ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 378 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 573,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 194

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 378 名订阅者。

根据 06 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 32,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.44%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.50% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 449 次浏览,首日通常累积 1 461 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 20

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 07 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 378
订阅者
-424 小时
-257
+3230
帖子存档
#ሐምሌ_ቂርቆስ #ወሥርዓተ_ማኅሌት ሐምሌ 19 ቀን የራማው ልዑል ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑ ቂርቆስንና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣን ከሚነደው እቶን እሳት ያዳነበት ዕለት ነው፡፡ ሦስት ዓመት እንኳን ሳይሞላው በሁለት ዓመት ከዘጠኝ ወሩ ታላቅ ሰማዕትነትን የተቀበለው ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ አባቱ ቆዝሞስ (ስምዖን) እናቱ ኢየሉጣ ይባላሉ፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ በሕዳር 15 ቀን ተወለደ፤ ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ነበርና መምለኬ ጣዖት የሆነው ንጉሥ እስክንድሮስ ቅድስት ኢየሉጣን ‹‹ለጣዖቴ ስገጂ›› ብሎ አስገደዳት፡፡ እርሷም ‹‹ሕፃኑ ልጄ መጥቶ ይመስክር›› ብላ ስትናገር ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ተጠራና ተጠየቀ፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ‹‹ለጣዖት አንሰግድም፣ ዘላለማዊ የሆነ የማይሻር አምላክ ስላለ ለእርሱ ነው የምንሰግደው›› ብሎ የአምላኩን ክብር በሕፃን አንደበቱ መሰከረ፡፡ ሕፃኑም ይህንን በመሰከረ ጊዜ ዕድሜው ገና ሁለት ዓመት ከዘጠኝ ወሩ ነበር፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ዳዊትም ‹‹ከልጆችና ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ›› ሲል እንደተናገረ ፡፡ቅዱስ ቂርቆስም በከሃዲው ንጉሥ ፊት የጌታችንን ክብር በመሰከረ ጊዜ ንጉሡ እጅግ ተቆጥቶ 40 ጋን ውኃ የሚይዝ በርሜል አስጥዶ 40 ቀን ሙሉ እሳት አስነድዶ ቅንጭብ፣ ዘይት፣ ዝፍጥና ሌላም በእጅጉ የሚጎዱ ነገሮችን በውስጡ ጨምሮ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣን ወደዚያ እቶኑ እሳት እንዲከቷቸው አዘዘ፡፡ ንጉሡ እስክንድሮስ ጭፍሮቹን "ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ሙጫ፣ እርሳስ፣ ብረትን፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምሩበት" ብሎ አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮችም ያዘዛቸውን ከፈጸሙ በኀላ መጥተው "ያዘዝከንን ሁሉ ጨምረንበት ነዶ ፈልቷል" አሉት፡፡ "ድምፁም እንደ ነጎድጓድ ይሰማል፤ ወላፈኑም እንደ ፀሐይ ያንፀባርቃል፡፡ የፍላቱም ኃይል 14 ክንድ ያህል እየዘለለ ይወጣል፡፡ በውስጡ የሚጣሉትን ሰዎች እዘዝ" አሉት፡፡ ያንጊዜም ህፃን ቂርቆስንና እናቱን ኢየሉጣን ይዘው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡ በክርስቶስ ስም ስላመኑ በእስር ቤት አግብተው አስረዋቸው ነበርና ፍላቱ ወደ ላይ በሚዘል በብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው በዚያን ጊዜም እልፍ ከአንድ ሺህ አራት መቶ ሰዎች እንዲወጡና በፈላው የብረት ጋን ውስጥ የቅዱሳንን አሟሟት እንዲያዩ ሹሙ አዘዘ፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም የፍላቱን ግርማ ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተጠብቆላት ያለውንም ዋጋ ትታ ልትክድ ፈለገች፡፡ ቅዱስ ቂርቆስም ይህን ባወቀ ጊዜ "እናቴ ሆይ ከብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ፤ ድንጋፄም አይደርብሽ" እያለ ከብሉይና ከሐዲስ እየጠቀሰ እንድትጸና አስተማራት፡፡ "ነገር ግን እናቴ ሆይ አናንያንና አዘርያን፣ ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከዕቶን እሳት እንዳወጣቸው እወቂ፤ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ውስጥ ሊያድነን ይችላል፡፡ እናቴ ሆይ ከሚያልፈው ከዚህ ዓለም ጭንቅ ልታመልጭ በሚያልፈው በዘለዓለም እሳት ልትቀጭ ትሻለች? እናቴ ሆይ ይህን አትርሺ፤ ይቅርብሽ አሁን እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ የእግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለም ይመስገን አለ፡፡ እኛም ይህንን መከራ ልንታገስና የተጠበቀልንን ልንከተል ይገባናል..." እያለ አብዝቶ መከራት፡፡ ነገር ግን በዚህም ምክር እናቱን መመለስና ለሰማዕትነት ማዘጋቸት አልቻለም፡፡ ከዚህ በኋላ ቂርቆስ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ መጸለይ ጀመረ፡፡ በዚያን ጊዜ ዲያብሎስ ከእርሷ ሸሽቶ ሄደ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ እንዲህ አለች፡- በመንግስተ ሰማያት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታህ ኃይል ስጠኝ፡፡ የሚጠብቀንን ገድላችንን እንፈፅምና ድል እንነሣ" አለችው፡፡ የብረት ጋኑን ሲነድ ሳየው በምንጭ ላይ በዝቶ እንደሚወርድ ጠል ሁኖ አየዋለሁና፡፡ ቅዱሳንም ይህንን ሲነጋገሩ አንስተው ከብረት ጋኑ ውስጥ ጨመሯቸው፡፡ በውስጡም አንገትን የሚቆለምም ልብን የሚያጣምም ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርንም የሚበጥስ መሣሪያ ነበረበት፡፡ ወዲያውም የራማው ልዑል ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ ከሰማይ ወረደና የብረት ጋኑን እሳት ፈጽሞ አበረደው። ከቅዱሳንም አንዱን እንኳን ሳይነካው የብረት ጋን ማቃጠሉና መፍላቱ ፀጥ አለ፡፡ እንደ ውኃም ሆነ፡፡ ንጉሡም እሳቱ እንዳልጎዳቸው ሲያውቅ ከዚያ አውጥቶ በሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ አፍና አፍንጫ መርዝ ከተተበት፣ ነገር ግን መርዙ ምንም አልጎዳውም እንዳውም ምግብ ሆነው፡፡ ዳግመኛም ጨውና በርበሬ በዐይኑ አነደደበት፡፡ አሁንም ምንም አልነካውም፡፡ ከዚህም በኀላ ሹም እስክድሮስም አስራ አራት የተሳሉና የጋሉ ብረቶች ያመጡ ዘንድ ዳግመኛ አዘዘ፡፡ ሰባቱን በእናቱ አካል ሰባቱን በሱ አካል ውስጥ ይተክሉ ዘንድ ከነዚሁም ሁለቱን በጆሮዎቹ ሁለቱን በዓይኖቹ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ አንዱን በልቡ ይተክሉ ዘንድ አዘዘ፡፡ በሕፃኑም ላይ ሹሙ እንዳዘዘው አደረጉበት፡፡ አሁንም ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና ፈወሳቸው፡፡ ዳግመኛም የሕጻኑን እራስ ከነቆዳው ገፈው በእሳት ውስጥ ይጨምሩ ዘንድ አንድ ሹም አዘዘ፡፡ እንዲሁም አደረጉበት፡፡ ዳግመኛም ቅዱስ ገብርኤል እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጥቶ ይህንን መከራ ከሕፃኑ አራቀለት፡፡ ዳግመኛም ሹሙ በመቃን ውስጥ ጨመረው በገመድ እንዲሰቅሉት አዘዘ፡፡ ከዚህም መከራ መልአኩ አዳነው፡፡ በዛሬዋ ዕለት ሐምሌ 19 ቀን በዓሉን በታላቅ ድምቀት የምናከብረው ይህንን ሁሉ የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤልን ተራዳኢነት በማሰብ ነው፡፡ የፊታችን እሁድ የሊቀ መልአኩ እና የሁለቱ ቁዱሳን ታቦታት ባሉባቸው አቢያተ ክርስቲያናት የሚቆመውን ሙሉ የማኅሌቱ ሥርዓት አቅርበንላችኋል፡፡ መልካም የምስጋና ሌሊት ይሁንላችሁ!!! የቅዱሳኑ ረድኤት በረከት ምልጃ ጸሎት ከእኛ ጋር ትሁን፡፡ የሊቀ መልአኩ ጠብቆት አይለየን፡፡

የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን የታነጸችው #ዛሬ_ሰኔ_20 በ51ዓ.ም ነበር፡፡ አናጺውም ደግሞ እራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ቦታው #ፊልጰስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ
የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን የታነጸችው #ዛሬ_ሰኔ_20 በ51ዓ.ም ነበር፡፡ አናጺውም ደግሞ እራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ቦታው #ፊልጰስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ #በእመቤታችን ስም ነበር። ✥ ✥ ✥ “…እግራችሁ ሁል ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም እንደማይናወጥ የብረት ችንካር በቤተ እግዚአብሔር የተተከለ ይሁን…” (ቅዳሴ አትናቴዎስ) ✥ ✥ ✥ #ፎቶ_ፍኖተ_ሕይወት

“ከሰው ልጆች እንደእኔ ጠዋትም ማታም የሚተክዝ የለም፤ ከመላእክትም እንደ አንተ ያዘኑትን የሚያጽናና መልአክ የለም። አንተን አውቄ ፈልጌሃለሁና #ቅዱስ_ገብርኤል ሆይ አረጋጋኝ፤ ድምጽህንም አሰማኝ፤
“ከሰው ልጆች እንደእኔ ጠዋትም ማታም የሚተክዝ የለም፤ ከመላእክትም እንደ አንተ ያዘኑትን የሚያጽናና መልአክ የለም። አንተን አውቄ ፈልጌሃለሁና #ቅዱስ_ገብርኤል ሆይ አረጋጋኝ፤ ድምጽህንም አሰማኝ፤ የማቀርብልህ የጸሎቴ ፍሬ ይህ ነውና።” (#መልክአ_ገብርኤል) ✥✥✥ #ፎቶ_ፍኖተ_ሕይወት

#ሕንጸተ_ቤታ_ለማርያም #ወሥርዓተ_ማኅሌት ሰኔ 21 ከእመቤታችን 33ቱ በዓላት አንዱ ነው፤ #ህንጸተ_ቤተክርስቲያን ይባላል። በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን በአምላክ እናት ስም የታነጸችው ሰኔ 20 ነው። አናጺውም ደግሞ እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ቦታው #ፊልጵስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ #በእመቤታችን_ስም ነው። ጥንተ ነገሩስ (ታሪኩ) እንደምን ነው ቢሉ:- ... ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርቱን ‹‹ሑሩ ወመሐሩ ኩሎ አሕዛበ፤ አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ፡፡›› /ማቴ. 28:19/ ባላቸው ቃል መሠረት ዓለምን በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል:: የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና (ዮሐ. 6:56) አበው ሐዋርያት ቁርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው ያቆርቡ ነበር:: በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን ፣ ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲህ ይከናወን ነበር:: ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኩራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቁጥር እጅጉን በዛ:: በተለይ‎ ቅዱስ ጳውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ:: በዚህ ምክንያት መምሕራን ሕዝቡን ‹‹ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?›› ቢሏቸው ‹‹እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት እንደው የለን›› ሲሉ መለሱላቸው:: ... ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት #ጳውሎስና_በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች ‹‹ለምን አናንጽም?›› ብለው ነበር:: ቅዱስ ጳውሎስ ግን ‹‹ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም›› አለ:: (ለዚህ ነው ዛሬም ሊቀ ጳጳስ ካልፈቀደ ቤተክርስቲያን የማይታነጸው፡፡) ከዚያ ቅዱሳን ጳውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን #ለቅዱስ_ጴጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹የጌታችን ፈቃዱ መሆኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ›› ብሎ አዋጅ ነገረ:: ... በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔያቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መልአክትን አስከትሎ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ፤ እመቤታችን በቀኙ ነበረች፡፡ ሁሉንም ሐዋርያት በሩቅም በቅርብም ያሉትን ደቀ መዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ ሰበሰባቸው፡፡ ከዚያም በስተምሥራቅ ከከተማ ወጣ ወዳለ ሥፍራ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ፡፡ 3ቱንም ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቦ አንሥቶ ጎተታቸው፡፡ ድንጋዮቹም እንደሰም ተለጠጡ፣ እንደ ግድግዳም ሆኑ፡፡ ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ለሐዋርያቱ ሠጣቸው፡፡ እነርሱም እሣት እንዳየው ሰም ከእጃቸው እየለመለሙ (እየተሳቡ) ቁመቱን 24 ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ግርምት የምትሆን 3 ክፍል ያላትን #የመጀመሪያዋን_ቤተክርስቲያን #በ52_ዓ.ም #ሰኔ_20 ቀን አነጹ፡፡ ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ፤ ጌታችንም በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ አድርጎ አነጻት፤ ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ለሐዋርያቱ ‹‹እንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ፡፡›› ብሏቸው ዐረገ፡፡ ... በማግስቱ ሰኔ 21 ዕለት ደግሞ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላዕክትን፣ ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዟት ወረደ:: ሐዋርያቱ አብዛኞቹ እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት 2 ነገሮችን አሳየ፤ አስቀድሞ ቤተክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን አሳየ:: ... ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስን ከመካከል አቁሞ ‹‹አርሳይሮስ›› ሲል ሾመው:: ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ‹‹አክዮስ›› እያሉ 3 ጊዜ አሰምተው ጮሁ:: #አክዮስ ማለት በግዕዙ #ይደልዎ በአማርኛው ደግሞ #ይገባዋል_ያሥምርለት እንደ ማለት ነው:: ... ጌታችን ይህን ከከወነ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ:: አማናዊት ማኅደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ሆኖ፣ ሐዋርያት ድንግልን ከበው፣ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቆመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ:: ... በዚያች ዕለት በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ:: ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው:: ‹‹ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን አንጹ፤ ይህችን ዕለት የሚያከብራትን አከብረዋለሁ::›› ብሏቸው ከድንግል እናቱ ከመላዕክቱ ጋር ዐረገ:: ... #ሰኔ_ጎልጎታ፦ በሌላ በኩል ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም በዚህ ቀን (ሰኔ 21) ልጇን ወዳጇን ጐልጐታ ላይ ለኃጥአን ምሕረትን ለምናዋለች:: ጌታችንም ‹‹ስምሽን የጠራውን፤ በቃል ኪዳንሽ ያመነውን ሁሉ እምርልሻለሁ፡፡›› ብሏታል:: የፊታችን እሁድ በሁሉም አቢያተ ክርስቲያናት የሚቆመውን የእናታችንን ሙሉ #የማኅሌቱ_ሥርዓት አቅርበንላችኋል፡፡ መልካም የምስጋና ሌሊት ይሁንላችሁ!!! የድንግል እመቤታችን ልመናዋ ክብሯ፣ ጣዕመ ፍቅሯና በረከቷ በሁላችን ላይ ይደርብን:: ... ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#የሰንበት_ትምህርት_ቤቱ_ጥያቄ አሁንም አጭርና ግልጽ ነው፡፡ #ሕንጻ_ማስገንባት_የሚችል_ቋሚ_የመማርያና_ማስተማርያ_ቦታ_ቅጽረ_ቤተክርስቲያን_ውስጥ_ማግኘት_ብቻ፡፡
#የሰንበት_ትምህርት_ቤቱ_ጥያቄ አሁንም አጭርና ግልጽ ነው፡፡ #ሕንጻ_ማስገንባት_የሚችል_ቋሚ_የመማርያና_ማስተማርያ_ቦታ_ቅጽረ_ቤተክርስቲያን_ውስጥ_ማግኘት_ብቻ፡፡

#ሕጻናቱ ብርድና ዝናብ በሚፈራረቅባቸው፣ የህጻናትን አዕምሮ መሰብሰብ በማይችሉ ቦታዎች እየተማሩ መሆናቸውን ልብ ይለዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ብዙ ወላጆች ልጆቻቸውን ለመላክ ፈቃደኞች አይደሉም፡፡ ታዲያ
#ሕጻናቱ ብርድና ዝናብ በሚፈራረቅባቸው፣ የህጻናትን አዕምሮ መሰብሰብ በማይችሉ ቦታዎች እየተማሩ መሆናቸውን ልብ ይለዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ብዙ ወላጆች ልጆቻቸውን ለመላክ ፈቃደኞች አይደሉም፡፡ ታዲያ ቤተክርስቲያን ልጀቿን የምታስተምርባቸው #የመማርያ_ክፍሎች አያስፈልጓትም?

ካልጠፋ ቦታ #አፀዶች_ተቆርጠው የሚሰጠንንስ ቦታ እንዴት በፀጋ እንቀበለዋለን? አፀዶች እንዲቆረጡ የሚያደርገው ውሳኔስ እንዴት ተቀባይነት ይኖረዋል?
ካልጠፋ ቦታ #አፀዶች_ተቆርጠው የሚሰጠንንስ ቦታ እንዴት በፀጋ እንቀበለዋለን? አፀዶች እንዲቆረጡ የሚያደርገው ውሳኔስ እንዴት ተቀባይነት ይኖረዋል?

#ጥንታዊ_አፀዶች_እንዲቆረጡ_እና_የሴቶች_መጠለያ_እንዲፈርስ_የሚያደርገው_ውሳኔ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለደብራችን ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት የተጻፈው የውሳኔ ደብዳቤ እና ደብሩ ለሰ/ት/ቤቱ ሰጥቻለሁ ያለው ቦታ (#የሴቶች_መጠለያ) የሚከተሉትን #ሁለት_መሠረታዊ_ነጥቦች ያላገናዘበ ነው፡፡ … #1ኛ_የደብሩን_አፀድ የዚህ ታላቅ ደብር አፀድ በተለያዩ ሀገር በቀል ዛፎች የተከበበ ሲሆን አብዛኛውን ቦታ የሚይዙት ግን የጥድ ዕጽዋቶች ናቸው፡፡ በሌሎች አድባራትና ገዳማት ባልተለመደ መልኩ እንደ መቀነት #በሰባ_ሁለቱ_አርድዕት_ምሳሌ የተተከሉት ጥዶች ለሁለቱም አቢያተ ክርስቲያናት ግርማ ሞገስ ሰጥተዋቸዋል፡፡ (ፎቶ ይመልከቱ) እነዚህ ዕጽዋት በአዲስ አበባ መኖርዎትን እስከሚረሱ ድረስ መንፈስን የመግዛት፣ አእምሮን የመሰብሰብ፣ ኅሊናን የመመሰጥ አቅም ለደብሩ አላብሰውታል፡፡ ከአዲስ አበባና ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚመጡ ምእመናን በመጀመሪያ ከሚደነቁባቸው ነገሮች አንዱና ዋነኛው እስከ አሁንም ድረስ አፀዱ ተጠብቆ የመቆየቱ ጉዳይ ነው፡፡ #ፓትርያርክ_ብፁዕ_ወቅዱስ_አቡነ_ማቲያስ ለንግሥ በዓላት ወደ ደብሩ ሲመጡ ዓይናቸው የሚያርፈው የካህናቱ ሽብሸባ እና #የደብሩ_አፀዶች ላይ ነው፡፡ በመጡ ቁጥር የደብሩን አፀድ እንደ አዲስ እያዩ አድንቀው፤ ጠብቀው የቆዩትን አባቶች አመስግነው ይሄዳሉ፡፡ የአፀዱ ማማር ከተለያዩ የሀገራችን ገዳማትና አድባራት ብዙ መነኮሳትና ሊቃውንት ሲመጡ እንዲያርፉበትና የጸሎት ቦታቸው እንዲሆን አስችሏል፡፡ … ይህ ከሀገረ ስብከቱ የተላከው የውሳኔ ደብዳቤ በቅዱስ ገብርኤል መጠለያ ውስጥ እና ከአካባቢው ያሉ አጸዶች እንዲቆረጡ ያደርጋል፡፡ እጅግ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህንን ውሳኔ ማደራጃ መምሪያው እንዳይወስን አስቀድመን በአካባቢው አጸዶች እንዳሉ ማሳሰባችን እና ይሄ ጉዳይ እየታወቀ መወሰኑ ነው፡፡ … በአንድ ወቅት ከማደራጃ መምሪያው ኃላፊ #መምህር_እንቁባህርይ ጋር ባደረግነው ውይይት ስለሚቆረጡት የደብሩ አፀዶች ጉዳይ ሲነሳ ‘‘ደሞ ስለ አፀድ ምን አገባችሁ!? እሱ የምዕመናን ጉዳይ ነው፤ ለምን የተሰጣችሁን ቦታ አሜን ብላችሁ አትቀበሉም?’’ የሚል ምላሽ ነበር ያገኘነው፡፡ በውኑ እነዚህ ታሪካዊ የደብሩ አፀዶች የምዕመናን ጉዳይ ብቻ ናቸው? ካልጠፋ ቦታ አፀዶች ተቆርጠው የሚሰጠንንስ ቦታ እንዴት በፀጋ እንቀበለዋለን? አፀዶች እንዲቆረጡ የሚያደርገው ውሳኔስ እንዴት ተቀባይነት ይኖረዋል? … #2ኛ_የሴቶች_መጠለያ የጸሎት ቤት የሆነቸው ቅድስት ቤተክርስቲያን ለምእመናን ካዘጋጀቻቸው የጸሎት ሥፍራዎች አንዱ የቤተክርስቲያንን አጥሮች ተጠግተው የሚሰሩ መጠለያዎች(ገረገራዎች) ናቸው፡፡ በእነዚህ መጠለያዎች ምእመናን ያስቀድሱባቸዋል፤ በግልና በማኅበር ሆነው ጸሎት ያደርሱባቸዋል፤ ከንስሐ አባቶቻቸው ጋር ሆነው ይመካከሩባቸዋል፤ ሱባኤ ይይዙባቸዋል፤ የተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮቻቸውን በመወያት ይፈቱባቸዋል፤ በማኅበር ጽዋ ይጠጡባቸዋል፡፡ … በደብራችን ለወንዶች እና ለሴቶች የተሰሩ ሁለት መጠለያዎች አሉ፡፡ እነዚህ መጠለያዎች ለምእመናን ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ቅዳሜ እና እሁድ ለሰ/ት/ቤቱ ሕጻናት ተማሪዎች መማርያ በመሆን የሰ/ት/ቤቱን የቦታ እጥረት ይቀርፋሉ፡፡ (ፎቶዎችን ይመልከቱ) … ይህ የደብሩን ደብዳቤ መሠረት አድርጎ የተወሰነው የሀገረ ስብከቱ ውሳኔ ከቅዱስ ገብርኤል በስተ ቀኝ የሚገኘውን የሴቶች መጠለያ #ሙሉ_በሙሉ እንዲፈርስ ያደርጋል፡፡ ቢቻል ይህንን ገረገራ ከሚሰጠው ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶች አንጻር በአዲስ መልክ እድሳት አድርጎና አስፋፍቶ መስራት ሲገባ እንዲፈርስ ውሳኔ መስጠት ግን እጅጉን አሳዛኝ ነው፡፡ መጠለያው መፍረሱ ከምንም በላይ ጸሎተኛ እና ሱባኤተኛ ምዕመናንን ይጎዳል፡፡ ካልጠፋ ቦታ መጠለያ ፈርሶ የሚሰጠንንስ ቦታ እንዴት በፀጋ እንቀበለዋለን? ገረገራ እንዲፈርስ የሚያደርገው የሀገረ ስብከቱስ ውሳኔ እንዴት ተቀባይነት ይኖረዋል? #የቤተ_መቅደሱንስ_ግርማ_የሚጋፋ ሕንጻ እንዲተከል መፍቀድ እንዴት ልክ ይሆናል? ግልጽና አጭር የሆነው የሰ/ት/ቤቱ ጥያቄ የሚፈልገው ግልጽና አጭርና መልስ ብቻ ነው፡፡ ጉዳዩን በዚህ መጠን ማወሳሰብ ተገቢ አይደለም፡፡ … #ሰንበት_ትምህርት_ቤቱ_እንደሁል_ጊዜው_አባቶቹን_አክባሪ_ነው፡፡ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ደብሩ በገቢ ሩሱን ለመቻል ለሚያደርገው ጥረት ሁሉ ደጋፊ ነው፡፡ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ልማቱን በገንዘብ፣ በዕውቀት፣ በጉልበት፣ በሀሳብ ለመርዳት ዝግጁ ነው፡፡ …. #የሰንበት_ትምህርት_ቤቱ_ጥያቄ አሁንም አጭርና ግልጽ ነው፡፡ #ሕንጻ_ማስገንባት_የሚችል_ቋሚ_የመማርያና_ማስተማርያ_ቦታ_ቅጽረ_ቤተክርስቲያን_ውስጥ_ማግኘት_ብቻ፡፡ #ሕጻናትና_ወጣቶች_ላይ_ትኩረት_አድርጋ_የማትሠራ_ቤተ_ክርስቲያን_ራዕይ_የሌላት_ናት_ብጹዕ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ ... ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ገሪማ_ገረምከኒ ከዕለታት አንድ ቀን #አቡነ_ገሪማ መቁነን(ለገዳማውያን የሚሰጥ ምግብ) ተቀብለው ከሌሎች መነኮሳት ወንድሞቻቸው ጋር ወደ መንገድ ሲሄዱ ቤተ ክርስቲያን ያገኛሉ። ለመሳለም እጅ ሲነሱ
#ገሪማ_ገረምከኒ ከዕለታት አንድ ቀን #አቡነ_ገሪማ መቁነን(ለገዳማውያን የሚሰጥ ምግብ) ተቀብለው ከሌሎች መነኮሳት ወንድሞቻቸው ጋር ወደ መንገድ ሲሄዱ ቤተ ክርስቲያን ያገኛሉ። ለመሳለም እጅ ሲነሱ የደብሩ ካህናት እየተቻኮሉ መጥተው “ቅዳሴ ሊታጎልብን ነውና ከእናንተ የሚቻለው አንድ ሰው ይርዳን እባካችሁ” አሏቸው። የቀሩት መቁነናቸውን ቀምሰውት ነበር። #አቡነ_ገሪማ ግን ቋጥረው ይዘዋት ስለ ነበር ከቅጥሩ ውጭ አስቀምጠዋት ገብተው ቀድሰው ወጡ። እነዚያ አብረዋቸው የነበሩ መነኮሳትም አቡነ_ገሪማ በልተው የቀደሱ መስሏቸው ለታላቁ አባት አባ ጰንጠሌዎን ሄደው ነገሯቸው፤ አባ ጰንጠሌዎንም አዘኑ። #አቡነ_ገሪማን አስጠርተው መነኮሳቱን “አድርጎት እንደሆነ እንዳያፍር፤ ለብቻው እንዳወራው ጥቂተ እልፍ በሉ!” አሏቸው። #አቡነ_ገሪማ ይህንን አውቆ “ሰዎች ብቻ አይደሉም፤ ዛፉም እንጨቱም ገለል ይበል” ቢሉ የቤተ ክርስቲያኑ አጸድ፣ እንጨቶችና ድንጋዮችም አንድ ምዕራፍ (800 ሜትር) ተጠራርገው ሸሹ። አባ ጰንጠሌዎን ያዩትና የሰሙት ሁሉ ደንቋቸው “ወልድየ ይስሐቅ #ገረምከኒ (ልጄ ይስሐቅ ገረምከኝ)” አሏቸው። ከዚህ በኋላ ይስሐቅ የሚለው የቀድሞ ስማቸው ቀርቶ #ገሪማ ተባሉ። አቡነ ገሪማ ወደ ገዳማቸው መደራ ሲሔዱ እነዚያ የሸሹ ዛፍና ድንጋዮች “ገሪማ ለእኛም ግሩም ነህ” እያሉ በዝማሬ ተከትለዋቸዋል። ይህንን መሠረት በማድረግ ቅዱስ ያሬድ በመዝሙሩ “#ገሪማ_ገረምከኒ፤ አስኬማከኒ አልባቲ ሙስና። አባ ገሪማ አስገረምኸኝ፤ ለምንኵስናህም እንከን የለባትም።” በማለት አመስግኗቸዋል፡፡ #ዛሬ ሰኔ ፲፯ #በዓለ_ዕረፍታቸው ነው። በረከታቸው ከእኛ ልጆቻቸው ጋር ትሁን! ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክ

የደብራችን አገልጋይ የሆነው #ዲያቆን_አብርሃም_ጸጋዬ #ቤተ_ክርስቲያናዊ በሆነ ዜማ ላሕይ የተዘጋጁ ኦርቶዶክሳዊ መዝሙራትን አቅርቦልናል። ያድምጧቸው! YOU TUBE 🔔 SUBSCRIBE 🔔 #ቤተ_አብርሃም_ዘቀጨኔ ወንድማችንን ለበለጠ አገልግሎት ያትጋልን!

“...እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ፤ ቦኑ ለከንቱ #ኪዳንኪ ኮነ። ...ያለ በጎ ሥራ የምጸድቅ ካልሆነ፤ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ #ቃል_ኪዳንሽ በከንቱ ነበርን?” (መልክአ ኪዳ
“...እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ፤ ቦኑ ለከንቱ #ኪዳንኪ ኮነ። ...ያለ በጎ ሥራ የምጸድቅ ካልሆነ፤ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ #ቃል_ኪዳንሽ በከንቱ ነበርን?” (መልክአ ኪዳነ ምሕረት) ✥ ✥ ✥ በቃል ኪዳኗ ትጠብቀን ✥ ✥ ✥

‹‹ከ600 ካሬ ውጪ 599 ካሬ እንኳን ቢሆን ተቀባይነት የለውም፤ ከ600 ካሜ ያነሰ ስፋት ያለው ቦታ በማቅረብ ወደፊት እንደ አስፈላጊነቱ እንሰጣለን የሚለውን ሀሳብ አንቀበልም›› የሚሉትን ውሳኔዎች #ሙሉ_በሙሉ በመቀልበስ ከጋራ ውሳኔው ትንሽ እንኳን የማይቀራረብ 295 ካሜ እንዲሰጥ በመወሰኑ እና በጋራ ጉባኤው እንዲያጣራ የተሰየመው ኮሚቴ ‹‹በቀን 07/06/2012 በተወያየነው መሠረት የተዘጋጀ አለመሆኑን እንገልጻለን›› ብሎ ያቀረበውን የመስክ ሪፖርት #በዜሮ_ያባዛ_በመሆኑ ነው፡፡ … ይህ የማደራጃው እና የሀገረ ስብከቱ ውሳኔ ወቅቱን የጠበቀ አለመሆኑም ሌላኛው አሳዛኝ ነገር ነው፡፡ በዓለማችን ላይ በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ቤተክርስቲያን ለረጅም ጊዜ በመዘጋቷ፤ ሰ/ት/ቤቱ ምዕመናን የህክምና ባለሙያዎችን ምክር እየሰሙ ዳግመኛ የቅድስት ቤተክርስቲያን ደጆች እንዳይዘጉ ርብርብ በሚያደርግበት እና ለውሳኔው ይግባኝ መጠየቅ በማይቻልበት ሰዓት መምጣቱ ሌላው የውሳኔው አሳዛኝ ገጽታ ነው፡፡ … #ይወቁት ይህ ውሳኔ ከደብሩ እኩል የተተከሉት እድሜ ጠገብ ዛፎች #እንዲቆረጡ_ያደርጋል፡፡ ይህ ውሳኔ የሴቶች መጠለያ #ሙሉ_በሙሉ_እንዲፈርስ_ያደርጋል፡፡ ይህ ውሳኔ 100 ዓመታትን ያስቆጠረው የደብሩ ቅርስ የሆነውን_አጥር_ያፈርሳል፡፡ ይህ ውሳኔ #የቤተ_መቅደሱንም_ግርማ_የሚጋፋ_ሕንጻ_እንዲተከል ይፈቅዳል፡፡ ይህ ውሳኔ በቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግሥ በዓላት ወቅት #ከፍተኛ_መጨናነቅ_እንዲኖር ያደርጋል፡፡ … የሰ/ትቤቱ_ጥያቄ እሁንም አጭርና ግልጽ ነው፡፡ #ሕንጻ_ማስገንባት_የሚችል_ቋሚ_የመማርያና_ማስተማርያ_ቦታ_ቅጽረ_ቤተክርስቲያን_ውስጥ_ማግኘት_ብቻ፡፡ … #ሰንበት_ትምህርት_ቤቱ_እንደሁል_ጊዜው_አባቶቹን_አክባሪ_ነው፡፡ ሰ/ት/ቤቱ ደብሩ በገቢ ራሱን ለመቻል ለሚያደርገው ጥረት ሁሉ ደጋፊ ነው፡፡ ሰ/ት/ቤቱ ልማቱን በገንዘብ፣ በዕውቀት፣ በጉልበት፣ በሀሳብ ለመርዳት ዝግጁ ነው፡፡ … #የሰንበት_ትቤቱን_የቋሚ_ቦታ_ጥያቄ_አወናብዶና_አጭበርብሮ_በማለፍ_ያሰብኩትን_አሳካለሁ_ማለት_ግን_ተገቢ_አይደለም፡፡ … ስለ ነገዋ ቤተክርስቲያን የምትጨነቁ ከሆነ የሰንበት ትምህርት ቤትን አገልግሎት በልባችሁ አኑሩ፡፡›› ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስካልዕ ... (LIKE, SHAREEE በማድረግ መልዕክቱን አስተላልፉ!!)፤ ... ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https:// www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-16 20932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/ medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w