Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 396 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 565,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 183 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 396 名订阅者。
根据 28 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 15,过去 24 小时变化为 5,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.32%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.24% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 282 次浏览,首日通常累积 1 576 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 29 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 396
订阅者
+524 小时
+287 天
+1530 天
帖子存档
(#ሥርዐተ_ጸሎት_ወስግደት_ዘዐርብ_ስቅለት_፡፡)
(እየሰገድን የምንላቸውም) ቃላት፡፡
፠ #፩ኛ #ስግደት፤ የወንጌል ምንባብ እንዳበቃ በማስከተል ተግሣጽ ተነቦ እንደተፈጸመ፤
*‹‹#ጸልዩ_በእንተ_ጽንዐ_ዛቲ_መካን›› የሚለውን ካህኑ ሲመራና ዲያቆኑ በየምዕራፉ ቃጭል ሲደውል፤
#ሕዝቡ_እየተቀበሉ_እግዚኦ_ተሣሀለነ (አቤቱ ይቅር በለን) በማለት ፳፪ት ጊዜ በግእዝ፥ በዕዝልና በአራራይ ዜማ እየተዜመ ይሰገዳል፡፡
፠ #፪ኛ #ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹#ለከ_ኃይል_ክብር_ወስብሐት›› የሚለውን ምቅናይ በመሪና በአንሺ ወገን መቀባበል ፮ት ፮ት ጊዜ (በድምሩ ፲፪ ጊዜ) ይበሉ፤ በመጨረሻም በ፲፫ኛው ከ‹‹ለከ ኃይል›› እስከ ‹‹ዕብል በአኰቴት›› ድረስ አንድ ጊዜ በኅብረት ይበሉ፡፡ /ከሆሳዕና ሠርክ እስከ ሰኞ ሰርክ መሪ በቀኝ፤ ተመሪ በግራ ሲሆን፡፡ ከማክሰኞ ሠርክ ጀምሮ ግን መሪ የነበረው ተመሪ፤ ተመሪ የነበረው መሪ ይሆናል፡፡/ እንዲህ እያሉ ይበሉ፤
+ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤
+ አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፤
+ ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤
+ ኃይልየ ወፀወንየ ውእቱ እግዚእየ፤ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኰቴት፤
+ አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ፥ ትምጻእ መንግሥትከ፥ ወይኩን ፈቃድከ፥ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር፥ ሲሳየነ ዘለለዕለትነ፥ ሀበነ ዮም፥ ኅድግ ለነ፥ አበሳነ ወጌጋየነ፥ ከመ ንህነኒ ንኅድግ፥ ለዘአበሰ ለነ፥ ኢታብአነ፥ እግዚኦ ውስተ መንሱት፥ አላ አድኅነነ፥ ወባልሐነ፥ እምኵሉ እኩይ፥ እስመ ዚአከ፥ ይእቲ መንግሥት፥ ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም፡
፠ #፫ኛ #ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹#ለአምላክ_ይደሉ››ን መጀመሪያ በመሪ እየቀደሙ በአንሺ እየተከተሉ አንድ ጊዜ ይዝለቁ፤ በ፪ኛው ክፍል ደግሞ እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይበሉ፡፡ እንዲህ እያሉ ይበሉ፤
+ ለአምላክ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለሥሉስ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለማሕየዊ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለዕበዩ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለዕዘዙ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለመንግሥቱ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለሥልጣኑ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለምኵናኑ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለኢየሱስ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለክርስቶስ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለሕማሙ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለመስቀሉ ይደሉ (ለዐርብ ብቻ)፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
ቀጥሎ ያለውን የመዝጊያ ጸሎት እያዜሙና እየሰገዱ ፫ት ጊዜ መላልሰው ይዝለቁት፡፡
+*+ ለከ ይደሉ ኃይል፥
ወለከ ይደሉ ስብሐት፥
ወለከ ይደሉ አኰቴት፥
+*+ ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም፡፡
፠ #፬ኛ #ስግደት፤ ዜማው አሁንም በቀኝና በግራ በመቀባበል ነው የሚባለው፡፡ በመሪ ወገን እየቀደሙ፤ በአንሺ ወገን ደግሞ እየተከተሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፤ ቀጥለውም በመሪና በተመሪ ወገን እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፡፡
* መሪ፤ ክርስቶስ አምላክነ፥ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ፥ በሕማማቲሁ ቤዘወነ፤
ተመሪ፤ ንሰብሖ፥ ወናልዕል ስሞ ኅቡረ፥ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በብዝኀ (በዕበየ) ሣህሉ፡፡ /በዐርብ፤ ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ/
* #ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ #ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን፥ ኪርያላይሶን፤
ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #እብኖዲ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
* ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ታኦስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ማስያስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
* ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ኢየሱስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ክርስቶስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
* ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #አማኑኤል ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ትስቡጣ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፡፡
**** ኪርያላይሶን የሚለውን ብቻ በመሪ ፳፩ ጊዜ፥ በተመሪ ወገን ፳ ጊዜ ይበሉ፤ ድምሩ ፵፩ ኪርያላይሶን ይኾናል፡፡
፠ የየሰዓቱን (የሌሊት፣ የነግህ፣ የጠዋት 3 ሰዐት፣ የቀትር/6 ሰዐት/፣ የተሰዐት/9ኝ ሰዐት/፣ የሰርክ /11 ሰዐት/፣ የንዋም) መልክአ ሕማማት በዜማ ይደርሳል፡፡
፠ካህኑ ቡራኬ ሰጥቶ፤ ዲያቆኑ ደግሞ ‹‹ሑር በሰላም›› ብሎ ሕዝቡን ያሰናብታል፡፡
፠ ሮማዊው ገዢ ጲላጦስ ጌታችንን በዳዊት ከተማ በጽዮን በቀራንዮ መካከል እንዲሰቀል አሳልፎ ከሰጠና ካሰቀለው በኋላ፤ ከመስቀሉ በላይ የሚጻፈውን የተለመደ የክስ ጽሕፈት (ሮማውያን በስቅላት የሚቀጡትን ሰው ለሞት ያበቃው ክስ ምን እንደሆነ በሰሌዳ ጽፈው በመስቀሉ ላይ ከፍ አድርገው የማሳየት ልማድ ነበራቸው፤ በዚያ ሥፍራ የሚያልፉ ሰዎችም ሁሉ የክሱን ጽሕፈት እያነበቡ ስለ ተሰቀለው ሰው ማንነትና ወንጀል ይረዱ ነበርና) ከቤቱ ቁጭ ብሎ ሲያስጨንቁት ያረፈዱትን የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ለመበቀል ነበር በሰሌዳ ላይ ያረቀቀው፡፡፠ የተጻፈውን መግለጫ የሚያነቡትም ‹አይሁድ ነጻ የሚያወጣቸውን የገዛ ንጉሣቸውን ሰቀሉ› ብለው እንዲሳለቁባቸው፤ ክርስቶስን እንደ ክፉ ወንጀለኛ እንዲታይና እንዲዋረድ ፈልገው ላሰቀሉት አይሁድ ለወደፊቱም ቢሆን ለወሬ እንዳይመቻቸው፥ ክርስቶስን እንደማይጠቅምና እንደ ክፉ ሰው አድርጎ የሚወቅሰው ሰው ኃይል እንዲያጣ የሚያደርግ ነበር፡፡ በዚህም ቅዱስ ዳዊት የተነበየው ትንቢት ‹‹አንሰ ተሰየምኩ ንጉሠ በላዕሌሆሙ ፤ በጽዮን በደብረ መቅደሱ›› (እኔ ግን በላያቸው ላይ ንጉሥ ሆኜ ተሾምሁ ፤ በቅድስናው ተራራ በጽዮን) /መዝ. ፪፥፮/ ያለው ተፈጸመ፡፡
፠ ‹የአይሁድ ንጉሥ ነኝ በማለቱ የተሰቀለው ኢየሱስ› ብሎ ሊጽፍ ሲገባው (መንፈስ ቅዱስ አፉን ከፍቶ ፊቱን ጸፍቶ) ‹ኢየሱስ ናዝራዊው የአይሁድ ንጉሥ› ብሎ ጻፈ፤ ይህም የክስ ጽሕፈት ሳይሆን የአንድን ድል አድራጊ ንጉሥ ማንነት የሚያስረዳ መግለጫ፥ ለጌታችን የተሰጠ የክብር ስም አደረገው፡፡ በገዛ ንጉሣቸው ላይ እንደተነሡ አድርጎ በማሳየት የሁሉንም አፍ ዘጋው፡፡ በዚያን ወቅት በስፋት በሚነገሩት በሦስት ቋንቋዎችም #በዕብራይስጥ፣ #በግሪክና #በሮማይስጥ ‹ኢየሱስ ናዝራዊ የአይሁድ ንጉሥ› ብሎ ጻፈ፡፡ በወታደሮቹ አማካይነትም ሰሌዳው ወደ ቀራንዮ ተወስዶ ሁሉም ሰው እንዲያየው ከጌታችን ከራሱ በላይ ተሰቀለ፡፡ ይህንንም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ወጸሐፈ ጲላጦስ መጽሐፈ ወይብል መጽሐፉ ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ፡፡ (ጲላጦስ መጽሐፍን ጻፈ ፤ መጽሐፉም ኢየሱስ ናዝራዊ የአይሁድ ንጉሥ ይላል፡፡››) ብሎ በድርሰቱ ገልጾታል፡፡
፠ ‹‹ኢየሱስ የተሰቀለበት ሥፍራ ለከተማ ቅርብ ነበርና ከአይሁድ ብዙዎች ይህንን ጽሕፈት አነበቡት›› /ዮሐ. ፲፱፥፳/
፠ ከመስቀሉ ሥር አንጋጥጠው ያነበቡት የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን በንዴት እየተብከነከኑ ከቀራንዮ ወደ ጲላጦስ ግቢ በብስጭት እየሮጡ መጡ፡፡ የሠራውን ሥራ የሚያውቀው ጲላጦስም የሚጠብቀው ነገር ነበርና ሊቃነ ካህናቱን አነጋገራቸው፡፡ እነርሱም ‹‹እርሱ የአይሁድ ንጉሥ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ›› አሉት፡፡ ጲላጦስ ግን ያቃጠሉትን ሊቃነ ካህናት አንጀት የሚያሳርርና የተዘጋጀበት የሚመስል አጭር መልስ መለሰላቸው ‹‹#የጻፍሁትን_ጽፌያለሁ::››
፠ አይሁድ ይህንን ጽሕፈት ሲያዩ በንዴት ተንገበገቡ ፤ ተሰቅሎም እንኳን የካህናት አለቆች ይቀኑበት ነበርና፡፡ ‹‹እናንተ እንደምትሉት ክርስቶስ ሙትና ደካማ ከሆነ ይህ ጽሕፈት ሊጎዳችሁ አይችልም፤ የክርስቶስ ስሙም ሊረሳ ይችላል፡፡ ‹ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ› ተብሎ መጻፉ ለምን ያስፈራችኋል?›› /ይላቸዋል ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/
*፠* በቤተ ልሔም ሲወለድ ‹‹የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ›› እያሉ የምሥራቅ ነገሥታት መሰከሩለት፤
*፠* በቀራንዮ ሲሰቀል ‹‹የተሰቀለው የአይሁድ ንጉሥ›› ብሎ የምዕራብ ንጉሥ እንደራሴ ጲላጦስ ደግሞ መሰከረለት፡፡
*፠* ነቢዩ ዳዊት ‹‹እምሥራቀ ፀሐይ እስከነ ዐረብ፥ ይትአኰት ስሙ ለእግዚአብሔር›› (የእግዚአብሔር ስሙ ከፀሐይ መውጫ (ምሥራቅ) እስከ መግቢያው (ምዕራብ) ድረስ ይመስገን፤) ብሎ የዘመረለት አምላካችን ከምሥራቅ ብቻ ሳይሆን ከምዕራብም ‹የአይሁድ ንጉሥ› ተብሎ ተመሰከረለት፡፡
፠ ጌታችን በምድር ላይ ባስተማረበት ወቅት ያስተማረው በአንድ ቋንቋ ብቻ ተወስኖ ነበር፤ ‹‹በሰናዖር ሜዳ ቋንቋዎችን የደባለቀውና ብዙ ቋንቋዎች እንዲናገሩ ያደረገው እርሱ ሆኖ ሳለ ስለ ትሕትናው በአንዲት ቋንቋ ብቻ አስተማረ›› /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ/፡፡ ጲላጦስ ደግሞ ወንጌላውያን ወንጌላቸውን ከመጻፋቸው ቀድሞ በሦስት ቋንቋዎች ጽሕፈቱን መጻፉ (ወንጌልን መስበኩ) የክርስቶስ መንግሥት የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በቋንቋ የማትገደብ በሕዝብና በአሕዛብ ላይ የምትጸና መሆኗን ያሳያል፡፡
፠፠ በጥቅሉ ‹ኢ.ና.ን.አ.› ማለት፤ /ዮሐ. ፲፱/
‹‹የምስጉኖችና የታማኞች ንጉሥ የሆነው መድኃኒት የተለየና የተቀደሰ አክሊልን የተቀዳጀ ነው፡፡›› የሚል ነው፡፡
ለቡ ፤ ልዩ ማስታወሻ፤ ዛሬም በአንገታችን ላይ የምናስረው መስቀል ከተለያዩ ቦታዎት ተቀርጾ ሲመጣ ‹‹ኢ.ና.ን.አ ›› ሊጻፍበት እንጂ የራችን ስሚ ሊጻፍበጽ ፈጽሞ አይገባም ፡፡
ꔰ ወስብሐት ለእግዚአብሔርꔰ
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ ::
#share
Contact: https://t.me/finotehiwot1927
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w,
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
Telegram https://t.me/medihanaelem
#ኢ. #ና. #ን. #አ. ‹‹#የጻፍሁትን_ጽፌያለሁ::››
#ኢ
፩ኛ) #፠#ኢየሱስ_፤
፠ አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ከሥጋ ማርያም ጋር ተዋሕዶ፤ ከሁለት አካል አንድ አካል፥ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሆኖ፤ በዘመነ ሥጋዌ ከተጠራባቸው ስሞች መካከል፤ ኢየሱስ፥ ክርስቶስ፥ አማኑኤል፥ መድኀኔ ዓለም፥ መድኅን፥ የሰው ልጅ፥ የእግዚአብሔር ልጅ፥ ቃል፥ እግዚአብሔር ወልድ፥ አንድዬ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ጌታ፥ … የሚሉ ዋነኞቹ ናቸው፡፡
፠ ኢየሱስና ክርስቶስ የሚሉት ስሞች ከጥንት ጀምሮ (የሰው አእምሮ ገና ያልበሰለ፤ ክፉዎች አይሁድም ነገሩን ለፌዝ፥ ለቧልት ያውሉት ነበርና፤ ምንም እንኳን በግልጽ ባየገለጹም)፤ በነቢያት የተነገሩና በመላእክት የተበሠሩ፤ የጌታን አምላክነት የሚያሳዩ፤ የጌታን አዳኝነት የሚያመለክቱ ስሞች ናቸው፤ /መ.አውሳብዮስ/፡፡ ለምሳሌ፤ ልበ አምላክ ዳዊት ‹‹እምቅድመ ፀሐይ ሀሎ ስሙ፤ ስሙ ከፀሐይ በፊት ነበረ፡፡›› /መዝ 71÷17/ ብሏል፤ እንዲሁም ነቢዩ ሙሴ በምሳሌ ጠርቶታል፤ የሊቀ ካህንነቱ አገልግሎት ሊቀ ካህኑ የክብርና የከፍታ ምልክት፣ የነዌ ልጅ ኢያሱም የአዳኛችንን ምሳሌ ተሸክሞ ነበር፡፡›› /ዘጸ. 25፥40፣ ዘሌ. 4፥5፡16፤ 6፥22/ ብሏል ይህንንም የመልክአ ኢየሱስ ደራሲም ‹‹አክሊለ ስምከ እንዘ ይትቄጸል በርእሱ፤ አኅጉረ ፀር ወረሰ ኢያሱ፡፡›› (የስምህን አክሊል በራሱ ላይ አድርጎ የጠላትን ሀገሮች ኢያሱ ወርሷል) ብሎ አመስጥሮታል፡፡
• ይህንን ከዓለም በፊት የነበረውን ስሙን ከሰማይ ተቀብሎ ለእመቤታችን እንዲናገር የተላከው መልአክ፤ መጋቤ ሐዲስ ቅዱስ ገብርኤል ሲሆን ‹‹ስሙን የመሰየም›› ሥልጣን የተሰጣት ደግሞ እመቤታችን ናት፡፡ ˝ኢየሱስ ትይዋለሽ˝ /ሉቃ 1÷31/
፠ #ኢየሱስ_ማለትም(ትርጓሜውም)፤
ሀ) መድኃኒተ ሥጋ ፥ መድኃኒተ ነፍስ ማለት ነው፡፡
* በዕብራይስጥ የሹኣ፥ ኢያሱ ወይም «ያሕዌ መድኃኒት ነው» የሚል ትርጉም አለው።
፠ እርግጥ ነው፥ በትንቢት፥ በምሳሌና በጥላ ቀድሞ ለተነሡት « አዳኞች» ኢያሱዎች ተሰጥቷል። (ለምሳሌ ዘካርያስ 3፥1 ላይ ሊቀ ካህናቱን ኢያሱን ያስታውሷል።) ሆኖም ግን እነዚህ « አዳኞች» ያዳኑት የእግዚአብሔርን ሕዝብ ነው፡፡ ያዳኑትም የእግዚአብሔርን ኃይልና ረድኤት አጋዥ በማድረግ ነው፤ ያዳኑት(የታደጉትም) ከምድራዊ ጠላቶቻቸው ስለሆነ ማዳናቸው ውሱን ነው፡፡
*****አማናዊው ኢያሱ አዳኛችን ግን ያዳነው « ሕዝቡን» (የራሱን ሕዝብ) ነው። ያዳነውም እግዚአብሔር ተጠቅሞበት ሳይሆን ራሱ እግዚአብሔር ስለሆነ መድኃኒት ሆኖ ነው። ሕዝቡን ያዳነውም «ከኃጢአታቸው» ነው። ይህ አነጋገር የሚገባው ለእግዚአብሔር ብቻ ነው። በመሆኑም እንደቀድሞዎቹ እግዚአብሔር በምሳሌና በጥላ ሳይሆን ራሱ በመካከላችን በማደሩ ‹‹አማኑኤል እግዚአብሔር ከእኛ ጋር፡፡›› እንደ ሆነና በዚህም የነቢዩ የኢሳይያስ ትንቢት ፍጻሜ እንዳገኘ ነበር የእግዚአብሔር መልአክ የገለጠው። ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ማዳኑም የአምላክነቱ መገለጫ ነው።
ለ) ሕዝቡን በኃጢአታቸው ከመጣባቸው ፍዳ የሚያድናቸው መድኀኒት ማለት ነው፡፡ /ማቴ 1፥21፣ ተረፈ ኤርምያስ) (ዳግመኛም ወገኖቹን ከኃጢአታቸው የሚያድናቸው ኢየሱስ ይባላል፡፡ /ቅ.ኤፍሬም/፡፡) (‹‹ኢየሱስ ስዱድ ተስፋሆሙ ለስዱዳን›› /ሰቈቃወ ድንግል/)
ሐ) ኃጢአታችንን የሚያስተሠርይልን ማለት ነው፤ ‹‹አመ ይእኅዝዎ ለኢየሱስ ፀሐይ ጸልመ›› /ቅዱስ ያሬድ፥ ድጓ/
መ) ዳግማይ አዳም ማለት ነው (የኢየሱስ የስሙ ቊጥር ከአዳም የስም ቊጥር ጋር የተባበረ ነውና)
*ኢየሱስ፡- አ=40, የ=90, ሰ=7, ሰ=7 ድምር =144፤
*አዳም፡-አ=40, ደ=100, መ=4 ድምር =144
*ዳግማይ አዳም የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ወደ ኤዶም ገነት አገባው ማለቱ
ኤዶም፡-አ=40, ደ=100, መ=4 ድምር =144
#ና.
፪ኛ) #፠#ናዝራዊ_፤ ከናዝሬት የመጣ /ማቴ 2፥ 23/፤ በሌላም ትርጕምም ቸር፥ እረኛ፣ በዕብራይስጥ ደግሞ የተለየ ፣ አክሊል የተቀዳጀ ፣ የተቀደሰ ማለት ነው፡፡
፠ ‹‹ኢየሱስ ናዝራዊ አምላኮሙ ለናዝራውያን›› እንዲል /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፤ መጽሐፈ ምሥጢር/
፠ ማቴ. 2÷23 «በነቢያት ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጻም ዘንድ ናዝሬት ወደ ምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ፡፡››
፠ ትንቢቱ (በማቴዎስ ወንጌል የተገለጠው) ልጄ እንደ ሶምሶን ናዝራዊ ይባላል የሚል ነው፤ ነገር ግን በ66ቱም ሆነ በ81ዱ መጻሕፍት አይገኝም፤ መጽሐፉ በምርኮ ጊዜ ጠፍቷል፤ ይህም ከ66ቱ መጻሕፍት ሌላ መጽሐፍ የለም ለሚሉ ወገኖች ማስረጃ እንደሆነ አስተውል፡፡
*፠* በመጽሐፍ ቅዱስ ስማቸው የተጠቀሰው ናዝራውያን 2ት ናቸው እነርሱም ሶምሶንና ጌታችን፤ በምን ይመሳሰላሉ ቢሉ::
**ሶምሶን በተናቀች በአህያ መንጋጋ ጠላቶቹን እንዳጠፋ፤ ጌታም አይሁድ፣ አጋንንት፣ መናፍቃን በናቁት ሞቱ ሞትን አጥፍቷል፡፡ /መሳ. 15÷9-19/
**ሶምሶን በሕይወተ ሥጋ ካጠፋቸው አሕዛብ ይልቅ በሞቱ ያጠፋቸው ይበዛሉ፡፡ ጌታም በሕይወተ ሥጋ ሳለ ካጠፋቸው አጋንንት ይልቅ በሞቱ ያጠፋቸው ይበዛሉ፡፡ /ምሳ. 16÷23-31/
#ና.
፫ኛ) #፠#ንጉሥ_፤ አፄ፣ ባለዘውድ፣ ሹም፣ አለቃ፣ ማለት ነው፡፡ /ንጉሦሙ ለእስራኤል ውእቱ ይብሉ ሆሳዕና በአርያም እንዲል፡፡/
#አ
፬ኛ) #፠#አይሁድ_፤ ማለት የታመኑ፣ ምስጉኖች፣ ምዕመናን ማለት ነው፡፡
፠ አይሁድ የሚከው ቃል እስከ ባባሎን ምርኮ ድረስ ከ12ቱ ነገደ ያዕቆብ (እስራኤል) የይሁዳ ብቻ ነበረ፡፡ ከምርኮ በኋላ እስከ ክርስቶስ ድረስ ግን ለእስራኤል ሁሉ (ለ12ቱም ነገድ) መጠሪያ ሆኗል፡፡ /ዘፍ. 29፥ 35/
#የአይሁድ_ንጉሥ (#ማዕከላዊ_ስም)
፠ ሰብአ ሰገል ስም ማዕከላዊ (የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ) እያሉ ነው ለጌታ መብዓ ይዘው የመጡት፤ ስለምንድነው ቢሉ?
* አምላክ (ስም ላዕላዊ) እያሉ ያልመጡበት፤ ሰማይና ምድር የማይችለው ምን ወስኖት ምን ችሎት ነው ብለው እንዳይዘባበቱባቸው፡፡ አንድም ትንቢት የተነገረልን ሱባዔ የተቈጠረልን እኛ እያለን እንዴት ለእነርሱ ተገለጠላቸው ብለው እንዳይዘባበቱባቸው፤ አንድም አሕዛብ ናቸው በየት አውቀውት ብለው እንዳዘብቱባቸው ነው፡፡
* የተወለደው ሕፃን (ስም ታህታዊ) እያሉ ያልመጡት፤ በእስራኤል ሃገር በአንድ ቀን ውስጥ ብዙ ሕፃናት ተወልደው ብዙ ሕፃናት ይሞታሉ፤ ስንቱን እናውቅላችኋለው ባሏቸው ነበርና፡፡
#ጸሎተ ሐሙስ ፣ #ሕጽበተ እግር ፣ #የምሥጢር ቀን
† በዚህች ዕለት ጌታችን በአልአዛር ቤት ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ ተቀመጡ፡፡ ከኅብስቱ ከፍሎ አማናዊ ሥጋ፤ ከወይኑ ከፍሎ አማናዊ ደም አድርጎ ባርኮ ቀድሶ አክብሮ እንካችሁ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ፡፡
በቃል ያስተማረውን ትምህርት በተግባር እንዴት መፈጸም እንዳለበት ያስተማረበት ዕለት በመሆኑ ይህ ዕለት #የምሥጢር_ቀንም ይባላል፡
፡
†በመብል ያጣነውን ክብር በመብል የተመለሰልን ዕለት በመሆኑ ጌታችን በሰጠን ሥልጣን ለኃጢአትና ለዲያብሎስ ባርያ ሆኖ መኖር በማብቃቱ #የነጻነት_ሐሙስም ጭምር ይባላል ይባላል፡፡
† በዚህ ዕለትም ሌላ የተፈጸመው ተግባር #ሕጽበተ_እግር ነው፡፡ ወንጌሉ «፡ተነሣ፡ልብሱንም፡አኖረ፥ማበሻም፡ጨርቅ፡ወስዶ፡ታጠቀ፤
፤በዃላም፡በመታጠቢያው፡ውሃ፡ጨመረ፥የደቀ፡መዛሙርቱንም፡እግር፡ሊያጥብና፡በታጠቀበትም፡ማበሻ፡ጨርቅ፡ሊያ ብስ፡ዠመረ።
፤ወደ፡ስምዖን፡ጴጥሮስም፡መጣ፤ርሱም፦ጌታ፡ሆይ፥አንተ፡የእኔን፡እግር፡ታጥባለኽን፧አለው።
፤ኢየሱስም፡መልሶ፦እኔ፡የማደርገውን፡አንተ፡አኹን፡አታውቅም፥በዃላ፡ግን፡ታስተውለዋለኽ፡አለው።
፤ጴጥሮስም፦የእኔን፡እግር፡ለዘለዓለም፡አታጥብም፡አለው።ኢየሱስም፦ካላጠብኹኽ፥ከእኔ፡ጋራ፡ዕድል፡የለኽም ፡ብሎ፡መለሰለት።
፤ስምዖን፡ጴጥሮስም፦ጌታ፡ሆይ፥እጄንና፡ራሴን፡ደግሞ፡እንጂ፡እግሬን፡ብቻ፡አይደለም፡አለው።
፤ኢየሱስም፦የታጠበ፡እግሩን፡ከመታጠብ፡በቀር፡ሌላ፡አያስፈልገውም፥ዅለንተናው፡ግን፡ንጹሕ፡ነው፤እናንተ ም፡ንጹሓን፡ናችኹ፥ነገር፡ግን፥ዅላችኹ፡አይደላችኹም፡አለው።
፤አሳልፎ፡የሚሰጠውን፡ያውቅ፡ነበርና፤ስለዚህ፦ዅላችኹ፡ንጹሓን፡አይደላችኹም፡አለው።
፤እግራቸውንም፡ዐጥቦ፡ልብሱንም፡አንሥቶ፡ዳግመኛ፡ተቀመጠ፥እንዲህም፡አላቸው፦ያደረግኹላችኹን፡ታስተውላ ላችኹን፧ >>ዮሐ 13 ፥ 1-10
በቃል ያስተማረውን ትኅትና በተግባር ለደቀ መዛሙርቱ አስተምሮል፡፡ “ከእኔ ተማሩ እኔ የዋሕ በልቤም ትሁት ነኝና” እንዲል /ማቴ. 11፥29/፡፡ ይህንም ሲፈጽም አሳልፎ ሊሰጠው ያለውን የአስቆሮቱን ይሁዳ አለየውም፡፡
† በዚህ ዕለት ይሁዳ አሳልፎ እንደሚሰጠው ተናገረ በዚህም ማንነቱን ጭምር ለይቶ ነገራቸው “እጁን በወጭቱ ያጠለቀው እኔን አሳልፎ የሚሰጥ ነው”
† የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ፤ ፍጹም ሰው መሆኑን ለማጠየቅ ለአርአያነት ጠላቶቹ መጥተው እኪይዙት ድረስ ሲጸልይ ማደሩ #ጸሎተ_ሐሙስ ለመባሉ ምክንያት ነው ፤ /ማቴ.26፥36-46፣ ዮሐ.17/በዚች ዕለት ጌታችን በአልአዛር ቤት ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ ተቀመጡ፡፡ ከኅብስቱ ከፍሎ አማናዊ ሥጋ፤ ከወይኑ ከፍሎ አማናዊ ደም አድርጎ ባርኮ ቀድሶ አክብሮ እንካችሁ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ፡፡
በቃል ያስተማረውን ትምህርት በተግባር እንዴት መፈጸም እንዳለበት ያስተማረበት ዕለት በመሆኑ ይህ ዕለት የምሥጢር ቀንም ይባላል፡፡
በመብል ያጣውን ክብር በመብል የመለሰበት ዕለት በመሆኑ ጌታችን በሰጠን ሥልጣን ለኃጢአትና ለዲያብሎስ ባርያ ሆኖ መኖር በማብቃቱ #የነጻነት_ሐሙስም ጭምር ይባላል ይባላል፡፡
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ ::
#share
Contact: https://t.me/finotehiwot1927
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w,
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
በየአመቱ በሚካሄደው የሰንበት ትቤቶች +የሕፃናቶች) የሆሳዕና ኅብረት መርሃ ግብር ላይ በተሄደው
1. የ ሥዕል ውድድር ላይ ፤ 1ኛ በመውጣት የሲት.ቤታችን ተማሪ መላኩ ኃይሉ እንዲሁም I
2. በጥያቄና መልስ ውድድር ላይ 4ኛ በመውጣት የሰ.ት.ቤታች ተማሪ ሶልያና ተስፋ ፤ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡
የዚህ አመት የሆሳዕና ኅብረት ተረኛ የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤክ ሰንበት ትምሕርት ቤት ነበር፡፡ በዕለቱም በረካታ መርኀ ግብሮች ተካሄደዋል ፡፡
Finotehiwotsundayschool.com
በየአመቱ በሚካሄደው የሰንበት ትቤቶች +የሕፃናቶች) የሆሳዕና ኅብረት መርሃ ግብር ላይ በተሄደው
1. የ ሥዕል ውድድር ላይ ፤ 1ኛ በመውጣት የሲት.ቤታችን ተማሪ መላኩ ኃይሉ እንዲሁም I
2. በጥያቄና መልስ ውድድር ላይ 4ኛ በመውጣት የሰ.ት.ቤታች ተማሪ ሶልያና ተስፋ ፤ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡
የዚህ አመት የሆሳዕና ኅብረት ተረኛ የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤክ ሰንበት ትምሕርት ቤት ነበር፡፡ በዕለቱም በረካታ መርኀ ግብሮች ተካሄደዋል ፡፡
ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ፥ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፥ ሆሣዕና በአርያም›› /መዝ. 8፥2፣ ሉቃ. 19፥38/
Finotehiwotsundayschool.com
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
