Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 382 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 588,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 193 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 382 名订阅者。
根据 10 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 43,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 23.36%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.42% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 592 次浏览,首日通常累积 1 449 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 23。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 11 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 382
订阅者
-324 小时
-27 天
+4330 天
帖子存档
#ፎቶ_ክምችት_10፤ የደመራ በዓል በምሥራቃዊት ኢትዮጵያ፤ መቄት፣ ራያ፣ ሰቆጣ፣ ከሚሴ፣ ከምቦልቻ፣ ወልድያ፣ ባቲ፣ ደሴ፡፡ እና በሰሜን ሸዋ (ጅሩ)
#ፎቶ_ክምችት_9፤ የደመራ በዓል በምዕራባዊት ኢትዮጵያ፤ አሶሳ፣ ወለንጪቲ፣ ወሊሶ፣ ጅማ፡፡
#ፎቶ_ክምችት_8፤ የደመራ በዓል በደቡባዊት ኢትዮጵያ፤ ሆሳዕና፣ ሻሸመኔ፣ አርባ ምንጭ፣ ወላይታ፣ የም ደሪ ከተማ፣ ጂንካ፣ ዲላ፣ ደራሼ ጊዴሎ፡፡
#ፎቶ_ክምችት_6፤ የደመራ በዓል በምሥራቅ ደቡባዊት ኢትዮጵያ፤ በድሬደዋና በሐረር፣ በቁልቢና በአሰበ ተፈሪ፡፡
#ፎቶ_ክምችት_6፤ የደመራ በዓል በማዕከላዊ ደቡባዊት ኢትዮጵያ፤ በናዝሬት /አዳማ/፣ አሰላና አርሲ፡፡
#ፎቶ_ክምችት_5፤ የደመራ በዓል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፤ በአዲስ አበባ፤ ዕለቱን ርጥብ ዛፍ ተቈርጦ ደመራ በሚደመርበት በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም፡፡ (በአረጓዴ ቢጫ ቀይ አምፑል የሚታየው መስቀል በማዕጠንት እየታጠነ የሚንቀሳቀስ መስቀል ሲሆን፤ የመጨረሻው ፎቶ፤ ከምሽቱ 3፡19 ደቂቃ ላይ ደመራው ወደ ደወል ቤቱ /በቀድሞ የደጀ ሰላም በር/ ሲወድቅ የሚያሳይ ነው፡፡)
#ፎቶ_ክምችት_4፤ የደመራ በዓል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፤ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ::
#ፎቶ_ክምችት_3፤ የደመራ በዓል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፤ በአዲስ አበባ ለመስቀል አደባባይ ተሰላፊዎች (የሰሜንና የደቡብ አዲስ አበባ ሰ/ት/ቤት ተማሪዎች፣ የማኅበረ ቅዱሳን ዘማሪያንና በገና ደርዳሪዎች፤ እንዲሁም ነጋሪት ጐሳሚና መለከት ነፊዎች፤ በጕዞ ወቅት፡፡)
#ፎቶ_ክምችት_2፤ የደመራ በዓል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፤ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች (በ6 ኪሎ፣ በአፍንጮ በር አካባቢ፣ በሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረትና በአዲስ ከተማ መርካቶ)
በሃገራችን የደመራ ክብረ በዓል እንደየአካባቢው መስከረም 16 ለ17 ማታ ላይና በ17 ቀን ቀትር ላይ ይደመራል፡፡
፠ ወደ ሰሜኑ ክፍል ያሉት በ17 ቀትር ላይ ዋናውን ሲደምሩ፤ በየቤታቸው ደግሞ ሌሊት ያበራሉ፡፡ (ለአብነትም ያህል፤ ጎንደር፣ ሞጣ፣ እስቴ መካነ ኢየሱስ፣ ገንዳ ውኃ፣ ደባርቅ፣ ደብረ ታቦር፣ ሰቆጣ ይጠቀሳሉ፡፡)
፠ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ (አዲስ አበባን ጨምሮ)፣ ምዕራብ፣ ምሥራቅና ደቡባዊት ኢትዮጵያ ደግሞ በ16 ለ17 አጥቢያ ምሽት ላይ ይደምራሉ፡፡
#ፎቶ_ክምችት_1፤ የደመራ በዓል በሰሜናዊት ኢትዮጵያ (በመቀለ፣ በጎንደር፣ በባሕር ዳርና በደብረ ማርቆስ)
መስከረም 18/2012 ዓ.ም.
እንኳን ለአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕርና ለአቡነ አኖሬዎስ ክብረ በዓል አደረሰን።
+**ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን።*+
፠፠፠ በደርቡሽ ተቃጥሎ ጠፍ ሁኖ የቆየው፥ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ የሆነውና ጽላቱ በደብረ ብርሃን ሥላሴ የቆየው የዳረገንዳ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ወደ ቀድሞ ርስቱ ቤተ ክርስቲያኑ ታንፆ ታቦተ ሕጉ ገብቶ ክብረ በዓሉ ተከብሮ ውሏል።
፠፠፠ እንዲሁም #የመስቀለ_ኢየሱስ_ቤተ_ክርስቲያን_(ትግራይ ከአዲግራት 80 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ኢሮብ ወረዳ አሲምባ ተራራ ላይ የሚገኝ) ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል፡፡
+**ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን።*+
/ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/
እንኳን ለአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕርና ለአቡነ አኖሬዎስ ክብረ በዓል አደረሰን።
+**ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን።*+
በደርቡሽ ተቃጥሎ ጠፍ ሁኖ የቆየው፥ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ የሆነውና ጽላቱ በደብረ ብርሃን ሥላሴ የቆየው የዳረገንዳ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ወደ ቀድሞ ርስቱ ቤ/ኑ ታንፆ ታቦተ ሕጉ ገብቶ ክብረ በዓሉ ተከብሮ ውሏል።
+**ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን።*+
/ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/
***12ኛ ክፍልን በ2011 ዓ.ም. ላጠናቀቃችሁ አባላቶቻችንና ወጣት ምዕመናን በሙሉ፤ እሑድ መስከረም 18/2012 ዓ.ም. በ10 ሰዐት ከደብረ ነጎድግዋድ ቅዱስ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ ሰ/ት/ቤት ጋራ በመተባበር የውይይት መርሐ ግብር ስለተዘጋጀ በሰዐቱ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ቦታ፤ በቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ. አዳራሽ።
እሑድ መስከረም 18/2012 ዓ.ም. በ10 ሰዐት
የመስከረም ፲፯ በዓለ አስተርእዮተ መስቀልን የት ሊያከብሩ አስበዋል?????
አዲስ አበባ ላላችሁ በማኅሌት፣ በሰዐታት፣ በኪዳን፣ በቅዳሴ፣ በዑደተ ታቦተ ሕግ፣ በሰርክ ጕባኤ በአዲስ አበባ የሚከብርባቸውን ቦታዎች እንጠቁማችሁ፡፡
፠ ቀጨኔ ደብረ ሰላም፤ ከንግሥት ዘውዲቱ ጀምሮ የመስቀል ክብረ በዓል የሚከበርበት፤ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ አገልጋይ ካህናቱ እንኳን ሳይቀር የመድኀኔ ዓለም አገልጋይና የመስቀል አገልጋይ ተብለው ምድብ የነበሩና፤ የመስቀል አገልጋዮች ደመወዝም ከቤተ ክሕነት የሚከፈልበት፡፡
፠ ደብረ ዕንቊ ልደታ ለማርያም፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የመስቀል ክብረ በዓል ይከብራል፡፡
፠ ደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ፤ የመስቀል ክብረ በዓል ይከብራል፡፡
የመስከረም ፲፮ የደመራ በዓል የምሥራቅ አ.አ ሰ/ት/ቤቶችና የማኅበረ ቅዱሳን የበገና የመሰንቆና የዝማሬ ተሰላፊዎች በከፊል ይህንን ይመስላሉ፡፡ በተለይ ውጭ ላላችሁ ባለን ካሜራና አቅም ይህችን ለመዘገብ ጥረት አድርገናል፤ ለወደፊቱ ግን የተደራጀ ነገር እንድንዘግብላችሁ የካሜራና የመቅርፀ ድምፅ ጉዳይን አስቡበት፡፡ /መልካም በዓል/
፠፠፠ #የመስቀል_ክብረ_በዓላት_
#መስከረም_16_የደመራ_በዓል_፤
#መስከረም_17_የመስቀል_በዓል_፤
#መስከረም_10_ተቀጸል_ጽጌ_፤
#መጋቢት_10_መስቀሉ_የተገኘበት_በዓል፤
#ደመራ_፤ ንግሥት እሌኒ በመስከረም 16 ደመራ አስደምራ እጣን አስጢሳ የመስቀሉን ቦታ ያወቀችበት ዕለት ነው፡፡ ጥንተ ታሪኩም፤ ክርስቶስ በሞተ ጊዜ የገነዙት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ በጌታ መካነ መቃብር ጎልጎታ ወስደው አኑረውታል፡፡ አበው ሐዋርያት የኢየሩሳሌሙ ኤጲስ ቆጶስ ሐዋርያው ያዕቆብ በኃላፊነት እንዲጠብቀው አድርገው እነርሱም ከየአህጉረ ስብከታቸው ሲመለሱ በእግረ መስቀሉ ሥር እየተሰበሰቡ ይጸልዩ ነበር፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጠዋትና ማታ በጎልጎታ በመስቀሉ ሥር ትጸልይ ነበር፡፡ ብዙ ሰዎች ታሪኩንና ቦታውን በክርስቶስ ደም የተቀደሰውን ክቡር መስቀሉን ለማየት ያመኑትም በረከት ለማግኘት ከየአቅጣጫው ይመጡ ነበር፡፡ በመስቀሉ ተአምራት ብዙዎች ከተለያዩ ደዌ /በሽታ/ መፈወስ ጀመሩ፤ ይህም በጣም ብዙ ሰዎች ክርስቶስን ወደ ማመን ሳባቸው፡፡ ይህን ድንቅ ሥራ የተመለከቱ የክርስቶስ ሰቃዮች /ሰቃልያነ ክርስቶስ/ በሁኔታው ባለመደሰታቸው መስቀሉን ከጎልጎታ አንስተው ወደ ሌላ ቦታ በመውሰድ ቀብረውት ለ300 ዓመታት ያህል የከተማው ጉድፍና ጥራጊ እየተጣለበት የተቀበረበት ቦታ ኮረብታ እስኪሆን ድረስ ቆየ፡፡ በ4ኛው መ/ክ/ዘመን ለክርስቲያኖች ነፃነት የሚያስብና የሚያስከብር ንጉሥ በሮም ተነሣ፡፡ የንጉሡም ስም ቈስጠንጢኖስ ይባል ነበር፡፡ ይህ ንጉሥ ክርስቲያኖችን ይበልጥ እንዲወድ ያደረገው በጠላቱ በማክሴንዲዩስ (መክስምያኖስ) ላይ በዘመተበት ጊዜ ገና በጕዞ ላይ እያለ ‹‹በዝንቱ ትዕምርተ መስቀል ትመውዕ ፀርከ /በዚህ ምልክት ድል ታደርጋለህ/›› የሚል በመስቀለኛ ቅርፅ የተጻፈ ጽሑፍ በጠፈር ሰማይ አይቶ በመስቀል ምልክት ድል በማድረጉ ነው፡፡
የንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እናት ንግሥት እሌኒ የመስቀሉ ፍቅር ያደረባት ቅድስት እናት ነበረች ቈስጠንጢኖስም በዘመነ መንግሥቱ በትዕምርተ መስቀል ብዙ የድል ሥራ ስለሠራ ለመስቀሉ ታላቅ አክብሮትና አድናቆት ነበረው፡፡ ንግሥት እሌኒም መስቀሉን ለማግኘት ሰው ብትጠይቅ የሚያውቅ አላገኘችም፡፡ በመጨረሻ ግን የመስቀሉ መውጣት የእግዚአብሔር ፈቃድ በመኾኑ ኪራኮስ የሚባል አረጋዊና መቃርስ የሚባል ኤጲስ ቆጶስ አገኘች፡፡ ከእነዚህም አረጋዊው ኪራኮስ ዕድሜው የሸመገለና በእስራኤል ባህልና ደንብ ያደገ ነበር፡፡ እሌኒም እሱን ጠይቃ መስቀሉን ለማግኘት እንዲተባበራት ጠየቀችው እርሱም ሦስት ተራሮችን ጠቆማትና ከሦስት ተራሮች የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ግን በእግዚብሔር ፈቃድ ሱባኤ እንድትይዝ ነገራት፤ ሱባኤም ያዘች፡፡ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ እንዲህ አላት ‹‹አንቺም ሰውም በከንቱ አትድከሙ እንጨት አሰብስበሽ /አስደምረሽ/ ዕጣን አፍስሺበትና በእሳት አያይዥው የዕጣኑ ጢስ ወደ ላይ ወጥቶ ወደ ታች ሲመለስ አቅጣጫውን ተመልክተሽ ጭሽ ያረፈበትን ቦታ አስቆፍሪው›› አላት፡፡ እርሷም መልአኩ እንዳላት እንጨት አሰብስባ ደመራ አስደመረች ዕጣንም አፈሰሰችበት ጭሱም ሰማይ ደርሶ ወደ ምድር ሲመለስ ቦታውን አመለከታት ይህም የሆነው መስከረም 16 ቀን ነው፡፡ እኛ ደመራ ብለን የምናከብረው ይህን አብነት በማድረግ ነው፡፡ ደመራ ማለትም፤ ደመረ፣ ጨመረ፣ አንድ አደረገ፤ ከሚለው የግእዝ ቃል የተወረሰ ሲሆን መቀላቀልን፣ መገናኘትን፣ መሰብሰብን፣ መጣመርን፣ መዋሐድን በአጠቃላይ ሱታፌን፣ አንድነትን እና ኅብረትን ያመለክታል፡፡
#መስቀል_፤ መስከረም 17 ንግሥት እሌኒ በመስከረም 16 ደመራ አስደምራ እጣን አስጢሳ የመስቀሉን ቦታ ካወቀች በኋላ ቁፋሮውን ያስጀመረችበት ዕለት ስለሆነ ነው፡፡ ከቁፋሮውም በኋላ የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ዳግመኛ በእግዚአብሔር ፈቃድ፤ በእሌኒ ተነሳሽነት፤ በረዳቶቿ አጋዥነት መስቀሉ እንደቀድሞ ድውያንን ሲያድን፣ ለምጻምን ሲያነጻ፣ ሽቦችን ሲያቀና፣ ሙታንን ሲያስነሳ፣ የማያምኑትን ወደ ማመን ሲመልስ ነበር፡፡ ዛሬም የክርስቶስ መስቀል በዓለም እያበራ ሕሙማንን እየፈወሰ ይገኛል፡፡
#ተቀጸል_ጽጌ_(#መስከረም_10_/#አፄ_መስቀል_/)፤ መስቀሉ ወደ ሃገራችን የገባባት ዕለት ነው፡፡
#መስከረም_21_፤ መስቀሉ መስከረም 10 ቀን ቀን ወደ ሃገራችን ከገባ በኋላ ‹‹መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ አስቀምጥ›› በተባለው ቃል መሠረት ከብዙ ፍለጋ በኋላ መስከረም 21 በግሸን ደብር ከርቤ ያረፈበት ዕለት ነው /ዝርዝሩን መስከረም 21 ይጠብቁ/፡፡
✤፠ንግስት እሌኒ በመስከረም 16 ቀን ደመራ አስደምራ፤ ፠፠✤✤መስከረም 17 ቁፋሮ አስጀምራ ፠፠፠✤✤✤በመጋቢት 10 ቀን ቁፋሮ ተጠናቅቆ መስቀሉ ተገኝቷል፡፡
(በደብራችን በአ.አ በብቸኝነት ከንግሥት ዘውዲቱ ጀምሮ በደብራችን የመስቀል ክብረ በዓል መስከረም 17ና መጋቢት 10 ይከብራል፤ ላልሰማው ያሰሙ፡፡ እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠቀሙበት ዘንድ ሙሉ ሥርዐተ ማኅሌቱን (ዘመድኀኔዓለምና ዘአደባባይ ብለን) አቅርበንላችኋል፡፡)
እንደ መድኀኔ ዓለም ፈቃድ፤ መስከረም 16ና 17፤ በደመራው (በርጥብ እንጨት ለሚደመረው ደመራ)፣ በዋይዜማው፣ በማኅሌቱ፣ በሰዐታቱ፣ በኪዳኑ፣ በቅዳሴው፣ በዑደተ ታቦተ ሕጉ፣ የመስቀሉን እምነት ግናባራችንን ለመቀባት በቀጨኔ ደብረ ሰላም እንገናኝ፡፡
፠ እኛንም በመስቀሉ ፈዋሽነት ይማረን፤ የመስቀሉን ፍቅር በልባችን ይሳልብን አሜን፡፡
፠ "በወንጌሉ ያመናችሁ፤ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ፡፡"
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
/ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ላይ ባጭሩ የተወሰደ፡፡/
የደመራ በዓል በደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም (ርጥብ ዛፍ በዕለቱ ተቀቈርጦ የሚደመርበት) በአዲስ አበባ በብቸኝነት የመስቀል ታቦት ክብረ በዓል የሚነግሥበት፡፡ ተወልደናሆ ተወልደ መድኅን፤
መድኅንን ያመነ መድኀኔ ዓለምን፡፡
ተወልደናሆ ተወልደ መድኅን፤
ተወልደናሆ ተወልደ መድኅን፡፡
የደመራ በዓል በመስቀል አደባባይ፤ ቀድሞና አሁን፡፡
ከፎቶ ማኅደራችን፤ በመስቀል አደባባይ የመስቀል ደመራ በዓል አቅራቢዎች፤ በ1995፣ በ2004 ና በ2007ዓ.ም.
