባ ዮሐኒ ደቀ መዝሙር ስለነበረው ስለ አባ አበይዶ በኅዳር ፬ ዐርኬው ላይ እንዲህ ብሎ የክብሩን ታላቅነት መስክሯል፤
‹‹ሰላም ለአበይዶ ዘመጠነ ዮሐኒ መጠኑ፤
እስመ ውእቱ ረድኡ ወውስተ ኲሉ ምእመኑ፡፡
ለዝ ጻማዊ ወፈጻሜ መልእክት ዘበበበይኑ፤
ጼና አልባሲሁ ከመ ጼና ስኂን ይጼኑ፤
ወይበርህ እምፀሓይ ምስብዒተ ሥኑ፡፡››
(የማዕርጉ መጠን እንደ ዮሐኒ ማዕርግ መጠን ለኾነ ለአበይዶ ሰላምታ ለርሱ አገልጋዩና በኹሉም ውስጥ ታማኙ ነውና፤ በየወገኑ አገልግሎትን ለሚፈጽምና ለዚኽ ትጉህ ለኾነ ሰው የልብሶቹ ሽታ እንደ ዕጣን መዐዛ ይሸታል፤ የልብሱ ሽታ እንደ ዕጣን ጢስ ይሸታሉ፤ ደም ግባቱም ከፀሓይ ሰባት እጅ ይበራል)፡፡
፠ ቅዱስ ያሬድም በመጽሐፈ ድጓ ላይ የአባ አበይዶን ተጋድሎ በተመለከተ እንዲህ ብሏል፤
‹‹ብፁዕ ውእቱ አባ አበይዶ ረድአ ዘኮኖ
ለአባ ዮሐኒ ብፁዕ ብእሲ በትዕግሥቱ ዘፈጸመ ገድሎ፤
(ለአባ ዮሐኒ አገልጋይ የኾነው አባ አበይዶ ንኡድ ፥ ክቡር ነው፤ ተጋድሎውን በትዕግሥቱ የፈጸመ የኾነ ርሱም ንኡድ ክቡር ነው)፡፡
፠ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ የአባ አበይዶን ክብር እንዲህ ገልጾታል፤
‹‹ሰላም ለአባ አበይዶ፤
ለጸላኢ ዘኬዶ፡፡››
(ጠላትን የረገጠው ለኾነ አባ አበይዶ ሰላምታ ይገባል)፨
(ምንጭ፤ የገዳሙ አባቶች የቃል አስረጅ፣ ገድለ አቡነ ዮሐኒ፣ የአስቴር (ዮሐኒ) የጕዞ ማስታወሻ)
(ታሪኩን ከቦታው ድረስ ሄዶ፤ አባቶችን ጠይቆ፤ መጻሕፍትን አገላብጦ ለዘገበልን ወንድማችን አምላከ አቡነ አሞኒ፥ ዮሐኒ ወአበይዶ በበረከት ይጎብኝልን፡፡)
/የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/
#ኅዳር_4ና5፤ #አባ_ዮሐኒ_ወአሞኒ_ወአበይዶ_፤ #ዘገዳመ_ዓሣ(ይ)፥#ቆላ_ተንቤን_፡፡
፠አባ አሞኒ ፥ ዮሐኒ ፥ አበይዶ፤ አያት፣ አባትና የልጅ ልጅ፡፡
፠አባ አሞኒና ዮሐኒ ታሪካቸው ከቅድስት እንባ መሪና ጋር የሚመሳሰልና ብዙ ትምህርት የሚገኝበት #የሚመስጥ_ታሪክ_ስለሆነ_እስከ_መጨረሻው_ያንብቡት_፤
፠ምንኵስና በተሰዓቱ ቅዱሳን ከመግባቱ በፊት የምነና ሕይወት በኢትየጵያ ለመኖሩ አስረጅ የሆኑ ቅዱሳን፤
፠ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናቸው ከ1600 ዓመታት በላይን ያስቈጠረና አሁንም ያለ እጅግ በጣም ጥንታዊ ገዳም፡፡
አባ ዮሐኒ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መግቢያ ላይ በትግራይ ተንቤን አውራጃ በሀገረ ሰላም ቀበሌ የተወለደ ቅዱስ ነው፡፡ በዚያን ዘመን ሥርዓተ ምንኵስና ወደ ኢትዮጵያ ባይገባም አበው በምናኔ በበረሃ ይኖሩ ነበር፡፡ ከ4ኛው መ/ክ/ዘ በፊት (ሥርዓተ ምንኵስና ወደ ሀገራችን የገባው በኢትዮጵያ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ /ከአባ መቃርስ ወደ አባ ጳኵሚስ፤ ከአባ ጳኵሚስ ወደ አባ ቴዎድሮስ፤ ከአባ ቴዎድሮስ ወደ አባ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ) ቢሆንም የብሕትውና ኑሮ ግን በሀገራችን ከዚያም ቀድሞ እንደነበረ ከሚጠቁሙን ዋነኛ ነገሮች አንዱ የገዳመ ዓሣ/ይ/ ታላላቆች የኾኑ ቅዱሳን አባቶቻችን ቅዱሳን አባ አሞኒ እና አባ ዮሐኒ ዋነኞቹ ናቸው፡፡
#ገዳመ_ዓሣ(ይ)
ገዳሙ ከ1600-1800ዓመታትን ያስቈጠረ ውቅር(ፍልፍል) ቤተክርስቲያኝ ሲኾን፤ ገዳሙ የሚገኝበት ተራራ ብቻውን ከ20ደቂቃ በላይ ያስጕዛል፤ እንደ ደረጃ ያሉ፥ ሠርጥ የኾኑና አንድ ድልድይን ካለፉ በኋላ ገዳመ ዓሣን እንዲኹም ወደ ላይ ተጨማሪ የ5 ደቂቃ ተራራ ሲወጡ አባ ዮሐኒ በሕፃንነታቸው (ከተወለዱባት እለት ጀምሮ እስከ 3 ዓመት እስከሚሞላቸው) ያደጉባትን ትንሽ ዋሻ ያገኛሉ፤ የአባ አሞኒና የአባ ዮሐኒ ታሪክም ከአባ መሪና ጋር በተወሰነ መልኩ ይመሳሰላል፤ ………. ለማንኛውም ከዚህ በታች ታሪኩ ይተረካል………፡፡
አባ ዮሐኒ ከመወለዱ በፊት፤ የእናቱ ባል የተንቤን ሹም ስለበር ለዘመቻም /ለንግድም/ ይላሉ ኖባና ላባ ወደሚባል አገር ሔዶ ለሰባት ወር ያህል ዘገየ፤ ታናሽ ወንድሙም የወንድሙን ሚስት ወንድሜ ዘገየ ከእንግዲህ ወዲህ አይመለስም /ሞቷልም ይላሉ/ ስለዚህ ሚስት ትሆኚኝ ዘንድ ነዪ ቃል ኪዳን እንግባ አላት፤ እሷም የባሏ ታናሽ ወንድምና በቤቷ ውስጥ ያሳደገችው ነበረና እንዴት ደፈርከኝ ብላ ተቆጣች፤ እርሱም ተቆጥቶ ደረሰባትና ጸንሳ ወንድ ልጅ ወለደች፡፡
በወለደችበት ቀንም ከብዙ ምርኮ ጋር ባሏ ወደ አገሩ ተመለሰ፤ ወደ ቤቱም በገባ ጊዜ ሚስቱ ከቤት የለችም ነበርና ሚስቴ ወዴት ሔደች ብሎ ጠየቀ፡፡ በቤቱ ውስጥ ያለ አንድ ሕፃን ባለቤትህ ታማለች አለው፤ ባለቤቷም በሽታዋ ምንድን ነው አለው? ያ ሕፃንም ዛሬ ልጅ ወለደች ብሎ መለሰለት፡፡ ይህንንም በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ተቆጣ፤ ያ ሕፃንም እየመራው ሚስቱ ወዳለችበት ገባሕ ይደበድባትም ጀመር፡፡
ደብረ ዓሣይ (በቆላ ተንቤን የሚገኝ) በሚባል ገዳም ስሙ አባ አሞኒ ዘናሕሶ የተባለ ገዳማዊ ነበር፤ በዚያ ገዳምም ለሃያ ዓመታት ያህል የቆየ ነው፡፡
የእግዚአብሔር መልአክም አባ አሞኒን ተነስተህ የተንቤን ሹም ወደ ሆነው ሰው ቤት ሂድ ከዚያም እግዚአብሔር የወደደውን ነገር ታገኛለህ አለው፤ አባ አሞኒም የእግዚአብሔር መልአክ እንዳዘዘው ከተራራው(ከገዳሙ) ወርዶ ወደ ተንቤን ሹም ቤት ደረሰ፤ ሚስቱም በቤቷ በር ፊት ለፊት አባ አሞኒን ባየችው ጊዜ ውስጡ ጥበበ እግዚአብሔር ነውና፤ ለባሏ የጸነስኩት ከዚህ መነኵሴ ነው አለችው፡፡
ያን ጊዜም ባሏ በቁጣ ወጥቶ አባ አሞኒን መታው፥ ደበደበው፤ ልጅህን ይዘህ ሒድ ብሎ ሕፃኑን ለአባ አሞኒ ሰጠው፡፡ አባ አሞኒም ሕፃኑ በተወለደበት ቀን በልብሱ አቀፈው፤ ወደ ገዳሙ (ደብረ ዓሣይ) ወስዶ እኔ ጡት የለኝ! ብሎ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ ከተራራው ከገደሉ ጀርባ እንደ መቃብር አስመስሎ ምድርን ቆፈረና፤ ለሕፃኑ የሰሌን ቅጠልን አንጥፎ በዚያ አስቀመጠው፥ ድንጋይም ከደነ፤ እግዚአብሔር ከወደደ ያድንህ፣ ይህቺ ጉድጓድ እናትህ ትሁን፤ ብሎ ከዚያ ትቶት ወደ በዓቱ ሔደ፡፡
በነጋውም ማልዶ ወደዚያ ሕፃን ገሠገሠ፤ ፌቆ/ሚዳቋ የምትመስል/ ከጉድጓዱ ድንጋዩን አስወግዳ ተንበርክካ ስታጠባው አያት፤ ፌቆዋም አባ አሞኒን ባየችው ጊዜ ከጉድጓዱ ውስጥ ሸሸች፤ አባ አሞኒም ያን ሕፃን ደስተኛ ሆኖ ዓይኖቹን ባየ ጊዜ የተደነቀው ቅዱስ አሞኒ ሕፃኑን "ዮሐኒ" ሲል ስም አወጣለት፤ ትርጕሙም ወላጆችህ ወይም አሳዳጊዎችህ አራዊት ናቸው እንደ ማለት ነው፡፡ አባ አሞኒም ይህን ዕፁብ ድንቅ ሥራ ያሳየኸኝ እግዚአብሔር ስምህ ይመስገን አለና ወደ ገዳሙ ተመለሰ፡፡
አባ አሞኒም ሕፃኑን ጠዋትና ማታ እየጎበኘው፤ ፌቆ እንደ እናቱ እያጠባችው ሦስት ዓመት ኖረ፤ እንዳይበርደውም ዝንጀሮ/አሞራም/ ያቅፈው ነበር፡፡ ሕፃኑም ከሦስት ዓመት በኋላ የፌቆዋን ጡት መጥባትን ተወ፤ አባ አሞኒም ወደ ገዳሙ ወስዶ እስከ ሰባት ዓመት ድረስ በዚያ አሳደገው፤ ከሰባት ዓመቱ ጀምሮ የዳዊትን መዝሙር፣ የነቢያትንና የሐዋርያትን መጻሕፍት እስከ ትርጓሜያቸው አስተማረው፤ ሕፃኑም ዐሥራ ሁለት ዓመት በኾነው ጊዜ፤ አባ አሞኒ ይህ ልጄ ትምህርትን ጨረሰ ዲያቆን ይኾን ዘንድ ወደ ጳጳስ ልውሰደው ብሎ መንገድ (ለጕዞ) ተነሡ፡፡
የስድስት ሰዓት መንገድንም ተጓዙ፤ አባ ዮሐኒ መንገድ ላይም ዐሥር ወጣት ሴቶች ውኃን በእንስራ ተሸክመው (ተሰባስበው ሲጫወቱ) ከልብሳቸው ተራቁተው አየ፤ አባ ዮሐኒም ከዚህ በፊት የሴት መልክን አይቶ አያውቅም ነበረና አባቴ ሆይ እነዚህ ጸጕራቸው የረዘመ፣ ደረታቸው ወደፊት የወጣ ፍጥረቶች ምንድን ናቸው? ሲል ጠየቀው፤ አባ አሞኒም ልጄ ዮሐኒ ሆይ እነዚህ ሴቶች ናቸው፤ ግን እንደ እኔና ላንተ ላሉ የበርሃ ሰዎች አይሆኑምና አትቅረባቸው አለው፡፡ አባ ዮሐኒ መልሶ አባቴ! ድንገት ቢመጡብኝ ምን ላድርግ? ሲል ጠየቀው፡፡ አባ አሞኒም ልጄ! ከዘለዓለም ርስት ከምትነቀል ሩጠህ ብታመልጥ ይሻላል አለው፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ ገዳማቸው ተመለሱ፡፡
#አባ_አበይዶ_
አባ አበይዶ የሚባል መነኵሴም የተጋድሎ ዜናቸውን ሰምቶ ረድዕ (አገልጋይ) ለመኾን ወደ ገዳማቸው መጥቶ ተጨመረ፡፡ ለምግባቸውና ለልብሳቸው አባ አሞኒና ልጁ አባ ዮሐኒ መጻሕፍትን እየጻፉ፤ አባ አበይዶ እየሸጠ እንዲህ ኾነው በብሕትውና ሲኖሩ፤ አባ አሞኒ አርባ ዓመት በገዳም ኑሮ (አባ ዮሐኒ በተወለደ ሃያ ዓመት ሲሞላው) ኅዳር 5 አረፈ በገዳማቸውም ቀበሩት፡፡
#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፪፡፡ Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡
ለምን እንፈተናለን፤
ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤
ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋቸው፤ ….
……እንዳያመልጣችሁ፤ በሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ በብዙ ጕባኤያት ላይ ያልተዳሰሱ ርዕሶች የሚዳሰሱበት ጕባኤ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ፤ #ደግመን_እንላለን_ይህ_ትምህርት_በፍጹም_እንዳያመልጣችሁ!!!!!
ለ፬ ተከታታይ ሳምንታት፤ ትምህርቱ ተከታታይነት ስላለው መቅረትና ማርፈድ አይመከርም!!፡፡
(፻፶፩ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ)
ዐርብ ኅዳር ፭ ጀምሮ ከ፲፪-፪ ሰዓት
አሁንም በድጋሚ እንላለን ለሕይወታችን ወሳኝና በብዙ የትምህርት ጕባኤያት ላይ የማይዳሰሱ ትምህርቶች
ስለሆኑ እንዳያመልጣችሁ!!!!
የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል
ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡
፠ልዩ ጕባኤ፤ በደብረ ባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ (ጎተራ፥ አጎና ሲኒማ አጠገብ)፡፡
ከኅዳር 4 እስከ 6፤ ከ10፡30 ጀምሮ
ኅዳር 7፤ ከ4፤00 ጀምሮ፡፡
(የዉሉደ ያሬድ ሰ/ት/ቤት 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ ዓመትን በማስመልከት የተዘጋጀ)፡፡
፠ ልዩ ጕባኤ፤ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የቤተ ክርስቲያን ምላሽ፡፡
ኅዳር 7 ከ10፡00 ጀምሮ፤ በደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ቤ/ክ፡፡
#አሳዛኝ_ሰበር_ዜና_፤ /ሁላችሁም SHAREEEEEEE ማድረጋችሁን እንዳትዘነጉ!!!!!!!!)
ውስተ ሃገረ አዲስ አበባ ህየ ነበርነ ወበከይነ፤
ውስተ ኵሃቲሃ ሰቀልነ እንዚራቲነ፤
ሶበ ተዘከርናሃ ዘተውዕያ ለምሥራቅ ሐረርጌ ቤተ ክርስቲያን ጽዮን እምነ፡፡
(በሃገረ አዲስ አበባ ተቀምጠን፤ በዛፎችዋ ላይ መሰንቆዎቻችንን ሰቀልን፤ በምሥራቅ ሐረርጌ ያለች የተቃጠለች እናት ጽዮን ቤተ ክርስቲያንና ባሰብናት ጊዜም አለቀስን፡፡)
ኅዳር 3 /2012 ዓ.ም. በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሚገኙ 2ት አብያተ ክርስቲያናትና በተለያዩ ቦታዎች (በተለይም በቀርሳና ወተር) በሚገኙ ምዕመናን ላይ ከፍተኛ ጥቃት መድረሱን የምስራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ገልጿል፡፡ የተቃጠሉት አብየተ ክርስቲያናትም፤
#ዋቅጅራ_መድኀኔ_ዓለም_
#ጥንታዊና_ታሪካዊቷ_ገንዲድ_ቅድስት_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን_ ሲሆኑ
የጥፋት ኀይሎች አደጋውን ወደ ቊልቢ ቅዱስ ገብርኤል ለመውሰድም ስለሚሠሩ ሁላችንም፤ በተለይም በቊልቢ አቅራቢያ የምንኝ #ክተት_ወደ_ቊልቢ_ ልናደርግ ይገባል፡፡
/ሁላችሁም SHAREEEEEEE ማድረጋችሁን እንዳትዘነጉ!!!!!!!!)
ወረብ ፲.፪.፩፤ ተመየጢ(፪)ማርያም ሀገረኪ ናዝሬት፤ (በመምህር ታቦር)
መልካም የተፈጸመ ጽጌ ማኅሌት ይሁንላችሁ፤ በተለይ ከሀገር ርቃችሁ ለምትገኙና የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱ ብቸኛ ወረቦች የሆኑትን ዘግበንላችኋል፡፡
ወረብ ፯.፩፤ዘቀጨኔ ደብረ ሰላም (የቤቱ ቀለም) (በአጋፋሪ ይሁኔ)
ኅብረ ሐመልሚል(፪) አርአያ ኰሰኰስ፤/፪/
ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ፡፡/፪/
ወረብ ፮፤ ሰአሊ ለነ ማርያም ሰአሊ ለነ ፤ (ዘቀጨኔ ደብረ ሰላም (የቤቱ ቀለም)፤ (በመሪጌታ ተክለ ያሬድ)
ወረብ ፭፤ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ (፪) ዘየኀቱ እምዕንቈ ባሕርይ፤ (በደብራችን መሪጌታ ሄኖክ)
ወረብ ፬፤ ንዒ ኀቤየ ምስለ መላእክት(፪)፤ ዘቀጨኔ ደብረ ሰላም (የቤቱ ቀለም)፤ (በሊቀ ጠበብት ይልማ የደብራችን የአቋቋም መምህርና በኢትዮጵያ ደረጃ የአቋቋም ተጠያቂና መምህር በሆኑት በመምህር ዳዊት)
ወረብ ፫፤ እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ(፪) ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ፤ (በደብራችን መሪጌታ፤ በ2007 ዓ.ም. የተቀዳ)
ወረብ ፪፤ እለ ትነብሩ ተንሥኡ፤ (በደብራችን መዘምር)
የጥቅምት ፴ (የተፈጸመ) ማኅሌተ ጽጌ ወረቦች፤
ወረብ ፩.፩፤ /ዘቀጨኔ ደብረ ሰላም (የቤቱ ቀለም) (በአጋፋሪ ይሁኔ)
ኢየኀፍር ቀዊመ ቅድመ ገጸ ስዕልኪወላዲተ አምላክ፤/፪
ጸውዖ ስምኪ ያነሥእ ዘወድቀ(፪)፡፡/፪/
