ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 453 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 521,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 192

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 453 名订阅者。

根据 01 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 64,过去 24 小时变化为 -8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 23.51%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.96% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 633 次浏览,首日通常累积 1 230 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 25

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 02 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 453
订阅者
-824 小时
+287
+6430
帖子存档
• ይህን ችግር ለመቅረፍ የተነሡት የዘመኑ ፓትርያርክ ከሀቢብ ጊዮርጊስና ከሌሎች ሁለት ምእመናን ጋር በመሆን ሐዋሪያዊ ጉዞ አደረጉ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር ሀቢብ በውጪ የሚገኙ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ወጣቶችን የሚሰበስብበትን ዘዴዎች መመልከት የቻለው፡፡ ወዲያውኑ ከጉዞው መልስም ህጻናትና ወጣቶች ተሰብስበው የሚመሩባቸውን ሰንበት ትምህርት ቤቶችን ለማደራጀትና የሚመጥናቸውን ሥርዓተ ትምህርት ለመቅረጽ መንፈሳዊ መዝሙራትንም ለማዘጋጀት አቅዶ ሥራውን ጀመረ፡፡ በዚህ ሥራውም በሌላ እምነት ተማርከው የነበሩትን መመለስ ችሏል፡፡ ሀቢብ ጊዮርጊስ #ጸሐፊነትን፣ #አስተዳዳሪነትን እና #ሰባኪነትን በእኩል ደረጃ አሳክቶ መያዝ የቻለ ሰው ነው፡፡ በአጠቃላይ #ሠላሳ_መጽሐፍትን አዘጋጅቷል፡፡ በመጨረሻ ዕድሜው ሲገፋ #ጤናውም_እየታወከ_መጣ፤ ቤቱም በደቀ መዛሙርቱ መሞላት ጀመረ፡፡ ለእርሱም የነበራቸውን ፍቅር ለመግለጽ መኝታን ከበው አብረውት ጸሎት በማድረግ ራሱ የደረሳቸውን #መዝሙራትም_ይዘምሩለት ነበር፡፡ በመጨረሻ ሀቢብ ጊዮርጊስ ነሐሴ 15 ቀን 1943 ዓ.ም (በ75 ዓመቱ) አረፈ፡፡ ዜና እረፍቱም በሀገረ ግብፅ ከዳር እስከ ዳር ተሰማ፡፡ ቀብሩም በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት መስከረም 17 ቀን 1944 ዓ.ም ተፈጸመ፡ ምንጭ፡-ሊቀ ዲያቆናት ሀቢብ ጊዮርጊስ እና ሥራዎቹ፣ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#ሊቀ_ዲያቆናት_ሀቢብ_ጊዮርጊስ #ለግብጽ_ቤተ_ክርስቲያን_የንጋት_ጎህ (ነሐሴ 15 እረፍቱ) #ሀቢብ_ጊዮርጊስ_ማነው? ሀቢብ ጊዮርጊስ በ1868 ዓም #በካይሮ_ከተማ ተወለደ፡፡ አባቱ በሕጻንነቱ ስለሞተበት እናቱ ለብቻዋ በፍቅረ ቤተ ክርስቲያን አንጻ አሳደገችው፡፡ ትምህርቱን የተከታተለው አቡነ ቄርሎስ አምስተኛ በመሠረቱት ትምህርት ቤት ውስጥ ነው፡፡ በዚያውም #ዲቁና ተቀብሎ ማገልገል ሲጀምር ዕድሜው #አሥራ_ሰባት ብቻ ነበር፡፡ በወቅቱ ፓትሪያርኩም በኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን የተከሰቱትንና የቤተክስቲያኒቱን አገልግሎት እጅጉን የጎዱ እንቅፋቶች በማስወገድ ወደ ለውጥ መንቀሳቀስ የጀመሩበት ጊዜ ነበር፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ሆኖ የተገኘው #የሰለጠኑ_ካህናትን_የሚያፈራ_ተቋም_መክፈት ስለነበር ለዚህ ወሰኝ ተልዕኮ የሚመጥን ይሆናል የሚሉትን ሰው ሲፈልጉ ምርጫቸው ያረፈው በወጣቱን አገልጋይ ሀቢብ ጊዮርጊስ ላይ ሆነ፡፡ ሀቢብ ጊዮርጊስ ኃላፊነቱን እንደተቀበለ ትኩረቱን ያደረገው ለተቋሙ ግንባታ የሚያስፈልገውን ገቢ ማሰባሰብ ላይ ነበር፡፡ በውጤቱም ከሀገር ሀገር እየተዘዋወረ ባደረገው ቅስቀሳ የምእመኑን የታመቀ ፍቅር ማቀጣጠል የቻለ ሲሆን በጥቂት ቀናት ውስጥ የተገኘው ድጋፍም በቂ ሆኖ ስለተገኘ ኮሌጁ እንደታሰበው ተገንብቶ ለአገልግሎት በቅቷል፡፡ ኮሌጁ ተከፍቶ ማስተማር ሲጀምር ደግሞ ሀቢብ ጊዮርጊስም ከመጀመሪያዎቹ ተማሪዎች አንዱ ለመሆን የቻለ ሲሆን በወቅቱ የተከሰተውን የመምህራን እጥረት መቅረፍ ግድ ሲሆን ደግሞ ተማሪ በሆነበት ዓመታት መምህርነትንም ደርቦ ያዘ፡፡ የሀቢብ አስደናቂ አገልግሎት በስፋት የተገለጠው ከተመረቀ በኋላ ሲሆን በሰባኪነት ተሰማርቶ የሰበካቸው ስብከቶች በወቅቱ ሰማዕያኑን የመሰጡ ብቻ ሆነው አልቀሩም፡፡ ይልቁንም ብዙዎች ከሞተ በኋላ እንኳ ሳይቀር የሚያስተውሷቸው እንዲሁም ታትመው የብዙዎችን ሕይወት ሲለውጡ የሚኖሩ ሆነዋል፡፡ ለመሠረተው ኮሌጅ ማደግ ከፍተኛ ራእይ የነበረው ሀቢብ ጊዮርጊስ በዚያ ወቅት ከሠራቸው ሥራዎች መሀከልም ጉልህ የነበረው በኮሌጁ ዙሪያ የነበሩ ቦታዎችን ባገኘበት አጋጣሚ ሁሉ በግል ገንዘቡ እየገዛ ለኮሌጁ ማስፋፊያ ይሆን ዘንድ ማበርከቱ ይጠቀሳል፡፡ በዚህና መሰል ወደር የለሽ ተግባራቱና ከፍ ያለ ትጋቱ የተደሰቱት ፓትሪያርኩ አቡነ ቄርሎስ #የሊቀ_ዲያቆንነት_ማዕረግን_ሰጡት፡፡ የሀቢብ ጊዮርጊስ ቀጣይ የአገልግሎት ምዕራፍ የኮሌጁ ርዕሰ መምህር በሞት በተለየ ጊዜ እርሱን በመተካት የርዕሰ መምህርነትን ኃላፊነት ሲጨምር የሚጀምረው ነው፡፡ በዚህ ወቅት ከሠራቸው ተግባራት መሀከልም ዋነኛው ኮሌጁን ከውጪ ተጽእኖ የተጠበቀ እንዲሆነ ማድረጉ የመጀመሪያው ሲሆን በመከላከል ብቻ ላይም ሳይወሰን ተቋሙ #የኦርቶዶክሳዊት_ቤተ_ክርስቲያንን_ትምህርት_በምልዓት_የሚያንጸባርቅ መብራት ማድረግ መቻሉ ደግሞ ሌላው ዘለዓለማዊ ስኬቱ ነው፡፡ በተለይ ኦርቶዶክሳዊያን ደቀመዛሙርት ወደ አንግሊካን የትምህርት ተቋማት ሄደው የከፍተኛ ትምህርት እንዲከታተሉ የሚል ግፊት ሲነሳና እንዲሁም የአንግሊካን ምሁራን በኮፕቲክ የሥነ መለኮት ኮሌጅ እንዲያስተምሩ ሐሳብ ሲመጣ ይህን በመቃወም ግፊቱ ከሐሳብ አልፎ በተግባር እንዳይውል ማድረግ መቻሉ ነበር፡፡ የሀቢብ ልዩ ችሎታ የነበረው በመቃወምና በመከላከል ላይ ብቻ አለመወሰኑ ይልቁንም ከተቃወመው ሐሳብ የተሻለ አማራጭ እንዲኖር መሥራቱ ነው፡፡ በዚህም የተነሣ በኦርቶዶክሳዊው የትምህርት ተቋም ውሰጥ የአንግሊካን ሊቃውንት እንዳያስተምሩ በማለት አጥብቆ ሲቃወም በምትኩ ደግሞ ኦርቶዶክሳዊውያን አስተምህሮ በጥልቀት የተረዱ ቀሳውስት እንዲኖሩ አጥብቆ ይሠራ ነበር፡፡ ሌላው የሀቢብ ጊዮርጊስ ጅምር የነበረውና ባለፉት ቅርብ ዓመታት ውሰጥ ለግብጽ ቤተ ክርስቲያን መነቃቃት መንስኤ የሆነው ተግባር ደግሞ ኮሌጁ የማታ የትምህርት መርሐ ግብር እንዲጀምር ማድረጉ ነው፡፡ የዚህ አዲስ መርሐ ግብር መከፈት በርካታ ምሁራንና ወጣቶች ወደ ቤተክርስቲያን እንዲመጡና በትምህርተ ሃይማኖት እንዲታነጹ እድል ከመስጠቱም በላይ በዚህ ምክንያትነት #የግብጽ_የትምህርት_ሚኒስቴር_ለኮሌጁ_እውቅና_ሊሰጠው_ችሏል፡፡ በማታው መርሐ ግብር ተካፍለው ከነበሩ ወጣት ምሁራን መካከል #ፖፕ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ አንዱ ናቸው፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ ለኮሌጁ እድገት ዕድሜውን ሁሉ የተጋው ሀቢብ ጊዮርጊስ ኮሌጁን በማሳደግ ዓለም አቀፍ ደረጃውን እንዲጠብቅ ማድረግ የቻለ ሲሆን መደበኛው የሥነ መለኮት ትምህርት በፍልስፍናና በሥነ ልሳን ትምህርቶች የታጀበ እንዲሆንና እንዲሁም በብቁ መምህራን የተሞላ በማድረግ የምርጥ አገልጋዮች መፍለቂያ እንዲሆን ስላደረገው በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በቤተ ክርስቲያን ክህነት የሚቀበሉ ሁሉ የኮሌጁ ዲፕሎማ እንዲኖራቸው የሚያስገድድ ሕግ ተሠራ፡፡ ሀቢብ ጊዮርጊስ በሕይወት ኖሮ የኮሌጁን አርባኛ ዓመት ለማክበር የበቃ ሲሆን በዚያው ዓመትም ‹‹#የነገረ_መለኮት_ኮሌጅ_ትናንትናና_ዛሬ›› የሚለውን መጽሐፉን ለሕትመት አብቅቷል፡፡ #የሰንበት_ትምህርት_ቤት_ጅማሮ ሀቢብ ጊዮርጊስ የመጀመሪያውን ሰንበት ትምህርት ቤት በማቋቋም ሥራውን ሲጀምር የ24 ዓመት ወጣት ነበር፡፡ ጊዜውም 1892 ዓም ቦታው ካይሮ ከተማ ውስጥ በሚገኙ የኮፕቲክ አብያተ ክርስቲያናት፡፡ ጅማሮው ሕጻናትን ሰብስቦ በማስተማር ነበር፡፡ በእግዚአብሔር ቸርነት አገልግሎቱ ተባርኮለት ሥርዓተ ትምህርት ለመቅረጽ ማዕከላዊ ኮሚቴ አቋቋመ፡፡ ይህም ውጥን በሀገሪቱ በሞላ ተስፋፍቶ አገልጋዮች እጅግ የበዙ ሆኑ፡፡ በሀቢብ ጊዮርጊስ የተቋቋሙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ በወጣቶች ልቡና ውስጥ መተከል እንዲችል ሕያው ምስክር ሆኑ፡፡ ከዚሁም ጋር ተያይዞ በግብጽ የመጻሕፍትና የበራሪ ጽሑፎች ስርጭት፣ ዐውደ ርእያት፣ ሴሚናሮች፣ ኮንፈረንሶች፣ ወደ አብያተ ክርስቲያናትና ወደ ገዳማት የሚደረጉ መንፈሳዊ ጉዞዎችንና የመሳሰሉ እንቅስቃሴዎች የመነጩት ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ነው፡፡ #የሰንበት_ትምህርት_ቤቱ_መስፋት_ምን_ጠቀመ? ሀቢብ ጊዮርጊስ የመሠረተው የሰንበት ትምርት ቤት እንቅስቃሴ ከተስፋፋ በኋላ በወቅቱ ቤተ ክርስቲያንን ይፈታተኑ የነበሩ ችግሮችን በእግዚአብሔር እርዳታ መፍታት የሚችል ሊሆን በቅቷል፡፡ ከነዚህም መሀከል የሚከተሉት ዐበይት ተግባራት አይዘነጉም፡፡ • መጽሔቶችን በማሳተም ስብከተ ወንጌልን የማስፋፋት ሥራ በብዛት የተሠራው በዚህ ዘመን ነው፡፡ • ወደ ቤተ ክርስቲያን ሳይመጡ የቀሩ ወጣቶች ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲቀርቡ አድርጓል፡፡ • በዘመኑ የነበሩ እንግሊዛውያን ሚስዮናውያን የቅኝ ገዢዎችን አካሄድ በመከተል ኦርቶዶሳውያንን ከእምነት ለማስወጣት ይጥሩ ነበር፡፡ • ሚስዮናውያኑ በተለይ የትምህርት ዕድል በመስጠትና በመሳሰሉ ዘዴዎች በመጠቀም ወጣቶችን ለማማለል ይሞክራሉ፡፡ ቤት ለቤት እየዞሩ ማራኪነት ባላው ጽሑፎችና ባሸበረቁ ሥዕላት ያዘጋጁዋቸውን ብሮሹሮች በመበተን የሚሠሩት የቅሰጣ ተግባር አልበቃ ብሏቸው የእናት ቤተ ክርስቲያንን ስም ጥላሸት እስከ መቀባት ደርሰው ነበር፡፡ በዚህም ተግባራቸው ብዙዎች ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጠፍተዋል፡፡

የ2018 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በጃንሜዳ አዘጋጅ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤ/ክ መሆኑን ያውቃሉ? እንግዲያውስ .... 1) ልብሰ ተክህኖ በሙካሽ እና በግሪክ ጨርቅ 2) የታቦተ ህጉ መጎናጸፊ
የ2018 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በጃንሜዳ አዘጋጅ  የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤ/ክ መሆኑን ያውቃሉ? እንግዲያውስ .... 1) ልብሰ ተክህኖ በሙካሽ እና በግሪክ ጨርቅ 2) የታቦተ ህጉ መጎናጸፊያ በሙካሽ 3) የመቀደሻ ንዋይ ቅድሳት 4) የሊቃውንት አባቶች ጥንድ ድርብ እና ልዩ ካባ 5) የሊቃውንት አባቶች የብር መቋሚያ እና ጽናጽል 6) የሰ/ትምህርት ቤት ዩኒፎርም እና ጥንድ ድርብ 7) የሰ/ት/ት ቤት ጽናጽል እና መቋሚያ እና የመሳሰሉት ንዋየ ቅድሳትን ለማሟላት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ለዚሁ በዓል ገቢ ማሰባሰቢያ በተከፈተው የኮሚቴው አካውንት አስተዋጽዎ ያድርጉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000636620991

#እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም ይህች ገዳም ታሪኳ ከታላቁ ገዳማችን ዋልድባ (ገዳመ ዋሊ) ለ2ኛ ጊዜ መሥፋፋት (መመሥረት ጋር) የተያያዘ ታሪክ ያላት ናት፡፡ ይኸውም የሸዋ አባቶች ወደ ዋልድባ በ485 ዓ.ም በንጉሥ አልአሜዳ ዘመነ መንግሥት ባቀኑ ጊዜ የተሰባሰቡባት ቦታ ናት፡፡ እነዚህም አበው ከመኖሪያ ቀዬቸው (ቡልጋ/ምንጃር) ሁለት ታቦታትን (ታቦተ ኪዳነ ምሕረት ዘምሕረት አምባ፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ዘአብየ ገዳምን) ይዘው ነበር፤ በዚህች በተቀደች ቦታ ይዘዋት በመጡት ታቦተ ኪዳነ ምሕረት ገዳመ ሐመረ ኖኅን መሥረተዋል፡፡ የመድኀኔዓለም ታቦትን ደግሞ በታላቁ ገዳም በዋልድባ አኑረዋል፡፡ ይህች ሐመረ ኖኅ፤ በ500 ዓ.ም በአባ ሊባኖስ የአንድነት ገዳም ሆና ተስፋፍታ ተቋቋመች፡፡ በ9ኛ መቶ ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት የአክሱም ጽዮንን ቤተ መቅደስ ለማቃጠል ስትነሳ ንጉሡ አንበሣ ውድም #ታቦተ_ጽዮንን በምሥጢር በማስያዝ ወደ ሸዋ መጥተው #በእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነምሕረት_ገዳም ታቦተ ጽዮንን አሳድረው ወደ ዝዋይ ደሴት ሲሄዱ ለገዳሟ ንዋየ ቅድሳት ስጦታ አበርክተዋል ጸበሏን ተጠምቀው ቦታውን መርቀው ሄደዋል፡፡ በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቁ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ #ከንጉሥ_ላሊበላ ጋር ወደ ዝቋላ አምባ ሲመጡ በዚህች ገዳም በእንግድነት አድረው በጸበሏ ተጠምቀው ቦታውን ባርከዋል፡፡ #አፄ_ዘርዓ_ያዕቆብም ወደዚህች ገዳም መጥተው አቀማመጧንና የጸበሏን ፈዋሽነት ተመልክተዋል ‹‹#ዳሯ_እሳት_መሐሏ_ገነት_ይሁን›› ብለው ብዙ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ #አፄ_ልብነ_ድንግልም ወደ ገዳሟ መጥተው ተማህጽኖ አድርገው በጸበሏ ተጠምቀው ታቦተ ልደታንና ብዙ ንዋየ ቅድሳት ሰጥተው ሄደዋል፡፡ #በንግሥት_ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት ይህች ገዳም #ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነምህረት ገዳም ተብላ ተሰይማለች፡፡ ይህች ቦታ ከታላቁ ገዳም #ከዋልድባ ጋር አሁንም ግንኙነቷ እንደጠነከረ ነው፤ ከዋልድባ ያሉ አባቶች በተለያየ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ በዋነኛነት የሚያርፉባት #ጥንተ_ርስታቸውም ናት፡፡ ይህች ቦታ በርካታ ቅዱሳን በኪደተ እግር የረገጧት እንደመኾኗ፤ ጸበሏ #የአጋንንት_ድል_መንሻ፤ #የብዙ_መነኮሳት_መጠጊያ፤ #የሕሙማን_መፈወሻ፤ የእመቤታችንን ቃል ኪዳን ለማግኘት ብዙን ጊዜ ለሱባኤ ከሚመረጡ ቦታዎችም አንዷ ናት፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#እንኳን_አደረሳቹሁ ፡፡ በዓለ ፍልሰታ ወዕርገታ ለማርያም ወፍልሰተ አጽሙ ለሊቀ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት ፍልሰታ የግእዝ ቃል ነው፤ #ፈለሰ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ተለየ፣ ሄደ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ መሄድን ያመለክታል፡፡ እመቤታችን እንደ ሰው ልማድ ሞትን ትቀምስ ዘንድ ግድ ስለኾነ፤ ጻዕርና ሕማም በሌለበት አሟሟት፤ ዕዝራ በመሰንቆ፥ ዳዊት በበገና እያጫወቷት፤ በተወለደች በ64 ዓመቷ ጥር 21 ቀን #በ48 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ አርፋለች። ሐዋርያትም እንደምታርፍ በመንፈስ ቅዱስ ስለተገለጸላቸው ከያሉበት (ከየሀገረ ስብከታቸው) ወደ መኖሪያ ቤቷ (የሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ቤት) ተሰባስበው ነበር። ነፍሷ ከሥጋዋ እንደተለየች ሥጋዋን ገንዘውና ሸፍነው ወስደው ለመቅበር ወደ #ጌቴሴማኒ ሲሄዱ አይሁድ ሰምተው መጡና ሐዋርያትን ከበቧቸው። የአይሁድ ተንኮል አስከሬኗን ከሐዋርያት እጅ ቀምተው በእሳት ለማቃጠል ነበር፤ ይህንንም ማድረግ የፈለጉበት ምክንያት፤ የሐዋርያት ትምህርት (የጌታችን ከሞት መነሳትና ለፍርድ ተመልሶ መምጣት)ከአይሁድ አልፎ ዓለም ሁሉ እያመነበት ስለመጣ እመቤታችንም ተነሥታ ዐርጋለች እያሉ ሐዋርያት ያስተምራሉ በሚል ስጋት ነበር። ‹‹የፈሩት ይነግሣል፥ የጠሉት ይወርሳል›› እንዲሉ አበው፤ የእመቤታችን ትንሣኤም ሆነ ዕርገት አይቀሬ ሁኗል። አይሁድ የእመቤታችንን ሥጋ ለመንጠቅ በሞከሩበት ጊዜም ታውፋኒያ የተባለ ጎልማሳ ሰው በጉልበቱና በድፍረቱ በአይሁድ ዘንድ ተመርጦ የእመቤታችንን ሥጋዋ ያረፈበትን ቃሬዛ ከሐዋርያት ነጥቆ መሬት ላይ ለመጣል ሲሞክር፤ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ ሁሉቱንም እጆቹን ቀንጥሶ (ቆርጦ) ጥሏቸዋል። ነገር ግን ጥፋቱን አውቆ ወዲያው ስለተፀፀተና ይቅርታ ስለጠየቀ በአምላክ ፈቃድ በእመቤታችን አማላጅነት በቅዱስ ጴጥሮስ አማካኝነት እጆቹ እንደገና ተመልሰውለት የእመቤታችንን እመ አምላክነት (የአምላክ እናት መሆኗ)ና ክብርን ለመመስከር በቅቷል። የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ በመላእክት ተነጥቆ ከተወሰደ በኋላ በገነት ውስጥ #በዕፀ ሕይወት ሥር መቀመጡ ከዮሐንስ በስተቀር ለሌሎች ሐዋርያት ለጊዜው ምሥጢር ሆኖባቸው ቆይቶ ነበር። ቆየት ብሎ ግን ሐዋርያው ዮሐንስ ስለ እመቤታችን ሥጋ ነገራቸው። ቅዱሳን ሐዋርያትም ለእመቤታችን ካላቸው ክብርና ፍቅር የተነሳ ለምን አልቀበርናትም? ለምንስ የሥጋዋ ምሥጢር ለዮሐንስ ተገልጾ ለኛ ይደበቅብናል? በማለት እያዘኑና እየለ መኑ ከጥር 21 አንስተው ለስድስት ወራት ከዐሥር ቀናት ቆይተዋል። ከዚህም በኋላ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ሱባዔ ይዘው ለ14 ቀናት እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ጠየቁት። በመጨረሻም የነገሩትን የማይረሳ፥ የለመኑትን የማይነሳ ልጇ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነሐሴ 14 ቀን ሥጋዋን አምጥቶ ስለሰጣቸው፤ ሳይውሉ ሳያድሩ በዕለቱ በጌቴሴማኒ በታላቅ ክብርና ዝማሬ ቀበሯት። በተቀበረችም በ3ኛው ቀን በነሐሴ 16 ከተቀበረችበት መቃብር ተነሥታ ወዲያውኑ በታላቅ ክብር በመላእክት አጃቢነት ወደ ሰማይ ዐርጋለች። ጥበበኛው ሰሎሞንም “ውዴ እንዲህ ይለኛል ሙሽራዬ ውዴ ሆይ! ተነሺ የእኔ ውብ ሆይ ነዪ አብረን እንሂድ” በማለት አመሣጥሮ የተናገረው በጥበበ እግዚአብሔር ተመርቶ እንደ ክርስቶስ ሆኖ ውዴ ያላት እመቤታችን መሆኗንና ልጇ ተነሥቶ እንደ ዐረገ እሷም መነሣቷንና ማረጓን እንረዳለን። /መሓ.፪፥፲/። እመቤታችን ባረገችበት ጊዜ ሐዋርያው #ቶማስ በመንፈስ ቅዱስ ጥበብ በደመና ተጭኖ ከሀገረ ስብከቱ (ሕንድ) ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ እመቤታችን በመላእክት ታጅባ ወደ ሰማይ ስታርግ ተገናኙ። በዚህ ጊዜ ቶማስ ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ ሳላይ አሁንም ደግሞ እርሷን ሳልቀብራት ከትንሣኤዋም ሳልደርስ ቀረሁ ብሎ አዘነ ከደመናው ላይ ሊወድቅም ፈለገ፤ ሆኖም እመቤታችን ዕርገቷን ከእርሱ በቀር ሌሎች አለማየታቸውን ገልጻ አረጋጋችው፤ ዕርገቷንም ለሐዋርያት እንዲነግርና ምልክትና ማስረጃ እንዲሆነው ተገንዛበት የነበረውን ሰበኗን/የከፈን ጨርቅ/ ሰጥታ አሰናበተችው። ቶማስም መሬት ለይ ወርዶ መቀበሯን፣ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያላወቀ መስሎ ሐዋርያትን ስለ እመቤታችን ሥጋ ጉዳይ ጠየቃቸው፤ እነርሱም ሱባዔ ገብተው እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቃቸውን፣ ከሱባዔያቸው በኋላ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ ሥጋዋን መላእክት አምጥተው እንደሰጧቸውና እንደቀበሯት አስረዱት። እርሱ ግን ‹‹ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር›› እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲል ተከራከራቸው። ሐዋርያትም ቶማስን ለማሳመንና ለማሳየት ወደ መቃብሯ ወሰዱት፤ ሆኖም መቃብሯ ባዶ ሆኖ አገኙትና ተደናገጡ፤ በዚህ ጊዜ ቶማስ የሆነውን ሁሉ ገልጾ ለምልክትና ለማረጋገጫ የሰጠችውን ሰበኗን /ተገንዛበት የነበረውን ጨርቅ/ አሳያቸው፤ የራሱን ድርሻም አስቀርቶ አከፋፍሎ ሰጣቸው፤ #ዛሬም_ካህናት ከእጅ መስቀላቸው ጋር የሚይዙት እራፊ ጨርቅ የሚይዙበት ምክንያት ሐዋርያት የተከፋፈሉት የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው። ሐዋርያትም የዕርገቷን ምሥጢር ካመኑ በኋላ ዕርገቷን ለማየት በዓመቱ በተመሳሳይ ሁኔታ እንደገና ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ለ፪ኛ ጊዜ ሁለት ሱባዔ ገቡ፣ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ በነሐሴ ወር በ16ኛው ቀን ጌታችን ሐዋርያትን ወደ ሰማይ አውጥቷቸው እመቤታችንን አግኝተዋት ከሷ ተባርከው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረዘይት ተመልሰዋል። /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

-ነሐሴ 14 1999 ዓ.ም. ሊቁ አለቃ አያሌው ታምሩ(1915-1999 ዓ.ም.) ያረፉበት ቀን ነበር፡፡ ሊቁን ሥራዎቻቸውን በማንበብና በማስነበብ እናስታውሳቸው፡፡ እሳቸው ዐይነ ሥውር ሁነው ይኽን ያኽ
-ነሐሴ 14  1999 ዓ.ም.  ሊቁ አለቃ አያሌው ታምሩ(1915-1999 ዓ.ም.) ያረፉበት ቀን ነበር፡፡  ሊቁን ሥራዎቻቸውን በማንበብና በማስነበብ እናስታውሳቸው፡፡ እሳቸው ዐይነ ሥውር ሁነው ይኽን ያኽል መጻሕፍት ከጻፉልን ዐይናማ ነን የምንለው መጻሕፍታቸውን ለማንበብ ለምንስ እንሰንፋለን? -ከጻፏቸው መጻሕፍት መሀከል  1.) መች ተለመደና ከተኲላ ዝምድና (፲፱፻፶፫ ዓ∙ ም∙) 2.) የኢትዮጵያ እምነት በሦስቱ ሕግጋት (፲፱፻፶፫ ዓ∙ ም∙) 3.) ምልጃ እርቅና ሰላም(፲፱፻፺፪ ዓ∙ ም∙) 4.) ወላዲተ አምላክ በኢትዮጵያ (፲፱፻፸፱ ዓ∙ ም∙) 5.) የኑሮ መሠረት ለሕፃናት (፲፱፻፶፫ ዓ∙ ም∙) 6.)  መልእክተ መንፈስ ቅዱስ(፲፱፻፺፭ ዓ∙ ም∙) 7.) የጽድቅ በር  (፲፱፻፸፱ ዓ∙ ም∙) 8.) ተአምርና መጽሐፍ ቅዱስ። (፲፱፻፺፫ ዓ∙ ም∙) 9.)  ዜና ሕይወት ዘቅድስተ ቅዱሳን እመ አምላክ። (፲፱፻፺፱ ዓ∙ ም∙) ከዲ/ን ዮሴፍ ፍሥሐ ገጽ የተወሰደ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

ደብረ ታቦር ደብረ ታቦር ከገሊላ ባሕር በምዕራባዊ በኩል 10 ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ተራራ ሲሆን፤ ከፍታው ከባሕር ወለል በላይ 572 ሜትር ይሆናል፡፡ በዚህ ተራራ ላይ ጌታችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን እንደሚገልጽ ምሳሌና ትንቢት ተነግሯል፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ “#ታቦርና #አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል” ብሎ የተናገረው ትንቢት እንዲፈጸም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተአምራቱን በዚህ ተራራ ላይ ገልጧል /መዝ. 88፥12/፡፡ በዘመነ መሳፍንት ባርቅ ሲሣራን ከነሠራዊቱ ድል ያደረገው በደብረ ታቦር ተራራ ላይ ነው፡፡ ምሳሌነቱም ባርቅ የጌታችን ሲሣራ ደግሞ የአጋንንት ነው፡፡ ጌታችን በደብረ ታቦር ክብሩን በመግለጥ በአይሁድ እያደረ አምላክነቱን እንዲጠራጠሩ ያደረጋቸውን አጋንንት ድል የማድረጉ ምሳሌ ነው /መሳ. 4፥6/፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን በቂሳርያ “የሰውን ልጅ ማን ይሉታል?” ብሎ ከጠየቃቸው ከስድስት ቀን በኋላ #አዕማድ ተብለው የሚጠሩ ሦስቱን ሐዋርያት ይዞ ወደ ረጅም ታቦር ተራራ ወጣ፡፡ በፊታቸውም ተለወጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ፡፡ እነሆም #ሙሴና #ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው፡፡ ቅዱስ #ጴጥሮስ መልሶ ጌታችን ኢየሱስን ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፡፡ ብትወድስ በዚህ #ሦስት ዳስ እንስራ አንዱን ለአንተ አንዱን #ለሙሴ አንዱን #ለኤልያስ አለ፡፡ በዚህ ጊዜ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፡፡ ከደመናውም በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት የሚል ድምፅም ተሰማ፡፡ ሐዋርያት ይህንን ሰምተው የጌታችንን መለኮታዊ ክብር አይተው በፊታቸው ወደቁ እጅግ ፈርተው ነበር፡፡ ጌታችንንም ተነሡ አትፍሩም አላቸው፡፡ በዚህ መልኩ አምላክነቱን ገለጠላቸው /ማቴ. 17፥1-10/፡፡ ፠፠፠ #አዕማደ_ሐዋርያት_(#ጴጥሮስ፣ #ያዕቆብና #ዮሐንስ )#ለምን_ተመረጡ አዕማደ ሐዋርያት "አዕማደ ሐዋርያት ተብለው የተጠሩት #ጴጥሮስ፣ #ያዕቆብና #ዮሐንስ ናቸው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ጴጥሮስ፣ ዮሐንስና ያዕቆብን “አዕማድ ሐዋርያት” እያለ ጠርቷቸዋል /ገላ. 2፥9/፡፡ ስያሜውን ያገኙበት ዋናው ምክንያት የኢየሩሳሌምን ቤተ ክርስቲያን በሓላፊነት ያስተባብሩ ስለነበረ ነው፡፡ ከዚህን በተጨማሪ ጌታችን በኢያኢሮስ ቤት ልጁን ሲፈውስ፣ በጌቴ ሴማኒ ሲጸልይና በደብረ ታቦር ምስጢረ መለኮቱን ሲገልጥ ከእሱ ስላልተለዩና ይዟቸው ስለሔደ ነው /ማር.5፥37-43/፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሦስቱ ደቀ መዛሙርት የተመረጡበትን ምክንያት ሲያትቱ እንዲህ ብለዋል፡፡ ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ሹመት፣ ሽልማትና ክብር ፈላጊዎች ነበሩ፡፡ ከዚህ ሃሳብ እንዲወጡ ከብልየታቸው እንዲታደሱ ለይቶ አውጥቷቸዋል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ለድኅነተ ዓለም የመጣው በሕማማቱ በሞቱ ቤዛ የሚሆነን አምላክ “ልሰቀል ነው” ባላቸው ጊዜ “አይሁንብህ” ብሎት ነበር፡፡ እንዲህ ያለው ሃሳብ የጠላት እንጂ የሰው ልጆች ሊሆን አይችልም ከሞቱ በቀር ድኀነት ሊያስገኝልን የሚችል የለምና፡፡ ደቀ መዝሙሩ ግን ከሞተ ክብሬ ምንድን ነው ብሏልና “አይሁንብህ” አለ፡፡ /ማቴ. 16/ በሌላም ስፍራ እንዲሁ “ሁሉን ትተን ተከተልንህ እንግዲያስ ምን እናገኝ ይሆን?” በማለት ይጠይቃል፡፡ /ማቴ.19/፡፡ ጌታ ግን ዋጋችሁ #ሰማያዊ #ክብራችሁ ዘላለማዊ ነው ሲል እስከ ፍጹማን መዓርግ /ነጽሮተ #ሥሉስ ቅዱስ/ አድርሶ ብርሃነ መለኮትን ገልጦ ተስፋውን ነገራቸው፡፡ ሁለቱ ወንድማማች ደቀ መዛሙርትም እናታቸውን ልከው ሹመት ሽልማት መዓርግ ለምነዋል፡፡ ስለዚህም ጌታችን በደብረ ታቦር “በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው ነገር” ስለሞቱ እንዲነጋገሩ አደረገ፡፡ ሞቱ እርግጥ ሆነ ማለት ነው፡፡ አባቱም “ኦሆ በልዎ ለክርስቶስ”፤ እሺ በሉት እርሱን ስሙት ሲል፡፡ ሞቱ እርግጥ በመሆኑ ከልባቸው እንዲጠፋ መርጦ ወደ ቅዱስ ተራራ ይዟቸው ወጥቷል፡፡ “እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም” እንዲል /ሚል 3፥6/ በእርሱ ዘንድ ወረት የለም፡፡ አስቀድሞ ከተዓምራቱ ከምሥጢሩ አይለያቸውም ነበርና ብርሃነ መለኮትን ለማየት አበቃቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ለማወቅ፣ ለመማር፣ ለመጠየቅ ያሳዩት ትጋት ምስጢር ተገልጦላቸዋል፡፡ ይህ ምስጢር ለሦስቱ ደቀ መዛሙርት ተገልጦ የሚቀር አይደለም፡፡ እስከ ዓለም ፍፃሜ እግዚአብሔር ለመረጣቸው ሲገለጥ፣ በመረጣቸውም ሲነገር የሚኖር ነው፡፡ደቀ መዝሙሩ ጴጥሮስ “አልክድህም አልተውህም” የሚለው /ማቴ. 26፥35/ ቢወድደው አይደለምን? ፍቅሩን መግለጡ ለክብር አብቅቶታል፡፡ ሁለቱ ደቀ መዛሙርትም “ጽዋዬን ልትጠጡ አትችሉም” ቢላቸውም /ማቴ. 20፥22/ አንዳችን በቀኝ ሌላችን በግራ ሆነን አብረንህ እንሞታለን ሲሉ በምስጢር ለምነዋል፡፡ ሞታቸውን ከሞቱ ጋር መደመራቸው ፍቅራቸውን መግለጣቸው ነው፡፡ ፠፠፠ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#ነሐሴ_፲፪ #ቅዱስ_ሚካኤል_ንጉሥ_ቆስጠንጢኖስን_ረደቶ_በድል_ያነገሠበት_ዕለት ንግሥት ዕሌኒም በ272ዓ.ም ታላቁ ቆስጠንጢኖስን ወለደችለት፤ ቆስጠንጢኖስም ገና በወጣትነቱ የአባቱ እንደራሴ ሆኖ እንደሠራ አባቱ ሞተ፡፡ የአባቱ ባለሟሎችና ህዝቡ ተስማምተው የ፲፰ ዓመቱን ቆስጠንጢኖስን በአባቱ ቦታ ሐምሌ ፳፭ ቀን ፫፻ ዓ.ም በሮም ምዕራብ ክፍል በገላትያ አነገሡት፡፡ በጦር ሜዳዎች ብዙ የጀግንነት ሥራዎች ስለሠራ በሠራዊቱ ዘንድ ይወደድ ነበር፡፡ ንግሥት ዕሌኒ ልጅዋን ቆስጠንጢኖስን ከልጅነቱ ጀምሮ ስለክርስትና ሃይማኖትና ስለክርስቲያኖች መከራ ታስተምረው ስለነበር በክርስቲያኖች ላይ የነበረው አመለካከት በሮም ከነገሡት ቄሣሮች ሁሉ የተሻለ ነበር፡፡ በተለይም በ፫፻፲፪ ዓ.ም ከጠላቱ ከመክስምያኖስ ጋር ለመዋጋት "ምታ ነጋሪት ክተት ሠራዊት" ብሎ ለዘመቻ እንደተሰለፈ በራእይ በሰማይ ላይ "በዚህ የመስቀል ምልክት ጠላትህን ድል ታደርጋለህ; የሚል መስቀልና ጽሑፍ ስላየ ለሠራዊቱ ሁሉ #የመስቀል_ምልክት በመሣሪያቸውና በሰንደቅ ዓላማው ላይ እንዲያደርጉ አዘዘ፡፡ ወደያው ጦርነት ቢገጥም #በቲቤር_ወንዝ_ድልድይ ላይ ጠላቱን ድል ነሥቶ በጠቅላላው የሮም መንግስት ግዛቶች ሁሉ ገዥ ሆነ፡፡ ይኸውም የሆነው በመላእክት አለቃ #በቅዱስ_ሚካኤል ረዳትነት ነው፡፡ #ሚካኤል ማለት #መኑ_ከመ_እግዚአብሔ "እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?" ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ለፍጥረታት ሁሉ የሚራዳና የሚያዝን የምሕረትና የመዳኛ፤ የሰላም መልአክ ነው፡፡ ‹‹በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል›› (ዳን.፲፪፥፩) በማለት በነቢዩ ዳንኤል የተነገረ ሲሆን በሌላ ቦታ ‹‹ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ›› (ዳን. ፲፥፲፫) በማለት ያስረዳል፡፡ በድርሳነ ሩፋኤል ላይ እንደተገለጸው ሰባት ሊቃነ መላእክት ቢኖሩም አለቃቸው #ቅዱስ_ሚካኤል ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል አርምሞ ትዕግሥትን የሚወድ መልአክ ነው፡፡ ‹‹የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም፡፡›› ቅዱስ ሚካኤል ከእግዚአብሔር በተሰጠው ኃይል ዲያብሎስን ድል የነሣ መልአክ ነው፡፡ "በሰማይም ሰልፍ ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉ። ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ፥ አልቻላቸውምም፥ ከዚያም ወዲያ በሰማይ ስፍራ አልተገኘላቸውም። ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ፡፡" ራእ ፲፪፥፯-፱፡፡ #ታላቁ_ቆስጠንጢኖስ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል ረዳትነት ጠላቶቹን ሁሉ ድል ነሥቶ በጠቅላላው የሮም መንግሥት ግዛቶች ሁሉ ገዥ ከሆነ በኋላ በ፫፻ ዓመታት ውስጥ ለመጀመርያ ጊዜ ለክርስቲያኖች የነጻነት ዐዋጅ ዐወጀ፡፡ ክርስትናም ብሔራዊ ሃይማኖት ተባለች፡፡ ንግሥት እሌኒም በተፈጠረላት አመች ሁኔታ በመጠቀም #የጌታችን_መስቀል ከተቀበረበት ለማውጣት በ፫፻፳፯ ዓ.ም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች፡፡ ዕሌኒ ልጅዋ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ከሆነላት ወደ ኢየሩሳሌም ሔዳ መስቀሉን ለመፈለግ እንዲሁም በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ለማነጽ ለእግዚአብሔር ተሳለች፡፡ ከዚህ በኋላ #ቆስጠንጢኖስ_አምኖ በ፫፻፴፯ ዓ.ም #ተጠመቀ፡፡ ቅድስት ዕሌኒ ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች ከእርሷም ጋር ብዙ ሠራዊት ነበር፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፡፡ እኛንም በጸሎቱ የምንታመን ሁላችንን የመልአክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን ረድኤት በረከቱን ያሳድርብን፡፡ በጸሎቱ ይማረን፡፡ ስንክሳር ዘወርሃ ነሐሴ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958