Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 380 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 573,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 194 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 380 名订阅者。
根据 06 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 32,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.44%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.50% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 449 次浏览,首日通常累积 1 461 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 20。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 07 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 380
订阅者
-424 小时
-257 天
+3230 天
帖子存档
#ሰሙነ_ፋሲካ (#ከትንሣኤ_እስከ_ዳግም_ትንሣኤ)
(ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ)
ከትንሣኤ እሑድ ቀጥለው ያሉት ዕለታት ሰሙነ ፋሲካ ወይም ትንሣኤ እየተባሉ የየራሳቸው ምሥጢራዊ ስያሜ አላቸው፡፡ ይኸውም፡-
✞ #ሰኞ፤ ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
ጌታችን በሞትና ትንሣኤው ነፍሳትን ከሲኦል አውጥቶ ወደ ገነት አሻግሮ ለማስገባቱ መታሰቢያ ሆና «ፀአተ ሲኦል ማዕዶት» ትባላለች፡፡ ዮሐ. 19-18 ሮሜ. 5-10-17
የዳግም ትንሣኤው ማግሥት ያለችው ግን ገበሬው፤ ወንዶቹ እርሻ ቁፋሮውን፣ ንግዱን፣ ተግባረ እዱን ሁሉ ሴቶቹ ወፍጮውን፣ ፈትሉን፣ ስፌቱን የሚጀምሩባት ዕለት ስለሆነች «እጅ ማሟሻ» ሰኞ ትባላለች፡፡
✞ #ማክሰኞ፤ ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
የትንሣኤው ዕለት እሑድ ማታ ጌታችን በዝግ ቤት ገብቶ ለሐዋርያት ሲገለጽ ቶማስ ሐዋርያ አልነበረም ኋላ ከሔደበት ሲመጣ ሌሎቹ ሐዋርያት ትንሣኤውን ቢነግሩት እኔ ሳላይ አላምንም በማለቱ በዚህ ጥያቄው መሠረት በሳምንቱ ጌታችን በድጋሚ ስለተገለጸ ለዚህ መገለጹ መታሰቢያ ሆና ዕለቲቱ «በቶማስ» ተሰየመች፡፡ ዮሐ. 20-24-30
✞ #ረቡዕ፤ አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
ከሞተና ከተቀበረ አራት ቀን በኋላ ከመቃብር ጠርቶ ላሥነሣው፣ አላዓዛር መታሰቢያ የእርሱንም ተነሥቶ በማየት በጌታችን ብዙ ሕዝብ ስለአመነበት ቀኒቱ «አላዓዛር» ተብላ ትታሰባለች፡፡ ዮሐ. 11-38-46
✞ #ኀሙስ፤ አዳም ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡ የአዳም ተስፋው ተፈጽሞለት ከነልጅ ልጆቹ ወደቀደመ የገነት ክብሩ ለመግባቱ መታሰቢያ ሆና «የአዳም ኀሙስ» ተብላ ይኸው ትከበራለች፡፡ ሉቃ. 24-25-49
✞ #ዐርብ፤ ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በክርስቶስ ደም ተዋጅታ በተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ መታሰቢያ በመሆኗ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ዐርብ «ቤተ ክርስቲያን» ተብላ ትጠራለች፡፡ ማቴ. 26-26-29 የሐ. ሥራ. 20-28
በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
✞ #ቅዳሜ፤ ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ቀዳሚት ሕዝቡ ከአንዳንዱ በስተቀር ገበያ እንኳን ስለማይገበይባት «የቁራ ገበያ» የገበያ ጥፊያ ስትባል በቤተ ክርስቲያን ግን በዘመነ ሥጋዌው በገንዘባቸውና ጉልበታቸው ለአገለገሉት በስቅለቱ ዋይ ዋይ እያሉ እስከ ቀራንዮ ለተከተሉት፣ የትንሣኤው ዕለት ገና ከሌሊቱ ወደ መቃብሩ ሽቱና አበባ ይዘው በመገሥገሣቸው ትንሣኤው ከሁሉ ቀድሞ ለተገለጸላቸው ቅዱሳት አእንስት መልካም መታሰቢያ ሆና «አእንስት» ተብላ ትጠራለች፡፡ ሉቃ. 23-27-33፣ 24-1-01፣ ማቴ. 25-1-11
✞ #እሑድ- ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
(የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት)
+ + + መልካም በዓል!!! + + +
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
#ሰሙነ_ፋሲካ (#ከትንሣኤ_እስከ_ዳግም_ትንሣኤ)
(ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ)
ከትንሣኤ እሑድ ቀጥለው ያሉት ዕለታት ሰሙነ ፋሲካ ወይም ትንሣኤ እየተባሉ የየራሳቸው ምሥጢራዊ ስያሜ አላቸው፡፡ ይኸውም፡-
✞ #ሰኞ፤ ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
ጌታችን በሞትና ትንሣኤው ነፍሳትን ከሲኦል አውጥቶ ወደ ገነት አሻግሮ ለማስገባቱ መታሰቢያ ሆና «ፀአተ ሲኦል ማዕዶት» ትባላለች፡፡ ዮሐ. 19-18 ሮሜ. 5-10-17
የዳግም ትንሣኤው ማግሥት ያለችው ግን ገበሬው፤ ወንዶቹ እርሻ ቁፋሮውን፣ ንግዱን፣ ተግባረ እዱን ሁሉ ሴቶቹ ወፍጮውን፣ ፈትሉን፣ ስፌቱን የሚጀምሩባት ዕለት ስለሆነች «እጅ ማሟሻ» ሰኞ ትባላለች፡፡
✞ #ማክሰኞ፤ ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
የትንሣኤው ዕለት እሑድ ማታ ጌታችን በዝግ ቤት ገብቶ ለሐዋርያት ሲገለጽ ቶማስ ሐዋርያ አልነበረም ኋላ ከሔደበት ሲመጣ ሌሎቹ ሐዋርያት ትንሣኤውን ቢነግሩት እኔ ሳላይ አላምንም በማለቱ በዚህ ጥያቄው መሠረት በሳምንቱ ጌታችን በድጋሚ ስለተገለጸ ለዚህ መገለጹ መታሰቢያ ሆና ዕለቲቱ «በቶማስ» ተሰየመች፡፡ ዮሐ. 20-24-30
✞ #ረቡዕ፤ አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
ከሞተና ከተቀበረ አራት ቀን በኋላ ከመቃብር ጠርቶ ላሥነሣው፣ አላዓዛር መታሰቢያ የእርሱንም ተነሥቶ በማየት በጌታችን ብዙ ሕዝብ ስለአመነበት ቀኒቱ «አላዓዛር» ተብላ ትታሰባለች፡፡ ዮሐ. 11-38-46
✞ #ኀሙስ፤ አዳም ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡ የአዳም ተስፋው ተፈጽሞለት ከነልጅ ልጆቹ ወደቀደመ የገነት ክብሩ ለመግባቱ መታሰቢያ ሆና «የአዳም ኀሙስ» ተብላ ይኸው ትከበራለች፡፡ ሉቃ. 24-25-49
✞ #ዐርብ፤ ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በክርስቶስ ደም ተዋጅታ በተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ መታሰቢያ በመሆኗ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ዐርብ «ቤተ ክርስቲያን» ተብላ ትጠራለች፡፡ ማቴ. 26-26-29 የሐ. ሥራ. 20-28
በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
✞ #ቅዳሜ፤ ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ቀዳሚት ሕዝቡ ከአንዳንዱ በስተቀር ገበያ እንኳን ስለማይገበይባት «የቁራ ገበያ» የገበያ ጥፊያ ስትባል በቤተ ክርስቲያን ግን በዘመነ ሥጋዌው በገንዘባቸውና ጉልበታቸው ለአገለገሉት በስቅለቱ ዋይ ዋይ እያሉ እስከ ቀራንዮ ለተከተሉት፣ የትንሣኤው ዕለት ገና ከሌሊቱ ወደ መቃብሩ ሽቱና አበባ ይዘው በመገሥገሣቸው ትንሣኤው ከሁሉ ቀድሞ ለተገለጸላቸው ቅዱሳት አእንስት መልካም መታሰቢያ ሆና «አእንስት» ተብላ ትጠራለች፡፡ ሉቃ. 23-27-33፣ 24-1-01፣ ማቴ. 25-1-11
✞ #እሑድ- ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
(የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት)
+ + + መልካም በዓል!!! + + +
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
+*" #ሰማዕታተ_ኢትዮጵያ "*+
፠ በዛሬዋ በሚያዝያ 11 ቀን የኢትዮጵያ ሰማዕታት በሊብያ አረፉ፤ ይህም የሆነው በሚያዝያ 11 2007 ዓ.ም. ሲሆን፤ አይሲስ በተባሉ ተንባላት ኢትዮጵያውያኖቹ ክርስትናቸውን እንዲክዱ፥ ማዕተባቸውን እንዲበጥሱ ቢጠይቋቸውም እምቢ በማለታቸው፤ ሓሳባቸውን ለማስቀየር በግፍና በመከራ፤ በውኃ ጥምና በረሃብ ቢቀጧቸውም ልባቸውን ለአምላካቸው ያጸኑ መኾናቸውን ሲረዱ አንገታቸውን በሰይፍ መቷቸው፡፡
፠ አመ ዐሡሩ ወአሚሩ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለት አዕረፉ ሰማዕታተ ኢትዮጵያ:: በረከቶሙ የሃሉ ምስሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡
ከመዝ ኮነ በውስተ ሀገረ ሊብያ በዕሥራ ምዕት ወሰብዐቱ ዐመተ ምሕረት፡፡ በአሜሃ ዘመን ተንሥኡ ተንባላት እለ ስሞሙ አይሲስ በውስተ ሀገረ ኢራቅ ወሶርያ ወሊብያ ወየመን፡፡ አሐዙ ይቅትሉ ሰብአ ዘረከቡ ወፈድፋደሰ እለ ኮኑ ክርስቲያነ በእምነቶሙ፡፡
ብዙሓን ክርስቲያን ተመትሩ አርእስቲሆሙ በአይሲስ ወተወክፉ አክሊለ ስምዕ እምእላ ሀገራት፡፡ በዝ ዘመን ውእቱ ዘረከቦሙ አይሲስ ለሰብአ ኢትዮጵያ በውስተ ሀገረ ሊብያ እንዘ የሐውሩ ኀበ ሀገረ ኢጣልያ በእንተ መፍቅደ ልቦሙ፡፡ እሉ ከሀድያን ውሉደ ሰይጣን ወአራዊተ ገዳም አሐዝዎሙ ወአዘዝዎሙ ወአፍርሕዎሙ ከመ ይክሀዱ ስሞ ለኢሱስ ክርስቶስ፡፡
ወእምዝ ዘበጥዎሙ በዘዚአሁ ዝብጠታተ በእንተ ዘኮኑ ክርስቲያነ ርእዮሙ ማዕተበ ክሣዶሙ፡፡ ውእቶሙሰ አበዩ ይእዜኒ ክሂደ ሃይማኖቶሙ እመኒ አመከርዎሙ በረሐብ ወጽምዕ ወበካልኣን ኵነኔያት፡፡ ሶበ አበዩ ክሂደ ወሰድዎሙ ኀበ ምድረ በድው ኀበ አልቦ እክል ወማይ ከመ ይእመኑ እምጽንዐ ረሐብ ወጽምዕ፡፡
ወእምዝ ጠየቅዎሙ ከመ ይብትኩ ማዕተበ ክሣዶሙ ወይክሀዱ ስሞ ለእግዚአብሔር አምላኮሙ፡፡ እሉሰ ሰማዕታት ይእዜኒ አበዩ ክሂደ ስሞ ለፈጣሪሆሙ፡፡ አዲ ይቤልዎ ለአይሲስ "ኦ አይሲስ ለእመ ክህልከ ቀቲሎታ ለሥጋነ ኢትክል ቀቲሎታ ለነፍስነ፡፡ ኢንፈርሕሂ ወኢንደነግጽ እምብልሐ ሰይፍከ እስመ አቅዲሙ ነገረነ አምላክነ እንዘ ይብል ኢትፍርሕዎሙ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ ወለነፍስክሙሰ ኢይክሉ ቀቲሎታ፡፡"
አዲ ይቤለነ በውስተ ወንጌሉ ቅዱስ እስመ ኵሉ ዘከቀተለክሙ ይመስሎ ከመ ዘመሥዋዕተ ያበውእ፡፡ ይእዜኒ አንተ ላእኩ ለዲያብሎስ ፈጽም በላዕሌነ መልእክተከ ሰይጣናዌ ወአብእ መሥዋዕተከ ርኩሰ ለእምላክከ ሰይጣናዊ፡፡ ንህነኒ ናበውእ ክሣደነ ንጹሐ ለእምላክነ ዘፈጠረነ እስመ ነአምር ዘከመ ያነሥአነ በትንሣኤሁ ቅድስት አመ ዳግም ምጽአቱ፡፡
አይሲስኒ አላዊ መተሮሙ አርእስቲሆሙ በሰይፍ ወኮኑ ሰማዕተ በከመ ዛቲ ዕለት፡፡ ወእምዝ ተሀውከት ኵላ ኢትዮጵያ ወኵላ ዐለም እስመ ትርእየ ትእይንተ ጥብሐቶሙ ለሰማዕታት በመስኮተ ትእይንት፡፡ ኵሎሙ ሰብአ ኢትዮጵያ አስቆቀዉ ወበከዩ ብካየ መሪረ እንዘ ይገብሩ ሰላማዌ ትእይንተ በበአዕዋዲሁ ወበበፍኖቱ፡፡
ወይብሉ በበቃሎሙ "አይሲስ አይሲስ እንተ ትቀትሎሙ ለሰማዕታት: ወታውሕዝ ደመ ንጹሓን በበፍናዊሁ ከመ ደመ አክልብት: ይደልወከ ትቁም ውስተ ዐውደ ፍትሕ ሰማያዊ፡፡"
በዝንቱ ዘመን ቈስለ ልቡ ለህዝብ በሐዘነ ሥጋ እስከነ ይብል "ፍትሐ ጽድቅ ዘዐርገት ውስተ ሰማይ ከመ ትንበር ምስለ ዘፈጠራ እግዚአብሔር እስመ ኢረከበት ውስተ ዛቲ ምድር ኀበ ትነብር ወኀበሂ ታጸልል፡፡ ናሁ ይጸርሕ ደሞሙ ለሰማዕታት ቅድመ ገጹ ለኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይረድ ፍትሐ ርትዕ ዲበ ምድር ወይሠረው አሲስ እምውስተ ገጻ ለምድር፡፡"
በረከቶሙ: ወጽንዐ ገድሎሙ ለእሉ ሰማዕታት ይሕድር ላዕሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡
**ሰላም ለክሙ በቃለ ማሕሌት ወእንዚራ፤
ምስለ ሰማዕታት ዘግብጽ መከራቲክሙ ዘሐብራ፡፡
ቅዱሳን ሰማዕታት ዘኦርቶዶሳዊት ሐራ፤
እፎ ክህልክሙ ተዐግሦ ጽኑዕ መከራ፤
እስከ ክሳውዲክሙ በአሲስ ተመትራ፡፡
(በአንድ ስሙን ባልጠቀሰ /ባልታወቀ/ ጸሓፊ የተጻፈ)
፠ ሰማዕታት ከኾኑት መካከል የቂርቆስ ልጆች አብዛኛው ስላሉበት የሚከተለውን ግጥም ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ በሚያዝያ 13 2007 ዓ.ም. ገጥሞላቸዋል፡፡
#የቂርቆስ_ልጆች
የቂርቆስ ልጆች መች ልብ አላቸው፤
ሁሌም ሁከት ነው የለት ሥራቸው፤
ይኸው ዛሬ ደግሞ እንደለመዱት፤
የኢትዮጵያን አንጀት በኀዘን ጎመዱት፡፡
የቂርቆስ ልጆች ያውቃሉ አድማ፤
ሌላው አይሸሽም አንዱ ሲደማ፤
ይኸው ባደባባይ ጎን ለጎን ቆመው፤
ሀገር አሳመሙ እነሱ ታመው፡፡
ድሮም አልወደው እኔ ያንን ሰፈር፤
ሰው እንዴት ይሠራል የሕፃን ነገር፡፡
ሕፃኑን ቂርቆስ እያዩ አድገው፤
አይቅርብን አሉ እሱ ያደረገው፡፡
ይኸው እንደ ቂርቆስ እንደ ኢየሉጣ፤
እነሱም አሉ የመጣው ይምጣ፡፡
አይ የቂርቆስ ልጆች፤
ሕፃኑን ሰምታችሁ እናንተም ትሔዱ?
እሱ እንደሆነ ይህ ነው ልማዱ፡፡
እናቱን እንኳን እየጎተተ፤
እንሙት ያለ የወተወተ፤
የሱን ምክር ቃል ስትሰሙ አድጋችሁ፤
ይኼው ይህ ሆነ መጨረሻችሁ፡፡
ሌላ ምን እላለሁ፤!?
እግዜር ይይላችሁ፡፡
የፊጥኝ ታስራችሁ መነዳታችሁን፤
ስለ ክርስቶስ ስም መመስከራችሁን፤
በባሕር ዳርቻ መንበርከካችሁን፤
እንደ በግ በስለት መቈረጣችሁን፤
በጥይት እሩምታ መደብደባችሁን፤
እግዜር ይይላችሁ!፡፡
የሕፃኑ መንገድ ያዋጣል ካላችሁ፤
ወደ እኛ እንዳትመጡ ቤት አለን ብላችሁ፤
ሕፃኑ ካለበት ማረፊያ ይስጣችሁ!፡፡
እንዲሁም፤
የቂርቆስ ልጆች እነ ሞት አይፈሬ፤
እርግፍ እርግፍ ያሉት እንደ ሾላ ፍሬ፡፡ ተብሎ ቅኔያዊ የሙሾ ግጥም ተገጥሞላቸዋል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
✿ ሰኞ መከሩ፤
ማግሰኞ ዘከሩ፤
ረቡዕ ዶለቱ፤
ኀሙስ ዐገቱ፤
ዐርብሳ ሰቀሉታ፤
ቅዳሜሳ ተንቀሳቀሰሳ፤
እሑድሳ እንጣጥ ብሎ ተነሣ፥ ጌታዬ አንበሳ፨
/ብሂለ ትምህርተ ባሕረ ሐሳብ/
✿ “አንሥአኒ በትንሣኤከ፤ አቤቱ በትንሣኤህ አንሣኝ።”
/ቅዱስ ያሬድ/
✿ ሙታንን ያስነሣ፤
በልዩ ትንሣኤ ተነሣ።
✿ ሞት ዳግም ላይገዛው ተነሣ፤
መቃብርም ድል ተነሣ።
✿ የሞት መዝጊያ ተሰበረ፤
የመቃብር ድንጋይም ተንከባለለ፨
/ቅ.ዮሐ.አፈ./
ከየቀ.ደ.ሰ. መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወትሰንበት ትምህርት ቤት፡፡
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ (https://t.me/medihanaelem
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
✿ ሰኞ መከሩ፤
ማግሰኞ ዘከሩ፤
ረቡዕ ዶለቱ፤
ኀሙስ ዐገቱ፤
ዐርብሳ ሰቀሉታ፤
ቅዳሜሳ ተንቀሳቀሰሳ፤
እሑድሳ እንጣጥ ብሎ ተነሣ፥ ጌታዬ አንበሳ፨
/ብሂለ ትምህርተ ባሕረ ሐሳብ/
✿ “አንሥአኒ በትንሣኤከ፤ አቤቱ በትንሣኤህ አንሣኝ።”
/ቅዱስ ያሬድ/
✿ ሙታንን ያስነሣ፤
በልዩ ትንሣኤ ተነሣ።
✿ ሞት ዳግም ላይገዛው ተነሣ፤
መቃብርም ድል ተነሣ።
✿ የሞት መዝጊያ ተሰበረ፤
የመቃብር ድንጋይም ተንከባለለ፨
/ቅ.ዮሐ.አፈ./
#ክርስቶስ_ተንሥአ_እሙታን
(ክርስቶስ ከሙታን መካከል ተነሣ)
#በዐቢይ_ኀይል_ወሥልጣን
(በታላቅ ኀይልና ሥልጣን)፤
#አሰሮ_ለሰይጣን_ (ሰይጣንን አሰረው)
#አግዐዞ_ለአዳም(አዳምን ነጻ አወጣው)፤
#ሰላም (ሰላም ፍቅርና አንድነት)
እምይእዜሰ (ከዛሬ ጀምሮ)
#ኮነ (ኾነ)
#ፍሥሐ_ወሰላም (ሰላምና ደስታ ኾነ)፡፡
፠ በማዕረግ ከፍ ያለው ካህንም፤ ከላይ ያለውን ዐውጆ ሲያበቃ «#ነዋ_መስቀለ_ሰላም» እያለ መስቀል ሲያሳልም
ካህናትና ሕዝቡም «#ዘተሰቅለ_ቦቱ_መድኀኔ_ዓለም» እያሉ ይሳለማሉ፡፡
በማዕረግ ከፍ ያለው ካህንም፤ «#እግዚአብሔር_ይፍታ» ይላል፡፡ ግብረ ሕማማት ሲነበብበት ከሰነበተው ጠበልም ይረጫል፡፡ የተረፈውንም ጠበል ሕዝቡ ለበረከት ወደየቤቱ ይወስደዋል፡፡
፠ ከዚያም ልኡካኑ ለቅዳሴ ይዘጋጃሉ፤ ሊቃውንት ደባትር መዘምራንም ምስማክ፥ መወድሱን ካዜሙ በኋላ በመቋሚያ ይዘምሙታል፡፡ አያይዞም በዓመት ፫ት ጊዜ የሚዘመረውን «ይትፌሣሕ ሰማይ …» የተባለውን መዝሙር ቃኝተው ከዘመሙ በኋላ «ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ፤ ተኀፂባ በደመ ክርስቶስ = ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ ፋሲካውን ታደርጋለች፡፡» እያሉ ይጸነጽላሉ፡፡ አያይዘውም የመዝሙሩን ሰላም (ፍጹመ ንጉሠ ኰነንዎ …)ን ይጸፋሉ፡፡
፠ ወዲያው መንፈቀ ሌሊት ሲሆን ቅዳሴ ተቀድሶ ይቈረባል፡፡ ከዚያም ዕጣነ ሞገር = በዕጣን ፈንታ ቅኔው ተቁሞ ሠርሖተ ሕዝብ = የሕዝብ ስንብት ከሆነ በኋላ ለመፈሰክ ሕዝቡ ወደየ ቤቱ ይሔዳል፡፡
#የትንሣኤ_አከባበር_በዕለቱ
፠ ሕዝቡ በየቤቱ፣ ካህናቱም ከቤተ ክርስቲያን በየአካባቢው ባህል በተለይ አክፋዮች መጀመሪያ ቅባት አጥቶ የሰነበተ ሆድ እንዲለሰልስ የተሞቀ የተልባ ጭልቃ ይጠጣና የሹሮ ወጥ በቅቤ፣ በአይብ፣ የበረታም በዶሮ ወጥ፣ ወይም በበግና በከብት ሥጋ ወጥ ይገድፋል፡፡
፠ በእርጎ፣ በአይብ የተደራረበ እንጀራ በግፍልፍል የሚገድፉም አሉ፡፡ በአንዳንድ የሰሜኑ ሀገራችን ደግሞ የተልባ፣ የኑግና የሱፍ ጭልቃ ከማር ጋር ታሽቶ ከተጠጣ በኋላ በእርጎ፣ በአይብ፣ በወተት፣ በቅቤና ድልህ በተቀባ እንጀራ ይገድፋሉ፡፡
፠ በዋልድባ ገዳም ከዓመት ዓመት ምግቡ ቋርፍ ብቻ መሆኑ ይታወቃል፤ ነገር ግን ለትንሳኤ በዓል ከሃገራችን ካሉ ቦታዎች በተለየ ሁኔታ በዓሳ ይገድፋሉ፤ ዓሳው ሲዘጋጅም ሙሉ ለሙሉ ሆድ ዕቃው ሳይወጣ ተወቅጦ ነው፡፡
፠ ሊነጋጋ ሲልም ከጾሙ አጋማሽ ጀምሮ ወንዱ ለእርድ የሚሆነውን ሰንጋውን፣ ሲቀልብ፣ በጉን ፍየሉን ሲሞክት ዶሮውን ሲመርጥ፣ ሲገዛ ሲለውጥ ሰንብቶ ነበርና በግልም በኅብረትም ያ ይታረዳል፡፡
፠ ሴቶችም ቅቤውን ሲያነጥሩ፣ በርበሬውን ሲደልሁ፣ ለእንጀራና ዳቦ የሚሆነውን ዱቄት ሲያዘጋጁ ለጠላ የሚሆነውንም እኸል ሲያሰናዱ አይቡን በልዩ ልዩ ቅመም መጣጣ ሲያደርጉና ባዶ ማለትም ወገሚት የተባለውን በሽንኩርት፣ በጤና አዳም፣ ጣዕሙ እንዳይለወጥ ሲቀምሙ፤ እንደ መከለሻ፣ ጥቁር አዝሙድ የመሳሰሉትንም ሰንብተው ዝግጅቱ ተከናውኖ ነበር፡፡
፠ ጧትም ይህ የመግደፊያ ዝግጅት በየቤታቸው ለሌላቸው ድኾች በየመንደሩ እየተዞረ «እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታላችሁ» እየተባለ ከሥጋውም፣ ከአይቡም፣ ከቅቤውም ከመጣጣሙም፣ ከእርጐውም ይታደላል፡፡
፠ ከትንሣኤ እሑድ ጀምሮ እስከ ዳግም ትንሣኤ ድረስ ሕዝበ ክርስቲያኑ «እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታላችሁ» እየተባባለ በመጠራራት ዐብሮ ሲበላ ሲጠጣ ልዩ ልዩ ጨዋታ ሲጨዋወት ለንስሐ አባትና ለሽማግሌዎች፤ ለወላጅ አባትና እናት፤ ለወንድምና ለእኅት ለወዳጅ ዘመድም የአክፋይ ዳቦ፣ ወይም የሥጋ ወጥና የድሮ ወጥ፣ ግፍልፍል ሲወስድ ይሰነብታል፡፡
፠ የቻለም ከትንሣኤ እስከ ዳግም ትንሣኤ እየተገባባዘ በዓሉን በፍስሐና በሐሴት ሲያከብር ይከርማል፡፡
‹‹ሕያው ተንሥአ እሙታን (ሕያው ከሙታን ተነሣ፡፡)›› /ጾመ ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ/
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
እንኳን በሰላምና በጤና አደረሰን፥ አደረሳችሁ፡፡
#ፋሲካ_ፋሲካ_ፋሲካ፤
#ተዝካረ_ትንሣኤሁ_ለክርስቶስ፡፡ /ቅዱስ ያሬድ/
#ትንሣኤ_ትርጕም_በዓሉና_አከባበሩ_
(ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል
ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ)
«ትንሣኤ» የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡ መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ የሚለው ግስ ሲሆን፡፡ «ትንሣኤ» ማለት = መነሣት፥ አነሣሥ፥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡
«ትንሣኤ» በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዓይነቱ ሲተረጐም ፭ት ክፍል አለው፡፡
፩ኛ) «ትንሣኤ» ማለት ኅሊና ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት ተዘክሮተ እግዚአብሔር ነው፡፡
፪ኛ) «ትንሣኤ» ማለት ልቡና ማለት ነው፡፡ የዚህም ምሥጢሩ ቃለ እግዘብሔርን መስማትና በንስሐ እየታደሱ በሕይወት መኖር ነው፡፡
፫ኛ) «ትንሣኤ» ለጊዜው የሙታን በሥጋ መነሣት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ድጋሚ ሞት ይከተለዋል፡፡
፬ኛ) «ትንሣኤ» የክርስቶስ በገዛ የባሕርይ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣት ነው፡፡ የዛሬው ትምህርታችንም ይህንን መሠረት ያደረገ ነው፡፡
፭ኛው)ና የመጨረሻው «የትንሣኤ» ደረጃም የባሕርይ አምላክ የጌታችን የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን «ትንሣኤ» መሠረት ያደረገ «ትንሣኤ ዘጕባኤ» ነው፡፡ ይህም ከዓለም ኅልፈት በኋላ ሰው ሁሉ እንደየሥራው ለክብርና ለውርደት፥ ለጽድቅና ለኩነኔ በአንድነት የሚነሣው የዘለዓለም ትንሣኤ ይሆናል፡፡
፠ ወደተነሣንበት ርዕስ ስንመለስ የትንሣኤ በዓል በቃሉም ምሥጢር በይዘቱም ስለሚመሳሰሉ ጥላው ምሳሌውም፣ ስለሆነ «ፋሲካ» ተብሎ ይጠራል፡፡
«#ፋሲካ_» ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ «ፌሳሕ» በጽርዕ (በግሪክኛ) «ስኻ» ይባላል፡፡ በግእዝና በዐማርኛ ፍሥሕ ዕድወት = ማዕዶት፣ በዓለ ናእት = የቂጣ በዓል፣ እየተቸኮለ የሚበላ መሥዋዕት፣ መሻገር፣ መሸጋገር ማለት ነው፡፡ በእንግሊዝኛ «ስኦቨር» ይሉታል፡፡ የዚህም ታሪካዊ መልእክቱ በዘመነ ኦሪት ይከበር የነበረው በዓለ ፋሲካ እስራኤል ዘሥጋ ከግብጽ የባርነት ቀንበር ወደነፃነት የተላለፉበት፣ ከከባድ ሐዘን ወደ ፍጹም ደሰታ የተሸጋገሩበት በዓል ነበር፡፡ በዚህ ኦሪታዊ ምሳሌ በዓል አሁን አማናዊው በዓል «ትንሣኤ» ተተክቶበታል፡፡
በዓለ ትንሣኤ በዘመነ ሐዲስ የምንገኝ እስራኤል ዘነፍስ የሆንን ምዕመናነ ክርስቶስ ትንሣኤውን የምናከብረው፤
በእርሱ ትንሣኤ ከኀጢአት፤ ወደ ጽድቅ፣
ከኀሳር ፥ ከውርደት፤ ወደክብር፣
ከጠላት ሰይጣን አገዛዝ፤ ወደ ዘለዓለማዊ ነፃነት፣
ከአደፈ፥ ከጐሰቆለ አሮጌ ሕይወት፤ ወደ ሐዲስ ሕይወት የተሻገርንበት ታላቅ መንፈሳዊ የነፃነት በዓል ነው፡፡ ስለዚህም እኛ ክርስቲያኖች የትንሣኤን በዓል በታላቅ ደስታና መንፈሳዊ ስሜት እናከብረዋለን፡፡ ስለዚህም ከበዓላት ሁሉ የበለጠ ሆኖ ይታያል፡፡
#የበዓሉ_አከባበር_«እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን»
መድኀኒታችን ሞትን በሞቱ ድል መትቶ፣ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ በሥልጣኑ የተነሣው በእለተ እሑድ፥መጋቢት 29፥ በ34 ዓ.ም እንደሆነ ታሪከ ቤተ ከርስቲያን ያስረዳል፡፡
የትንሣኤ በዓል መከበር የጀመረው በቅዱሳን ሐዋርያትና በሰብዐ አርድእት፣ ኋላም በየጊዜው በተነሡት ሊቃውንትና ምእመናን ነው፡፡ ድምቀቱና የአከባበር ሥርዐቱ ይበዛ ይቀነስ እንደሆን እንጂ መከበሩ ተቋርጦ አያውቅም፡፡ እንደ ዋልድባ፣ ማኅበረ ሥላሴ፣ ኢየሩሳሌም ባሉ ታላላቅ ገዳማት ደግሞ በዓሉ እጅግ በጣም በታላቅና በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡
#የበዓሉ_አከባበር_ከዋይዜማው_ጀምሮ_እስከ_ሌሊት_የሚከተለውን_ይመስላል፤
በዋይዜማው ማታ በ2 ሰዓት «ለጸሎት ተሰብሰቡ» የሚል ደወል ድምፅ ይደወላል፡፡ እንደ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ባሉ ታላላቅ አድባራት የተጋብኦ ከበሮ ይመታል፡፡
ካህናቱ ዲያቆናቱና ምዕመናኑ ነጭ ልብስ ይልበሱ፤ ጧፍ ያብሩ፤ ዲያቆናት ጥላ ያጥሉ፡፡
በላይ ቤት አቋቋም በሚቆሙ፤ የነቢያት ጸሎት የለም
/በታች ቤት/፤ የነቢያት ጸሎት (ጸሎተ ሐና፣ ጸሎተ ሕዝቅያስ፣ ጸሎተ ምናሴ፣ ጸሎተ ዮናስ፣ ጸሎተ ዳንኤል፣ ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅ፣ ጸሎተ ዕንባቆም፣ ጸሎተ ኢሳይያስ፣ ጸሎተ እግዝእትነ ማርያም፣ ጸሎተ ዘካርያስ፣ ጸሎተ ስምዖን) ይድገሙ፡፡
ውዳሴ ማርያምንና ክስተተ አርያምን በዜማ ያድርሱ፡፡
‹‹ተፈሥሒ ማርያም ለአዳም ፋሲካሁ›› የሚለውን ግጥማዊ የደስታ መዝሙር ይዘምራሉ፡፡
መልክአ ሥዕል ከትንሣኤ እስከ በዓለ ፶ ድረስ አይደረስም
እሰግድ ለኪ ብለህ ተዓምረ ማርያምና ተዓምረ ኢየሱስን አንብብ እንዳበቃ ጸሎተ አኰቴት ይደርሳል፡፡
ዲያቆኑ ነጭ ልብሰ ተክህኖ ለብሶ፥ አክሊል ደፍቶ፥ የመጾር መስቀል ይዞ፥ እንደ እርሱ ነጭ ልብሰ ተክህኖ በለበሱ ደማቅ የጧፍ መብራት በሚያበሩና ድባብ ፥ ጃንጥላ በያዙ ሁለት ዲያቆናት በግራ በቀኝ ታጅቦ ከመቅደስ ብቅ ብሎ በቅድስት ይቆማል፡፡ (ይህም በጌታችን መቃብር በራስጌና በግርጌ በታዩት መላእክት ምሳሌ ነው፡፡ ዮሐ.20-12) ቀጥሎም በመዝሙረ ዳዊት /መዝ.፸፯፥፳፭/ ያለውን፤
‹‹ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃሕ እምንዋም፤
ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን፤
ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ፡፡
(ትርጕም፤ እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ፤ የወይን ስካር እንደተወው ኀያል ሰውም፣ ጠላቱን በኋላው ገደለ፡፡» የሚለውን ምስባክ ይላል፤
ካህናቱና ሕዝቡ ከበሮ እየመቱና እያጨበጨቡ በእርጋታ እያጨበጨቡ የምስባኩን ተሰጥኦ ይመልሱ፡፡
ምስባኩንም በዲያቆኑ 2 ጊዜ በመላው ካህናትም 2 ጊዜ ለመጨረሻ ጊዜ ዲያቆኑም መላው ካህናትም አንድ ጊዜ ብለው 5 ጊዜ ይሆናል፡፡ 5,500 ዘመን ሲፈጸም በጌታችን ሞትና ትንሣኤ ዓለም ለመዳኑ ምሳሌያዊ ማስረጃ ነው፡፡
ቀጥሎም ካህኑ ትንሣኤውን የሚያበሥር ወንጌል ከማቴዎስ፣ ከማርቆስና ከሉቃስ አውጥቶ ያነባል፡፡ ከዮሐንስ ወንጌል ያለው የትንሣኤው ወንጌል ኋላ ለቅዳሴው ጊዜ ይቆያል፡፡ ዮሐ. 20፥1-9
በማስከተል ከሊቃውንት ደባትር መዘምራን የተመደበው መዘምር የዲያቆኑን መፆር መስቀል ይዞ «ትንሣኤከ ለእለ አመነ» የሚለውን እስመ ለዓለም ከቃኘ በኋላ ለበዓሉ ተስማሚ የሆነው 2 አርያም (ሃሌ ሉያ ለአብ፥… የሚለው) ተመርቶ በመቋሚያ ይዘመማል፤
በማስከተልም «ዮም ፍሥሐ ኮነ በሰንበተ ክርስቲያን፣ እስመ ተንሥአ ክርስቶስ እሙታን = ክርስቶስ ከሙታን ቀድሞ ተለይቶ ተነሥቷልና በሰንበተ ክርስቲያን ዛሬ ደስታ ሆነ፡፡...» የሚለውን አንገርጋሪ ያመለጥናል (ይመራል)፡፡ በግራ በቀኝ እየተነሣ መዘምራኑም ይዘምሙታል ይጸፉታል፤ ያለዝቡታል፤ ወዲያውም «ብርሃነከ ፈኑ፤ ለእለአመነ = ለአመነው ብርሃንህን ላክልን፡፡» የሚለውን እስመ ለዓለም እየወረቡ መብራት እያበሩ ዑደት ያደርጋሉ = ቤተ ክርስቲያኑን በውስጥ ይዞራሉ፡፡
በዚህ ጊዜ «በጨለማ የነበራችሁ ሕዝቦች ኑ የትንሣኤውን ብርሃን እዩ፣ ብርሃኑንም ወስዳችሁ የብርሃኑ ተካፋይ ሁኑ፡፡» እያለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስታዘጋጅ የሰነበተችውን ጧፍ ለምዕመናን እንዲያበሩ ታድላቸዋለች፡፡ ሕዝቦቹም ካህናቱን ተከትለው በታላቅ ደስታና ድምቀት ዑደት ያደርጋሉ፡፡
፠ መዘምራኑና ካህናቱ ከዑደት ሲመለሱ «ይእቲ ማርያም» የተባለው የኪዳን ሰላም ይጸፋና ኪዳን ተደርሶ ሲያበቃ እንደ በማዕርግ ከፍ ያለው ካህን ዘለግ ባለ ድምፅ በንባብ የሚከተውን ፫ት ጊዜ ሲያውጅ ካህናቱና መዘምራኑም ይቀበሉታል፤
#ቀዳሚት_ሥዑር_ (#ሥዑር_ቅዳሜ)፤ #ገብረ_ሰላመ_፤ (#ለምለም_ቅዳሜ)
#ሰንበት_ዐባይ #ቅዱስ_ቅዳሜ፤ #ቀዳሚት_ሰንበት
#ቀዳሚት_ሰንበት፤ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ ከፈጸመ በኋላ ያረፈባት ስለሆነች፤ የእግዚአብሔር የዕረፍት ዕለት፤ ቀዳሚት ሰንበት (የዕረፍት ቀን) ትባላለች፡፡
#ሰንበት_ዐባይ (ታላቋ ሰንበት)፤ የመጀመሪያዋ ሰንበት በመሆኗ ታላቋ ሰንበት ትባላላች፡፡
#ቀዳሚት_ሥዑር_ (#ሥዑር_ቅዳሜ)፤ እግዚአብሔር ሥነ ፈጥረትን ከመፍጠር ዕረፍት እንዳደረገባት ዅሉ፣ የፍጥረት ርእስ የኾነውን አዳምን ለማዳን ሕማምና ሞት የተቀበለው አምላካችን ክርስቶስ በከርሰ መቃብር አርፎባታል፡፡ (ማቴ. ፳፯፥፷፩)፡፡
፠ ‹ሥዑር› የተባለችበት ምክንያትም በዓመት አንድ ቀን ስለምትጾም (የጾም ቀን በመኾኗ) ነው፡፡
የጌታችን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ወዳጆቹ ቅዱሳን ሐዋርያትና ሌሌችም የጌታ ወዳጆች ጌታችን ተላልፎ ከተሰጠበት ዕለት ጀምሮ ብርሃነ ትንሣኤውን እስኪያዩ ድረስ እህል ውኃ በአፋቸው አልዞረም፡፡ ይመኩበትና ተስፋ ያደረጉት የነበረ አምላካቸው በመቃብር ስላረፈ ዕለቷን ሞቱን በማሰብና ትንሣኤውን በመናፈቅ በጾም አክብረዋታል፡፡
፠ የቻልን ሕዝበ ክርስቲያንም ይህን መነሻ በማድርግ ከዐርብ ጀምረን በማክፈል (በመጾም) እህል ውኃ ሳንቀምሱ ለሁለት ቀናት እናድራለን (እንካፍላለን)፡፡ እንደ ዋልድባና ማኅበረ ሥላሴ ባሉ ገዳማት ያሉ ታላላቅ አባቶችና ወንድሞች ደግሞ ከሆሳዕና አንዳንዶችም ከዕለተ ረቡዕ ጀምረው ለ7ት ቀናት ወይም ለ3ት ቀናት ያከፍላሉ፡፡
#ገብረ_ሰላመ_፤ (#ለምለም_ቅዳሜ)
ቅዳሜ የጠዋቱ ጸሎት ሲፈጸም ካህናቱ ‹‹ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፤ (በመስቀሉ ሰላምን አደረገ፥ መሠረተ)›› እያሉ በቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰቡ ምእመናን የምሥራች ቄጠማ ያድላሉ፡፡
፠ ቄጠማው በኖኅ ዘመን በንፍር ውኃ ምደር በተጠለቀለቀች ጊዜ፤ ኖኅ ወደ መርከብ ይዟቸው ከገባው እንስሳት መካከል የውኃውን መጉደል ለመረዳት ርግብን በመርከብ መስኮት አሾልኮ ልኮ እርሷም ቄጠማ በአፏ ይዛ በመመለስ የምሥራች ምልክት፥ የውኃውን መድረቅ እንደተነገረችውና እንደተደሰተ ሁሉ (ዘፍ. ፱፥፩-፳፱)፡፡ ‹‹በክርስቶስ ሞት፤ ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ፤›› ስንል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቅዳሜ ጠዋት ደባትር መዘምራን ዝማሬን ካቀረቡ በኋላ ለልጆቿ ቄጠማ ታድለናለች፡፡ የምሥራች ተምሳሌት የኾነውን ቄጠማም፤ ከሲኦል ቃጠሎ ወደ ጥንተ ማኅደራችን ገነት መመለሳችንን ለመመስከር በግንባራችን እናስረዋለን፡፡
#ቅዱስ_ቅዳሜ፤ ለ5500 በሲኦል ሲማቅቁ የነበሩ ነፍሳትን ሰላም ለሁላችሁን ይሁን ብሎ ወደ ገነት አስገብቷቸዋልና፤ ይህች ቅዳሜ ቅዱስ (የተለየች) ቅዳሜ ትባላለች፡፡
አውረድዎ፥ አውረድዎ፥ አውረድዎ እምዕፅ፤
ወአምጽኡ አፈዋተ ከርቤ ሕዉስ፡፡
ሃሌ ሉያ ዮሴፍ ወኒቆዲሞስ ገነዝዎ ለኢየሱስ፤
በሰንዱናት ለዘተንሥአ እሙታን፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
የማርያም መቀነት (ቀስተ ደመና) በታላቁ ደብር ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ዳግማዊ ቀራንዮ፡፡
፠ እሠይም ቀስትየ በውስተ ደመና ‹‹ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ መካከል ሁሉ ያለውን የዘለዓለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ።›› /ዘፍ .፱፥፲፮/
፠*፠ በርካታ ቅዱሳን (አብርሃ ወአጽብሃ፣ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ ቅዱስ ላልይበላ፣ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ረድኦቻቸው፣ አቡነ ተክለ ሐዋርያት፣ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ አቡነ በኪሞስ፣ አቡነ ኤልያስ ዘእንጦጦ /ዘጋራ መድኀኔዓለም/፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫና ረድኦቻቸው፣ ……….. ) ሌሎችም በርካታ ቅዱሳን በኪደተ እግራቸው እየተመላለሱ የባረኳት መዲናችን አዲስ አበባ ላይ ዛሬ ሚያዝያ 9/2012 ዓ.ም. (በሌሊት አቈጣጠር በ19፤ በጨረቃ በ23ኛው፤ አበቅቴ 6 በሆነበት) በዕለተ ዐርብ፥ በበዓለ ስቅለት ከቀኑ 11 ሰዐት ላይ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ 2ት ቀስተ ደመናዎች (የማርያም መቀነቶች) አጠገብ ለአጠገብ በአንድ ላይ ሆነውና ሕብር ሠርተው፥ በምሥራቅ መታየት ጀምረው ደብራችንን ጨምሮ በመላዋ ከተማ እንደ ድባብ ከአንዱ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ረብቦ አምሽቷል፡፡ በአዲስ አበባ ላይ ቀስተ ደመና ከታየ በርካታ ጊዜያትንም አሳልፎ ነበር፡፡
፠ ‹‹ምልክትንም ለመልካም ከእኔ ጋር አድርግ የሚጠሉኝ ይዩ ይፈሩም፥ አቤቱ፥ አንተ ረድተኸኛልና፥ አጽንተኸኛልምና።›› /መዝሙር 86፥17/
፠ ‹‹እግዚአብሔር መልካም ነው፤ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል›› /ትንቢተ ናሆም 1፥7/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
፠ እሠይም ቀስትየ በውስተ ደመና፡፡
፠ ‹‹ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ መካከል ሁሉ ያለውን የዘለዓለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ።›› /ዘፍ .፱፥፲፮/
፠*፠ በርካታ ቅዱሳን (አብርሃ ወአጽብሃ፣ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ ቅዱስ ላልይበላ፣ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ረድኦቻቸው፣ አቡነ ተክለ ሐዋርያት፣ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ አቡነ በኪሞስ፣ አቡነ ኤልያስ ዘእንጦጦ /ዘጋራ መድኀኔዓለም/፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫና ረድኦቻቸው፣ ……….. ) ሌሎችም በርካታ ቅዱሳን በኪደተ እግራቸው እየተመላለሱ የባረኳት መዲናችን አዲስ አበባ ላይ ዛሬ ሚያዝያ 9/2012 ዓ.ም. (በሌሊት አቈጣጠር በ19፤ በጨረቃ በ23ኛው፤ አበቅቴ 6 በሆነበት) በዕለተ ዐርብ፥ በበዓለ ስቅለት ከቀኑ 11 ሰዐት ላይ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ 2ት ቀስተ ደመናዎች (የማርያም መቀነቶች) አጠገብ ለአጠገብ በአንድ ላይ ሆነውና ሕብር ሠርተው፥ በምሥራቅ መታየት ጀምረው በመላዋ ከተማ እንደ ድባብ ከአንዱ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ረብቦ አምሽቷል፡፡ በአዲስ አበባ ላይ ቀስተ ደመና ከታየ በርካታ ጊዜያትንም አሳልፎ ነበር፡፡
/ፎቶዎቹ፤ ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ላይ የተነሡ/
፠ ‹‹ምልክትንም ለመልካም ከእኔ ጋር አድርግ የሚጠሉኝ ይዩ ይፈሩም፥ አቤቱ፥ አንተ ረድተኸኛልና፥ አጽንተኸኛልምና።›› /መዝሙር 86፥17/
፠ ‹‹እግዚአብሔር መልካም ነው፤ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል›› /ትንቢተ ናሆም 1፥7/
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም https://t.me/medihanaelem
#ኢ. #ና. #ን. #አ.
፠ ሮማዊው ገዢ ጲላጦስ ጌታችንን በዳዊት ከተማ በጽዮን በቀራንዮ መካከል እንዲሰቀል አሳልፎ ከሰጠና ካሰቀለው በኋላ፤ ከመስቀሉ በላይ የሚጻፈውን የተለመደ የክስ ጽሕፈት (ሮማውያን በስቅላት የሚቀጡትን ሰው ለሞት ያበቃው ክስ ምን እንደሆነ በሰሌዳ ጽፈው በመስቀሉ ላይ ከፍ አድርገው የማሳየት ልማድ ነበራቸው፤ በዚያ ሥፍራ የሚያልፉ ሰዎችም ሁሉ የክሱን ጽሕፈት እያነበቡ ስለ ተሰቀለው ሰው ማንነትና ወንጀል ይረዱ ነበርና) ከቤቱ ቁጭ ብሎ ሲያስጨንቁት ያረፈዱትን የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ለመበቀል ነበር በሰሌዳ ላይ ያረቀቀው፡፡
፠ የተጻፈውን መግለጫ የሚያነቡትም ‹አይሁድ ነጻ የሚያወጣቸውን የገዛ ንጉሣቸውን ሰቀሉ› ብለው እንዲሳለቁባቸው፤ ክርስቶስን እንደ ክፉ ወንጀለኛ እንዲታይና እንዲዋረድ ፈልገው ላሰቀሉት አይሁድ ለወደፊቱም ቢሆን ለወሬ እንዳይመቻቸው፥ ክርስቶስን እንደማይጠቅምና እንደ ክፉ ሰው አድርጎ የሚወቅሰው ሰው ኃይል እንዲያጣ የሚያደርግ ነበር፡፡ በዚህም ቅዱስ ዳዊት የተነበየው ትንቢት ‹‹አንሰ ተሰየምኩ ንጉሠ በላዕሌሆሙ ፤ በጽዮን በደብረ መቅደሱ›› (እኔ ግን በላያቸው ላይ ንጉሥ ሆኜ ተሾምሁ ፤ በቅድስናው ተራራ በጽዮን) /መዝ. ፪፥፮/ ያለው ተፈጸመ፡፡
፠ ‹የአይሁድ ንጉሥ ነኝ በማለቱ የተሰቀለው ኢየሱስ› ብሎ ሊጽፍ ሲገባው (መንፈስ ቅዱስ አፉን ከፍቶ ፊቱን ጸፍቶ) ‹ኢየሱስ ናዝራዊው የአይሁድ ንጉሥ› ብሎ ጻፈ፤ ይህም የክስ ጽሕፈት ሳይሆን የአንድን ድል አድራጊ ንጉሥ ማንነት የሚያስረዳ መግለጫ፥ ለጌታችን የተሰጠ የክብር ስም አደረገው፡፡ በገዛ ንጉሣቸው ላይ እንደተነሡ አድርጎ በማሳየት የሁሉንም አፍ ዘጋው፡፡ በዚያን ወቅት በስፋት በሚነገሩት በሦስት ቋንቋዎችም #በዕብራይስጥ፣ #በግሪክና #በሮማይስጥ ‹ኢየሱስ ናዝራዊ የአይሁድ ንጉሥ› ብሎ ጻፈ፡፡ በወታደሮቹ አማካይነትም ሰሌዳው ወደ ቀራንዮ ተወስዶ ሁሉም ሰው እንዲያየው ከጌታችን ከራሱ በላይ ተሰቀለ፡፡ ይህንንም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ወጸሐፈ ጲላጦስ መጽሐፈ ወይብል መጽሐፉ ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ፡፡ (ጲላጦስ መጽሐፍን ጻፈ ፤ መጽሐፉም ኢየሱስ ናዝራዊ የአይሁድ ንጉሥ ይላል፡፡››) ብሎ በድርሰቱ ገልጾታል፡፡
፠ ‹‹ኢየሱስ የተሰቀለበት ሥፍራ ለከተማ ቅርብ ነበርና ከአይሁድ ብዙዎች ይህንን ጽሕፈት አነበቡት›› /ዮሐ. ፲፱፥፳/
፠ ከመስቀሉ ሥር አንጋጥጠው ያነበቡት የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን በንዴት እየተብከነከኑ ከቀራንዮ ወደ ጲላጦስ ግቢ በብስጭት እየሮጡ መጡ፡፡ የሠራውን ሥራ የሚያውቀው ጲላጦስም የሚጠብቀው ነገር ነበርና ሊቃነ ካህናቱን አነጋገራቸው፡፡ እነርሱም ‹‹እርሱ የአይሁድ ንጉሥ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ›› አሉት፡፡ ጲላጦስ ግን ያቃጠሉትን ሊቃነ ካህናት አንጀት የሚያሳርርና የተዘጋጀበት የሚመስል አጭር መልስ መለሰላቸው ‹‹#የጻፍሁትን_ጽፌያለሁ::››
፠ አይሁድ ይህንን ጽሕፈት ሲያዩ በንዴት ተንገበገቡ ፤ ተሰቅሎም እንኳን የካህናት አለቆች ይቀኑበት ነበርና፡፡ ‹‹እናንተ እንደምትሉት ክርስቶስ ሙትና ደካማ ከሆነ ይህ ጽሕፈት ሊጎዳችሁ አይችልም፤ የክርስቶስ ስሙም ሊረሳ ይችላል፡፡ ‹ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ› ተብሎ መጻፉ ለምን ያስፈራችኋል?›› /ይላቸዋል ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/
*፠* በቤተ ልሔም ሲወለድ ‹‹የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ›› እያሉ የምሥራቅ ነገሥታት መሰከሩለት፤
*፠* በቀራንዮ ሲሰቀል ‹‹የተሰቀለው የአይሁድ ንጉሥ›› ብሎ የምዕራብ ንጉሥ እንደራሴ ጲላጦስ ደግሞ መሰከረለት፡፡
*፠* ነቢዩ ዳዊት ‹‹እምሥራቀ ፀሐይ እስከነ ዐረብ፥ ይትአኰት ስሙ ለእግዚአብሔር›› (የእግዚአብሔር ስሙ ከፀሐይ መውጫ (ምሥራቅ) እስከ መግቢያው (ምዕራብ) ድረስ ይመስገን፤) ብሎ የዘመረለት አምላካችን ከምሥራቅ ብቻ ሳይሆን ከምዕራብም ‹የአይሁድ ንጉሥ› ተብሎ ተመሰከረለት፡፡
፠ ጌታችን በምድር ላይ ባስተማረበት ወቅት ያስተማረው በአንድ ቋንቋ ብቻ ተወስኖ ነበር፤ ‹‹በሰናዖር ሜዳ ቋንቋዎችን የደባለቀውና ብዙ ቋንቋዎች እንዲናገሩ ያደረገው እርሱ ሆኖ ሳለ ስለ ትሕትናው በአንዲት ቋንቋ ብቻ አስተማረ›› /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ/፡፡ ጲላጦስ ደግሞ ወንጌላውያን ወንጌላቸውን ከመጻፋቸው ቀድሞ በሦስት ቋንቋዎች ጽሕፈቱን መጻፉ (ወንጌልን መስበኩ) የክርስቶስ መንግሥት የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በቋንቋ የማትገደብ በሕዝብና በአሕዛብ ላይ የምትጸና መሆኗን ያሳያል፡፡
፠፠ በጥቅሉ ‹ኢ.ና.ን.አ.› ማለት፤ /ዮሐ. ፲፱/
‹‹የምስጉኖችና የታማኞች ንጉሥ የሆነው መድኃኒት የተለየና የተቀደሰ አክሊልን የተቀዳጀ ነው፡፡›› የሚል ነው፡፡
ልዩ ማስታወሻ፤ ዛሬም በአንገታችን ላይ የምናስረው መስቀል (በተለይም ከአኵሱም ተቀርጾ የሚመጣው ላይ ሊጻፍበት የሚገባው የጌታችን ስም (‹ኢ.ና.ን.አ.›) የሚለው እንጂ የራሳችን ስም መሆን የለበትም!!!! (እንዳይረሳ!!)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለወላዲቱ ድንግል፤ ወለመስቀሉ ክቡር አሜን፡፡
(ኢየሱስ ጌታ ነው…..፤ ቤተ ክርስቲያናችን ‹‹ኢየሱስ›› ለሚለው ለአምላካችን ስም የምትሰጠው ክብርን በመተለከተ ለብቻው ወደፊት በሌላ ጽሑፍ ይጠብቁን)፡፡
(FINOTE HIWOT የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት)
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
#ኢ. #ና. #ን. #አ. ‹‹#የጻፍሁትን_ጽፌያለሁ::››
፩ኛ) #፠#ኢየሱስ_፤
፠ አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ከሥጋ ማርያም ጋር ተዋሕዶ፤ ከሁለት አካል አንድ አካል፥ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሆኖ፤ በዘመነ ሥጋዌ ከተጠራባቸው ስሞች መካከል፤ ኢየሱስ፥ ክርስቶስ፥ አማኑኤል፥ መድኀኔ ዓለም፥ መድኅን፥ የሰው ልጅ፥ የእግዚአብሔር ልጅ፥ ቃል፥ እግዚአብሔር ወልድ፥ አንድዬ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ጌታ፥ … የሚሉ ዋነኞቹ ናቸው፡፡
፠ ኢየሱስና ክርስቶስ የሚሉት ስሞች ከጥንት ጀምሮ (የሰው አእምሮ ገና ያልበሰለ፤ ክፉዎች አይሁድም ነገሩን ለፌዝ፥ ለቧልት ያውሉት ነበርና፤ ምንም እንኳን በግልጽ ባየገለጹም)፤ በነቢያት የተነገሩና በመላእክት የተበሠሩ፤ የጌታን አምላክነት የሚያሳዩ፤ የጌታን አዳኝነት የሚያመለክቱ ስሞች ናቸው፤ /አውሳብዮስ/፡፡ ለምሳሌ፤ ልበ አምላክ ዳዊት ‹‹እምቅድመ ፀሐይ ሀሎ ስሙ፤ ስሙ ከፀሐይ በፊት ነበረ፡፡›› /መዝ 71÷17/ ብሏል፤ እንዲሁም ነቢዩ ሙሴ በምሳሌ ጠርቶታል፤ የሊቀ ካህንነቱ አገልግሎት ሊቀ ካህኑ የክብርና የከፍታ ምልክት፣ የነዌ ልጅ ኢያሱም የአዳኛችንን ምሳሌ ተሸክሞ ነበር፡፡›› /ዘጸ. 25፥40፣ ዘሌ. 4፥5፡16፤ 6፥22/ ብሏል ይህንንም የመልክአ ኢየሱስ ደራሲም ‹‹አክሊለ ስምከ እንዘ ይትቄጸል በርእሱ፤ አኅጉረ ፀር ወረሰ ኢያሱ፡፡›› (የስምህን አክሊል በራሱ ላይ አድርጎ የጠላትን ሀገሮች ኢያሱ ወርሷል) ብሎ አመስጥሮታል፡፡
• ይህንን ከዓለም በፊት የነበረውን ስሙን ከሰማይ ተቀብሎ ለእመቤታችን እንዲናገር የተላከው መልአክ፤ መጋቤ ሐዲስ ቅዱስ ገብርኤል ሲሆን ‹‹ስሙን የመሰየም›› ሥልጣን የተሰጣት ደግሞ እመቤታችን ናት፡፡ ˝ኢየሱስ ትይዋለሽ˝ /ሉቃ 1÷31/
፠ #ኢየሱስ_ማለትም(ትርጓሜውም)፤
ሀ) መድኃኒተ ሥጋ ፥ መድኃኒተ ነፍስ ማለት ነው፡፡
* በእብራይስጥ የሹኣ፥ ኢያሱ ወይም «ያሕዌ መድኃኒት ነው» የሚል ትርጉም አለው።
፠ እርግጥ ነው፥ በትንቢት፥ በምሳሌና በጥላ ቀድሞ ለተነሡት « አዳኞች» ኢያሱዎች ተሰጥቷል። (ለምሳሌ ዘካርያስ 3፥1 ላይ ሊቀ ካህናቱን ኢያሱን ያስታውሷል።) ሆኖም ግን እነዚህ « አዳኞች» ያዳኑት የእግዚአብሔርን ሕዝብ ነው፡፡ ያዳኑትም የእግዚአብሔርን ኃይልና ረድኤት አጋዥ በማድረግ ነው፤ ያዳኑት(የታደጉትም) ከምድራዊ ጠላቶቻቸው ስለሆነ ማዳናቸው ውሱን ነው፡፡
*****አማናዊው ኢያሱ አዳኛችን ግን ያዳነው « ሕዝቡን» (የራሱን ሕዝብ) ነው። ያዳነውም እግዚአብሔር ተጠቅሞበት ሳይሆን ራሱ እግዚአብሔር ስለሆነ መድኃኒት ሆኖ ነው። ሕዝቡን ያዳነውም «ከኃጢአታቸው» ነው። ይህ አነጋገር የሚገባው ለእግዚአብሔር ብቻ ነው። በመሆኑም እንደቀድሞዎቹ እግዚአብሔር በምሳሌና በጥላ ሳይሆን ራሱ በመካከላችን በማደሩ ‹‹አማኑኤል እግዚአብሔር ከእኛ ጋር፡፡›› እንደ ሆነና በዚህም የነቢዩ የኢሳይያስ ትንቢት ፍጻሜ እንዳገኘ ነበር የእግዚአብሔር መልአክ የገለጠው። ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ማዳኑም የአምላክነቱ መገለጫ ነው።
ለ) ሕዝቡን በኃጢአታቸው ከመጣባቸው ፍዳ የሚያድናቸው መድኀኒት ማለት ነው፡፡ /ማቴ 1፥21፣ ተረፈ ኤርምያስ) (ዳግመኛም ወገኖቹን ከኃጢአታቸው የሚያድናቸው ኢየሱስ ይባላል፡፡ /ቅ.ኤፍሬም/፡፡) (‹‹ኢየሱስ ስዱድ ተስፋሆሙ ለስዱዳን›› /ሰቈቃወ ድንግል/)
ሐ) ኃጢአታችንን የሚያስተሠርይልን ማለት ነው፤ ‹‹አመ ይእኅዝዎ ለኢየሱስ ፀሐይ ጸልመ›› /ቅዱስ ያሬድ፥ ድጓ/
መ) ዳግማይ አዳም ማለት ነው (የኢየሱስ የስሙ ቊጥር ከአዳም የስም ቊጥር ጋር የተባበረ ነውና)
*ኢየሱስ፡- አ=40, የ=90, ሰ=7, ሰ=7 ድምር =144፤
*አዳም፡-አ=40, ደ=100, መ=4 ድምር =144
*ዳግማይ አዳም የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ወደ ኤዶም ገነት አገባው ማለቱ ኤዶም፡-አ=40, ደ=100, መ=4 ድምር =144
፪ኛ) #፠#ናዝራዊ_፤ ከናዝሬት የመጣ /ማቴ 2፥ 23/፤ በሌላም ትርጕምም ቸር፥ እረኛ፣ በዕብራይስጥ ደግሞ የተለየ ፣ አክሊል የተቀዳጀ ፣ የተቀደሰ ማለት ነው፡፡
፠ ‹‹ኢየሱስ ናዝራዊ አምላኮሙ ለናዝራውያን›› እንዲል /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፤ መጽሐፈ ምሥጢር/
፠ ማቴ. 2÷23 «በነቢያት ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጻም ዘንድ ናዝሬት ወደ ምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ፡፡››
፠ ትንቢቱ (በማቴዎስ ወንጌል የተገለጠው) ልጄ እንደ ሶምሶን ናዝራዊ ይባላል የሚል ነው፤ ነገር ግን በ66ቱም ሆነ በ81ዱ መጻሕፍት አይገኝም፤ መጽሐፉ በምርኮ ጊዜ ጠፍቷል፤ ይህም ከ66ቱ መጻሕፍት ሌላ መጽሐፍ የለም ለሚሉ ወገኖች ማስረጃ እንደሆነ አስተውል፡፡
*፠* በመጽሐፍ ቅዱስ ስማቸው የተጠቀሰው ናዝራውያን 2ት ናቸው እነርሱም ሶምሶንና ጌታችን፤ በምን ይመሳሰላሉ ቢሉ::
**ሶምሶን በተናቀች በአህያ መንጋጋ ጠላቶቹን እንዳጠፋ፤ ጌታም አይሁድ፣ አጋንንት፣ መናፍቃን በናቁት ሞቱ ሞትን አጥፍቷል፡፡ /መሳ. 15÷9-19/
**ሶምሶን በሕይወተ ሥጋ ካጠፋቸው አሕዛብ ይልቅ በሞቱ ያጠፋቸው ይበዛሉ፡፡ ጌታም በሕይወተ ሥጋ ሳለ ካጠፋቸው አጋንንት ይልቅ በሞቱ ያጠፋቸው ይበዛሉ፡፡ /ምሳ. 16÷23-31/
፫ኛ) #፠#ንጉሥ_፤ አፄ፣ ባለዘውድ፣ ሹም፣ አለቃ፣ ማለት ነው፡፡ /ንጉሦሙ ለእስራኤል ውእቱ ይብሉ ሆሳዕና በአርያም እንዲል፡፡/
፬ኛ) #፠#አይሁድ_፤ ማለት የታመኑ፣ ምስጉኖች፣ ምዕመናን ማለት ነው፡፡
፠ አይሁድ የሚከው ቃል እስከ ባባሎን ምርኮ ድረስ ከ12ቱ ነገደ ያዕቆብ (እስራኤል) የይሁዳ ብቻ ነበረ፡፡ ከምርኮ በኋላ እስከ ክርስቶስ ድረስ ግን ለእስራኤል ሁሉ (ለ12ቱም ነገድ) መጠሪያ ሆኗል፡፡ /ዘፍ. 29፥ 35/
#የአይሁድ_ንጉሥ (#ማዕከላዊ_ስም)
፠ ሰብአ ሰገል ስም ማዕከላዊ (የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ) እያሉ ነው ለጌታ መብዓ ይዘው የመጡት፤ ስለምንድነው ቢሉ?
* አምላክ (ስም ላዕላዊ) እያሉ ያልመጡበት፤ ሰማይና ምድር የማይችለው ምን ወስኖት ምን ችሎት ነው ብለው እንዳይዘባበቱባቸው፡፡ አንድም ትንቢት የተነገረልን ሱባዔ የተቈጠረልን እኛ እያለን እንዴት ለእነርሱ ተገለጠላቸው ብለው እንዳይዘባበቱባቸው፤ አንድም አሕዛብ ናቸው በየት አውቀውት ብለው እንዳዘብቱባቸው ነው፡፡
* የተወለደው ሕፃን (ስም ታህታዊ) እያሉ ያልመጡት፤ በእስራኤል ሃገር በአንድ ቀን ውስጥ ብዙ ሕፃናት ተወልደው ብዙ ሕፃናት ይሞታሉ፤ ስንቱን እናውቅላችኋለው ባሏቸው ነበርና፡፡
(#ሥርዐተ_ጸሎት_ወስግደት_ዘዐርብ_ስቅለት_፡፡)
(እየሰገድን የምንላቸውም) ቃላት፡፡
፠ #፩ኛ #ስግደት፤ የወንጌል ምንባብ እንዳበቃ በማስከተል ተግሣጽ ተነቦ እንደተፈጸመ፤
*‹‹#ጸልዩ_በእንተ_ጽንዐ_ዛቲ_መካን›› የሚለውን ካህኑ ሲመራና ዲያቆኑ በየምዕራፉ ቃጭል ሲደውል፤
#ሕዝቡ_እየተቀበሉ_እግዚኦ_ተሣሀለነ (አቤቱ ይቅር በለን) በማለት ፳፪ት ጊዜ በግእዝ፥ በዕዝልና በአራራይ ዜማ እየተዜመ ይሰገዳል፡፡
፠ #፪ኛ #ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹#ለከ_ኃይል_ክብር_ወስብሐት›› የሚለውን ምቅናይ በመሪና በአንሺ ወገን መቀባበል ፮ት ፮ት ጊዜ (በድምሩ ፲፪ ጊዜ) ይበሉ፤ በመጨረሻም በ፲፫ኛው ከ‹‹ለከ ኃይል›› እስከ ‹‹ዕብል በአኰቴት›› ድረስ አንድ ጊዜ በኅብረት ይበሉ፡፡ /ከሆሳዕና ሠርክ እስከ ሰኞ ሰርክ መሪ በቀኝ፤ ተመሪ በግራ ሲሆን፡፡ ከማክሰኞ ሠርክ ጀምሮ ግን መሪ የነበረው ተመሪ፤ ተመሪ የነበረው መሪ ይሆናል፡፡/ እንዲህ እያሉ ይበሉ፤
+ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤
+ አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፤
+ ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤
+ ኃይልየ ወፀወንየ ውእቱ እግዚእየ፤ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኰቴት፤
+ አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ፥ ትምጻእ መንግሥትከ፥ ወይኩን ፈቃድከ፥ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር፥ ሲሳየነ ዘለለዕለትነ፥ ሀበነ ዮም፥ ኅድግ ለነ፥ አበሳነ ወጌጋየነ፥ ከመ ንህነኒ ንኅድግ፥ ለዘአበሰ ለነ፥ ኢታብአነ፥ እግዚኦ ውስተ መንሱት፥ አላ አድኅነነ፥ ወባልሐነ፥ እምኵሉ እኩይ፥ እስመ ዚአከ፥ ይእቲ መንግሥት፥ ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም፡
፠ #፫ኛ #ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹#ለአምላክ_ይደሉ››ን መጀመሪያ በመሪ እየቀደሙ በአንሺ እየተከተሉ አንድ ጊዜ ይዝለቁ፤ በ፪ኛው ክፍል ደግሞ እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይበሉ፡፡ እንዲህ እያሉ ይበሉ፤
+ ለአምላክ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለሥሉስ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለማሕየዊ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለዕበዩ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለዕዘዙ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለመንግሥቱ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለሥልጣኑ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለምኵናኑ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለኢየሱስ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለክርስቶስ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለሕማሙ ይደሉ፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
+ ለመስቀሉ ይደሉ (ለዐርብ ብቻ)፤
ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
ቀጥሎ ያለውን የመዝጊያ ጸሎት እያዜሙና እየሰገዱ ፫ት ጊዜ መላልሰው ይዝለቁት፡፡
+*+ ለከ ይደሉ ኃይል፥
ወለከ ይደሉ ስብሐት፥
ወለከ ይደሉ አኰቴት፥
+*+ ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም፡፡
፠ #፬ኛ #ስግደት፤ ዜማው አሁንም በቀኝና በግራ በመቀባበል ነው የሚባለው፡፡ በመሪ ወገን እየቀደሙ፤ በአንሺ ወገን ደግሞ እየተከተሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፤ ቀጥለውም በመሪና በተመሪ ወገን እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፡፡
* መሪ፤ ክርስቶስ አምላክነ፥ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ፥ በሕማማቲሁ ቤዘወነ፤
ተመሪ፤ ንሰብሖ፥ ወናልዕል ስሞ ኅቡረ፥ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በብዝኀ (በዕበየ) ሣህሉ፡፡ /በዐርብ፤ ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ/
* #ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ #ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን፥ ኪርያላይሶን፤
ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #እብኖዲ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
* ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ታኦስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ማስያስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
* ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ኢየሱስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ክርስቶስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
* ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #አማኑኤል ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤
ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ትስቡጣ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፡፡
**** ኪርያላይሶን የሚለውን ብቻ በመሪ ፳፩ ጊዜ፥ በተመሪ ወገን ፳ ጊዜ ይበሉ፤ ድምሩ ፵፩ ኪርያላይሶን ይኾናል፡፡
፠ የየሰዓቱን (የሌሊት፣ የነግህ፣ የጠዋት 3 ሰዐት፣ የቀትር/6 ሰዐት/፣ የተሰዐት/9ኝ ሰዐት/፣ የሰርክ /11 ሰዐት/፣ የንዋም) መልክአ ሕማማት በዜማ ይደርሳል፡፡
፠ካህኑ ቡራኬ ሰጥቶ፤ ዲያቆኑ ደግሞ ‹‹ሑር በሰላም›› ብሎ ሕዝቡን ያሰናብታል፡፡
፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
