Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 336 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 639,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 190 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 336 名订阅者。
根据 16 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -77,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.04%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.47% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 380 次浏览,首日通常累积 1 605 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 23。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 17 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 336
订阅者
+124 小时
-97 天
-7730 天
帖子存档
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
#ታላቁ_ሰማዕት_ቅዱስ_መርቆሬዎስ፤ የወላጆቹ አገር አስሊጥ የምትባል ስትኾን እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው፡፡ አያቱና አባቱ ሥራቸው አውሬ ማደን ስለነበር አንድ ቀን እንደልማዳቸው አውሬ ሲያድኑ ከገጸ
ከለባት (ውሻ ) ወገን የሆኑ ሁለት ወንዶች አግኝተዋቸው የመርቆሬዎስን አያት በሉት፡፡ አባቱንም ሊበሉት ሲሉ የታዘዘ መልአክ ከለከላቸው፡፡ ዙሪያቸውንም በእሳት አጥሮ ከበባቸው፡፡ እነርሱም በተቸገሩ ጊዜ ለመርቆሬዎስ አባት ሰገዱለት፡፡
በዚያን ጊዜም እግዚአብሔር ፍጥረታቸውን ወደገራምነት ለወጠውና እንደበጎች የዋሆች ሆነው አብረውት ወደ መንደር ገቡ፡፡
ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ ተወለደና ስሙ ፒሉፓዴር ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸውም በእርሱ ዘንድ ብዙ ዘመናት ኖሩ፡፡ ከዚህም በኋላ ክርስቲያኖች ሆኑ፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም ወላጆች አስቀድመው አረማውያን ነበሩና
የክርስትና ጥምቀትን በጸጋ ተቀበሉ፡፡ አባቱን ኖህ እናቱንም ታቦት ብለው ሰየሟቸው፡፡ ቀድሞ ፒሉፓዴር የነበረውም ስሙ ተለውጦ መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸው ግን መልአኩ በተገለጠላቸው ጊዜ እንደነገራቸው ለቅዱስ
መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባትና የውሻ መልክ ያላቸውን ዜናቸውን ሲሰማ ወታደሮቹን ልኮ በፊቱ አቆማቸው፡፡ እግዚአብሔርም የቀድሞ ፍጥረታቸውን መልሶላቸው አራዊት አደረጋቸውና
ንጉሡን እጅግ አስፈሩት፡፡ ንጉሡም የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት የአራዊት ተፈጥሯቸውን ያርቅለት ዘንድ ለመነው፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም አባት በለመነ ጊዜ ተፈጥሯቸውን መልሶላቸው ገራሞች ሆኑ፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ገዥና
የሠራዊቱ አለቃ አድርጎ ሾመው፡፡ የውሻ ፊት ያላቸውም አብረው ያገለግሉት ስለነበር ሁሉም ይፈራው ነበር፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ወደ ጦርነት ከላከው በኋላ ሳይመለስ ስለቀረ ሚስቱን ሊያገባት አሰበ፡፡ የመርቆሬዎስ አባትም
የመርዶሳውያን አገሮች ሁሉ ገዢ በነበረው ንጉሥ ተይዞ ቢማረክም ገዥው ክርስቲያን መሆኑን አይቶ አከበረው፡፡ ቆይቶም በሀገሩ ላይ ሾመው፡፡ ሚስቱም ጠፍታ ከሀገሯ ወጥታ ሄዳ ስለነበር ከባሏ ተገናኝተው በዚያው መኖር ጀመሩ፡፡
መርቆሬዎስም አባቱና እናቱ ከሞቱ በኋላ ንጉሡ በአባቱ ፈንታ በመርዶሳውያን አገር ላይ ሾመው፡፡ መርቆሬዎስ መኰንንነት በተሾመም ጊዜ ገጸ ከለባቱ አብረውት ነበሩ፡፡ ለመዋጋትም በወጣ ጊዜ የቀድሞው የአራዊት የሆነ ተፈጥሯቸውን
እግዚአብሔር ይመልስለት ስለነበር ማንም አይቋቋመውም ነበር፡፡ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠውና ዜናው በሁሉም ሀገሮች ተሰማ፡፡ በሮሜ ሀገር ጣዖትን የሚያመልከው ዳኬዎስ የተባለውም ንጉሥ የበርበር ሰዎች
ጋር ጦርነት ሊገጥም በወጣ ጊዜ እጅግ ሲበዙበት ፈራ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በጦሩ መሀል የተሳለ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔርን መልአክ ስላየ ንጉሡን እግዚአብሔር ያጠፋቸዋልና አትፍራ›› አለው፡፡ መልአኩም ሰይፉን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰጠውና
‹‹ጦርነቱን ድል ባደረግህ ጊዜ እግዚአብሔርን አስበው›› አለው፡፡
ጦርነቱን ድል አድርጎ ሲጨርስም መልአኩ ድጋሚ ተገልጦለት ‹‹ለምን የፈጣሪህን ስም መጥራት እረሳህ?›› አለው፡፡ ከጦርነቱም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን አደረገ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በዚያ ስላልተገኘ ለጣዖታቱ
ዕጣን በማሳረጉ እንዳልተባበረ ንጉሡ ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስመጣው፡፡ ንጉሡም ‹‹ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም?›› ባለው ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ ትጥቁንና ልብሱን አውልቆ ከወረወረለት በኋላ ‹‹ክብር ይግባውና አምላኬ ኢየሱስ
ክርስቶስን ፈጽሞ አልክደውም፣ ለረከሱ ጣዖቶችህም አልሰግድም›› አለው፡፡ ንጉሡም ተናዶ ልዩ ልዩ በሆኑ ሥቃዮችም እጅግ አሠቃየው፡፡ ንጉሡም ስለ መርቆሬዎስ ብለው የአገሩ ሰዎች እንዳይነሱበት ፈርቶ በብረት ችንካር ቸንክሮ የቀጰዶቅያና
የእስያ ክፍል ወደሆነች ወደ ቂሳርያ ከደብዳቤ ጋር ላከው፡፡ በዚያም እጅግ ካሠቃዩት በኋላ ንጉሡ ዳኬዎስ እንዳዘዘ ኅዳር 25 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ፡፡ የሕይወትንም አክሊል ተቀዳጀ፡፡ በዓለሙ ሁሉ አብያተ
ክርስቲያናት ታነጹለት፡፡ እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም አደረገ፡፡
✤ከብዙ ተአምራቱም አንዱ የቂሳርያውን ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስን እንዲሁም ጎርጎርዮስን ረድቶ ከሃዲውን ዑልያኖስን የገደለበት ነው፡፡ ዑልያኖስ ነግሦ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክዶ ጣዖታትን ማምለክና ክርስቲያኖችን ማሠቃየት ጀመረ፡፡ የቂሳርያው
ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስም አስተምሮ ሊመልሰው ወደ ንጉሡ ቢመጣ ክብር ይግባውና ዑልያኖስ ጌታችንን ሰድቦ ባስልዮስንም አሰረው፡፡ ባስልዮስም በእሥር ቤት ሳለ በቅዱስ መርቆሬዎስ ሥዕል ፊት ጸለየ፡፡ ሥዕሉም ወዲያው ተሰወረው፡፡ ያንጊዜም
ወደ ከሃዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ዘንድ ሄዶ በጦር ወግቶ ገደለውና ወዲያው ወደ ቦታው ተመለሰ፡፡ በስዕሉ ላይ ያለው የቅዱስ መርቆሬዎስ ይዞ ከተሳለው ጦር ጫፍ ላይም ደም ይንጠፋጠፍ ነበር፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ከሃዲውን ንጉሥ እንደገደለው
ዐውቆ ‹‹የክርስቶስ ምስክር ጌታዬ ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን?›› አለው፡፡ ሥዕሉም ያን ጊዜ አዎን እንደሚል ራሱን ዘንበል አደረገ፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ደስ ብሎት እግዚአብሔርን አመሰገነ፡፡
✤ሌላው ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በተአምሩ ከእስልምና እምነት መልሶ ክርስቲያን ያደረገው አንድ እስላም ሰው አለ፡፡ ይኸውም የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያኑ በተሠራችበት በምስር አገር የሚኖር ከመሳፍንት ወገን የሆነ ወጣት ነበረ፡፡
ከብዙ ሰዎችም ጋር ሆኖ ወደ መሐመድ መቃብር ለመሄድ እንዳሰበ ለአባቱ ሲነግረው ስንቅ ሰንቀው በሰላም ወደ መካ መዲና ሸኙት፡፡ መካ ደርሰውም ሥራቸውም ፈጽመው ወደቤታቸው እየተመለሱ ሰባት ቀን ተጓዙ፡፡ በሌሊትም ሲጓዙ ስለ ሥጋዊ
ግዳጁ ያ እስላም ወጣት ከግመል ላይ ወርዶ ለመጸዳዳት ዘወር አለ፡፡ እነርሱም አብሯቸው የሚጓዝ መስሏቸው ስለነበር ባልንጀሮቹም በበረሃው ውስጥ ትተውት ሄዱ፡፡ እርሱም ወዴት እንደሚሄድ ስላላወቀ አራዊትም እንዳይበሉት ፈርቶ እጅግ ደነገጠ፡፡
በዚያም ጊዜ በምስር አገር በአባቱ ቤት አቅራቢያ ያለች የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስን ቤተ ክርስቲያን አስታውሶ በልቡ ቅዱስ መርቆሬዎስን እንዲያድነው በመለመን ተሳለ፡፡ ወዲያውም ቅዱስ መርቆሬዎስ በፈረሱ ተቀምጦ ወደ እርሱ መጣና
‹‹ከወዴት ነህ? ከዚህ በረሃ ውስጥስ እንዴት ጠፋህ?›› አለው፡፡ ወጣቱ እስላምም የሆነውን ነገረው፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም ‹‹ና በኋላዬ በፈረሱ ላይ ተፈናጠጥ›› አለውና በአየር ላይ እየበረረ በምስር አገር ወዳለች የቅዱስ መርቆሬዎስ
ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ዐይን ጥቅሻ አደረሰውና እንደተዘጋች በውስጧ አስገባውና ከእርሱ ተሰወረ፡፡ ይህም ወጣት በኋላ አምኖ ተጠምቆ ብዙ ሰማዕትነት ተቀብሏል፡፡ ገዳምም ገብቶ ብዙ ከተጋደለ በኋላ እንደገና ወደ አገሩ ተመልሶ ብዙዎችን ወደ ክርስትና አምጥቷል፡፡ በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም ቤተ ክርስቲያን አሠርቶ አበ ምኔትም ሆኖ ብዙ መነኰሳትን አፍርቷል፡/
#ስዕሉ_የሚያሸበሽበው_የቅዱስ_መርቆሬዎስ_ስዕል_፤ በጋሹ አምባ አርማንያ ቅዱስ መርቆሬዎስ (ሰሜን ሸዋ፤ ደብረ ሲና) የሚገኝ፡፡
መርቆሬዎስ መርቆሬዎስ ገባሬ ተአምር፡፡
#ቪዲዮውን_ሁሉም_ሊያየው_የሚገባ__ተዓምር፡፡ የቻላችሁ በአካል ሰሜን ሸዋ (ቅርብ የትራንስፖርት መንገድ ነው) ሂዳችሁ፤ ያልቻላችሁ ቪዲዮውን እንድታዩት አቅርበንላችኋል፤ ዛሬም ድረስ ተዓምር አድራጊውና በበዓለ መርቆሬዎስ እለት የሚያሸበሽበው የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል፤ (ቀድሞም ባስልዮስና ጎርጎርዮስ ዑልያኖስ የሚባል ጠላት ሲመጣባቸው ወደ ቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ጸለዩ፤ ቅዱስ መርቆሬዎስም ከስዕሉ ላይ ወጥቶ ዑልያኖስን ገደለላቸው)፤ ዛሬም ድረስ የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ተዓምራትን ያደርጋል፡፡ በጻድቃን ሰማዕታት፤ በመላእክት በእመቤታችን ላይ አድሮ እግዚአብሔር እንደሚመሰገን አስተውሉ፡፡
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
ወርኀ_ሐምሌ_የሰማዕታት_መታሰቢያ_ወር (ሐምሌ 5 ጴጥሮስና ጳውሎስ፤ ሐምሌ 15 ቂርቆስና ኢየሉጣ፤ ሐምሌ 24 አባ ኖብ ድንግል፤ ሐምሌ 25 መርቆሬዎስ)
#share
#ሐምሌ_፳፭_የምናከብረው_ክብረ_በዓል፤ ፨ ታላቁ ሰማዕት (‹‹ካልዕ ሊቀ ሰማዕታት››) ቅዱስ #መርቆሬዎስ (ፒሉፓዴር) ዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ
1. ✤ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ ልደቱ ሲሆን ድንቅ ተአምር ያደረገበትና ቅዳሴ ቤቱም በዚሁ ዕለት ነው፡፡ እንዲሁም በሐምሌ 25 ዓመታዊ በዓላቸው የኾነ ቅዱሳንም የሚከተሉት ናቸው፡፡
2. ✤ዳግመኛም ከበሬ ጋር ተጠምደው ሰማዕትነት የተቀበሉት የኢትዮጵያዊው የአቡነ ሕፃን ሞዐ ዕረፍታቸው ነው፡፡
3. ✤የነቢዩ ሄኖክ ዕርገቱ ነው፡፡
4. ✤የቅዱስ ጳውሎስ ረዳት የነበረችው የሰማዕቷ የቅድስት ቴክላ ዕረፍቷ ነው፡፡
5. ✤ሰማዕቱ ቅዱስ ዱማድዮስ ዕረፍቱና ፍልሰተ ሥጋው ነው፡፡
6. ✤ሰማዕቱ ቅዱስ አበከረዙን ዕረፍቱ ነው፡፡
7. ✤ሰማዕቷ ቅድስት ኢላርያ ዕረፍቷ ነው፡፡
8. ✤ሰማዕታቱ ቅድስት ቴክላ እና ቅድስት ሙጊ ዕረፍታቸው ነው፡፡
9. ✤ሰማዕቱ ቅዱስ እንዲኒና ዕረፍቱ ነው፡፡
10. ✤ሰማዕቱ አቡነ ይስሐቅ ዕረፍቱ ነው፡፡
11. ✤የ600 ሰማዕታት መታሰቢያቸው በዓላቸው ነው፡፡
12. ✤እንዲሁም ዛሬ የ25 ሺህ የአትሪብ ሰማዕታት መታሰቢያቸው ነው፡፡
በዚህ ወርም (ሐምሌ 22 ዕ ብጽዑ አባታችን አቡነ ጴጥሮስ በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ ፣ ወጣቶች ፣ መዘምራን ወ.ዘ.ተ ይዘከራሉ )
#በሃገራችን_ከሚገኙ_የቅዱስ_መርቆሬዎስ_ክብረ_በዓል_ከሚከብርባቸው_ዋነኞቹ፡፡
✥1. ደብረ ጽባሕ ጸዶየ መርቆሬዎስ፤ በአጼ ይኵኖ አምላክ ዘመን የተመሠረተ፡፡
✥2.ደረስጌ ደብረ ጽዮን ማርያም፤ ‹‹ደጃች ውቤ ደረስጌ ደብረ ጽዮንን በወርቅና በዕንቊ ከመሥራታቸውም በላይ ታቦተ መርቆሬዎስን ማምጣታቸው ተብሎ የሚነገርለት›› ተዓምር አድራጊ ስዕል የሚገኝበት ቤ.ክ (ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የነገሠበት)፤ ራስ ደጀን አጠገብ፤ ጃናሞራ (መካነ ሰላም ከተማ)
✥3. ጎንደር ደብረ ፀሐይ ቊስቋም ማርያም፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ
✥4. ጋሹ አምባ አርማንያ ቅዱስ መርቆሬዎስ (ሰሜን ሸዋ፤ ደብረ ሲና)፤ ስዕሉ በበዓለ መርቆሬዎስ ቀን የሚያሸበሽበው፡፡
✥5. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኡል (አ.አ)፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ
✥6. ደብረ ሲና ቅ.እግዚአብሔር አብ(አ.አ)፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ
✥7. አዲስ አበባ ጎፋ ደብረ መዊዕ ቅዱስ መርቆሬዎስ ወዮሐንስ መጥምቅ ቤ.ክ
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
«ልጆቼ ዓላማዬን ተከተሉ!»
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ (1932 ዓ.ም— 1982 ዓ.ም)
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ከአቶ ገበየሁ እሰዬና ከወ/ሮ አሰለፈች ካሣ በ1933 ዓ.ም በስእለት የተወለዱ ሲሆን ወደ ተቀደሰው የእግዚአብሔር ጎዳና ያመሩት ገና በሕፃንነታቸው ነበር። ዝናቸው ከታወቀው የተለያዩ ኢትዮጵያ ገዳማትና ብቃታቸው ከተመሰከረላቸው ሊቃውንት ዘንድ ዜማ፣ትርጓሜ መጻሕፍት፣ባሕረ ሐሳብ እና ቅኔ ተምረው ተመርቀዋል።
በዘመናዊ ትምህርታቸውም በየደረጃው ከአቴና ዩኒቨርስቲ በቲኦሎጂ (ነገረ መለኮት ) በማስትሬት ዲግሪ ተመርቀዋል እንዲሁም ፈረንሳይኛና ዐረብኛ ቋንቋ አጥንተዋል።
በመንፈሳዊ አገልግሎታቸው፣በትምህርታቸው፣በምርምር፣በሥነ ጽሑፍ እና በማስተማር ዘዴያቸው ባለተሰጥኦ እንደነበሩ ይነገራል።
የኢትዮጵያ አርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በነበሩት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት እንብሮተ እድ በ1971 ዓ.ም ጳጳስ ሆነው ከተሾሙበት ጊዜ አንስቶ ሕይወታቸው በመኪና አደጋ እስካለፈበት ቀን ድረስ በጣም ድንቅና በርከታ ሥራዎችን አከናውነዋል።
በተለይም የዝዋይን የከህናት ማሠልጠኛ በገዳም ሥርዓት እንዲተዳደር አስወስነው በሺህ የሚቆጠሩ ካህናት እንዲሠለጥኑ፣ አባትና እናት የሌላቸው ሕፃናት እንዲያድጉበት ከማድረጋቸውም በላይ፣ አብያተ ክርስቲያናትን በማነጽና በዚሁ ሥፍራ የተለያዩ የልማት አውታሮችን በመዘርጋት አርአያነት ያለው ተግባር ፈጽመዋል።
ትምህርታቸው ልቡናን ሰብሮ የሚገባ፣በምሳሌዎች የተደገፈ እና ጥልቀት ያለው ነበር በአጠቃላይ «ትምህርታቸው እንደ ዐባይ ውኃ የሚፈስ ነበር» ።
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ በአስተሳሰበቸው ሀገራቸውን፣ሕዝባቸውን የሚወዱ፣ በኢትዮጵያዊነት የሚያምኑ፣እናት ለልጅዋ እንደምታስብ ሀገራቸውን የሚወዱ፣ሥጋዊ ጥቅም የማያታልላቸው፣በሃይማኖትም ሆነ በሀገራቸው ጉዳይ አድርባይነት የሌለበቸው፣ፍርሀት የሌለባቸው፣ እውነት የሚናገሩ እንደነበሩ ብዙዎች ይመስክራሉ፡፡
ለወጣቶች የተለየ ፍቅርና እንክብካቤ ያደርጉ የነበሩ፣በአቀራረባቸው የሚወደዱ እና ወጣቶችን “እናንተ የቤተ ክርስቲያን የስስት ልጆች ናችሁ፣የሰንበት ተማሪዎች የቤ ተክርስቲያን ችግኞች ናችሁ» በማለት በሃይማኖታዊ ፍቅር ይኮተኩቱ ነበር፡፡
ብፁዕነታቸው በዓለም መድረክ የቤተ ክርስቲያን መልእክተኛ የነበሩ ሲሆን ሦስት ጃማይካውያንን በዝዋይ አስተማረው ለማዕረገ ቅስና አብቅተዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ራብዕ፣ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ካልዕ፣ብፁዕ አቡነ ኤልያስ ሣልስ፣ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ፣ብፁዕ አቡነ ማርቆስ እና ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ ከብፁዕነታቸው ፍሬዎች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡
አቡነ ጎርጎርዮስ የሃይማኖትና የታሪክ ተመራማሪም የነበሩ ናቸው፡፡ በሕይወት ዘመናቸው ስምንት መጻሕፍት ጽፈዋል። እነርሱም፡- መሠረተ እምነት፣የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ፣ትምህርተ ሃይማኖት (ዶግማ)፣የስብከት ዘዴ( ኦርቶዶክሳዊ)፣ቤተ ክርስቲያንህን ዕወቅ፣ሥርዓተ ኖሎት እና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ሲሆኑ እነዚህም መጻሕፍቶቻቸው በምርምር ላይ የተመረኮዙ፣ጥልቅ ምሥጢር ያካተቱ እና በውብ አገላለጽ የተሞሉ ናቸው።
በጻፉት የቤተ ክርስቲያን ታሪክ መጽሐፋቸው ኢትዮጵያ በዘመነ ኦሪት፣ኋላም የክርስትናን እምነት ከተቀበለችበት ወቅት አንስቶ እስከ አሁን የተጓዘችባቸውን የታሪክ ሂደቶች የሚያሳይ፣በሥዕላዊ ቃላትና ጥልቅ ሐሳቦችን የሚገልጽ ድንቅ መጽሐፍ ነው።
በተጨማሪም መጽሐፉ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት(ዶግማ)፣የታበት፣የሥዕልና የመስቀልን ክብር፣የአማላጅነት ምስጢር፣የቤተ ክርስቲያን ትውፊት እና ሥሪትን የሚያብራራ ነው።
ሐምሌ 22 ቀን 1982 ዓ.ም ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ተኩል ወደ መቂ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ለአገልግሎት ሲሄዱ በድንገተኛ የመኪና አደጋ በተወለዱ በሃምሳ ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል፡፡
ብፁዑነታቸው ከተናገሯቸው ድንቅ አባባሎች ውስጥ ስለ እመቤታችን መናገር የምንችለው ስለሰውና ስለ እግዚአብሔር ስናውቅ ብቻ ነው፣ የቤተ ክርስቲያን ሕይወት በመስቀል ላይ ነውና ፈተና ይበዛበታል ስለዚህ ከግል ሕይወታችሁ ይልቅ የቤተ ክርስቲያናችሁን አቋም አጠናክሩ፣ሰው ፍላጎቱን ካላሸነፈ የእግዚአብሔር ሊሆን አይችልም፣ሥጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ሕይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው፣ኢትዮጵያ ለእግዚአብሔር የምሥጢር ሀገር ናት፡፡
ለሠሩት እና ላበረከቱተት አስተዋጽኦዎች ትምህርት ቤቶች፣አዳራሾች፣ቤተ መጻሕፍት እና ሐውልት በስማቸው ተሰይሞላቸዋል፡፡
ምንጭ፡- የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በኢትዮጵያ
አብነቶቻችን
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በመንፈስ ቅዱስ ለመንጋው የተሾሙ እስከ ሞትም የታመኑ እውነተኛ እረኞች ናቸው። ሥልጣናቸውም የሚመነጨው ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምህሮ ነው። ቸር ጠባቂያችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መልካም እረኝነት የባሕርዩ ነው፡፡ ‹‹አነ ውእቱ ኖላዊ ኄር ዘበአማን፤ እውነተኛ ቸር ጠባቂ እኔ ነኝ፤›› በማለት እንደ ተናገረው (ዮሐ. ፲፥፲፩)፡፡ ጌታችን ይህን መለኮታዊ ሥልጣኑን ለቅዱሳን በጸጋ አድሏቸዋል፡፡ ‹‹… ግልገሎቼን አሰማራ፤ ጠቦቶቼን ጠብቅ፤ በጎቼን አሰማራ›› በማለት ለቅዱስ ጴጥሮስ የሰጠው ሥልጣን ለዚህ ማሳያ ነው (ዮሐ. ፳፩፥፲፭-፲፯)፡፡
ስለ መልካም እረኛ ሲነሣ በአብነት ከሚጠቀሱ የቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል በረከታቸው ይደርብንና ኢትዮጵያዊው ሰማዕት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ አንደኛው ናቸው፡፡ ጠላት አገራችንን በወረረበት፣ በመንጋው ላይ መከራ እና ችግር በጸናበት፣ እንደዚሁም የንጹሐን ደም በግፍ በፈሰሰበት በዚያ በፈተና ወቅት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ለቤተ ክርስቲያንም ለአገርም የሚያስቡ መልካም እረኛ እንደ ነበሩ የታሪክ መዛግብት ማስረጃዎች ናቸው፡፡ ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ከዐርበኞች ጋር ኾነው ሕዝቡ ለጠላት እጁን እንዳይሰጥና ሃይማኖቱን እንዳይለውጥ ከማስተማራቸው፣ ከማጽናናታቸው ባሻገር በጠላት ፊት ለፍርድ በቀረቡበት ጊዜም መልካም እረኝታቸውን በዐደባባይ መስክረው፣ ለሕዝብ፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለአገር በመቆርቆራቸው በጥይት ተደብድበው በሰማዕትነት አልፈዋል፡፡
ክብር ይግባውና ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን ወደ በጎች ስፍራ በበሩ የማይገባ፥ በሌላም በኩል የሚገባ ሌባ፥ ወንበዴም ነው፡፡ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች ጠባቂ ነው፡፡ ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ቃሉን ይሰሙታል፤ እርሱም በጎቹን በየስማቸው ይጠራቸዋል፤ አውጥቶም ያሰማራቸዋል፡፡ ምንደኛ (ቅጥረኛ) እረኛ ግን ለበጎቹ አይጨነቅም፤ በጎቹም አያውቁትም (ዘካ. ፲፩፥፬-፭፤ ዮሐ. ፲፥፩-፲፪)፡፡ ዛሬም በእናት ቤተ ክርስቲያናችን የተሾሙ አባቶች እንደነ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ለቤተ ክርስቲያንም ለአገርም የሚጨነቁ ሊኾኑ ይገባል፡፡
ጳጳሳት የህዝብን አንድነት የሚጠብቁ። በበጎቻቸው የማያደሉ ስለ በመንጋው አንድነት የሚገዳቸው ሊሆኑ ይገባል። እኛ ምእመናንም እግዚአብሔር አምላካችን መልካም እረኞችን እንዳያሳጣን መለመን ይኖርብናል፡፡ እንደዚሁም ራሳችንን ለሃይማኖታችን ማስገዛት፣ መልካም እረኞችንም አብነት ማድረግና መከተል ይጠበቅብናል፡፡
ወርኀ_ሐምሌ_የሰማዕታት_መታሰቢያ_ወር (ሐምሌ 5 ጴጥሮስና ጳውሎስ፤ ሐምሌ 15 ቂርቆስና ኢየሉጣ፤ ሐምሌ 24 አባ ኖብ ድንግል፤ ሐምሌ 25 መርቆሬዎስ)
#share
#ሐምሌ_፳፭_የምናከብረው_ክብረ_በዓል፤ ፨ ታላቁ ሰማዕት (‹‹ካልዕ ሊቀ ሰማዕታት››) ቅዱስ #መርቆሬዎስ (ፒሉፓዴር) ዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ
1. ✤ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ ልደቱ ሲሆን ድንቅ ተአምር ያደረገበትና ቅዳሴ ቤቱም በዚሁ ዕለት ነው፡፡ እንዲሁም በሐምሌ 25 ዓመታዊ በዓላቸው የኾነ ቅዱሳንም የሚከተሉት ናቸው፡፡
2. ✤ዳግመኛም ከበሬ ጋር ተጠምደው ሰማዕትነት የተቀበሉት የኢትዮጵያዊው የአቡነ ሕፃን ሞዐ ዕረፍታቸው ነው፡፡
3. ✤የነቢዩ ሄኖክ ዕርገቱ ነው፡፡
4. ✤የቅዱስ ጳውሎስ ረዳት የነበረችው የሰማዕቷ የቅድስት ቴክላ ዕረፍቷ ነው፡፡
5. ✤ሰማዕቱ ቅዱስ ዱማድዮስ ዕረፍቱና ፍልሰተ ሥጋው ነው፡፡
6. ✤ሰማዕቱ ቅዱስ አበከረዙን ዕረፍቱ ነው፡፡
7. ✤ሰማዕቷ ቅድስት ኢላርያ ዕረፍቷ ነው፡፡
8. ✤ሰማዕታቱ ቅድስት ቴክላ እና ቅድስት ሙጊ ዕረፍታቸው ነው፡፡
9. ✤ሰማዕቱ ቅዱስ እንዲኒና ዕረፍቱ ነው፡፡
10. ✤ሰማዕቱ አቡነ ይስሐቅ ዕረፍቱ ነው፡፡
11. ✤የ600 ሰማዕታት መታሰቢያቸው በዓላቸው ነው፡፡
12. ✤እንዲሁም ዛሬ የ25 ሺህ የአትሪብ ሰማዕታት መታሰቢያቸው ነው፡፡
በዚህ ወርም (ሐምሌ 22 ዕ ብጽዑ አባታችን አቡነ ጴጥሮስ በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ ፣ ወጣቶች ፣ መዘምራን ወ.ዘ.ተ ይዘከራሉ )
#በሃገራችን_ከሚገኙ_የቅዱስ_መርቆሬዎስ_ክብረ_በዓል_ከሚከብርባቸው_ዋነኞቹ፡፡
✥1. ደብረ ጽባሕ ጸዶየ መርቆሬዎስ፤ በአጼ ይኵኖ አምላክ ዘመን የተመሠረተ፡፡
✥2.ደረስጌ ደብረ ጽዮን ማርያም፤ ‹‹ደጃች ውቤ ደረስጌ ደብረ ጽዮንን በወርቅና በዕንቊ ከመሥራታቸውም በላይ ታቦተ መርቆሬዎስን ማምጣታቸው ተብሎ የሚነገርለት›› ተዓምር አድራጊ ስዕል የሚገኝበት ቤ.ክ (ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የነገሠበት)፤ ራስ ደጀን አጠገብ፤ ጃናሞራ (መካነ ሰላም ከተማ)
✥3. ጎንደር ደብረ ፀሐይ ቊስቋም ማርያም፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ
✥4. ጋሹ አምባ አርማንያ ቅዱስ መርቆሬዎስ (ሰሜን ሸዋ፤ ደብረ ሲና)፤ ስዕሉ በበዓለ መርቆሬዎስ ቀን የሚያሸበሽበው፡፡
✥5. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኡል (አ.አ)፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ
✥6. ደብረ ሲና ቅ.እግዚአብሔር አብ(አ.አ)፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ
✥7. አዲስ አበባ ጎፋ ደብረ መዊዕ ቅዱስ መርቆሬዎስ ወዮሐንስ መጥምቅ ቤ.ክ
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
መልክአ ማርያም.pdf4.62 MB
እንኳን #ለብርሃን_መልአክ_ከሣቴ_ምሥጢር_ለሆነው #ቅዱስ_ዑርኤል_ሊቀ_መልአክ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ
#ሐምሌ ፳፪፤ #በዓለ_ቅዱስ_ዑራ(ር)ኤል_ቅዳሴ_ቤቱ_የሚከበርበትና
(ሐምሌ ፳፩ ደግሞ ለዕዝራ ጽዋዕ ልቡና ያጠጣበት ነው፡፡)
#ዑራኤል ማለት “ብርሃነ እግዚአብሔር” ማለት ነው። “ዑራኤል ሥዩም ላዕለ ኵሎሙ ብርሃናት፤ #ዑራኤል በብርሃናት ላይ ሁሉ የተሾመ ነው” እንዲሁም “ዑራኤል አሐዱ እመላእክት ቅዱሳን እስመ ዘረዓም ወዘረዓድ፤ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ ዑራኤል በመብረቅና በነጎድጓድ የተሾመ ነው” እንዲል፡፡ (ሄኖክ ፮፥፪) ከሊቃነ መላእክት አንዱ መሆኑንና ፍርሃት ረዓድ ላለባቸው ረዳታቸው እንደሆነ የመላእክትን ነገር የተናገረ ሄኖክ ነግሮናል፡፡ “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል” በማለት ነቢዩ ዳዊት እንደተናገረ እግዚአብሔርን በሚፈሩና በሚያከብሩት ሰዎች ጭንቀት ጊዜ በመካከላቸው እየተገኘ ያጽናናቸዋል። (መዝ.፴፫፥፯) ምሥጢር ይገልጥላቸዋል፤ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይጠብቃቸዋል።
#ቅዱስ_ዑራኤል ምሥጢር ገላጭ ነው። ምሥጢር ማናገር #የመንፈስ_ቅዱስ ሥራ ቢሆንም የተሠወረውን መግለጥ፣ በአዲስ ቋንቋ ማናገር ለመላእክት የተሰጠ ጸጋቸው መሆኑም ግልጽ ነው። በዚህ ሀብትነትም የተወደደ ሥራ ለሚሠሩና እንዲያውቁ ለተፈቀደላቸው ሁሉ #ቅዱስ_ዑራኤል ምሥጢር ይገልጣል፤ #ለዕዝራ_ሱቱዔል የሆነለትም እንዲህ ነው።
#መልአኩ_ዑራኤል “አፍህን ክፈት፤ እኔም የማጠጣህን ጠጣ” … ብሎ አእምሮ ለብዎውን ገልጦለታል። (ዕዝ.ሱት. ፲፫፥፴፰) የዚህን ተአምር መታሰቢያ ሐምሌ ፳፪ በየዓመቱ ቤተ ክርስቲያናችን ታከብራለች። ለሄኖክም ምሥጢረ ሰማይንና ዕውቀትንም ሁሉ የገለጠለት እርሱ እንደሆነ በመጽሐፈ ሄኖክ ተጽፏል። (ሄኖክ ፳፰፥፲፫) አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ልቡናውን ያበራለት ይህ መልአክ እንደሆነ ገዳሙ ባሳተመው ገድሉ ላይ ተጽፏል። በዚህ አገልግሎቱም ሊቃውንቱ #ከሣቴ_ምሥጢር ይሉታል።
አፋቸውን ከፍተው የምስጋና ቃል ለሚናገሩ ሁሉ ክብርና ጥበቃን ከመላእክት እንደሚቀበሉ ከላይ በተመዘገበው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ለዕዝራ ሱቱዔል የተደረገለትን መረዳት ይገባል። ዕዝራ ለረጅም ወራት እግዚአብሔርን ደጅ ጸንቶ ነበር። የነገሩትን የማይረሳ እግዚአብሔር መልአኩን ላከለት፤ የሰማዩን ምሥጢርም ዐወቀ።
ይህ መልአክ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ግብጽ ተራሮች በተሰደደች ጊዜ በመካከላቸው ሁኖ መንገድ ይመራቸው እንደነበር በድርሳነ ዑራኤል ተገልጿል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ አደባባይ ደሙን በፈቃዱ ሲያፈስም በጽዋዕ የተቀበለው መልአክ እርሱ መሆኑን በዕለተ ዓርብ በሚነበበው ግብረ ሕማም ተጽፏል።
ሐምሌ ፳፪ ከሚታሰበው በዓሉ በተጨማሪም ፤ በሊቀ መላእክትነት የተሾመበትን በማሰብ ጥር ፳፪ ቀን፣ ከጌታችን የፈሰሰውን ደም በጽዋዕ የተቀበለበትን ቀን በማሰብ መጋቢት ፳፯ ቀን ይከበራል።
የሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን!
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
#በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በመላው_ዓለም_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፳፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን)
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#በአዲስ_አበባ_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፲፫) #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ፤
አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ካዛንቺስ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ካዛንቺስ፡፡
፪. ኤረር በር ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ዑራኤል፡፡
አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ኤረር በር፤
ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ→ ኤረር በር፤
፫. አዲስ ሰፈር አንፎ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ዑራኤል፣ መጥምቁ ዮሐንስና ልደታ ለማርያም፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አዲስ ሰፈር፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → አንፎ፡፡
፬. ፉሪ ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ፉሪ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → ፉሪ፡፡
፭. ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም መካነ ብርሃን ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ
አድራሻ፤ ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጎፋ ካምፕ → ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#እንዲሁም_በድርብነት_፤
፮. ድልበር መካነ ጎልጎታ መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ቶታል/ድል በር/ (ጎጃም በር)፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → አዲሱ ገበያ → ቶታል፡፡
፯. አስኮ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለምና ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንየ ክፍለ ከተማ፥ አዲስ ሰፈር፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ /ከአቡነ ጴጥሮስ/ → አስኮ፡፡
፰. አውግስታ ደብረ ጽዮን ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አውግስታ ሸሚዝ ፋብሪካ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → አውግስታ ሸሚዝ ፋብሪካ፡፡
፱. ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ታቦት ማደርያ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → ታቦት ማደርያ፡፡
፲. ቱሉ አቦ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፤ ቅዱስ ዑራኤልና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቱሉ አቦ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → አቃቂ → ቱሉ አቦ፡፡
፲፩. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚከኤል፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ፡፡
፲፪. ላፍቶ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለምና መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ፤
አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ላፍቶ፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መካኒሳ → ላፍቶ፡፡
፲፫. ሐመረ ወርቅ ማርያምና አርሴማ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ፡፡
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፮ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩ መንዝ ዕመጓ ደብረ ቆጵሮስ ኢየሱስ ቅዱስ ዑርኤል ገዳም፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መንዝ፡፡
፪. ግሸን ቅዱስ ዑርኤል፤
አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ግሸን ደብረ ከርቤ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ግሸን፡፡
፫. ጎንደር ደብረ ኀይል ቅዱስ ዑርኤል ወበዓታ፤
አድራሻ፤ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡
፬. ደብረ ታቦር አንቀፀ አድህኖ ቅዱስ ዑርኤል፤
አድራሻ፤ ደ. ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ታቦር ከተማ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ታቦር፡፡
፭. የወልዲያ ቅዱስ ዑርኤል ፤
አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ወልዲያ ከተማ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ወልዲያ ፡፡
፮. ደብረ ብርሃን ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል ፤
አድራሻ፤ ሰ. ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ብርሃን ከተማ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን፡፡
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#ከኢትዮጵያ_ውጭ_የሚከበርባቸው_ #፫ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. ጀርመን ደብረ ኃይል ቅዱስ ዑርኤል ወቅዱስ ያሬድ፤
አድራሻ፤ ጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት
፪. ደብረ ብርሃን ቅዱስ ዑርኤል ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አሜሪካ ሜንሶታ
፫. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑርኤል ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አሜሪካ ሎሳንጀለስ ካሊፎርኒያ
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
