Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 398 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 565,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 183 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 398 名订阅者。
根据 29 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 18,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.46%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.24% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 305 次浏览,首日通常累积 1 576 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 30 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 398
订阅者
+224 小时
+327 天
+1830 天
帖子存档
‹‹የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦትን ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡›› ኢያሱ ፫፥፫
የ2013 ዓ.ም የ #በዓለ_ጥምቀት ማስታወሻዎች
ፎቶ ስብስብ 3
ꔰበ1959 ዓ.ም የተወሰደ (የተነሳ) ፍቶ ፤
ꔰ ꔰ ꔰአነ ውእቱ ኖላዊ ሔር
ꔰ ꔰ ꔰ መድኀኔዓለም ዘደብረሰላም
ꔰጥምቀት ሲመጣ ትዝ የሚለን በፍቶ የምትመለከቱት ይህ የደብራችን መለያ የሆነው የጥልፍ ስዕል 57 ዓመታትን አገልግሎናል ፡፡
#ፎቶውን ላጋሩን ለ፤ ሂስትሪክ ኢትዮጲያ ትሩ ካሜራ ሌንስን እጅግ አረገን እናመሰግናልን፤ ፎቶውን መረጃ ያደረገው ‹‹ National Library of Australia›› ነው፡፡
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord
#በዓለ_እግዚእነ #በዓለ_ጥምቀት #Holy_Ephipany
፠ ፠ ፠ #አቃቂ_ቃሊቲ_ክፍለ_ከተማ_ (9ኝ ጥምቀተ ባሕር)
#፵፰ኛ) #ወረዳ_1 #አቃቂ_በሰቃ_ወንዝ
1ኛ. ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል
2ኛ. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ
3ኛ. ጃቲ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
4ኛ. ሰርጢ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም
5ኛ. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔ ዓለም
6ኛ. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል
7ኛ. ፈንታ ደ/ጽ/ቅዱስ ሩፋኤልና ቅድስት አርሴማ
8ኛ. ቀርሣ ፈለገ ብርሃን ቅድስት ልደታ ለማርያም
#፵፱ኛ) #ወረዳ_5 #ከቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ
1ኛ. ቃሊቲ ደብረ ቊስቋም ማርያምና ቅዱስ ሚካኤል
#፶ኛ) #ወረዳ_4 #ሰርቲ_መድኀኔ_ዓለም_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ
1ኛ. ሰርቲ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም
#፶፩ኛ) #ወረዳ_9 #ገብረ_መንፈስ ቅዱስ_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ
1ኛ. ኮዬ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
#፶፪ኛ) #ቃሊቲ_አካባቢ
1ኛ. ሠፈረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል
#፶፫ኛ) #ወረዳ_9 #ሥላሴ_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ
1ኛ. ቂሊንጦ ቅድስት ሥላሴ
#፶፬ኛ) #ወረዳ_10 #ገላን_ጉራራ_ገብርኤል_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ
1ኛ. ገላን ጉራራ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል
#፶፭ኛ) #ወረዳ_11 #ገላን_ኢዶሮ_ገብርኤል_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ
1ኛ. ገላን ኢዶሮ ቅዱስ ገብርኤል
#፶፮ኛ) #መጠሊ_ገብርኤል_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ
1ኛ. መጠሊ ደ/አ/ቅዱስ ገብርኤል
፠ ፠ ፠ #ቦሌ_ክፍለ_ከተማ_ (19ኝ ጥምቀተ ባሕር)
#፶፯ኛ) #ጉምሩክ_ወረዳ_3
1ኛ. ቦሌ ደብረ ሳሌም መድኀኔ ዓለም ወመጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ወአቡነ አረጋዊ
#፶፰ኛ) #ወረዳ_23 #አየር_መንገድ
1ኛ. ደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ክርስቶስ ሰምራ
#፶፱ኛ) #ወረዳ_06 #መገናኛ
1ኛ. መገናኛ መንበረ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ
#፷ኛ) #ወረዳ_02 #ሩዋንዳ_አካባቢ
1ኛ. ቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል
2ኛ. ቦሌ አየር ማረፊያ መንበረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ
#፷፩ኛ) #ወረዳ_13 #አድዋ_ፓርክ
1ኛ. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም
2ኛ. ገርጂ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ
3ኛ. ኤ(የ)ረር ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ዑርኤል
#፷፪ኛ) #ወረዳ_9 #ሰሚት_አደባባይ
1ኛ. ቦሌ ሰሚት መካነ ሰላም መድኀኔ ዓለም
2ኛ. ቦሌ ሰሚት ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ
3ኛ. ቦሌ ሰሚት ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
4ኛ. በሻሌ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም
#፷፫ኛ) #ወረዳ_12 #ቡልቡላ
1ኛ. ቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም
2ኛ. ቦሌ ቡልቡላ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ሳሙኤል ወቅዱ አማኑኤል
3ኛ. ቦሌ ቡልቡላ ፍኖተ ሕይወት ቅድስት ማርያም
#፷፬ኛ) #ወረዳ_9 #ጎሮ_ሰፈር_ባሕረ_ጥምቀት
1ኛ. ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብኤል
2ኛ. ኤረር ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ
3ኛ. ኤረር መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል
#፷፭ኛ) #ወረዳ_13 #አያት_አደባባይ_ #4_ኪሎ_ሰፈር
1ኛ. አያት መ/ሕ/መድኀኔ ዓለም
#፷፮ኛ) #ወረዳ_13 #መሪ_አያት
1ኛ. መሪ ምሥራቀ ፀሐይ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
2ኛ. አያት ጌቴ ሴማኒ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
3ኛ. መሪ ቅዱስ ፋኑኤል
4ኛ. መሪ ቅድስት ሥላሴ
#፷፯ኛ) #በሻሌ
1ኛ. ቦሌ በሻሌ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ እስጢፋኖስ
2ኛ. የቃጥላ ደብረ ፀሐይ ቅድሰት ማርያም
#፷፰ኛ) #ወቄ_አካባቢ
1ኛ. ወረገኑ ቅዱስ ሚካኤል
#፷፱ኛ) #አያት_ጨፌ
1ኛ. አያት ጨፌ ደብረ ኢያሪኮ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ
#፸ኛ) #ወረዳ_11 #ለሚ_ኮንዶሚኒየም
1ኛ. ቦሌ ሰሚት ቅዱስ ሩፋኤልና ኤዎስጣቴዎስ
#፸፩ኛ) #ወረዳ_11 #አራብሳ
1ኛ. አራብሳ ቅዱስ ገብርኤል
2ኛ. ዋሻው አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
#፸፪ኛ) #ለሚ
1ኛ. ቦሌ ለሚ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
2ኛ. ቦሌ ለሚ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
#፸፫ኛ) #አያት_ኮንዶሚኒየም
1ኛ. አያት ጨፌ ቅዱስ ገብርኤል
2ኛ. አያት ፈለገ ሕይወት ቅዱስ ዮሐንስ
#፸፬ኛ) #ቦሌ_ቡኒ
1ኛ. ቦሌ ቡኒ ደብረ ቤቴል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ
#፸፮ኛ) #ሪፈንቲ
1ኛ. ሪፈንቲ ቅዱስ ገብርኤል
2ኛ. ቦሌ ሰሚት መካነ ሕያዋን ዋሻው ቅዱስ ገብርኤል
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord
#በዓለ_እግዚእነ #በዓለ_ጥምቀት #Holy_Ephipany
፠ ፠ ፠ #ኮልፌ_ቀራንዮ_ክፍለ_ከተማ_(9ኝ ጥምቀተ ባሕር)
#፳፮ኛ) #መድኀኔ_ዓለም_ከፍተኛ_መሠናዶ_ትምህርት_ቤት_(ራስ ኀይሉ ሜዳ)
1ኛ. መርካቶ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል
2ኛ. ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሩፋኤል
3ኛ. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል
4ኛ. ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ
5ኛ. ጠሮ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ
#፳፯ኛ) #ሳንሱሲ_መናፈሻ_አጠገብ
1ኛ. አስኮ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል
2ኛ. አስኮ ደብረ መንክራት ቅዱስ ጊዮርጊስ
3ኛ. መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
4ኛ. ፍኖተ ሎዛ ብርጭቆ ማርያም
#፳፰ኛ) #ወረዳ_15_(አርሴማ ጠበል /አወልያ ትምህርት ቤት ጋር/)
1ኛ. ቃሎ ተራራ አቡነ ሀብተ ማርያም
#፳፱ኛ) #ገዳመ_ኢየሱስ_ቤተ_ክርስቲያን_ቅጽር_ግቢ_ውስጥ
1ኛ. ደብረ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም
2ኛ. ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ
3ኛ. ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ
4ኛ. ወይብላ ደብረ ጽዮን ማርያም
5ኛ. ፊሊዶሮ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
6ኛ. መርካቶ ደብረ ገሊላ አማኑኤል
7ኛ. ገዳመ ኢየሱስ
#፴ኛ) #ወረዳ_5_ #ጻድቃኔ_አካባቢ_ታቦት_ማደርያ
1ኛ. ደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ገብረ ክርስቶስ
2ኛ. ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ
3ኛ. አውግስታ ደብረ ጽዮን ማርያም
4ኛ. ጻድቃኔ ማርያም
5ኛ. ፈለገ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት
6ኛ. ወይራ ገነተ ሰማይ ቅድስት አርሴማና ዕጨጌ ዮሐንስ
#፴፩ኛ) #ወረዳ_4_ #አየር_ጤና_ኪዳነ_ምሕረት_ቤተ_ክርስቲያን_አጠገብ
1ኛ. አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
2ኛ. ጀሞ ፈለገ ኮሬብ ቅድስት ሥላሴና ቅድስት ማርያም
3ኛ. ዓለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል
#፴፪ኛ) #ወረዳ_1_ #በቴል_አጠገብ_(ኳስ ሜዳ)
1ኛ. ቤቴል ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል
2ኛ. አንፎ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል
#፴፫ኛ) #በላፍቶ_ክፍለ_ከተማ_ወረዳ_4 #ገብርኤል_ጠበል
1ኛ. ሰፈረ ገነት ቅድስት ሥላሴ
#፴፬ኛ) #ወረዳ_2_ #ሮል_ሳሙና_ፋብሪካ_ፊት_ለፊት
1ኛ. ረጲ ደብረ ጎልጎታ መድኀኔ ዓለም
2ኛ. ካራ ቆሬ ቅዱስ ሩፋኤል
3ኛ. ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል
4ኛ. ግራር ደ/አ/ቅድስት አርሴማ
5ኛ. ወይብላ ደብረ ጽዮን ማርያም
፠ ፠ ፠ #ነፋስ_ስልክ_ላፍቶ_ክፍለ_ከተማ_ (13ት ጥምቀተ ባሕር)
#፴፭ኛ) #ደብረ_ኢያሪኮ_መድኀኔ_ዓለም_ቤተ_ክርስቲያን_አጠገብ
1ኛ. ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል
2ኛ. ፉሪ ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ማርያም
3ኛ. ደብረ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለም
4ኛ. ደብረ ወርቅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
5ኛ. ፈለገ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ
6ኛ. ፉሪ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል
#፴፮ኛ) #ጎፋ_ሠፈር
1ኛ. ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል
2ኛ. ቤዛ ብዙኃን ኪዳነ ምሕረት
3ኛ. ቄራ መብራት ኀይል ደብረ መዊዕ ቅዱስ መርቆሬዎስና ዮሐንስ መጥምቅ
#፴፯ኛ) #ጀሞ_መድኀኔ_ዓለም
1ኛ. ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት
2ኛ. ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል
#፴፰ኛ) #ቻይና_ካምፕ
1ኛ. ፈለገ ዮርዳኖስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና ቅድስት ማርያም
#፴፱ኛ) #ጀሞ_ቊጥር_3_አደባባይ
1ኛ. ጀሞ ቊጥር 3 ቅዱስ ገብርኤል
#፵ኛ) #ቶታል_አደባባይ
1ኛ. ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል
2ኛ. መካኒሳ ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
#፵፩ኛ) #መካኒሳ_ኮንዶሚንየም
1ኛ. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል
#፵፪ኛ) #ዮሴፍ_አካባቢ
1ኛ. ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
2ኛ. ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ
3ኛ. ብሔረ ጽጌ ቅድስት ማርያም
4ኛ. አዲስ አምባ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
5ኛ. ሐመረ ወርቅ ቅድስት ማርያም
#፵፫ኛ) #ብሥራተ_ወንጌል
1ኛ. ደብረ ቢ/ያ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
#፵፬ኛ) #ደብረ_ዕንቊ_ቅዱስ_ገብርኤል
1ኛ. ደብረ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል
#፵፭ኛ) #ፉሪ_ኆኅተ_ብርሃን_ቅድስት_ማርያም
1ኛ. ፉሪ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም
#፵፮ኛ) #ፉሪ_ደብረ_ገነት_ቅዱስ_ዑር(ራ)ኤል
1ኛ. ፉሪ ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል
#፵፯ኛ) #ቡልቡላ_ ኤምባሲ_አጠገብ
1ኛ. ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል
2ኛ. ለቡ በዓለ ወልድ
(‹‹የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦትን ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡›› ኢያሱ ፫፥፫)
#ጥምቀትን_በአዲስ_አበባ__በየትኛው_ጥምቀተ_ባሕር_ያከብራሉ_፤
#በአዲስ_አበባ_በ10ሩም #ክፍለ_ከተሞች_የሚገኙ
#76ት #የጥምቀተ_ባሕር_ቦታዎችና_ወደ_ጥምቀተ_ባሕሩ_የሚወርዱትን_179 #ገዳማትና_አድባራት_እነሆ_ጽፈንላችኋል፡፡
(እኛ በአ.አ. ከሚገኙ 76ት ጥምቀት ባሕር መካከል፤ ብዙ ታቦታት የሚወርዱበትን የጃንሜዳን ፎቶ ለጥፈንላችኋል፤ እናንተም በየአካባቢያችሁ ያሉትን በ‹ኮሜንት› መጻፊያ ላይ ለጥፉልን፡፡)
#share
፠ ፠ ፠ #በአራዳና_ጉለሌ_ክፍለ_ከተማ_ (7ት ጥምቀተ ባሕር)
#፩ኛ) #በጃንሆይ_ሜዳ_ (በጃንሜዳ)፤ /በአዲስ አበባ ትልቁና የ12 አብያተ ክርስቲያናት ታቦታት የሚያድሩበት)
1ኛ. መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ.ክ.፤
2ኛ. ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም፤
3ኛ. መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤
4ኛ. መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ.፤
5ኛ. ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.፤ (የምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ታቦተ ወደ ጥምቀተ ባሕር ስለማይወጣ ሕዝቡና ሰ/ት/ቤቱ አብሮ ነው የሚያከብረው)
6ኛ. መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም
7ኛ. ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ.፤
8ኛ. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (አብሮም ቅዱስ ሚካኤል ይወርዳል)፤
9ኛ. ቀበና መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ.፤
10ኛ. ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ.ክ.፤
11ኛ. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ.፤
12ኛ. ፈለገ ሰላም ቤላ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና አቡተ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ (ቀበና 18 ፓርክ አጠገብ)፡፡
#፪ኛ) #እንጦጦ_ኀሙስ_ገበያ_ሜዳ
1ኛ. እንጦጦ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል ወኤልያስ ቤ.ክ.
2ኛ. እንጦጦ ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም
#፫ኛ) #ሽሮ_ሜዳ_ወረዳ_01 ፥ #ቀበሌ_02_
1ኛ. ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት
2ኛ. መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ
#፬ኛ) #አዲሱ_ገበያ_
1ኛ. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ
2ኛ. መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ተክለሃይማኖት
#፭ኛ) #ወረዳ_3ና_4 (19 ቀበሌ)
1ኛ. መንበረ ንግሥት ቊስቋም ማርያም
#፮ኛ) #ሸጎሌ_መንገድ_
1ኛ. ጉለሌ(ሸጎሌ) ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
2ኛ. ድልበር መድኀኔ ዓለም
#፯ኛ) #ወረዳ_7_ቀበሌ_15(ቤልኤር፤ ኳስ ሜዳ)
1ኛ. ቀበና ምሥራቀ ፀሐይ መድኀኔ ዓለም
፠ ፠ ፠ #በየካ_ክፍለ_ከተማ_ (14ት ጥምቀተ ባሕር)
#፰ኛ) #ወረዳ_8(22 አካባቢ፤ ባልደራስ አጠገብ)
1ኛ. የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል
2ኛ. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል
3ኛ. ቀበና ቤዛዊተ ዓለም ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
#፱ኛ) #ወንድይራድ_ትምህርት_ቤት_አካባቢ_(ኮተቤ)
1ኛ. ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቅዱስ ገብርኤል
2ኛ. ኮተቤ (ኋላ ሲ.ኤም.ሲ.) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል
3ኛ. መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
4ኛ. ሲ.ኤም.ሲ. አቡነ ተክለ ሃይማኖት
5ኛ. ደብረ አራራት ቅዱስ አማኑኤል
6ኛ. ሀገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ
7ኛ. ኮተቤ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ
#፲ኛ) #ዋሻ_ተክለ_ሃይማኖት_ጠበል_ቦታ
1ኛ. ዋሻ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት
2ኛ. አንቆርጫ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል
#፲፩ኛ) #በግ_ተራ
1ኛ. ኮተቤ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
#፲፪ኛ) #ላምበረት_ቤተ_ክርስቲያኑ_አካባቢ
1ኛ. ላምበረት ደብረ ፀሐይ አቡነ አረጋዊ
#፲፫ኛ) #ጉራራ_አካባቢ
1ኛ. ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
2ኛ. ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ
#፲፬ኛ) #ወረዳ_10 #ከጉራራ_ከፍ_ብሎ_ፖሊስ_ሴንተር_አጠገብ
1ኛ. ደብረ መድሐኒት ዳንሴ መድኀኔዓለም
2ኛ. ምሥራቀ ፀሐይ ዳንሴ ቅዱስ ሚካኤል
#፲፬ኛ) #ሎቄ_ቤተ_ክርስቲያን_አካባቢ
1ኛ. ሎቄ መ.ጸ. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
#፲፭ኛ) #ኬንያ_ኤምባሲ_ጀርባ_(በግ ተራ)
1ኛ. ደብረ ዕንቊ ልደታ ለማርያም
#፲፮ኛ) #መሪ_አደባባይ
1ኛ. መሪ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ሥላሴ
2ኛ. መሪ ደብረ ታቦር ቅዱስ ፋኑኤል
#፲፯ኛ) #አባዶና_ካራ_አሎ_አርሴማ_ጠበል_አካባቢ_(ገበያው መሐል)
1ኛ. ካራ አሎ ደብረ ቀርሜሎስ መድኀኔ ዓለምና አቡነ ገሪማ
2ኛ. ካራ አሎ ቅድስት ሥላሴ
3ኛ. አባዶ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ
4ኛ. ኮተቤ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ
#፲፰ኛ) #አባዶ_አካባቢ
1ኛ. አባዶ ገ/አ/ ቅዱስ ሚካኤል
#፲፱ኛ) #አያት_አካባቢ
1ኛ. ጣፎ መ/ብ/ ቅዱስ ገብርኤል
2ኛ. አያት ደ/ክ ቅድስት ማርያም
#፳ኛ) #አባዶ_ኮንዶሚንየም
1ኛ. አባዶ ጽርሐ አርያም ቅድስት ማርያም
2ኛ) ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሩፋኤል
3ኛ) ደብረ ልዕልና ቅድስት አርሴማ
4ኛ) ደብረ መንግሥት መድኀኔ ዓለም
5ኛ) አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
6ኛ. ቅዱስ ሚካኤልና ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ
7ኛ. ኢያሪኮ ቅዱስ ገብርኤል
፠ ፠ ፠ #ልደታ_አዲስ_ከተማና_ቂርቆስ_ክፍላተ_ከተማ_ (5ት ጥምቀተ ባሕር)
#፳፩ኛ) #ቂርቆስ_አካባቢ
1ኛ. ደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ
#፳፪ኛ) #ኦሎምፒያ_ቦሌ_ማተሚያ_ቤት_አካባቢ
1ኛ. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ
2ኛ. ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ
#፳፫ኛ) #ልደታ_ክፍለ_ከተማ_ሜትሮሎጂ_ጀርባ
1ኛ. ደብረ አሚን ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
2ኛ. ጎላ ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ቅዱስ ሚካኤል
#፳፬ኛ) #ሳር_ቤት_ኮንዶሚንየም
1ኛ. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም
#፳፭ኛ) #ቄራ_አካባቢ
1ኛ. አፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል
#ዘመነ_አስተርእዮ
፠ “አስተርእዮ” በገሀድ መታየት በይፋ መገለጥ ማለት ነው፡፡ በጽርዕ ቋንቋም ኤጲፋኒ(Epiphany) ይባላል፡፡ ዘመነ አስተርእዮ ከጥምቀት በዓል (ጥር 11) አንስቶ አስከ ጾመ ነነዌ ድረስ ያለው ጊዜ ነው፡፡ አስተርእዮ የተባለበት ምክንያትም የማይታየው የአምላክ አካልና ባሕርይ ከሚታየው የሰው አካልና ባሕርይ ጋር ተዋሕዶ የተገለጠበትና ማንነቱ በገሀድ (በዮርዳኖስ ባሕር) የታወቀበት፥ ምሥጢረ ሥላሴም የተገለጠበት ወቅት ስለሆነ ነው፡፡ በዚህ ዘመን የሚውሉ ማንኛውም በዓላት የአስተርእዮ በዓል ይባላሉ፤ ለምሳሌ ጥር 21 እመቤታችን በዓለ ዕረፍቷ ሆኖ ሳለ ‹‹የአስተርእዮ ማርያም›› ይባላል፡፡
#share
#በዓለ_ጥምቀት_የጥምቀት_በዓል
፠ የጥምቀት በዓል በየዓመቱ ጥር 11 ዕለት ይውላል በዓሉ የሚጀምረውም ከጥር 10 ዕለት ጀምሮ ሲሆን፤ ኦሪት ለወንጌል አምሳል፣ መርገፍ እንደሆነች፤ በዘመነ ብሉይ የተሠሩ አጽዋማትና በዓላትም በዘመነ ሐዲስ ለተሠሩ አጽዋማትና በዓላተ አምሳል መርገፍ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያተ በብሉይ ይከበር በነበረው በበዓለ መጸለት(ዳስ በዓል) በዓለ ጥምቀት ገብቶበታል፡፡ ይኸውም እንደምን ነው ቢሉ በመጸለት ቀድሞ ካህናተ ኦሪት ለ7ት ቀናት ታቦት ይዘው ወንዝ ወርደው ድንኳን ተክለው ድባብ አጥልተው ጃንጥላ ጥለው ሕዝቡ እህል አከማችተው አባቶቻችን በኢያሱ መሪነት ውኃውን አቁሞ የዮርዳኖስን ወንዝ አሻገራቸው እያሉ ያስቡበት ነበር፤ በዘመነ ሐዲስ በጥምቀተ በዓልም ካህናተ ወንጌል ታቦት ይዘው፤ ወንዝ ወርደው /ውሃ ከትረው/ ድንኳን ተክለው ድባብ አጥልተው ጃንጥላ ጥለው ጌታችን ወደ ዮርዳኖስ ሄዶ በእደ ዮሐንስ በማየ ዮርዳኖስ ተጠመቀ እያው ያስቡበታልና፡፡ /ዘሌ.23÷39-43፣ ኢያ. 3÷16/
#ለጥምቀት_በዓል_ምዕመናን_የምንይዘው_ዥንጉርጉር_በትር_ምሳሌው፣
፠ ያዕቆብ ከወንድሙ ከኤሳው ሸሽቶ በአጐቱ በላባ ቤት ብዙ ዓመታት ስላገለገለ ለአገልግሎቱ ዥንጉርጉር ሆነው የሚወለዱት በጐች ለያዕቆብ እንዲደረግና ምልክት የሌለባቸውን ለላባ እንዲሰጠው አዘዘው፡፡ ያዕቆብም በጐቹ ምልክት ያለባቸው ሆነው እንዲወለዱ ዥንጉርጉር እንጨት ውኃ በሚጠጡበት ውስጥ ጨምሮ በጐቹም እንደበትሩ ዥንጉርጉር እንደወለዱ እናያለን፡፡ /ዘፍ. 30÷31/ ይህ ምሳሌ ነው፡፡
፠ በጐቹ የምዕመናን፤
፠ ውኃው የጥምቀት፤
፠ አውራዎቹ የመምህራን አንድም የቀሳውስት የሚጸነሱት በትሩን እንጂ አውራውን እንደማይመስሉ ምዕመናንም ሥላሴን ይመስላሉ እንጂ ያስተማራቸውን መምህራንን ቀሳውስትን አይመስሉምና፤
፠ እንጨቱ ዥንጉርጉር መሆኑ ጌታችን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው /አምላክ ወሰብእ/ ለመሆኑ ምሳሌ፤
፠ ያዕቆብ የጌታ ላባ የዲያብሎስ ምሳሌ ነው፡፡ ምልክት ያላቸው ለያዕቆብ ምልክት የሌላቸው ለላባ እንደሆኑ ሀብተ ወልድ፥ ሕይወተ ልቡና ያላቸው ለጌታ፤ ሀብተ ወልድና ሕይወተ ልቡና የሌላቸው ለዲያብሎስ የመሆናቸው ምሳሌ ነው፡፡ ምዕመናን ዥንጉርጉር በትር መያዛቸው ሰው የሆነ አምላክ /አምላከ ወሰብእ/ ጌታችንና አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ በመሠረተልን ጥምቀት ተጠምቀን ሀብተ ወልድና ሕይወተ ልቡናን አግኝተን የሥላሴ ልጆች መሆናችንን ለማሳየት ነው፡፡
#ጥምቀት_መንከር፣ መድፈቅ፣መዝፈቅ፣ማጥመቅ፣ሲሆን በተገብሮ ደግሞ መነከር፣ መዘፈቅ፣ መጠመቅ፣ መላ አካልን በውኃ ውስጥ ማስገባት ማለት ነው፡፡ከዚህ በተጨማሪም አጠማመቅ፣ ጠመቃ፣ የማጥመቅና የመጠመቅ ሥራ፣ኀጽበት በጥሩ ውሃ የሚፈፀም፣ የበዓል ስም፤ ጌታችን የተጠመቀበት ዕለት ማለትም ነው፡፡
በብሉይና በሐዲስ ኪዳን የተለያዩ የጥምቀት ዓይነቶች አሉ እነርሱም፡-
#ጥምቀት_በብሉይ_ኪዳን_ (የአይሁድ ጥምቀ፣ የኤሲያንስ ጥምቀትና የዮሐንስ ጥምቀት ነበሩ)
#ጥምቀት_በሐዲስ_ኪዳን፤
፩. #የጌታችን_ጥምቀት፤
#የጥምቀት_መሥራች_ማነው_በምንስ_ተመሠረተ?
የጥምቀት መስራቹ ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን አመሠራረቱም በትምህርት /ዮሐ.351/፣ በተግባር /ማር.19፣ ማቴ.313/ እና በትዕዛዝ /ማቴ.2813/ ነው፡፡
#ጥንተ_ጥምቀት_ጌታችን_መቼ_ተጠመቀ?
ዓለም በተፈጠረ በ5531 ዓመተ ዓለም(በ31 ዓመተ ምሕረት)፤ በዘመነ ሉቃስ፤ በዕለተ ማክሰኞ፤ ጥር 11 ዕለት፤ ሌሊት በ10 ሰዓት ነው፡፡ በተጠመቀም ጊዜ ዕድሜው 30 ዓመት ከ13 ቀን ነበር፡፡ /ፍት.ነገሥ.አን.19፣ ድስቅ.29፣ ተረፈ.ቄርሎስ፣ ሉቃ.323/
#ጌታችን_ለምን_ተጠመቀ_?
ሀ. ምሥጢረ ሥላሴን ለመግለጥ
ለ. ሰው /አዳም/ በበደል ምክንያት ያጣውን ልጅነት ለመመለስ
ሐ. የአዳምና የሔዋንን ዕዳ ደብዳቤ ለመደምሰስ
ሠ. ትንቢተ ነቢያትን ለመፈፀም /መዝ.76$16/
ረ. በእርሱ ጥምቀት የእኛን ለመባረክ
ሰ. የእግዚአብሔር ልጅ እንድንሆን /ገላ.3$26፣ገላ.4$4፣ሮሜ.8$14፣ዮሐ.1÷13፣1ኛ.ዮሐ.3÷1/
#ጌታችን_ለምን_በዮርዳኖስ_ተጠመቀ?
*ትንቢቱን(/መዝ.113$1-8/)፣
*ምሳሌውን(ዮርዳኖስ ከላይ ነቅዑ /ምንጩ/ አንድ ነው ዝቅ ብሎ ለሁለት ‹‹ዮር›› እና ‹‹ዳኖስ›› ተብሎ ይከፈላል፣ ፣ዘፍ.14$14-20፣ መጽሐፈ ነገስት ካልእ 6$1 አንድምታ ና መጽ.ነገሥት ካልዕ 5$16
*ምሥጢሩን (በዮርዳኖስ ተጥሎ የነበረውን የአዳምንና የልጆቹን ደብዳቤ ለመደምሰስ /ቆላ.2$14፣ ኤፌ.2$15፣ ውዳሴ ማርያም ዘሰኑይ ቊ.1/፡፡) ለመፈጸም ነው፡፡
#share
#ጌታችን_ለምን_በውኃ_ተጠመቀ?
ትንቢቱ፡-
ሀ. ‹‹ጥሩ ውሃንም እረጫችኋለሁ እናንተም ከርኵሰታችሁ ትነፃላችሁ›› ጥሩ ውሃ የተባለ የጥምቀት ውሃ ነው፡፡ /ት.ሕዝ.36$25/
ለ. ‹‹አቤቱ ውኖች አዩህ ውኖች አይተው ፈሩ›› /መዝ.76$16/
ሐ. ድሆችና ምስኪኖች ውኃ ይሻሉ /ኢሳ.41$17/
መ. ‹‹ወይቤ ኩሎሙ እለ ጸምዑ ይሑር ኀበ ማይ፣ እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ ወደ ውኃ ሂዱ›› /ት.ኢሳ. 55$1/
ምሳሌው፡-
ዘፍ.1$2፣ አክሲማሮስ ዘሐሙስ
#ጌታችን_ለምን_ወደ_ዮሐንስ_ሄደ_ለምንስ_በዮሐንስ_እጅ_ተጠመቀ?
1. ትህትናን ለማስተማር፡
2. ለአብነትና ሥርዐትን ሊደነግልልን፡-
#ጌታችን_በማን_ስም_ተጠመቀ?
ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹ሌላውን ሰው በአንተ ስም፣ በባሕርይ አባትህ በአብ፣ በባሕርይ ሕይወትህ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠምቃለሁ አንተን ግን በማን ስም /ምን እያልኩ/ አጠምቅሃለሁ አለው›› ጌታችንም ‹‹ወልዱ ለብሩክ ከሳቴ ብርሃን ተሣሀለነ …፣ እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዐት አንተ የዓለም ካህን ብርሃንን የምትገልጥ የአብ የባሕርይ ልጅ ሆይ ይቅር በለን$ ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘየአትት ኃጢአተ ዓለም፣ እነሆ የዓለምን ሀጢአት የምታስወግድ የእግዚአብሔር በግ /መስዋዕቱ/ እያልክ አጥምቀኝ›› አለው፡፡ /ዮሐ. 1÷30/
#የጥምቀት_ጥቅም_በጥምቀት_የሚገኝ_ጸጋ)
ከውኃና ከመንፈስ ዳግመኛ እንወለዳለን፡-
ድህነትን እናገኛለን፡-
የኃጢአት ሥርየትን እናገኛለን
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord
#በዓለ_እግዚእነ #በዓለ_ጥምቀት #Holy_Ephipany
#የጥምቀት_በዓል_አከባበር_በአዲስ_አበባ_ከእንጦጦ_ጋራ_ጥግ_እስከ_ጃንሆይ_ሜዳ_
በአዲስ በአበባ ያሉ ገዳማትና አድባራትም በቦታ ርቀት እስከ ተለያዩበት ቀን ድረስ በእንጦጦ ጋራ ጥግ በአንድ ላይ በመፈናኘት ያድሩ ነበር፤ ኋላ ከቦታ ርቀት በኋላ የተቀሩት በጃንሆይ ሜዳ ማደር ጀምረዋል፡፡ እያደረም ሌሎች ገዳማትና አድባራት ሲመሠረቱ ከጃንሆይ ሜዳ በተጨማሪ ለአጥቢያቸው በሚቀርብ ቦታ ማደር ጀመሩ፡፡
#share
፠ በዓለ ጥምቀት በጃን ሜዳ (ጃንሆይ ሜዳ) መከበር የጀመረው ከ1887 ዓ.ም. አንስቶ መሆኑ ይነገራል፡፡ ስያሜውምና አጀማመሩም ጃንሜዳ የሚለው ጃን፥ ጃኖ ከሚለው ጋራ የተዛመደ ሲሆን ነገሥታት ለመሾም ለመሻር፣ ዳኝነት ለመስጠት፣ ሊቃውንትን ለመሾምና፣ ዐዋጅ ሲያስነግሩ በቤተ መንግሥታቸው አቅራቢያ በሚገኝ ሜዳ ላይ የጃኖ ድንኳን ተክለው ያስነግራሉ፤ ይህም ሜዳ ከጃኖ ጋራ እየተናበበ የቦታ መጠሪያ ሁኗል፡፡ ለምሳሌ፤
‹‹ጃን ተከል›› በጎንደር ነገሥታት፤
‹‹ጃን መራቂ›› በላስታ ነገሥታት፤
‹‹ጃን ተራራ›› በአማራ ሳይንት በአፄ በዕደ ማርያም
‹‹ጃን ሜዳ›› በደብረ ታቦርና በአዲስ አበባ ናቸው፡፡
፠ አዲስ አበባ መዲና በሆነችበት ሰዓት ‹‹መሐል ሰፋሪ‹‹ የሚባሉ የመኳንንት ጕባኤ በዚሁ በጃንሜዳ በስውር ዐድማ የሚያደርጉበት ሆነ አድማውን ሲያደርጉም በጃን ሜዳ ያለው የጃኖው ድነኳን ከሩቅ እንዳይታይ በማቅ ይሸፈን ነበር፡፡ እቴጌ ጣይቱ ይህን የመሰለ ሜዳ የክፉ ምክር መምከሪያ ሆኖ ከሚኖር ተባርኮ ለጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቢሆን ብለው ለአፄ ምኒልክ ሃሳብ አቀረቡላቸው፤ አፄ ምኒሊክም ማለፊያ ብለው ሐሳባቸውን በመቀበል ጃን ሜዳ የጥምቀት በዓል ማክበሪያ እንዲሆን አዘዙ፡፡ እንዲሁም የአፄ ምንሊክ አልጋ ወራሻቸው ልጅ ኢያሱ መሆኑን በግንቦት 10 ቀን 1901ዓ.ም. ዐዋጅ ያስነገሩበት፤ ‹‹ንሥረ ተፈሪ›› የተባለው የመጀመሪያው አውሮፕላንም በ12921ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ያረፈውም በዚሁ ሜዳ በመሆኑ ጭምር ስያሜው ጃንሆይ ሜዳ ተባለ፡፡
፠ በ1887ዓ.ም. በዓለ ጥምቀትን ለመጀመሪያ ጊዜ በጃን ሜዳ በሕብረት ያከበሩት የመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተክርስቲያን፣ የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ነበሩ፡፡
፠ እስከ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ መን ድረስ ግን ታቦታቱ ወደ ቀበና ወንዝ (አፈ ንጉሥ ጥላሁን ሰፈር፤ ከፈረንሳይ ኤምባሲ በታች) ከከተራው አንስቶ አድረው በጥምቀት ዕለት ወደ ጃንሜዳ ይመለሱ ነበር፡፡
ሌሎችም በየሰበካቸው በሚገኝ አምች ቦታ ሲያከብሩ ቆይተው በ1939ዓ.ም. ከንሜዳ እጅግ በጣም ብዙ ያልራቁት (የካ ሚካኤልና ቅዱስ ዑራኤል) በንጉሠ ነገሥቱ ጥሪ ተደርጎ ወደ ጃናሜዳ እንዲመጡ ተደርጎ ነበር፤ ሆኖም ሕዝብ እየበዛ ስላስቸገረ በየአቅራቢያቸው እንዲያድሩ ተድርጓል፡፡
፠ ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኀይለ ሥላሴ በ1936 ዓ.ም በስፍራው የውኃ ቧንቧ እንዲዘረጋ፣ ባሕረ ጥምቀት ገንዳ በግንብ እንዲሰራ፣ የኤሌክትረክ መብራት በቦታው እንዲገባ አድርገዋል፡፡ ዙሪያውን በግንብ ተሰርቶ በቧንቧ የብረት ማገር ውብ ሆኖ እንዲታጠርና በዐፀድና በአበባዎች እንዲያጌጥ አድርገዋል፡፡ ይህ ቦታ ኋላ በ1994ዓ.ም. እድሳት ተደርጎለታል፡፡
፠ እስከ ቅርብ ጊዜያትም ድረስ ወደ ባሕረ ጥምቀት የሚወርዱ ታቦታት ከነድርባቸው ነበር፤ ለምሳሌ ቀቀጨኔ ደብረ ሰላም ከቅዱስ ገብርኤል ጋራ ነበረ፤ ኋላ ግን ድርብ ታቦታት ቀርተው ዋናውን ይዘው የሚወርዱ ሆኗል፡፡ በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ ውስጥ እስከ 2010ዓ.ም ድረስ ….. ባሕረ ጥምቀት (አብሕርተ አጥማቃት) አሉ፡፡
፠ እስከ 1958ዓ.ም. በምስካየ ኅዙናን ተምሮ ማስተማር ማኅበርና በጠቅላይ ቤተ ክህነት የታሪክ ድርሰትና ስብከት ክፍል አስተባባሪነት ከኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ. ሐዋርያዊ ድርጅት፣ ከሊቃውንትና ከመምህራን፣ ከሰዋስወ ብርሃንና ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በተውጣጡ መምህራን በባሕረ ጥምቀቱ የስብከተ ወንጌልና፣ የመዝሙርና የድራማ መርሐ ግብር ያቀርቡ ነበር፡፡ በ1959ዓ.ም. አካባቢ ጥቂት ሰንበት ት/ቤቶች የደንብ ልብስና ነጠላ በማድረግ ታቦታቱን አጅበው አውጥውና አጅበው በመመለስ የበዓሉ ድምቀት እየሆኑ መጡ፡፡
በአሁኑ ወቅት በጃንሜዳ የሚያድሩ ታቦታት 12 ናቸው እነርሱም፤
1ኛ. መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ.ክ.፤
2ኛ. ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም፤
3ኛ. መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤
4ኛ. መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ.፤
5ኛ. ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.፤ (የምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ታቦተ ወደ ጥምቀተ ባሕር ስለማይወጣ ሕዝቡና ሰ/ት/ቤቱ አብሮ ነው የሚያከብረው)
6ኛ. መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም
7ኛ. ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ.፤
8ኛ. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (አብሮም ቅዱስ ሚካኤል ይወርዳል)፤
9ኛ. ቀበና መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ.፤
10ኛ. ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ.ክ.፤
11ኛ. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ.፤
12ኛ. ፈለገ ሰላም ቤላ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና አቡተ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ (ቀበና 18 ፓርክ አጠገብ)፡፡
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord
#በዓለ_እግዚእነ #በዓለ_ጥምቀት #Holy_Ephipany
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
