ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 335 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 641,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 191

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 335 名订阅者。

根据 14 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -76,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.40%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.40% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 435 次浏览,首日通常累积 1 595 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 25

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 15 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 335
订阅者
-124 小时
-67
-7630
帖子存档
እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓል በሰላም አደረሳችኁ ! ታኅሣሥ_፲፱  በዓለ ቅዱስ ገብርኤል  ሊቀ መላእክት  ፡፡ ቅዱስ ገብርኤል፤ #ሊቀ_መላእክት_በመላእክት_ሁሉ_ላይ_የተሾመ_ነው_ሄኖክ_10፥14 #የአርባብ_የ10ሩ_ነገደ_መላእክት_አለቃ_ነው #ከከበሩ_መላእክት_አንዱ_ነው_ሄኖክ_6፥7፤ #አካሉ እንደ ቢረሌ የሚመስል (ጽሩይ የሆነ) ፥ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ የሆነ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነው፡፡/ዳን.10፥5-9/ #መልአከ_ራማ_ዘራማ_ልዑል_ነው፤ (የራማ ልዑል ነው) #አብሣሬ_ትስብእት_ነው፤ #መጋቤ_ሐዲስ_ነው፤ ቅዱሳንመላእክት #በእግዚአብሔር_ፊት_የሚቆም_መልአክ_ነው_ሉቃ_1፥19፤ #ለቅዱሳን_እውቀትን_የሚገልጽላቸውና_ከአላውያን_የሚታደጋቸው_ነው_ /ድርሳነ_ገብርኤል/ #መልአከ_ሰላሞሙ_ወመልአከ_ኪዳኖሙ_መልአከ_አድኅኖ_መልአከ_ኀይል_መልአከ_ፍስሐ (የሰላም መልአክ ፥ የኪዳን መልአክ፥ አዳኝ መልአክ፥ ኀያል መልአክ ፥ የደስታ መልአክ ነው) #ከሣቴ ጥበብ (ጥበብን የሚገልጽ ነው) /ት.ዳን./ #ናዛዜ_ኅዙናን_ (ያዘኑትን_የሚያጽናና_) መልአክ_ነው፨ ✤ ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔር ልጅ ማለት ነው፤ የወልደ እግዚአብሔርን መወለድ አብሥሯልና፨ አንድም የሁለት ቃለት ጥምር ነው እነዚህም ገብር እና ኤል ሲሆኑ ትርጕማቸውም ገብር አገልጋይ ማለት ሲሆን ኤል ማለት ደግሞ አምላክ ማለት ነው፤ በተገናኘ ገብርኤል ማለት የአምላክ አገልጋይ /የእግዚአብሔርን ልጅ የሚመስል የአምላክ አገልጋይ/ ማለት ነው፡፡ ✼ ነቢዩ ዳንኤል “ዐይኖቼንም አነሣሁ” አለና አስከትሎ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡… ይህንንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኃይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኃይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡(ዳን.10፥5-9) ነቢዩ ዳንኤል እንዲህ ብሎ የተናገረው የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ ነበር፡፡ ፠ “እነሆ ከዋነኞቹ አለቆች” አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ”(ዳን.10፥13) ብሎ በተናገረው ንግግሩ በመላእክት ላይ የተሾሙ ሌሎች አለቆች እንዳሉ ማስተዋል እንችላለን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በቅዱሳን መላእክት ዘንድ ስላሉት ነገዶች ሲገልጽ “… በሰማይ ያለውን በምደር ያለውን የሚታየውንና የማይታየውን መናብርትም ቢሆኑ አጋእዝትም ቢሆኑ መኳንንትም ቢሆኑ ቀደምትም ቢሆኑ ሁሉም በእጁ ሆነ፤ ሁሉም በእርሱ ለእርሱ ተፈጠረ” (ቈላ.1፥16) በማለት ይዘረዝራቸዋል፡፡ ከዚህ ተነሥተን መላእክት በተለያዩ ዐበይት ነገዶች የተከፈሉና ለእያንዳንዱም ነገድ የራሱ የሆነ አለቃ እንዳለው ማስተዋል እንችላለን፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ከእነዚህ ዐበይት የመላእክት ነገዶች መካከል አንዱ በሆነው አርባብ በሚባለው ዐቢይ ነገድ ላይ የተሾመ ሲሆን ከ100ው ነገደ መላእክት መካከል ከበታቹ የሚመራቸው ዐሥር ነገደ መላእክት አሉት፤ ከተማቸውም በሰማየ ራማ ነው፡፡ ✼ ቅዱሳን መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ፊት አውራሪነት የሰው ልጆች ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ተዋግተው ድል ከመንሳታቸው አስቀድሞ፤ እንደ አምላክ ሊመለክ የወደደውን ሳጥናኤልን ቅዱስ ገብርኤል በመቃወም ‹‹ንቁም በበህላዌነ እስከ ንረክቦ (ነአምሮ) ለአምላክነ “አይዟችሁ ፈጣሪያችን እስክናገኘው፣ እስክናውቀው ድረስ በያለንበት ጸንተን እንቁም፡፡” (አክሲማሮስ ገጽ.35) በማለት መላእክትን ያረጋጋ መልአክ ነው፡፡ ✼ ቅዱስ ገብርኤል በተወዳጁ መልአክ በቅዱስ ሚካኤል መሪነት የሰው ልጆች ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ተዋግተው ድል እንዲያደርጉ ወደ ጥልቁ እንዲጣል አድርጓል ራእ12፥7፤ ነቢዩ ኢሳይያስ በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፤… በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምድር ጥልቅም ትወርዳለህ” (ኢሳ.14፥16) በማለት ገለጠልን፤ ወደ ምድር የጣሉት በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል መሪነት እነ ቅዱስ ገብርኤል ናቸው፡፡ ✼ ቅዱስ ገብርኤል ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ከሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው ብሏል (ሉቃ 1፥19)፤ ✼ ታላቁ ነቢይ ሄኖክም ስለ ነገረ መላእክት በተናገረበት አንቀጽ እንዲህ ሲል መስክሯል ‹‹በአበቦች ላይ በገነትም በጻድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾሙ ከከበሩ መላእክት አንዱ ገብርኤል ነው፡፡›› ሄኖክ 6፥7፤ ‹‹በሦስተኛውም በመላእክት ሁሉ ላይ የተሾመ ቅዱስ ገብርኤል ነው›› ሄኖክ 10፥14 እያለ የመልአኩን ክብር ተናግሯል፡፡ ** ቅዱስ ገብርኤል መንፈሳዊ እውቀቱን የሚያካፍላቸው መልአክ ብቻ አይደለም፤ ለእግዚአብሔር በመገዛታቸው ምክንያት ከአላውያን ገዢዎች ከሚደርስባቸው መከራም የሚታደጋቸው መልአክም ነው፡፡ ነገር ግን ያደረጋቸው ተዓምራቶች በመጽሐፍ ቅዱስ፣ በመልክኡ፣ በድርሳኑ፣ በተአምሩ፣ …. የተጻፉ ቢሆንም፤ ✤✼ ታኅሣሥ 19  ካደረጋቸው ተራዳኢነት.. ፠ አናንያና(ሚሳቅ)፣ አዛርያ(ሲድራቅ) እና ሚሳኤል(አብደናጎ) ያዳናቸው ያዳነበት ቀን ነው፡፡ አናንያና(ሚሳቅ)፣ አዛርያ(ሲድራቅ) እና ሚሳኤል(አብደናጎ) የፋርስ ባቢሎን ንጉሥ የነበረው ናብከደነፆር በዱራ(አዱራን) በሚባል ስፍራ ላይ ላቆመው ጣየዖት ምስል ስገዱ ሲላቸው …. የምናምነው አምላክ ያድነናል፤ ባያድነን እንኳን (አምላካችን በእሳት ሰማዕት እንድንሆን ፈቃዱ ቢሆነረ አንኳን) አንተ ላቆምከው ምስል አንሰግድም ብለውታል፡፡ ንጉሡም ወደ እቶን እሳት እንዲጣሉ አድርጓቸዋል፤ በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት ግን ከእቶን እሳቱ የልብሳቸው ዘርፍ እንኳን እሳት ሳይነካው ከእሳቱ ድነዋል፡፡እኛንም ያድነን አሜን:: እንዲሁም ታኀሣሥ 19፤ #ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘሀገረ_ቡርልስ_በዓለ_ዕረፍቱ_ እንዲሁም #ኢትዮጵያዊው_አቡነ_ስነ_ኢየሱስ_ (#ገዳማቸው_በሰሜን_ጎንደር_ትክል_ድንጋይ_አካባቢ_የሚገኘው_) #በዓለ_ዕረፍታቸው_ነው_፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#የቀጨኔ_ደብረ_ትጉሃን_ቅዱስ_ገብርኤል_አመሠራረት ፨ በ1964 ዓ.ም አመጣጡ ያልታወቀ ባሕታዊ  ለዚህ ደብር ታላቅ ሞገስ የሚኾን  ለደብሩም ስመ ገናናነት የቅዱስ ገብርኤል ጽላት የገባ እንኾነ ነው ብሎ ለሊቃ ውንቱ ተናግሮ እንደሄደ ይነገራል ፡፡  ይኼም ባሕታዊ በዓመቱ መጥቶ ታቦተ ሕጉን እንዳልገባ ባየ ጊዜ ለኹለተኛ ጊዜ መልእክቱን አስተላልፏል ፡፡ ፨ የደብሩ ሊቃውንትም የተነገራቸው የመንፈስ ቅዱስ መልእክት መኾኑን ተረድተው ከምእመናን ጋር ተመካክረው ታቦተ ሕጉን ከመድኀኔዓለም ጽላት ጋር አንድ ላይ በማድረግ በየወሩ በማኅሌት ፤ በቅዳሴ ፣  በውዳሴ ብቻ እየተከበረ እስከ 1967 ዓ.ም ቆየ ፡፡ ፨ እማሆይ በለጡ ገብሬ የተባሉት መንፈሳዊ እናት ለቤ.ክርስቲያን በአበረከቱት ገንዘብ በጠላት ዘመን ለደብሩ አስተዳዳሪ #ሊቀ_ሊቃውንት_ገብረ_መስቀል ኋላ #ብፁዕ_አቡነ_ዮሐንስ ከደብሩ ምእመናን ጋር በመመካከር ለአብነት ት/ት ቤት እንዲኾን ብለው አዳራሽ አሠርተው እስከ #አፄ_ኃይለ_ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ድረስ አገልግሎት እየሰጠ  ሲቆይ የነበረውን አዳራሽ  ፤ የደርግ መንግሥት እንደተተካ  1968 ዓ.ም የቀበሌው አስተዳደር አዳራሹን  ለቀበሌው ኪነት መዝናኛ ማዕከል አንዲኹም ለአብዮታዊት ኢትዮጵያ  ወጣቶች ማኅበር  መሰብሰቢያ  ቦታ ለማድረግ ባለሥልጣኑ ወስዶት ስለነበር እስከ ጥቅምት 1972 ዓ.ም ለአራት ዓመታት በቤተ ክርስቲያኑ ውጪ ሆኖ  በወቅቱ ከፍተኛ 9 ቀበሌ 20 ትእዛዝ የአብነት ት/ት ቤቱ አገልግሎት እንዲቋረጥ ተደርጎ ስለነበር ፤ ካህናቱና ምእመናኑ በዚሁ ድርጊት ሲያዝኑና ሲቆረቆሩ ወደ እግዚአብሔር ጸሎት ሲያደረጉ ቆይተዋል ፡፡ ፨ በዚህ እኩይ ድርጊት የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደር ለሚመለካታቸው አካላት ቢያሳውቁም መልስ ፈጽሞ ሊያገኙ አልቻሉም ነበር ፡፡ ልዩ ልዩ የኪነ - ጥብብ ሥራዎች በቤተ-ክርስቲያኑ ቅፅር መካሄዱን እያደረ ሲቀጥል ፤ ልዩ ልዩ ተአምራቶች መታየት ጀመሩ ከእነዚህም መካከል አዳራሽ ውስጥ እኩይ ተግባራቶቹ በተደረጉ ጊዜ የእሳት ፈንዳት በተደጋጋሚ መነሳቱ ነው ፡፡ ከዚህም ቀጥሎ መድጋሚ በአቶ ታደሰ ወ/ኪዳን እና በመ/ሬ ታደሰ መልካሙ ለአ.አ ማዘጋጀ ቤት ጉዳዩን በድጋሚ በመጠየቅ አዳራሹ እንዲለቀቅ ኾኗል ፡፡ ፨ ከዚም በኋላ አዳራሹን በድጋሚ ለሌሌች እኩይ ተግባራት እንዲውሉ ቢታሰብም ፤ የደብሩ አገልጋዮች የመድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን ሊታደስ በመኾኑ ታቦታቱ ወደ እዛ እንዲገቡ በብፁዕ አቡነ ናትናኤልን ፍቃድ በመጠየቅ የተከናወነ ሲሆን በድጋሚ ከእሳቸው ፈቃድ በመጠየቅ እድሳቱ ካለቀ በኋላ የቅዱስ ገብርኤል ታቦት በዛው እንዲቀር ሆኗል ፡፡ ይህ የኾነውም በ1972 ዓ.ም በግንቦት ወር ሲኾን ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በየዓመቱ ክብረ በዓሉ እየታሰበ ፣ ታቦቱ እየወጣ ሲከበር እስከ 1992 ዓ.ም  ቆይቷል ፡፡ ፨ ይህ ገናና የቅዱስ ገብርኤል ታቦተ ሕግ በመቃኞ ቤት መኖር ስለሌለበት ቦታው በቋሚነት  የማያገልግ ስለኾነ አዲስ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ራሱን ችሎ እንዲሠራ ሃሳብ ቀርቦ የተለያዩ ውይይቶች ከተደረጉ በኋላ ሚያዝያ 25 ቀን 1989 ዓ.ም #በብፁዕ_ወቅዱስ_አቡነ_ጳውሎስ_ፓትርያርክ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጦ ፤ ኅዳር 11 ቀን 1990 ዓ.ም የመሠረት ቁፋሮ ተጀምሮ በኹለት ዓመት ሊጠናቀቅ ችሏል ፡፡ ፨ በዚህም  በአ.አ ከተማ በዘመናዊ የቤ.ክ ሕንፃ ሥራ ታሪክ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ በመሠራት የመጀመርያነቱን ይዟል ፡፡ #ቅዳሴ_ቤቱም ሐምሌ 19 ቀን 1992 ዓ.ም ተከብሯል ፡፡ የቤተ ክርስቲያኑም ስያሜ #ደብረ_ትጉሃን_ቅዱስ_ገብርኤል  ተብሏል ፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#በመዲናችን_በአዲስ_አበባ__የቅዱስ_ገብርኤል_ በዓል_የሚከበሩባቸው  #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩) ፠ (መ.መ.ገ.) መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ በ1889 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ፠ አስኮ ቅዱስ ገብርኤል፤ ፠ ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል፤ ፠ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል) ፭) ፠ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ፠ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል በ.ክ. ፠ ደብረ ገነት ፉሪ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት አርሴማና አቡነ አዳም ቤ.ክ. ፲) ፠ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፲፭) ፠ ደብረ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ጋራ ኦዳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አንቆርጫ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፳፠ አቃቂ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቦሌ ሃራብሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቦሌ ቡልቡላ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፳፭) ፠ ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ (የቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. በድርብነት በውስጥ አለ) ፠ ቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ቦሌ መንበረ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ ገሊላ አማኑኤል ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፴) ፠ ጀሞ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ.ክ. ፠ አቃቂ ጃቲ መካነ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ የካ አባዶ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኮልፌ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤል ፴፭) ፠ ኮልፌ ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ. (አዲሱ ሚካኤል) (በድርብነት ይከብራል) ፠ ካራ ቆሬ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ድልበር መካነ ጎልጎታ መድኀኔዓለም (በድርብነት ይከብራል) ፠ አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ (አዲስ ሰፈር) ፵)፠ ደብረ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም ስር የሚገኘው ሙት አንሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ መንበረ ልዑል ገብርኤልና ማርያም ቤ.ክ.፤ ፠ አየርጤና ደብረ ብሥራት ገብርኤልና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ. ፠ ቱሉ ዲምቱ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቀበና ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅ/ገብርኤል ቤ.ክ. ፵፭) ፠ መጠሊ ደብረ አሮን ፍልፍል ዋሻ ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ.ክ. ፠ ቂሊንጦ ደብረ ብሥራት ገብርኤልና ማርያም፤ ፠ ደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)፡፡ ፠ አንቀጸ ምሕረት (ራስ ካሣ) ቅዱስ ሚካኤል፤ (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ ዕንቊ ልደታ ለማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል) ፶) ፠ ቦሌ ቡልቡላ ድብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም፤ (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል) ፠ ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ይከብራል) ፠ ፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል) ፶፬) ፠ ብሥራተ ወንጌል ቅድስተ ማርያም ቤ.ክ.፤ (በድርብነት ይከብራል) #በሃገራችንና_በዓለም_አቀፍ__በዓላቸው_የሚከበሩባቸው_ጥንታውያን   #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩) ዘብር ቅዱስ ገብርኤል (መንዝ ሰ ሸዋ) ፪) ወይቅን ቅዱስ ገብርኤል (ቆላ ተንቤን) ፫) ክብራን ገብርኤል (ጣና ጎጃም) ፬) ቦሎ ገብርኤል (መርሐ ቤቴ) ፭) ጎንደር አቡን ቤት ገብርኤል ፭) ደሴ ገብርኤል ፮) ናዝሬት ገብርኤል ፯) ቁልቢ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ፰) ባሕር ዳር ዐባይ ማዶ ገብርኤል ፱) ሐዋሳ ገብርኤል ፲) ድሬደዋ ሳባ ገብርኤል /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w