Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 368 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 616,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 192 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 368 名订阅者。
根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -4,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 20.07%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.16% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 085 次浏览,首日通常累积 1 254 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 368
订阅者
-124 小时
+357 天
-430 天
帖子存档
#በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም
አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ እንጦጦ፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ ጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (ከመርካቶ) → ሽሮ ሜዳ → እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት፡፡
#ለቅምሻ_በአጭሩ፤ #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም
፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ደግሞ ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡
፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው፥ ጠበሏን አፍልቀው፥ ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡
፠ በ1967 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡
፠ ባለውለታዋን ዘንግታ የቆየችው እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳምም ከ በኋላ በዕለተ እሑድ ጥር 3/2012 ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ ታቦተ ሕጉን አውጥታ አክብራለች፨
፪. አያት ጣፎ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ን፡፡ (በድርብነት ይከበራል)
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አያት 2 ኮንዶሚንየም
ትራንስፖርት፤ ከመገናኛ → አያት(በሲኤምሲ) አደባባይ ወደ ጣፎ በሚወስደው መንገድ
ወይም ከመገናኛ በኮተቤ ጣፎ /አባ ኪሮስ ጋር ወርደው/ በባጃጅ (በታክሲ) ያገኙታል፡፡
#በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፱ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. ደብረ ወርቅ ገዳመ መጣዕ አቡነ ሊባኖስ፤ (በ523 ዓ.ም. በጻድቁ በአቡነ ሊባኖስ የተገደመና በአፄ ገብረ መስቀል የታነጸ፥ ገደል ወገብ ላይ የታነፀና የሚያስደንቅ፡፡) (የጻድቁ የከበረ አጽም የሚገኝበት፥ ሙት ያስነሳበት፥ ዕውር ያበራበት ገዳም ነው)
አድራሻ፤ ደቡብ ኤርትራ፥ አካለ ጉዛይ አውራጃ፥ ሃም ታርካ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ (በአውሮፕላን) → ኤርትራ → አካለ ጉዛይ → ሃም ታርካ፡፡
፪. አኵሱም አጠገብ የሚገኝ አባ ሊባኖስ፤ (ጻድቁ የዋሻ በዓት ሠርተው የጸለየበት፥ 7ት ዓይነት ጠበል ያፈለቀበት፤ አንዲት እናት ውኃ ነው ብላ ብትዳፈር ልጇ ሞቶባት እንደ ኤልያስ ያስነሳበት፥ የአከባቢው ካህናት ቢያድሙበት እንደ ኤልያስ በዚህ አካባቢ ላይ ለ3ት ዓመት ዝናብ እንዳይዘንብ የከለከለበት ኋላ ደግሞ በይቅርታ ቢጠይቁት ዝናብ ያዘነበበት ነው)
(ልጅ ያጡ የሚወልዱበት መታሻ ደንጊያ ያለበት፥ ከዐለት ላይ የሚፈልቅ ተአምረኛ ጠበል ያለበት)
(ገዳሙ ዋሻና ለእኅቶች ደግሞ ክብ ሕንፃ ቤ/ን አለ)
አድራሻ፤ አኵስም ሃገረ ስብከት
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ በጎንደር/በሽሬ/ → አኵስም → የ10 ብር ትራንስፖርት(የ2ሰዐት የእግር መንገድ) ወይም
ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ በደሴ/ወልድያ/መቀለ/ → አኵስም → የ10 ብር ትራንስፖርት(የ2ሰዐት የእግር መንገድ)
፫. ተንቤን አምበራ አቡነ ሊባኖስ (በአፄ ገብረ መስቀል የታነፀ)
አድራሻ፤ ትግራይ
ትራንስፖርት፤ ከአኵሱም → ተንቤን
፬. ላስታ ላሊበላ ቤተ አባ ሊባኖስ (ቅዱስ ላሊበላ ለ23ት ዓመታት ካነጻቸው አንዱ፥ በላስታ ከሚገኙት 11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ አንዱ የኾነና ከ11ዱ ሙሉ ለሙሉ ከተራራ ላይ ተፈልፍሎ ባለመውጣቱ በአሠራሩ ልዩ የኾነ)
አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ላስታ፥ ላሊበላ ከተማ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ በደሴ/በጋሸና/ → ላሊበላ
ወይም ከአ.አ. (በአውሮፕላን) → ላሊበላ
ወይም ከጎንደር (ባህር ዳር) /በወረታ/ /ደብረ ታቦር/ /ጋሸና/ → ላሊበላ
ወይም ከመቀለ በወልድያ መስመር/ጋሸና/ → ላሊበላ
፭. ዛራ ሐሙሲት አካባቢ የሚገኘው አባ ሊባኖስ (ቅዱስ ላሊበላ ለ23ት ዓመታት ካነጻቸው አንዱ)
አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት
ትራንስፖርት፤ ከባህር ዳር /በጎንደር መስመር/ → ሐሙሲት
፮. ጎንደር ግራርጌ (ቆላ ድባ) ፈለገ ሕይወት አቡነ ሊባኖስ፤ (በአፄ ገብረ መስቀል እንደተመሠረተ የሚነገርለት፥ አጸዱ እጅግ በጣም የሚማርክ /ዕድሜ ጠገብና አርስ በእርሱ የገጠመ 4 ትላልቅ ወርካና 4 ጽድ የሚገኝበት፤ ወርካውን ፈልፍለው መነኰስ ይኖሩበት የነበረው ለምስክር ቆሞ የሚገኝበት፥ 1ዱ ጽድ በ1880 አካባቢ ወድቆ እስካሁን ዝናብና ፀሐይ እየፈራረቀበት ሳይበሰብስ የሚገኝበት)፤ ውሎ ቅዳሴ የሚቀደስበት፤ የአከባቢው ገበሬ እህሉን ወደ ጎታው ከቅዳሴ በኋላ የሚያስገባበት የበረከት ቃል ኪዳን የተሰጠው ምድር፡፡
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደንቢያ ወረዳ፥ ቆላ ድባ ከተማ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከጎንደር (አዘዞ) → ወደ ጎርጎራ መስመር (በደረስጌና በቆላ ድባ መሃል ላይ ያገኙታል) (በ25 ኪ.ሜ አስፓልቱ ዳር)
፯. በመንዝ ቀያ ሀገረ ገራዴ አባ ሊባኖስ አፅመ ቅዱሳን ዋሻ (ፈዋሽ ጠበልና አስገራሚ ዋሻ ያለበት)፡፡
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ፥ ዘመሮ ከተማ፥ በንዲ ቀበሌ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ዘመሮ → 9 ኪ.ሜ ያህል እንደተጓዙ በንዲ ቀበሌ (ከአዲስ አበባ 328 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ይገኛል)
፰. መንዝ ላሎ አንጀትላ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፥ ዘብር፥ ላሎ፥ አንጀትላ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ዘብር(247 ኪ.ሜ.) → የ2ት ሰዐት የእግር መንገድ → የአንጀትላ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፡፡
፱. *** ነገር ግን የመሠረቱት፥ ለ40 ዓመታት በዓት ሠርተው የኖሩበትና፥ በስማቸው የሚጠራው ታላቁ ገዳም ደብረ ሊባኖስ ግን ባለፉት 10ር ዓመታት ውስጥ ገድላቸውን በግእዝና በአማርኛ ከማሳተም የዘለለ የሚጠበቅበትን ሥራ አልሠራም፡፡
(ያልጠቀስናቸውን አሳውቁን)
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
ጥር 3 የደብረ_ሊባኖስ_ገዳምን_የመሠረቱና_በስማቸው_የተሠየመላቸው እና የእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳምን_ጸበል_ያፈለቁ የታላቁ አባት አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ በዓለ ዕረፍት ነው ።
#ጥር ፫፤ #የአቡነ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ_በዓለ_ዕረፍት_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፲፩ ገዳማትና አድባራት (ከታች)፡፡
#በአ.አ. #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት ቀድሞ በቅዳሴና በውዳሴ ታቦተ ሕጋቸው ሲከበር የቆየው የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ታቦተ ሕጋቸው #ረቡዕ_ጥር 3/2015 ዓ.ም.
አራተኛ ጊዜ_ታቦተ_ሕጋቸው_ወጥቶ_ይከብራል፡፡ (ሁላችሁም እንድትገኙ ገዳሟ ጥሪዋን አስተላልፋላች)፡፡
አባ ሊባኖስ #የደብረ_ሊባኖስ_ገዳምን_የመሠረቱና_በስማቸው_የተሠየመላቸው፤
፠ ቅዱስ ላሊበላ ከ11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱን በስማቸው ያነፀላቸው፡፡
፠ #ከደረቅ_ዐለት_ላይ_ውሃ_እያፈለቁ_ድውያንን_የሚፈውሱ_ተአምረኛ_አባት
፠ በኤርትራ አካለ ጉዛይ ገዳመ መጣዕ፣ በአኵሱም ከተማ አጠገብ፣ በላስታ ላሊበላ፣ ደብረ ወርቅ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፣ እንዲሁም ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ በአ.አ. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ገዳም ክብረ በዓል የሚከበርላቸው።
፠ አባታቸው አብርሃም እናታቸው ንግሥት ሊድሯቸው ሲሉ መመነን በመፈለጋቸው መልአክ በሌሊት መጥቶ ወደ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡
፠ አባ ጳኩሚስም ሥርዐተ ገዳምን፥ አስኬማ መላእክትን፥ ቅናተ ዮሐንስን አስተማሯቸው፤ አመነኮሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡
፠ ቀድሞ የመራቸው መልአክ ከአባ ጳኩሚስ ‹‹ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድሎህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአኵሱም ተቀመጡ፡፡
፠ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው (ቀድሞ የዋልድባን ገዳም ባስፋፉ አባቶች የተመሠረተችውን #የእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳምን እስፋፍተው፡፡) ተመልሰው ወደ አኵሱም ሄዱ፡፡
፠ በአኵሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ፥ ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአኵሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል ‹‹ተራ ውሃ ነው›› ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጥጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ ‹‹አምላከ አባ ሊባኖስ›› ብሎ አመሰገነ፡፡ (ስዕላቸው የሚገልጸው ይህንን ተአምር ነው፡፡)
፠ ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው ‹‹ምትሃት ነው የሚያሳየው›› ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡
፠ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአኵሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ፤ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው ‹‹አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን›› ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡ አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡
፠ ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ (የአሁኗ ደብረ ሊባኖስ) መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው ‹‹ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ (አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኮሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል›› አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን ‹‹ደብረ ሊባኖስ›› ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡
፠ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አኵሱም ወሰዳቸው፡፡ ከዚያም ‹‹ታሪክ ወደምትሠራበት ዕጣ ክፍልህ ወደሆነው ቦታ አደርስሃለሁ›› አላቸውና ወደ ኤርትራ አካለ ጉዛይ አውራጃ ልዩ ስሙ መጣዕ ወደተባለው ቦታ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም አባታችን ድውያንን እየፈወሱ፣ ለምፃሞችን እያዳኑ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ወንጌልን እየሰበኩ ‹‹ሊባኖስ ዘመጣዕ›› የሚባለውን ትልቁን ገዳማቸውን መሠረቱ፡፡ በወቅቱ የነበረው አፄ ገብረ መስቀልም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን አሠራላቸው፡፡
፠ ቅዱስ ላሊበላ 23 ዓመት ሙሉ ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶች ውስጥ አንደኛውን በአባ ሊባኖስ ስም ሰይሞላቸዋል፡፡ አፄ ገብረ መስቀል ያሠራላቸው ሌላኛው ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ የሚታወቁት አባታችን እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን ላይ ብርሃንን አብርተዋል፡፡
፠+፠ በመጨረሻም ጥቅምት 2 ቀን ተፀንሰው ፤
፠+፠ ሐምሌ 3 ቀን ተወለደው፤
፠+፠ በ140 ዓመታቸው ጥር 3 ቀን በክብር ዐርፈዋል፡፡
፠+፠ ቅዳሴ ቤታቸው ደግሞ ሐምሌ 3 ነው፡፡ ይኸውም ለመጀመሪያ ጊዜ በዐፄ ገብረ መስቀል ጊዜ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ የተመረቀበት ዕለት ነው፡፡
* እኛም ለክብረ በዓሉ የሚሆነውን ከዋይዜማው ጀምሮ ሙሉውን ሥርዐተ ማኅሌት እነሆ ብለናል፡፡
#እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም
፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡
፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው ጠበሏን አፍልቀው ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡
፠ በ197 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለአቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡
፠ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ይመስገን፨
#ጥር ፫፤ #የአቡነ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ_በዓለ_ዕረፍት_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፲፩ ገዳማትና አድባራት፡፡
(አባ ሊባኖስ በሃገራችን ላይ 80 ገዳማትን መሥርተዋል)
በ79 ገዳማትና አድባራት ላይ ሲከበሩ ዐበይቶቹ የሚከተሉት ናቸው፤
አድራሻ፤ ጉራጌ ሃገረ ስብከት፥ ማፌድ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ሆሳዕና → ማፌድ፡፡
፳፩. እዣ ስራይ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ጉራጌ ሃገረ ስብከት፥ እዣ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ሆሳዕና → እዣ፡፡
፳፪. ደብረ ዘይት ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ፤
አድራሻ፤ ምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ አድአ ወረዳ → ደብረ ዘይት፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ዘይት፡፡
፳፫. አለም ገና ቤ/ን (ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ በድርብነት ይከብራል)፤
አድራሻ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ አለም ገና፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → ጀሞ → አለም ገና፡፡
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ጥር ፬፤ #በዓለ_ስዋሬሁ_ለዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ_፡፡
#በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የቅዱስ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ_በዓለ_ስዋሬ_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው #ገዳማትና_አድባራት፡፡
#በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፫ #ገዳማትና_አድባራት_፡፡
፩. ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ማርያም ቤ.ክ.
ታቦተ ሕጉ ከኢየሩሳሌም የመጣ፥ ከዐፄ ዮሐንስ ጋር በመቀለ፤ ከራስ ጉግሳ ወሌ ጋር በደብረ ታቦር፤ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ከደብረ ታቦር ወደ አዲስ አበባ መናገሻ ገተ ጽጌ ያመጣችው፤ አፄ ኀይለ ሥላሴ ደግሞ አሁን ያለውን ሕንፃ ያሠሩት፤ በአዲስ አበባ በወልደ ነጐጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም በመሰየም ብቸኛው ቤ.ክ.፤
አድራሻ፤ አራዳ ክፍለ ከተማ፥ ሰባራ ባቡር፥ አባ ኮራን፥ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል
ታክሲ፤ ከፒያሳ ጴጥሮስ ዐደባባይ → ዊንጌት አስኮ በሚለው ታክሲ ተሳፍረው ቤተ ክርስቲያኑን ያገኛሉ፡፡
ወይም ከመርካቶ ጎጃም በረንዳ → አዲሱ ገበያ (ቀጨኔ) በሚሉ ታክሲዎች ተሳፍረው ቤተ ክርስቲያኑን ያገኛሉ፡፡
፪. ብሔረ ጽጌ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያምና መድኀኔዓለም ቤ/ክ (የሐዋርያው ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ታቦት ቤተ ክርስቲያኑ ከተመሠረተበት ከ፲፱፻፹፮ ዓ.ም ጀምሮ በድርብነት ይከብራል)
አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ፥ ብሔረ ጽጌ፤ ከብሔረ ጽጌ መናፈሻ 100 ሜትር ያህል ገባ እንዳሉ፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሰታዲየም)(መርካቶ)(መገናኛ)→ አደይ አበባ/ሳሪስ/ → ብሔረ ጽጌ፡፡
፫. ምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም (ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ባይከብርም፥ ከቀድሞ ጀምሮ በኪዳንና በሰዐታት፤ በውዳሴ፥ በቅዳሴ ይከበራል፡፡)
አድራሻው፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ 6 ኪሎ
ታክሲ፤ ከፒያሳ(4 ኪሎ) → ሽሮሜዳ በሚለው ታክሲ (ምስካየ ኅዙናን ጋር)
ወይም ከመርካቶ ራጕኤል (ከጊዮርጊስ)→ ሽሮሜዳ በሚለው → መነን (የካቲት 12 ት/ቤት) ተወርዶ → ምስካየ ኅዙናን፡፡
#በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፳፫ #ገዳማትና_አድባራት_፡፡
፩. መአቁዲ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ (ጥንታዊው ደብር፤ ለአንድ ቀን ብቻ ጠበል የፈለቀበት)፤
አድራሻ፤ ትግራይ፤
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ወልድያ → መአቁዲ፡፡
፪. ደቡብ ወሎ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ (ጥንታዊው ደብር፤ ከመካነ ሥላሴ አጠገብ የሚገኝ)፤
አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → መካነ ሥላሴ፡፡
፫. ሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ
አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ሐይቅ
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ደሴ → በወልድያ መስመር (ሐይቅ ከተማ)
፬. ደብረ በንኰል ገዳም አጠገብ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ
አድራሻ፤ ትግራይ፥ ሰለኽላኻ፥ ከታላቁ ገዳም ደብረ በንኰል አጠገብ
ትራንስፖርት፤ ከመቀለ(አኵሱም) → ሽሬ → ሰልኽላኻ → ደብረ በንኰል መስመር የቅ/ዮሐንስን ደብር ያገኙታል፡፡
ወይም ከጎንደር በሊማሊሞ ሽሬ (ዳንሻ፤ ሁመራ፤ ሽሬ) መስመር → ሰልኽላኻ → ደብረ በንኰል መስመር የቅ/ዮሐንስን ደብር ያገኙታል፡፡
፭. አደቁዋረክ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤
አድራሻ፤ አኵስም (ማዕከላዊ ትግራይ) ሃገረ ስብከት፥ ማኅበረ ዴጎ አጠገብ/፤፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → በደሴ → ወልድያ → መቀለ → አኵስም → ማኅበረ ዴጎ → አደቁዋረክ፤
ወይም ከአ.አ. (በአውሮፕላን ) → አኵስም → ማኅበረ ዴጎ → አደቁዋረክ፤
ወይም ወይም ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በቡሬ/በሞጣ/ ባህርዳር → ጎንደር → ከጎንደር በሊማሊሞ ሽሬ (ዳንሻ፤ ሁመራ፤ ሽሬ) መስመር → ሽሬ → አኵስም → ማኅበረ ዴጎ → አደቁዋረክ፤
፮. ገደፈና_ዮሐንስ /ማይጨው አጠገብ/፤
አድራሻ፤ ትግራይ፥ ማይጨው
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → በደሴ → ወልድያ → ማይጨው → ገደፈና፤
፯. መንዝ ማማ ሞላሌ ደዋ ዮሐንስ (900 ዓመታት በላይ ያስቈጠረ)
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፥ ሞላሌ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ሞላሌ → ደዋ፤
፰. ዣት ደብረ ፀሐይ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ጅሩ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → በደብረ ብርሃን በኩል → ጅሩ ፥ እነዋሪ → ዣት፤
ወይም ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በሙከጡሪ (መርሐ ቤቴ መስመር) → ለሚ → ጅሩ ፥ እነዋሪ፤
፱. ዘንስር ደብረ ተድላ ዮሐንስ ማዕከላ ለጐንደር፤ /ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱና ዋነኛው፤ በጎንደር ከተማ የማኅሌተ ጽጌ ቁመት ወደ ግምጃ ቤት ማርያም ከመዛወሩ በፊት በብቸኝነት የጎንደርና የመላው ኢትዮጵያ ሊቃውንት የማኅሌተ ጽጌን ቁመት ለመቆም የሚተሙት ታላቅ ደብር/፤
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አራዳ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በቡሬ /በሞጣ/ መስመር → ባህር ዳር → ወረታ → ጎንደር ከተማ፡፡
ወይም ከመቀለ /አኵሱም/ → ሽሬ → በሊማሊሞ (በሁመራ ዳንሻ) → ጎንደር ከተማ፤
ወይም ከደሴ → ወልድያ → ደብረ ታቦር → ወረታ → ጎንደር ከተማ፤
፲. ሞያሌ ደጋ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤
አድራሻ፤ ሞያሌ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. → ሞያሌ፤
፲፩. ደምበጫ አጠገብ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤
አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ ደምበጫ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → /በባህር ዳር መስመር/ ደምበጫ፤
፲፪. ቦኮሙራ ወልደ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ.ን፤
አድራሻ፤ ሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት፥ ሚሻ ወረዳ፥ ቦኮሙራ ቀበሌ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ስልጤ → በኮሙራ፤
፲፫. ናዝሬት(አዳማ) ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ምሥራቅ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ናዝሬት(አዳማ)፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → በደብረ ዘይት (በፈጣን መንገድ) → ናዝሬት (አዳማ) ከተማ፤
፲፬. ደሴ ዩኒቨርሲቲ ደብረ ነጎድጓድ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ደሴ ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ደሴ ከተማ፤
፲፭. መቱ ደብረ ሳሌም ወነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፤ (በ1915 ዓ.ም. የተመሠረተ)
አድራሻ፤ ም.ወለጋ ሃገረ ስብከት፥ መቱ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ወለጋ/መቱ፤
፲፮. ጨንቻ ዶርዜ አይራ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤
አድራሻ፤ ጋሞ ጎፋ ሃገረ ስብከት ፥ ጨንቻ ወረዳ፥ ዶርዜ አይራ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ወለጋ/መቱ፤
፲፯. ፎገራ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤
አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት ፥ ፎገራ ወረዳ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በቡሬ /በሞጣ/ መስመር → ባህር ዳር → ወረታ → ፎገራ፡፡
ወይም ከመቀለ /አኵሱም/ → ሽሬ → በሊማሊሞ (በሁመራ ዳንሻ) → ፎገራ፤
ወይም ከደሴ → ወልድያ → ደብረ ታቦር → ወረታ → ፎገራ፤
፲፰. ሐዋሳ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤
አድራሻ፤ ሐዋሳ ሃገረ ስብከት ፥ ሐዋሳ ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ሐዋሳ፡፡
፲፱. ሆሳዕና ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤
አድራሻ፤ ጉራጌ ሃገረ ስብከት፥ ሆሳዕና፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ሆሳዕና፡፡
፳. ማፌድ ጓረባ ጠብረሪ ደብረ ዕንቊ ቅድስት ልደታ ወዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ፤
#ታኅሣሥ 29 ልደታቸው ከጌታችን ልደት ጋር የተባበረላቸው ቅዱሳን፤
#አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፤
#ቅዱስ ላሊበላ፤
#ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ፤
#አቡነ አብሳዲ ዘደብረ መጕና
#ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ፤
#ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃ፤
#አቡነ አካለ ክርስቶስ፤
#አቡነ መዝራእተ ክርስቶስ፤
#መስፍኑ ኢያሱ፤
#የገርአልታው አቡነ ዳንኤል፤
#ዳግማዊ ቂርቆስ ዘቡልጋና ሌሎችም ቅዱሳን አሉ፤ ነገር ግን ከቅዱሳን በዓል በላይ የጌታ በዓል መከበር ስለሚገባው የቅዱሳኑ ዋና በዓላቸው በሌላ ቀናት /በዕረፍታቸው…../ ቀን ይታሳባል፡፡
በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ጾም #አጽዋማት #fasting's
#ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord
#Orthodox_Quotes
✤✤ #እቲሣ_ገዳም ( የአቡነ ተክለሃይማኖት የልደት ሥፍራ )
እቲሳ ገዳም (ዞረሬ /ጽላልሽ/ /ምስካየ ኅዙናን/፡፡ ክርስትናን በመላዋ ኢትዮጵያና እስከ ጎረቤት ሀገሮች መዳረሻ ድረስ በስፋት የሰበኩ ፥ ገዳማትና አድባራት የተከሉ ፤ ከዋክብት ሰማይን በብርሃናቸው እንደሚያደምቁት ፥ እንዳስጌጡት ሁሉ፤ በጽድቃቸው፥ በትሩፋታቸው ለቤተ ክርስቲያን ፋና የሆኑ፤ የ99 ቅዱሳን፥ የ566 መናንያን ቅዱሳን መፍለቂያ፤ 17 የጥንት ዋሻዎች፣ 31 አዳዲስ ዋሻዎች የሚገኙበት ነው እቲሳ ገዳምና ዙሪያው፡፡ ገዳሙ ከአዲስ አበባ ከተማ በቅርብ ርቀት በደሴ በር (በደብር ብርሃን መስመር) በ38 ኪ.ሜ ላይ ፤ ከአሌልቱ በስተቀኝ በመታጠፍ ….. ይገኛል፡፡
✤✤ #ይህ_ታላቅ_ገዳም
#በቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃና አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን የተመሠረተ፤ ሲመሠረትም በታቦተ ኢየሱስና አርባዕቱ እንስሳ ነው፤
#ሊቀ ካህናት አበይድላ ከአኵስም 300 ታቦታትና 300ካህናት ይዞ መጥቶ በጽላልሽ የተቀመጠባት ናት፤
#ፀሐይ አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱባት (የተወለዱባት ጠፍጣፋ ደንጊያ አሁንም በቦታው አለች)፣
#አባታቸውና ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእኀረያ የተወለዱበት፤ ኋላም ክብሩ አጽማቸው ያረፈበት ነው፡፡
#ቅዱስ ያሬድ 3 ዓመት ጸልዮባታል፤
#ቅዱስ ላሊበላ 7 ዓመት ጸልዮባታል፤
#ተሰዓቱ ቅዱሳን 20 ዓመት የጸለዩበት፤
#ሐርቤ በሚባለው ቦታ ላይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ 7 ዓመት ጸልየውበታል፤
#ታቦተ ጽዮን 12 ዓመት (ከ9ሺህ ሕዝብ) ጋር መጥታ ኖራበታለች፤
#በአምሳለ ሲዖል የተሠራ አስደናቂ የጨለማ ዋሻ ያለበት ነው፤
#ብዙ የታሪክ ቅርስ ያለበት ነው፤
#በቅዱስ ሚካኤልና ጸጋ ዘአብ ቤተ ክርቲያን ውስጥ ካየን በኋላ፤ እዚሁ ቦታ በሚገኘው ፈዋሽ ጠበል ተጠምቀንና ጠጥተን ጕዟችንን ወደ
ቦታው ከአ.አ በቅርብ ርቀት በደብረ ብርሃን መንገድ አሌልቱ ከተማ ላይ በመታጠፍ ይገኛል፡፡
#ሥርዐተ_ማኅሌቱን እንደየደብራችሁ ይትበሃል እንድትጠቀሙበት (በላይ ቤትና በታች ቤት) (#ዘአባጃሌ_ተክለ_ሃይማኖትና_ዘአደባባይ_ተክለሃይማኖት) አዘጋጅተነዋል፡፡
ጸሎትና በረከታቸው፤ ረድኤትና ምልጃቸው በመላው ሕዝበ ክርስቲያንና በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ሁሉ አድሮ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ኢትዮጵያውያን_ቅዱሳን
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
