ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 381 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 584,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 199

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 381 名订阅者。

根据 03 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 21,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.13%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.50% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 250 次浏览,首日通常累积 1 462 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 16

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 04 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 381
订阅者
-724 小时
+117
+2130
帖子存档
#ጥር_18 #እንኳን_ለቅዱስ_ጊዮርጊስ_ስባረ_ዓፅሙ ፠ ዐላውያን ነገሥታት በደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የሊቀ ሰማዕቱን ሥጋውንና አጥንቱ በመንኰራኵር ፈጭተው በነፋስ ለበተኑበት፤ ነገር ግን ለአምላካችን
+4
#ጥር_18 #እንኳን_ለቅዱስ_ጊዮርጊስ_ስባረ_ዓፅሙ ፠ ዐላውያን ነገሥታት በደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የሊቀ ሰማዕቱን ሥጋውንና አጥንቱ በመንኰራኵር ፈጭተው በነፋስ ለበተኑበት፤ ነገር ግን ለአምላካችን የታመነ ሰማዕት በመሆኑ ያረፈበት መሬትና ዕፅዋት ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር እያሉ ያመሰገኑበት ነው፡፡ ፠ አማን በአማን፤ አማን በአማን፤ ኮከበ ልዳ ፀሐየ ፋርስ፡፡ ፠ እንደ ጎንደር አበራ ጊዮርጊስ ባሉት ክብረ በዓሉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርዶና አድሮ ነው በዓሉ የሚከበረው፡፡ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

#ጥር_18 #እንኳን_ለቅዱስ_ጊዮርጊስ_ስባረ_ዓፅሙ ፠ ዐላውያን ነገሥታት በደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የሊቀ ሰማዕቱን ሥጋውንና አጥንቱ በመንኰራኵር ፈጭተው በነፋስ ለበተኑበት፤ ነገር ግን ለአምላካችን የታመነ ሰማዕት በመሆኑ ያረፈበት መሬትና ዕፅዋት ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር እያሉ ያመሰገኑበት ነው፡፡ ፠ አማን በአማን፤ አማን በአማን፤ ኮከበ ልዳ ፀሐየ ፋርስ፡፡ ፠ እንደ ጎንደር አበራ ጊዮርጊስ ባሉት ክብረ በዓሉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርዶና አድሮ ነው በዓሉ የሚከበረው፡፡

በዓለ ጥምቀት 2013 ዓ.ም #ፎቶ_ስብስብ_2 .. ከፎቶ ማሕደራችን፡፡ የ2013 ዓ.ም አጫብር አቅራቢዎች ፣ ጳጳሳት ፣ ስራ አመራር ፣ አገልግሎት……
+5
በዓለ ጥምቀት 2013 ዓ.ም #ፎቶ_ስብስብ_2 .. ከፎቶ ማሕደራችን፡፡ የ2013 ዓ.ም አጫብር አቅራቢዎች ፣ ጳጳሳት ፣ ስራ አመራር ፣ አገልግሎት……

በዓለ ጥምቀት 2013 ዓ.ም #ፎቶ_ስብስብ_2 .. ከፎቶ ማሕደራችን፡፡ የ2013 ዓ.ም አጫብር አቅራቢዎች ፣ ጳጳሳት ፣ ስራ አመራር ፣ አገልግሎት……
+9
በዓለ ጥምቀት 2013 ዓ.ም #ፎቶ_ስብስብ_2 .. ከፎቶ ማሕደራችን፡፡ የ2013 ዓ.ም አጫብር አቅራቢዎች ፣ ጳጳሳት ፣ ስራ አመራር ፣ አገልግሎት……

በዓለ ጥምቀት 2013 ዓ.ም #ፎቶ_ስብስብ_2 .. ከፎቶ ማሕደራችን፡፡ የ2013 ዓ.ም አጫብር አቅራቢዎች ፣ ጳጳሳት ፣ ስራ አመራር ፣ አገልግሎት……

#የ2013_ዓ.ም_ከተራ_በዓል ፍቶ ስብስብ 1.. ( 2013 ዓ.ም) ከፍቶ ማህደራችን :: ካህናት ፣ ሰ/ት/ቤት ፣ ማኀበራት እና የአጥቢያችን ወጣቶች

#ጥር_15 ቅዱስ_ቂርቆስ_በ3_ዓመት_ከ1_ወር_ከ3#ቀኑ_አንገቱን_በሰይፍ_ተቆርጦ_ሰማዕትነትን_የተቀበለበት_በዓለ_ዕረፍቱ_ነው፡፡ ##ጥር_16 #እናቱ_ቅድስት_ኢየሉጣ_በክብር_ያረፈችበት_ነው፡፡ #ጌታችን ስምህ_በተጠራበት_ቤተ_መቅደስህ_በታነጸበት_ስዕልህ_ባለበት_ቦታ_ሁሉ_የሕፃናት_እልቂት_የከብት_በሽታ_የእህል_እጦት_ረሀብ_ቸነፈር_አይደርስም የሚል ቃልኪዳንም ጌታችን ገብቶለታል፡፡ #በገባለት ቃል ኪዳንም መሠረት በመዲናችን #በአዲስ_አበባ በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ዘመን የሰው እልቂት የከበት በሽታ ገብቶ በነበረበት ወቅት የቂርቆስ ደብር #መካነ_ሰማዕት ሲተከል የሰውም በሽታ ርቋል፥ የከብት እልቂትም አቁሟል፡፡ #በጎንደር_ደብረ_መንክራት_ቅዱስ_ቂርቆስ_ቤክ_ደግሞ_#ጽዋ_ማስደፋት_ የሚል ሥርዐት አለ ፡፡ በዚህ ሥርዐትም የሰረቀውን ሰው ቅዱስ ቂርቆስ የሚያጋልጥበትና አሁንም ድረስ የሚታይ አስደናቂ ተዓምር ነው፡፡ #share #የሕፃኑ_ቅዱስ_ቂርቆስ ፠ የሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ አባቱ #ቆዝሞስ (ስምዖን) እናቱ #ኢየሉጣ ሲባሉ፤ የተወለደው #በዘመነ_ሰማዕታት በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በኅዳር 15 ቀን ነው፡፡ የትውልድ ሀገሩ በታችኛው እስያ ልዩ ስሙ #አንጌቤን ይባላል፡፡ ፠ #አንጌቤናይት ብጽዕት #ኢየሉጣም ባሏ በሕይወት ባለ መኖሩ በመበለትነት ትኖር ነበር፤ በዘመኑ የነበረው መምለኬ ጣዖት የሆነው ንጉሥ እስክንድሮስ ቅድስት ኢየሉጣን ‹‹ለጣዖቴ ስገጂ›› ብሎ አስገደዳት፡፡ እርሷም ‹‹ሕፃኑ ልጄ መጥቶ ይመስክር›› ብላ ስትናገር ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ተጠራና ተጠየቀ፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ‹‹ለጣዖት አንሰግድም፣ ዘላለማዊ የሆነ የማይሻር አምላክ ስላለ ለእርሱ ነው የምንሰግደው›› ብሎ የአምላኩን ክብር በሕፃን አንደበቱ መሰከረ፡፡ ሕፃኑም ይህንን በመሰከረ ጊዜ ዕድሜው ገና ሁለት ዓመት ከዘጠኝ ወሩ ነበር፡፡ ፠ ንጉሡም እጅግ ተቆጥቶ 40 ጋን ውኃ የሚይዝ በርሜል አስጥዶ 40 ቀን ሙሉ እሳት አስነድዶ ቅንጭብ፣ ዘይት፣ ዝፍጥና ሌላም በእጅጉ የሚጎዱ ነገሮችን (ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል) በውስጡ አስጨመረ፤ የእሳቱ ድምፅ እንደ ነጎድጓድ እስኪሰማ፥ ወላፈኑም እንደ ፀሐይ እስኪያንጸባርቅ ድረስ ሆነ፡፡ የፍላቱም ኃይል 14 ክንድ ያህል እየዘለለ ወጣ፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣን ወደዚያ እቶኑ እሳት እንዲከቷቸው አዘዘ፡፡ በዚያን ጊዜም 11,004 እስረኞች ከእስር ወጥተው እንዲያዩ ሹሙ አዘዘ፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም የፍላቱን ግርማ ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተጠብቆላት ያለውንም ዋጋ ትታ ልትክድ ፈለገች፡፡ ቅዱስ ቂርቆስም ይህን ባወቀ ጊዜ "#እናቴ_ሆይ_ከብረት_ጋን_ግርማ_የተነሳ_አትፍሪ፤_ድንጋፄም_አይደርብሽ" እያለ ከብሉይና ከሐዲስ እየጠቀሰ እንድትጸና አስተማራት፡፡ ፠ እናቴ ሆይ #አናንያ #አዛርያንና #ሚሳኤልን ያዳናቸው እግዚአብሔር እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ውስጥ ሊያድነን ይችላል፡፡ እናት ሆይ ከሚያልፈው ከዚህ ዓለም ጭንቅ ልታመልጭ በሚያልፈው በዘለዓለም እሳት ልትቀጭ ትሻለች፡፡ እናት ሆይ ይህን አትፈልጊ፤ ይቅርብሽ አሁን እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡... እያለ አብዝቶ መከራት፡፡ ነገርግን በዚህም ምክር እናቱን መመለስና ለሰማዕትነት ማዘጋጀት አልቻለም፡፡ ከዚህ በኋላ ቂርቆስ ዓይኖቹን ወደሰማይ አቅንቶ መጸለይ ጀመረ፡፡ ‹‹#እግዚአብሔር_ሆይ_ይህች_ባርያህ_ከምትክድ_ከሕይወት_መጽሐፍ_እኔን_ፋቀኝ...›› ብሎ ጸለየ፡፡ በዚያን ጊዜ ዲያብሎስ ከእርሷ ሸሽቶ ሄደ፡፡ ፠ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ እንዲህ አለች፤ በመንግሥተ ሰማያት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታህ ኃይል ሰጠኝ፡፡ የሚጠብቀንን ገድላችንን እንፈጽምና ድል እንነሣ›› አለችው፡፡ የብረት ጋኑን ሲነድ ሳየው በምንጭ ላይ በዝቶ እንደሚወርድ ጠል ሁኖ አየዋለሁና፡፡ እያለች እየነገረችው ሳለ አንሠተው ከብረት ጋኑ ውስጥ ጨመሯቸው፡፡ በውስጡም አንገትን የሚቆለምም ልብን የሚያጣምም ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርንም የሚበጥስ መሣሪያ ነበረበት፡፡ ወዲያውም #የራማው_ልዑል_ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ገብርኤል እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ ከሰማይ ወረደና የብረት ጋኑን እሳት ፈጽሞ አበረደው፡፡ ከቅዱሳንም አንዱን እንኳን ሳይነካው የብረት ጋን ማቃጠሉና መፍላቱ ፀጥ አለ፡፡ እንደ ውኃም ሆነ፡፡ ፠ ንጉሡም እሳቱ እንዳልጎዳቸው ሲያውቅ ከዚያ አውጥቶ፤.. * በአፍና አፍንጫቸው መርዝ ከተተበት፣ ነገር ግን መርዙ ምንም አልጎዳቸውም እንዳውም ምግብ ሆነላቸው፡፡ * ጨውና በርበሬ በዐይናቸው አነደደበት፡፡ አሁንም ምንም አልነካቸውም፡፡ * ዐሥራ አራት የተሳሉና የጋሉ ብረቶች፤ ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል፥ ሰባቱን በቂርቆስ አካል ውስጥ (ከነዚሁም ሁለቱን በጆሮዎቹ፥ ሁለቱን በዓይኖቹ፥ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ፥ አንዱን በልቡ) ተከሉ፤ አሁንም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ፈወሳቸው፡፡ * በ4 ችንካሮች ላይ አስቀመጧቸው፤ መልአኩ ፈወሳቸው * የራስ ጠጕራቸውን ከቆዳቸው ጋር ገፈው በእሳት ውስጥ ጨመሩት፤ ቅዱስ ገብርኤል እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጥቶ ፈወሳቸው፡፡ * በመቃን ውስጥ ጨመረው በገመድ ሰቀሏቸው፤ መልአኩ አዳናቸው፡፡ (#ሐምሌ_19 ቀን የምናከብረው ክብረ በዓል ከላይ ያሉትን ሁሉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ለቅዱስ ቂርቆስና ኢየሉጣ የተራዳበትን በማሰብ ነው፡፡) ፠ ንጉሡም በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ በብዙ ጭንቅና ሥቃይ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣን ለ3 ዓመታት አሠቃያቸው፡፡ እነርሱም መከራን እየተቀበሉ በከሀዲው ንጉሥ ፊት የአምላካቸውን ስም እየጠሩ መሰከሩ፡፡ ፠ በመጨረሻም ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ተጋድሎውን ፈጽሞ ጥር 15 ቀን በ3 ዓመት ከ1 ወር ከ3 ቀኑ አንገቱን በሰይፍ ተቆርጦ ሰማዕትነትን ተቀበለ፡፡ ሲሰየፍም ከአንገቱም ደም፣ ውኃና ወተት የወጣ ሲሆን ሦስት አክሊላትም ወርደውለታል፡፡ ፠ ሕፃኑም በምድር ላይ አልተቀበረም ይልቁንም ጌታችን በኤልያስ ሰረገላ ሥጋውን አሳርጎለታል፤ ሄሮድስ ላስፈጃቸው #144,000 የቤቴልሔም ሕፃናትም አለቃቸው ነው፡፡ እናቱ ቅድስት ኢየሉጣም በጥር 16 ቀን ሰማዕትቷን በክብር ፈጽማለች፡፡ በዚሁ ዕለት የቅዱስ ቂርቆስ ማኅበርተኞች የሆኑ 11,004 ሰዎች የጌታችንን ክብር እየመሰከሩ በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ ፠ #በነገታው_በጥር_16ም #እናቱ_ቅድስት_ኢየሉጣ_በክብር_ያረፈችበት_ነው (ምንጭ፤ የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰሌዳ መጽሔት፣ ከገድላት አንደበትና ዝክረ ቅዱሳን) #የቅዱስ ቂርቆስ በዓል ከሚከብሩባቸው ዋነኛ ቦታዎች ፠ጎንደር ደብረ መንክራት ቅዱስ ቂርቆስ ቤክ ፠አዲስ አበባ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤክ .. ሌሎቹን ካሉ ጨምሩባቸው #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

#ዘመነ_አስተርእዮ ፠ “አስተርእዮ” በገሀድ መታየት በይፋ መገለጥ ማለት ነው፡፡ በጽርዕ ቋንቋም ኤጲፋኒ(Epiphany) ይባላል፡፡ ዘመነ አስተርእዮ ከጥምቀት በዓል (ጥር 11) አንስቶ አስከ ጾመ ነነዌ ድረስ ያለው ጊዜ ነው፡፡ አስተርእዮ የተባለበት ምክንያትም የማይታየው የአምላክ አካልና ባሕርይ ከሚታየው የሰው አካልና ባሕርይ ጋር ተዋሕዶ የተገለጠበትና ማንነቱ በገሀድ (በዮርዳኖስ ባሕር) የታወቀበት፥ ምሥጢረ ሥላሴም የተገለጠበት ወቅት ስለሆነ ነው፡፡ በዚህ ዘመን የሚውሉ ማንኛውም በዓላት የአስተርእዮ በዓል ይባላሉ፤ ለምሳሌ ጥር 21 እመቤታችን በዓለ ዕረፍቷ ሆኖ ሳለ ‹‹የአስተርእዮ ማርያም›› ይባላል፡፡ #share #በዓለ_ጥምቀት_የጥምቀት_በዓል ፠ የጥምቀት በዓል በየዓመቱ ጥር 11 ዕለት ይውላል በዓሉ የሚጀምረውም ከጥር 10 ዕለት ጀምሮ ሲሆን፤ ኦሪት ለወንጌል አምሳል፣ መርገፍ እንደሆነች፤ በዘመነ ብሉይ የተሠሩ አጽዋማትና በዓላትም በዘመነ ሐዲስ ለተሠሩ አጽዋማትና በዓላተ አምሳል መርገፍ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያተ በብሉይ ይከበር በነበረው በበዓለ መጸለት(ዳስ በዓል) በዓለ ጥምቀት ገብቶበታል፡፡ ይኸውም እንደምን ነው ቢሉ በመጸለት ቀድሞ ካህናተ ኦሪት ለ7ት ቀናት ታቦት ይዘው ወንዝ ወርደው ድንኳን ተክለው ድባብ አጥልተው ጃንጥላ ጥለው ሕዝቡ እህል አከማችተው አባቶቻችን በኢያሱ መሪነት ውኃውን አቁሞ የዮርዳኖስን ወንዝ አሻገራቸው እያሉ ያስቡበት ነበር፤ በዘመነ ሐዲስ በጥምቀተ በዓልም ካህናተ ወንጌል ታቦት ይዘው፤ ወንዝ ወርደው /ውሃ ከትረው/ ድንኳን ተክለው ድባብ አጥልተው ጃንጥላ ጥለው ጌታችን ወደ ዮርዳኖስ ሄዶ በእደ ዮሐንስ በማየ ዮርዳኖስ ተጠመቀ እያው ያስቡበታልና፡፡ /ዘሌ.23÷39-43፣ ኢያ. 3÷16/ #ለጥምቀት_በዓል_ምዕመናን_የምንይዘው_ዥንጉርጉር_በትር_ምሳሌው፣ ፠ ያዕቆብ ከወንድሙ ከኤሳው ሸሽቶ በአጐቱ በላባ ቤት ብዙ ዓመታት ስላገለገለ ለአገልግሎቱ ዥንጉርጉር ሆነው የሚወለዱት በጐች ለያዕቆብ እንዲደረግና ምልክት የሌለባቸውን ለላባ እንዲሰጠው አዘዘው፡፡ ያዕቆብም በጐቹ ምልክት ያለባቸው ሆነው እንዲወለዱ ዥንጉርጉር እንጨት ውኃ በሚጠጡበት ውስጥ ጨምሮ በጐቹም እንደበትሩ ዥንጉርጉር እንደወለዱ እናያለን፡፡ /ዘፍ. 30÷31/ ይህ ምሳሌ ነው፡፡ ፠ በጐቹ የምዕመናን፤ ፠ ውኃው የጥምቀት፤ ፠ አውራዎቹ የመምህራን አንድም የቀሳውስት የሚጸነሱት በትሩን እንጂ አውራውን እንደማይመስሉ ምዕመናንም ሥላሴን ይመስላሉ እንጂ ያስተማራቸውን መምህራንን ቀሳውስትን አይመስሉምና፤ ፠ እንጨቱ ዥንጉርጉር መሆኑ ጌታችን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው /አምላክ ወሰብእ/ ለመሆኑ ምሳሌ፤ ፠ ያዕቆብ የጌታ ላባ የዲያብሎስ ምሳሌ ነው፡፡ ምልክት ያላቸው ለያዕቆብ ምልክት የሌላቸው ለላባ እንደሆኑ ሀብተ ወልድ፥ ሕይወተ ልቡና ያላቸው ለጌታ፤ ሀብተ ወልድና ሕይወተ ልቡና የሌላቸው ለዲያብሎስ የመሆናቸው ምሳሌ ነው፡፡ ምዕመናን ዥንጉርጉር በትር መያዛቸው ሰው የሆነ አምላክ /አምላከ ወሰብእ/ ጌታችንና አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ በመሠረተልን ጥምቀት ተጠምቀን ሀብተ ወልድና ሕይወተ ልቡናን አግኝተን የሥላሴ ልጆች መሆናችንን ለማሳየት ነው፡፡ #ጥምቀት_መንከር፣ መድፈቅ፣መዝፈቅ፣ማጥመቅ፣ሲሆን በተገብሮ ደግሞ መነከር፣ መዘፈቅ፣ መጠመቅ፣ መላ አካልን በውኃ ውስጥ ማስገባት ማለት ነው፡፡ከዚህ በተጨማሪም አጠማመቅ፣ ጠመቃ፣ የማጥመቅና የመጠመቅ ሥራ፣ኀጽበት በጥሩ ውሃ የሚፈፀም፣ የበዓል ስም፤ ጌታችን የተጠመቀበት ዕለት ማለትም ነው፡፡ በብሉይና በሐዲስ ኪዳን የተለያዩ የጥምቀት ዓይነቶች አሉ እነርሱም፡- #ጥምቀት_በብሉይ_ኪዳን_ (የአይሁድ ጥምቀ፣ የኤሲያንስ ጥምቀትና የዮሐንስ ጥምቀት ነበሩ) #ጥምቀት_በሐዲስ_ኪዳን፤ ፩. #የጌታችን_ጥምቀት፤ #የጥምቀት_መሥራች_ማነው_በምንስ_ተመሠረተ? የጥምቀት መስራቹ ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን አመሠራረቱም በትምህርት /ዮሐ.351/፣ በተግባር /ማር.19፣ ማቴ.313/ እና በትዕዛዝ /ማቴ.2813/ ነው፡፡ #ጥንተ_ጥምቀት_ጌታችን_መቼ_ተጠመቀ? ዓለም በተፈጠረ በ5531 ዓመተ ዓለም(በ31 ዓመተ ምሕረት)፤ በዘመነ ሉቃስ፤ በዕለተ ማክሰኞ፤ ጥር 11 ዕለት፤ ሌሊት በ10 ሰዓት ነው፡፡ በተጠመቀም ጊዜ ዕድሜው 30 ዓመት ከ13 ቀን ነበር፡፡ /ፍት.ነገሥ.አን.19፣ ድስቅ.29፣ ተረፈ.ቄርሎስ፣ ሉቃ.323/ #ጌታችን_ለምን_ተጠመቀ_? ሀ. ምሥጢረ ሥላሴን ለመግለጥ ለ. ሰው /አዳም/ በበደል ምክንያት ያጣውን ልጅነት ለመመለስ ሐ. የአዳምና የሔዋንን ዕዳ ደብዳቤ ለመደምሰስ ሠ. ትንቢተ ነቢያትን ለመፈፀም /መዝ.76$16/ ረ. በእርሱ ጥምቀት የእኛን ለመባረክ ሰ. የእግዚአብሔር ልጅ እንድንሆን /ገላ.3$26፣ገላ.4$4፣ሮሜ.8$14፣ዮሐ.1÷13፣1ኛ.ዮሐ.3÷1/ #ጌታችን_ለምን_በዮርዳኖስ_ተጠመቀ? *ትንቢቱን(/መዝ.113$1-8/)፣ *ምሳሌውን(ዮርዳኖስ ከላይ ነቅዑ /ምንጩ/ አንድ ነው ዝቅ ብሎ ለሁለት ‹‹ዮር›› እና ‹‹ዳኖስ›› ተብሎ ይከፈላል፣ ፣ዘፍ.14$14-20፣ መጽሐፈ ነገስት ካልእ 6$1 አንድምታ ና መጽ.ነገሥት ካልዕ 5$16 *ምሥጢሩን (በዮርዳኖስ ተጥሎ የነበረውን የአዳምንና የልጆቹን ደብዳቤ ለመደምሰስ /ቆላ.2$14፣ ኤፌ.2$15፣ ውዳሴ ማርያም ዘሰኑይ ቊ.1/፡፡) ለመፈጸም ነው፡፡ #share #ጌታችን_ለምን_በውኃ_ተጠመቀ?  ትንቢቱ፡- ሀ. ‹‹ጥሩ ውሃንም እረጫችኋለሁ እናንተም ከርኵሰታችሁ ትነፃላችሁ›› ጥሩ ውሃ የተባለ የጥምቀት ውሃ ነው፡፡ /ት.ሕዝ.36$25/ ለ. ‹‹አቤቱ ውኖች አዩህ ውኖች አይተው ፈሩ›› /መዝ.76$16/ ሐ. ድሆችና ምስኪኖች ውኃ ይሻሉ /ኢሳ.41$17/ መ. ‹‹ወይቤ ኩሎሙ እለ ጸምዑ ይሑር ኀበ ማይ፣ እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ ወደ ውኃ ሂዱ›› /ት.ኢሳ. 55$1/  ምሳሌው፡- ዘፍ.1$2፣ አክሲማሮስ ዘሐሙስ #ጌታችን_ለምን_ወደ_ዮሐንስ_ሄደ_ለምንስ_በዮሐንስ_እጅ_ተጠመቀ? 1. ትህትናን ለማስተማር፡ 2. ለአብነትና ሥርዐትን ሊደነግልልን፡- #ጌታችን_በማን_ስም_ተጠመቀ? ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹ሌላውን ሰው በአንተ ስም፣ በባሕርይ አባትህ በአብ፣ በባሕርይ ሕይወትህ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠምቃለሁ አንተን ግን በማን ስም /ምን እያልኩ/ አጠምቅሃለሁ አለው›› ጌታችንም ‹‹ወልዱ ለብሩክ ከሳቴ ብርሃን ተሣሀለነ …፣ እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዐት አንተ የዓለም ካህን ብርሃንን የምትገልጥ የአብ የባሕርይ ልጅ ሆይ ይቅር በለን$ ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘየአትት ኃጢአተ ዓለም፣ እነሆ የዓለምን ሀጢአት የምታስወግድ የእግዚአብሔር በግ /መስዋዕቱ/ እያልክ አጥምቀኝ›› አለው፡፡ /ዮሐ. 1÷30/ #የጥምቀት_ጥቅም_በጥምቀት_የሚገኝ_ጸጋ) ከውኃና ከመንፈስ ዳግመኛ እንወለዳለን፡- ድህነትን እናገኛለን፡- የኃጢአት ሥርየትን እናገኛለን፡- #በጥር_11_በጥምቀት_በዓል_የምንረጨውና_የምንጠመቀው_ጥምቀት_ለቡራኬ_ነው፡፡ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem