Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 371 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 624,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 193 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 371 名订阅者。
根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -34,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.49%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.98% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 457 次浏览,首日通常累积 1 226 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 22。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 371
订阅者
+224 小时
+327 天
-3430 天
帖子存档
✤✤ #እቲሣ_ገዳም ( የአቡነ ተክለሃይማኖት የልደት ሥፍራ )
እቲሳ ገዳም (ዞረሬ /ጽላልሽ/ /ምስካየ ኅዙናን/፡፡ ክርስትናን በመላዋ ኢትዮጵያና እስከ ጎረቤት ሀገሮች መዳረሻ ድረስ በስፋት የሰበኩ ፥ ገዳማትና አድባራት የተከሉ ፤ ከዋክብት ሰማይን በብርሃናቸው እንደሚያደምቁት ፥ እንዳስጌጡት ሁሉ፤ በጽድቃቸው፥ በትሩፋታቸው ለቤተ ክርስቲያን ፋና የሆኑ፤ የ99 ቅዱሳን፥ የ566 መናንያን ቅዱሳን መፍለቂያ፤ 17 የጥንት ዋሻዎች፣ 31 አዳዲስ ዋሻዎች የሚገኙበት ነው እቲሳ ገዳምና ዙሪያው፡፡ ገዳሙ ከአዲስ አበባ ከተማ በቅርብ ርቀት በደሴ በር (በደብር ብርሃን መስመር) በ38 ኪ.ሜ ላይ ፤ ከአሌልቱ በስተቀኝ በመታጠፍ ….. ይገኛል፡፡
✤✤ #ይህ_ታላቅ_ገዳም
#በቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃና አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን የተመሠረተ፤ ሲመሠረትም በታቦተ ኢየሱስና አርባዕቱ እንስሳ ነው፤
#ሊቀ ካህናት አበይድላ ከአኵስም 300 ታቦታትና 300ካህናት ይዞ መጥቶ በጽላልሽ የተቀመጠባት ናት፤
#ፀሐይ አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱባት (የተወለዱባት ጠፍጣፋ ደንጊያ አሁንም በቦታው አለች)፣
#አባታቸውና ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእኀረያ የተወለዱበት፤ ኋላም ክብሩ አጽማቸው ያረፈበት ነው፡፡
#ቅዱስ ያሬድ 3 ዓመት ጸልዮባታል፤
#ቅዱስ ላሊበላ 7 ዓመት ጸልዮባታል፤
#ተሰዓቱ ቅዱሳን 20 ዓመት የጸለዩበት፤
#ሐርቤ በሚባለው ቦታ ላይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ 7 ዓመት ጸልየውበታል፤
#ታቦተ ጽዮን 12 ዓመት (ከ9ሺህ ሕዝብ) ጋር መጥታ ኖራበታለች፤
#በአምሳለ ሲዖል የተሠራ አስደናቂ የጨለማ ዋሻ ያለበት ነው፤
#ብዙ የታሪክ ቅርስ ያለበት ነው፤
#በቅዱስ ሚካኤልና ጸጋ ዘአብ ቤተ ክርቲያን ውስጥ ካየን በኋላ፤ እዚሁ ቦታ በሚገኘው ፈዋሽ ጠበል ተጠምቀንና ጠጥተን ጕዟችንን ወደ
ቦታው ከአ.አ በቅርብ ርቀት በደብረ ብርሃን መንገድ አሌልቱ ከተማ ላይ በመታጠፍ ይገኛል፡፡
#ሥርዐተ_ማኅሌቱን እንደየደብራችሁ ይትበሃል እንድትጠቀሙበት (በላይ ቤትና በታች ቤት) (#ዘአባጃሌ_ተክለ_ሃይማኖትና_ዘአደባባይ_ተክለሃይማኖት) አዘጋጅተነዋል፡፡
ጸሎትና በረከታቸው፤ ረድኤትና ምልጃቸው በመላው ሕዝበ ክርስቲያንና በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ሁሉ አድሮ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#ኢትዮጵያውያን_ቅዱሳን
#ከኢትዮጵያ_ውጭ_የሚከበርባቸው_ #፲፯ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. ኢየሩሳሌም ምስካበ ቅዱሳን ተክለ ሃይማኖት ገዳም (ኢየሩሳሌም፤ በአላዓዛር)
፪. ቨርጂኒያ ምሥራቀ ፀሐይ ተክለ ሃይማኖት (አሜሪካ)
፫. ብሪታንያ ሊቨርፑል መካነ ቅዱሳን ተክለ ሃይማኖት (እንግሊዝ)
፬. ስቶክሆልም ምዕራፈ ቅዱሳን ተክለ ሃይማኖት (ስዊዲን)
፭. ክላርክስተን ዳግማዊ ቁልቢ ደብረ ብሥራት ገብርኤልና ተክለ ሃይማኖት
፮. ግብጽ እስክንድርያ ተክለ ሃይማኖት፤
፯. ግብጽ እስክንድርያ አል አጋሚ ተክለ ሃይማኖት፤
፰. ግብጽ እስሙናይ (እል መኖፊያ) ተክለ ሃይማኖት፤
፱. ግብጽ ኤል ዛግዚክ ተክለ ሃይማኖት፤
፲. ግብጽ ኤል ሙሐራቅ አስዩት ተክለ ሃይማኖት፤
፲፩. ኬንያ ማሴኖ ተክለ ሃይማኖት (የግብጽ)
፲፪. ሎስ አንጀለስ ተክለ ሃይማኖት (የግብጽ)
፲፫. ኦታዋ ኦንታሪዮ ተክለ ሃይማኖት (የግብጽ)
፲፬. ብራምፕተን ኦንታርዮ ተክለ ሃይማኖት (የግብጽ)
፲፭. ፐርዝ አውስትራልያ ተክለ ሃይማኖት (የግብጽ)
፲፮. ሲድኒ አውስትራልያ ዳርዊን ተክለ ሃይማኖት
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
፶፫. አምስትያ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ (ደቡብ ጎንደር፥ እብናት)
፶፬. አጣ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጠበል (ደቡብ ጎንደር፥ ፋርጣ፥ ጋሳይ ከተማ (ከደ/ታቦር ከተማ በ18ኪሜ ርቀት) አካባቢ የሚገኘው
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፶፬ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡
(፩-፫) ✣፫ቱ ደብረ ሊባኖሶች፥ ፪ቱ በእጨጌዎች የሚመሩ
፩. ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ (የበርካታ ቅዱሳን መፍለቂያና አጽማቸው በክብር ያረፈበት)
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት፥ ደብረ ሊባኖስ
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ሊባኖስ (ገዳም) የሚል ትራንስፖርት ያገኛሉ፡፡
ወይም ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ፍቼ(ባህር ዳር) በሚሄድ ትራንስፖርት ደብረ ጽጌን እንዳለፉ ጫገል የምትባል መንደር ላይ ወርደው በታክሲ(በባጃጃ) (በእግር) በመጓዝ ያገኙታል፡፡
፪. ጎንደር፥ አዘዞ ደብረ ሊባኖስ፤
የኢትዮጵያ ርዕሰ መዲና ከ300 ዓመታት በላይ ጎንደር ላይ በነበረበት ወቅት ዳግማዊት ደብረ ሊባኖስ ሆኖ በእጨጌ እየተመራ የቆየ ታላቅ ገዳም፡፡
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አዘዞ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ (ባሕር ዳር) → በጎንደር መስመር → ጎንደር ከተማ ሊገቡ ሲሉ አዘዞ ከተማ መግቢያ ላይ ወደ ደንቢያ፥ ቆላ ድባ መታጠፊያ ላይ ያኙታል፡
፫. ኤርትራ ሺምዛና ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፡፡
አድራሻ፤ ኤርትራ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → ኤርትራ → ሺምዛና፡፡
፭. ኮራ ተክለ ሃይማኖት፤ (ጻድቁ የጸለዩበት)
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት፥ ሰላሌ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከደብረ ሊባኖስ ገዳም ወደ ቆላው በእግር በመሄድ ያገኙታል፡፡
፮. ወይንጌ(ዬ) ተክለ ሃይማኖት፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ደብረ ብርሃን፡፡
ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ መናኸሪያ → ደብረ ብርሃን ከተማ → በባጃጅ (በእግር) በመጓዝ ያገኙታል፡፡
፯. አጆራ ተክለ ሃይማኖት፤
(አቡነ ተክለ ሃይማኖት በኢትዮጵያ በባለ መንታ ፏራቴነት ብቸኛ በሆነው አጆራ ላይ ከእጨጌ ዮሐንስና ከሌሎችም ደቀ መዛሙርቶቻቸው ጋር መቶሎሚ በቀፎ አድርጎ የወረወረበት፥ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ያዳናቸው ቦታ፡፡
ታሪክን ታሪክ ደግሞት 3ኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በቦታው ላይ ሱባኤ በመግባት በግራኝ መሐመድ ጊዜ ጠፍ ሆኖ የነበረውን ቤተ ክርስቲያንና ንዋያተ ቅድሳት ያገኙበት)
አድራሻ፤ ደቡብ፥ ሌሾ፥ አጆራ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ አየር ጤና መናኸሪያ → ደቡብ (ሌሾ፥ አጆራ)
፰. ደብረ ገሪዛን (ገርዜን) ጕንዳጕንዶ ማርያም፤ (የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ/ክ ለብቻው አለ)
አድራሻ፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት ፥ አዲግራት
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. → አዲግራት → በእዳጋ ሐሙስ መስመር → ወደ አሲምባ የሚወሰደውን መንገድ በመተው ወደ ጕንዳጕንዶ በመሄድ ያገኙታል፡፡
፱. አንጋራ ተክለ ሃይማኖት፤ (ከጣና ገዳማት አንዱ)
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጣና ደሴት
ትራንስፖርት፤ ከአ. መርካቶ መናኸሪያ → ጎንደር → ጎርጎራ (ወይም ከባሕር ዳር) → አንጋራ (በደንገል (በመርከብ /በጀልባ/) በመጓዝ ያገኙታል፤
፲. አባ ጃሌ ተክለ ሃይማኖት፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ)
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ
ትራንስፖርት፤ ከአ. መርካቶ መናኸሪያ → ጎንደር → ፒያሳ
፲፩. አደባባይ ተክለ ሃይማኖት፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ)
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ
ትራንስፖርት፤ ከአ. መርካቶ መናኸሪያ → ጎንደር → አራዳ በሚል ታክሲ
፲፪. መቀለ ተክለ ሃይማኖት፤
አድራሻ፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ መቀለ
ትራንስፖርት፤ ከአ. ጉርድ ሾላ መናኸሪያ → መቀለ
፲፫. ግሸና ተክለ ሃይማኖት፤
አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ግሸና
ትራንስፖርት፤ ከጎንደር → ደቡብ ጎንደር (ደብረ ታቦር) → ግሸና ተክለ ሃይማኖት፡፡
፲፬. ሚጣቅ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ አንኮበር፥ ሚጣቅ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ መናኸርያ → ደብረ ብርሃን ፥ በአንኮበር መስመር ሚጣቅ፡፡
፲፭. ጎንድ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንድ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ መናኸርያ → በጎንደር መስመር ማክሰኚት → ጎንድ፡፡
፲፮. ደብረ ድማኅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤
(በ352 ዓ.ም. በአቡነ ሰላም ከሣቴ ብርሃን በታቦተ መድኃኔዓለምና ማርያም የተመሠረተ)
አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ደላንታ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ መናኸርያ → ደሴ /ደላንታ/፡፡
፲፯. ወላይታ ሶዶ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤
አቡነ ተክለ ሃይማኖት 12 ዓመት ቆመው የጸለዩበት፤ ከሞተሎሜ ቤተ መንግሥት ዳሞት ተራራ ግርጌ የሚገኝ፤
የሀገረ ስብከቱ መንበረ ጵጵስና ያለበት፡፡
አድራሻ፤ ወላይታ ሀገረ ስብከት፥ ወላይታ ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና መናኸርያ → ወላይታ፡፡
፲፰. አኵስም ተክለ ሃይማኖት፤ (ከደብረ ጽዮን አኵስም አጥር ለአጥር የተያያዘ ቤ/ን)
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከጸለዩበት የአኵስም ጽዮን ቤ/ን አጠገብ የተሠራ፡፡
አድራሻ፤ አኵሰም ሀገረ ስብከት፥ አኵስም ከተማ፥ ጽዮን፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. → አኵስም፡፡
፲፱. ጣራ ዋሻ ተክለ ሃይማኖት፤
አድራሻ፤ ማዕከላዋ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጣራ ገዳም፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ መናኸሪያ → በጎንድር መስመር (ጣራ ገዳም)፡፡
፳. ጥዑመ ግራራ አጆራ ተክለ ሃይማኖት፤
(አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከእጨጌ ዮሐንስ ጋራ ሆነው በሞተለሜ ትእዛዝ በአጆራ ባለ 2ት ፏፏቴ በንብ ቀፎ የተወረወሩበትና ቅዱስ ሚካኤል ያዳናቸው)
አድራሻ፤ ወላይታ ሶዶ ሀገረ ስብከት፥ ጣራ ገዳም፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና መናኸሪያ → ወላይታ /አጆራ/ → ጥዑመ ግራርያ፡፡
፳፩. መርጠሉ ማርያም ደብረ ቢታንያ ተክለ ሃይማኖት (ደቡብ ወሎ፤ ንጉሥ አብርሃና አጽብሃ ከአባ ሰላማ ጋር በ333 ዓ.ም. የመርጡለ ማርያምን ገዳም ሲገድሙ ሱባኤ ከያዙባቸው አንዷ ተራራ)
፳፪. ቈየፃ ተክለ ሃይማኖት
፳፫. አንኮበር ተክለ ሃይማኖት (ሰሜን ሸዋ)
፳፬. ወግዲ ተክለ ሃይማኖት (ሰሜን ሸዋ)
፳፭. መንዝ ኮረብቲት ተክለሃይማኖት (ሰሜን ሸዋ)
፳፮. ራዛ ተክለ ሃይማኖት (ትግራይ)
፳፯. እምባይቶ ተክለ ሃይማኖት (ትግራይ)
፳፰. አራሮ ተክለ ሃይማኖት (ትግራይ)
፳፱. አፈር ባይኔ ተክለ ሃይማኖት
፴. ደጋ ዳሞት ተክለ ሃይማኖት (ምዕራብ ጎጃም)
፴፩. ባሕር ዳር ተክለ ሃይማኖት (ምዕተራብ ጎጃም፥ ባሕር ዳር ከተማ)
፴፪. ሰነቦ ተክለ ሃይማኖት (ምዕራብ ጎጃም)
፴፫. ቆላድባ ተክለ ሃይማኖት (ጎንደር፥ ደምቢያ፥ ቆላድባ)
፴፬. ደብረ ታቦር አንቀጸ አድኅኖ ዑራኤል ወተክለ ሃይማኖት (ደቡብ ጎንደር )
፴፭. ሽና ተክለ ሃይማኖት
፴፮. ጉባ ላፍቶ ተክለ ሃይማኖት (ወሎ)
፴፯. ደሴ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (ሰሜን ወሎ፥ ደሴ)
፴፰. ዳቦት ተክለ ሃይማኖት
፴፱. የጁ ከረዩ ተክለ ሃይማኖት
፵. ጃናሞሬ ተክለ ሃይማኖት
፵፩. ገሬኖ ተክለ ሃይማኖት
፵፪. ቃሊቲ ገላን ጎሮ ተክለ ሃይማኖትና ኪሮስ
፵፫. ደብረ ዘይት (ቢፍቱ) ተክለ ሃይማኖት
፵፬. ሻሸመኔ ተክለ ሃይማኖት
፵፭. ሐዋሳ ተክለ ሃይማኖት
፵፮. ወንጂ ደብረ ፀሐይ ተክለ ሃይማኖት
፵፯. ሆሳዕና ደብረ ፀሐይ ተክለ ሃይማኖት
፵፰. አርባ ምንጭ ተክለ ሃይማኖት
፵፱. ሐረር ተክለሃይማኖት
፶. ጅግጅጋ ተክለ ሃይማኖት
፶፩. ባሌ ጎባ ደበረ ሰላም ተክለ ሃይማኖት ገዳም
፶፪. ወጠቅ ደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት፤
የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን በዓለ ልደት የት ሊያከብሩ ዐስበዋል ?? share
#በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በመላው_ዓለም_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፺፫ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
(በተለይም በድርብነት ያሉ በዓለ ልደቱን ላያከብሩ ስለሚችሉ ሲሄዱ አጣርተው ይሂዱ )
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን)
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#በአዲስ_አበባ_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፳፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፬. ደብረ ጽላልሽ (ዞረሬ) አቲሣ ተክለ ሃይማኖት፡፡ (#ጻድቁ_የተወለዱበት)
አድራሻ፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት፥ ጽላልሽ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. → በደብረ ብርሃን መንገድ አሌልቱ ከተማ ላይ በመታጠፍ ያገኙታል፡፡
፩ ✣ ጥንታዊው በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤
(ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዋሻ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም)
/በአብርሐ ወአጽብሐ ዘመን በ‹‹ሐ›› ቅርጽ በልዩ አሠራር የታነጸ ፍልፍል ዋሻ፤ ከ1600 ዓመታት በላይ ያስቈጠረ፡፡/
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሾላ (መገናኛ)
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (4 ኪሎ) → ሾላ (መገናኛ) → የካ ሚካኤል → በእግር የ30 ደቂቃ መንገድ፤
ወይም ወደ ኮተቤ በአዲሱ መንገድ ሲሄዱ መንገድ ላይ ወርደው ተራራውን እንደወጡ ያገኙታል፡፡
፪ ✣ደብረ አሚን ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤
/ከዓመት እስከ ዓመት ከበዓለ ሃምሳ ውጭ እንደ ደብረ ሊባኖስ ውሎ ቅዳሴ የሚቀደስበት/
አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ መርካቶ ተክለ ሃይማኖት፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (ከአውቶቡስ ተራ) → መርካቶ ተክለ ሃይማኖት
፫ ✣ መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል፥ አቡነ ተክለሃይማኖትና ቅድስት አርሴማ ገዳም፤
አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ በቀጨኔ በአዲሱ ገበያና በእንጦጦ መሃል ከደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ/ክ በላይ ጉብታው ላይ የሚገኝ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → ቀጨኔ(አዲሱ ገበያ) → የ20 ደቂቃ የእግር መንገድ፡፡
፬ ✣ ሲ.ኤም.ሲ. መካነ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅድስት ልደታ፤
አድራሻ፤ የካ ክ/ከ፤ ሲ.ኤም.ሲ.፤ መሪ ሎቄ፤ ለገጅጃ
ትራንስፖርት፤ ከመገናኛ ሲ.ኤም.ሲ.
፭ ✣ ኮልፌ ፊሊዶሮ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከ፥ ፊሊዶሮ፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → መርካቶ → ኮልፌ አጣና ተራ /ፊሊዶሮ/፡፡
፮ ✣ ፍኖተ ሎዛ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ (በድርብነት ይከብራል)
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከ፥ ብርጭቆ ኮንዶሚንየም
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ አረዳ → ብርጭቆ
፯ ✣ (ጀሞ) ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → ጀሞ
፰ ✣ ደብረ ቢታንያ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ፥ 5 ቊጥር (2 ቊጥር) ማዞርያ
ትራንስፖርት፤ ከፒያሰ (መርካቶ)→ ሜክሲኮ → ንፋስ ስልክ
፱ ✣ ቦሌ ቡልቡላ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ሥላሴ ገዳም፤
(አስደናቂ ጠበል ያለበት)
አድራሻ፤ ቤሌ ክ/ከ፥ ቡልቡላ
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (ከመገናኛ) → ሳሪስ አቦ → ቡልቡላ መድኀኔዓለም
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#እንዲሁም_በአንድነት_፤
፲ ✣ መጠሊ ደብረ አሮን ፍልፍል ዋሻ ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ገላን ጉራ ገበሬ ማኅበር፥ መጠሊ፤
ታክሲ፤ ከቃሊቲ → ገላን፡፡
፲፩ ✣ (ቀበና) ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሲግናል ዐደባባይ → ዐድዋ ድልድይ → ኮንጎ ሰፈር (ከበአታ ቤ/ን ፊት ለፊት)፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ካዛንቺስ (22) /በአዋሬ በኩል በሚሄዱት)፡፡
፲፪ ✣ ቱሉዲምቱ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ/ክ፤
አድራሻ ፤አቃቂ ቃቲ ክፍለ ከተማ፥ ቱሊ ዲምቱ አደባባይ ወደ አለም ባንክ መንገድ ላይ ነዳይ ማደያ ጋር፤
ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉ ዲምቱ → ዐደባባይ አለም ባንክ፡፡
ወይም ከቃሊቲ → ቱሊዲምቱ (አለም ባንል,ክ ነዳጅ ማደያው ጋር)
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#እንዲሁም_በድርብነት_፤
፲፫ ✣ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል፥ 24ቱ ካህናተ ሰማይና ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → የካ አባዶ፡፡
፲፬ ✣ ቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኀኒት መድኀኔዓለም ቤ/ክ
አድራሻ፤ ቤሌ ክ/ከ፥ ቡልቡላ
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (ከመገናኛ)→ ሳሪስ አቦ → ቡልቡላ መድኀኔዓለም
፲፭ ✣ ገነተ ኢየሱስና ገነተ ማርያም (እናትና ልጇ) ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ፤
ታክሲ፤ ከ4(6) ኪሎ → ፈረንሳይ፡፡
፲፮ ✣ ቤላ መጥምቀ መለከት ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ቤላ ፈረንሳይ ፓርክ፤
ታክሲ፤ ከ4 (6 ኪሎ) → ቤላ (ፈረንሳይ)
፲፯ ✣ ሰርጢ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከ፥ ሰርጢ
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (ከመገናኛ) (ከመርካቶ)→ አቃቂ
፲፰ ✣ ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ.
አድራሻ፤ ኮለረፌ ቀራንዮ ክ/ከ፥ ቤተል
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → ቤተል/ዓለም ባንክ/
፲፱ ✣ ኤ(የ)ረር በር መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤልና ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ጎሮ፤
ታክሲ፤ ከመገናኛ (ቦሌ) → ኤረር በር (ጎሮ)፡፡
፳. ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሩፋኤልና ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ሩፋኤል፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (ጴጥሮስ ዐደባባይ) → ሩፋኤል፡፡
ወይም ከአዲሱ ገበያ/ቶታል/ → በእግር
፳፩ ✣ ገዳመ ኢየሱስ፤
አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ሆላንድ ኤምባሲ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ኮልፌ አጠና ተራ፡፡
ወይም ከጦር ኀይሎች → ኮልፌ (ቀለበት መንገዱ ላይ)
፳፪ ✣መሪ አያት ምሥራቀ ፀሐይ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክ/ከ፥ መሪ አያት
ትራንስፖርት፤ ከመገናኛ → መሪ አያት
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
http://www.finotehiwotsundayschool.com
#ታኅሣሥ 22 (በዓለ ደቅስዮስ ) ብሥራተ ገብርኤል
በዚህችም ዕለት እመቤታችንን ድንግል ማርያምን የከበረ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በአበሠራት መሠረት ደቅስዮስ በዓልን አደረገ፡፡
ደቅስዮስ የተባለው ኤጲስ ቆጶስ ከፍቅሩ ጽናት የተነሳ የተአምራቷን መጽሐፍ ሰብስቦ ያዘጋጀ ነው፡፡ መጽሐፉን ስለጻፍክ ብላ እመቤታቸን ደስ መሰኝቷን ነግራው ተሰውራለች ፡፡ ይህንን በራዕይ ባየ ጊዜ የእርሷን ክብረ አብዝቶ ይጨምር ዘንድ አሰበ ፡፡ ሰዎችም አስበውት የማያውቁትን የቅዱሰ ገብርኤል ብሥራት በዓሏን አከበረ ሰዎችም እጅግ ተደሰው በዓሉን በታላቅ ድምቀት አከበሩት ፡፡ይህችም በዓል በጵጵስናው ዘመን ተሰራታ እስከ አሁን ትኖራለች፡፡
እመቤታችን ለቅዱስ ደቅስዮስ ዳግመኛ በተገለጸችበት ጊዜ የከበረ ልብስ ይዛ ፤ ደቅስዮስ ሆይ ስለ አከበርከኝ ደስ አለኝ እኔም ዋጋህን ልከፍኽ መጣሁ ይህችን ልብስ ልበስ በላዩም ትቀመጥ ዘንድ ወንበር አመጣሁልህ ከሰው ወገን ይህን ልብስ ሊለብስ እና እዚህ ወንበር ላይ ሊቀመጥ ከቶ የሚችል የለም ፡፡ ደቅስዮስም ከአረፈ በኃላ ሊለብሱ እና ሊቀመጡ የነበሩ በመሞታችው ዛ ፤ በዙሃን የእመቤታችንን ተአምር አይተው አደነቁ ፡፡
#የብሥራቱም ነገር እንዲህ ነው ፡፡
እመቤታችንን ያን የተጠማ ውሻ ውኃ ባጠጣችው ጊዜ ፤ በዚህ ዘመን አምላክ ከድንግል ይወለዳል ያላት ካንቺ ይሆን እያሉ ይዘባበቱባት ነበር ፡፡ ወዲውኑ ከኃላዋ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ትጸንሲ አላት ፡፡ ዞር ብትል አጣቸው አባቴ አዳምን እና እናቴ ሔዋንን ያሳተ ጠላት ይሆናል ብላ ዝም ብላ ሄደች ፡፡
ዳግመኛም ቤት ከደረሰች በኃላ ትጸንሲ አላት ፡፤ ይህ ነገር ተደጋገመ ብላ ወደ ቤተ መቅደስ ነገሩን ልትረዳ ሄደች ፡፡ በወርቅ ወንበራ ተቀምጣ ከደናግለ እሥራኤል ጋር የተካፈለችውን ሐር እና ወርቅ እያስማማች ስትፈትል ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾ
‹‹ተፈሥሒ ፍሥሕት ኦ ምልዕተ ጸጋ ›› ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበለሽ አላት ፡፡ ይህን ሰምታ በደነገጠችም ጊዜ
‹‹ኢትፍርሂ ማርያም እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር ›› በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ባለሟልነትን አግኝተሻል አትፍሪ እነሆ ትጸንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ እግዚአብሔርም የአባቱን የዳዊት ዙፋን ይሰጠዋል አለቸው ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም አላት ፡፡ ……ይህ ነገር እንደምን ይሆንልኛል አለችው ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ይመጽእ ላዕሌኪ ወኃይለ ልዑል ይጼልለኪ›› መንፈስ ቅዱስ ባንቺ ላይ ይመጣል የልዑል ኃይልም ይጋርድሻል ብሎ የተቀመጠችበትን የወንበሩን እጀታ አለምልሞ ይህን ማን አደረገው ቢላት እግዚአብሔር አለችው፡፡ ይህንንም የሚያደርግ እግዚአብሔር ነው ‹‹አስመ አልቦ ዘይሰአኖ የሚሳነው የለምና ኤልሳቤጥ እንኳን ጸነሰች ይህ ስድስተኛው ወር ነው አላት ፡፡
ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ ‹‹ እንደቃልህ ይሁንልኝ ይደረግልኝ ›› አለችው፡፡ ይህን ቃሏን ምክንያት አድርጎ ወልድ ዋህድ እግዚአብሔር በማኀፀኗ አደረ ፡፡ ይህ የሆነው መጋቢት 29 ቀን ነው ታኅሣሥ 22 እንዲከበር ያደረገው ግን ከላይ እንደገለጽነው ኤጲስ ቆጶሱ ቅዱስ ደቅስዮስ ነው ፡፡ መጋቢት 29 በጾም ምክንያት በሚገባ አይገበርም ነበርና ከበዓለ ልደቱ ሰባት ቀን አስቀድሞ ታኅሣሥ 22
በታላቅ ድምቀት ተከብሯል፡፡
የእመቤታችን ምልጃዋ አይለየን
አሜን!
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/
#share
.Facebook...
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
.YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
.Telegram...
https://t.me/medihanaelem
http://tiktok.com/@finotehiwot
www.finotehiwotsundayschool.com
#Angeles #ቅዱሳን_መላእክት
#ክብረ_በዓላት #Feasts #Our_mother_Virgin_mary #እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
