ch
Feedback
✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት📚

✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት📚

前往频道在 Telegram

ይህ ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ታላላቅ የድሮና አዳዲስ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን የጠበቁ መጽሐፍት በPDF ያቀርባል

显示更多

📈 Telegram 频道 ✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት📚 的分析概览

频道 ✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት📚 (@eotc_books_by_pdf) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 128 164 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 246,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 207

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 128 164 名订阅者。

根据 22 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -2 686,过去 24 小时变化为 -62,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 9.57%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 0 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ይህ ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ታላላቅ የድሮና አዳዲስ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን የጠበቁ መጽሐፍት በPDF ያቀርባል

凭借高频更新(最新数据采集于 23 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

128 164
订阅者
-6224 小时
-4737
-2 68630
帖子存档
“ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም፤ በማርያም ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታ ሆነ!” (ቅዱስ ያሬድ) ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በአድባረ ሊባኖስ ግንቦት አንድ ቀን ወለዷት፡፡ በዚያን ጊዜ ጠላታቸውን ለመሸሽ በስደት ላይ ስለነበሩ ምግብ አልያዙም፤ ስንቃቸውም ‹‹ንፍሮና ጥራጥሬ›› ነበር፡፡ በዚህም የእመቤታችን ማርያምን የልደት በዓል በሕዝበ ክርስቲያን ዘንድ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ የነቢያቱ ትንቢት የተፈፀመበት፣ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰው ልጆች ሁሉ (ለሕያዋን ሁሉ) ታላቅ የደስታ ቀን ነው፡፡ በንጽህናዋ እና በቅድስናዋ ተደንቀው ሰማያውያን ቅዱሳን መላእክትም ያመሰግኗታል፡፡ ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ከዚህ ታላቅ በዓል በረከት ረድኤትን እንድናገኝበት ነው፡፡ የክርስቶስ እናት ዛሬ ተወልዳለችና፤ በሥርዓት ቤተ ክርስቲያን መሰረት በቀናች በተዋሕዶ እምነት ሆነን፤ የድኅነታችን ምክንያት የሆነችውን ድንግል ማርያምንም እያመሰገንን ልናከብረው ይገባል፡፡ በመጻሕፍት አምላካውያት (አሥራው መጻሕፍት) እና በሊቃውንት አበው አስተምህሮ የተነገሩ የእመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያም ንጽሕናዋን ቅድስናዋን የሚመሰክሩ መውድሳት ቅኔያትና ዝማሬያት እንዲሁም በሰፊው የተገለጡትን ምስክርነቶች ስንመለከት እንዲሁ እንደ እንግዳ ደራሽ የተገኙ እንዳልሆነ አስተዋይ ሰው በቅጥነተ ሕሊና ቢረዳው የሚያውቀው እውነት ነው፡፡ ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ሲነሳ፣ በተለይም እመቤታችንን ማመስገን ማለት እርሷን እንደ ፈጣሪ መመልከት፤ ከዚያም ባለፈ እንደ አምልኮ  ባዕድ አድርገው የሚመለከቱት እና ያልታደሉ የዘመኑ እንክርዳዶች እና አረሞች፣ ጸላዔ ሠናያት በከንቱ ትጋት የሚያገለግሉ መናፍቃን  ቁጥራቸው ከጊዜ ወደጊዜ መብዛት በተጣመመ የሐሰት ትምህርታቸው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የምትመሰገንበትን ምስጋና መቃወም ዛሬ የተጀመረ ሳይሆን ቀድሞም የነበረ ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለእመቤታችን ድንግል ማርያም የምታቀርበው ምስጋና የመቃወም ነገር መሠረቱ ምንድን ነው? ስንል የመጀመሪያው በክህደት እና በኑፋቄ ትምህርት መወሰድ ሁለተኛ ደግሞ የተስተካከሉ እና እንከን የሌለውን የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ባለመረዳት እና በስሜት መነዳት (መመራት) መሆኑን የምንመለከተው ነው፡፡ በኦርቶዶክሳዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ለተሰበሰቡ ክቡራን ምእመናን የቤተ ክርስቲያናቸውን አስተምህሮ በአግባቡ ከርቱዓን መምህራን እና በቅዱሳት መጻሕፍት አማካኝነት ማወቁ፤ በተለይ በዘመናችን ለሚዘራው የክህደት አስተምህሮ እንደ ጽድቅ ጋሻ ሆኖ የሚያገለግል ነው፡፡ በተለይ ስለ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ስለሚሰጣት ክብር እና ሞገስ ማወቅ ማለፊያ ነው፡፡ በዚህም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ለማመስገን የሚያስፈልግ መሠረታዊ ነገር ምንድን ነው? ለመሆኑ ሰው እንዲሁ ከመሬት ተነስቶ ለእመቤታችን ምስጋና እና ክብር መስጠት ይችላልን? እመቤታችንን አለማመስገን እና አለማክበርስ ውጤቱ ምንድን ነው የሚለውን በአጭሩ እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡ @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

.Trustwallet.com/cardTrust Wallet introduces its newly launched card system. Get your virtual card for only $1 and enjoy excl
.Trustwallet.com/card
Trust Wallet introduces its newly launched card system. Get your virtual card for only $1 and enjoy exclusive benefits. Receive a 25 USDT bonus when you load 100 USDT to your card. Additionally, earn up to 15% cashback on all your e-commerce and POS purchases. Spend your USDT and USDC balances freely, including ERC20 and TRC20 networks. If you get a card using my link, I’ll earn $25 https://taap.it/OrQKP5G

#ግንቦት_ልደታ_ለማርያም ግንቦት ልደታ ለምን ይከበራል? ግንቦት ልደታ (ግንቦት 1) የሚከበረው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት ለማሰብ ነ
#ግንቦት_ልደታ_ለማርያም ግንቦት ልደታ ለምን ይከበራል? ግንቦት ልደታ (ግንቦት 1) የሚከበረው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት ለማሰብ ነው። በዓሉ የሰው ልጅ የመዳን ተስፋ መጀመሪያ የሆነችው ማርያም ከአባቷ ከኢያቄም እና ከእናቷ ከሐና በአድባረ ሊባኖስ የተወለደችበትን ዕለት የሚያከብር ታላቅ በዓል ነው።  የበዓሉ ዋና ዋና ምክንያቶች፦ የድንግል ማርያም ልደት፦ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በግንቦት 1 ቀን መወለዷን ለማሰብ። የትንቢት መፈጸምያ፦  በብሉይ ኪዳን የነበሩ ነቢያት ስለ መሲሁ መምጣት የተነበዩት ትንቢት መፈጸሚያ የሆነችው የጌታ እናት የተወለደችበት ቀን በመሆኑ። የመዳን ምስራች፦  የሰው ልጅ ሁሉ መዳን ምክንያት የሆነችውና የሰማይ እና ምድር ፈጣሪን የማኅፀኗ ፍሬ ያደረገችው ድንግል ማርያም መወለዷን ለማብሰር። ደስታና ምስጋና፦  ቅዱስ ያሬድ “ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም” (በማርያም ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታ ሆነ) ብሎ እንደዘመረው፣ ይህ ዕለት የዓለም ሁሉ የደስታ ቀን ተደርጎ ይወሰዳል።  በአጠቃላይ፣ ግንቦት ልደታ የድንግል ማርያምን በጎ ስብዕና እና ለሰው ልጅ ያላትን ትልቅ ቦታ የምናስብበትና የምናመሰግንበት በዓል ነው። @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

† እንኳን ለጌታችን እና መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሳኤ በሰላም አደረሰን † ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤ አሰሮ ለሰይጣን፤ አግዐዞ ለአዳም፤ ሠላም እምይዕዜሰ፤ ኮ
† እንኳን ለጌታችን እና መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሳኤ በሰላም አደረሰን † ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤ አሰሮ ለሰይጣን፤ አግዐዞ ለአዳም፤ ሠላም እምይዕዜሰ፤ ኮነ፤ ፍስሐ ወሠላም፡፡” መልካም በዓል ! @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

#ህማማት በህማማት ሳምንት (Holy Week) የየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታላቅ እና ቅዱስ ሳምንት ነው ፤ የኢየሱስ ክርስቶስ መከራ፣ ሞት እና ትንሣኤ ይዘከራል። በዚህ ሳምንት የሚ
#ህማማት በህማማት ሳምንት (Holy Week) የየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታላቅ እና ቅዱስ ሳምንት ነው ፤ የኢየሱስ ክርስቶስ መከራ፣ ሞት እና ትንሣኤ ይዘከራል። በዚህ ሳምንት የሚደረጉ ነገሮች እነዚህ ናቸው፦ 1. ጾም (ጾመ ህማማት) ከሌሎች ጾሞች የበለጠ ጠንካራ ነው ምግብ እስከ ማታ ይቆያል (አንዳንድ ሰዎች ሙሉ ቀን ይጾማሉ) ስጋ እና የእንስሳ ምርቶች ፈጽሞ ይከለከላሉ ። 2. ጸሎት እና ስግደት ቤተክርስቲያን ብዙ ጊዜ መገኘት ረጅም ጸሎቶች እና ስግደት (መስገድ) መጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ። 3. የቀናት ልዩ ትርጓሜ ሰኞ  ፣ ማክሰኞ ፣ ረቡዕ :  የተለመዱ ጸሎቶች እና ጾም ይከናወናል። ሐሙስ (ጸሎተ ሐሙስ): የመጨረሻ እራት ዝክር ዓርብ (ስቅለት): የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ላይ መሞት የሚዘከር ቀን (እጅግ ጥልቅ ጾም) ቅዳሜ (ቀዳም ስድስት): የ ዝምታ እና አርምሞ ቀን 4. መንፈሳዊ ሥነ ምግባር ርህራሄ ማድረግ (ለድሆች መርዳት) ጥላቻ መተው እና ይቅር መባባል ፤ ንጹሕ የንሰሀ ሕይወት መኖር ። 5. ዝምታ እና ሀዘን የጌታን ህመሙን እና ስቃዩን እያሰቡ የደስታ ነገሮችን (ከመዝናኛ፣ ድምፅ ያለውን ዜማ ሳቅ ከመሳሰሉት መቆጠብ! ) ራስን መመርመር እና መንፈሳዊ ህይወትን ማደስ። በ አጠቃላይ ይህ ሳምንት የንስሐ፣ የጸሎት እና የመንፈሳዊ ትኩረት ጊዜ ነው! @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

No Kings. No Senseless Wars. Standing with the millions who marched on March 28th. Power belongs to the People, not the warmo
No Kings. No Senseless Wars. Standing with the millions who marched on March 28th. Power belongs to the People, not the warmongers. https://t.me/No_king_No_King

የዐቢይ ጾም ሳምንታት ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ስሙ ጐልቶ ከሚነሳባቸው ጉዳዮች አንዱ በዐቢይ ጾም ውስጥ ለሚገኙ ሳምንታት የየራሳቸው መጠሪያ በመስጠቱ ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ለሳምንታቱ ስያሜዎችን ሲሰጥ ጌታችን የሠራቸውን የቸርነት ሥራዎችን፣ ያስተማራቸው ትምህርቶችን፣ ተጠቅሟል፡፡ በአጠቃላይ በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚገኙ ሳምንታት ስያሜያቸው . . . 1/ ዘወረደ 2/ ቅድስት 3/ ምኩራብ 4/ መፃጉ 5/ ደብረ ዘይት 6/ ገብር ኄር 7/ ኒቆዲሞስ 8/  ሆሣዕና @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

Special news page on X. Follow uncensored Middle East news right here. https://tglink.io/0b3a5dd2be4480
Special news page on X. Follow uncensored Middle East news right here. https://tglink.io/0b3a5dd2be4480

Special news page on X. Follow uncensored Middle East news right here. https://tglink.io/0b3a5dd2be4480
Special news page on X. Follow uncensored Middle East news right here. https://tglink.io/0b3a5dd2be4480

# ቅድስት_ሥላሴ "ሥላሴን " " ቅድስት ሥላሴ እያልን የመጥራታችን ምስጢር ምንድን ነው ? አንዲት ሴት ወይም እናት ልጆቿን አልወለደችም ተብላ አትጠረጠርም ፤ ሥላሴም ይህንን ዓለም ፈጥረዋል እናም
# ቅድስት_ሥላሴ "ሥላሴን " " ቅድስት ሥላሴ እያልን የመጥራታችን ምስጢር ምንድን ነው ? አንዲት ሴት ወይም እናት ልጆቿን አልወለደችም ተብላ አትጠረጠርም ፤ ሥላሴም ይህንን ዓለም ፈጥረዋል እናም አልፈጠሩም ተብለው አይጠራጠሩም ። አንዲት ሴት በባሕሪይዋ ልጅን ታስገኛለች ፤ ሥላሴም ይህንን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥተው ስለፈጠሩት በሴት አንጻር # ቅድስት ተብለው ይጠራሉ ። አንድም ሴት አዛኝ ናት ፤ ለታናሹም ይሁን ለታላቁ ትራራለች ሥላሴም እንደዚሁ ለፍጥረት ሁሉ ያዝናሉ ፥ ይራራሉ ፥ ምህረት ይሰጣሉ ። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንዲህ ይላል ። ምህረታችሁ ከልክም በላይ የበዛ በሴት አንቀጽ ቅድስት ተብላችሁ የተጠራችሁ ሥላሴ " በማለት ያመሰጥራል ። ስለዚህ ቅድስት ለምን ተባሉ ቢባል በረከታቸው ፥ ርህራሄያቸውና ፥ ይቅር ባይነታቸው መሆኑን ማወቅ አለብን ። አንድም ሴት ልጇ ቢታመምባት አትወድም ፤ ሥላሴም አንድም ልጅ በዲያብሎስ እጅ ተይዞ በኃጢአት እንዲታመሙ አይወዱም ፥ አይፈቅዱም በመሆኑም #ቅድስት ይባላሉ ። አንድም ሴት ልጅ የልጇን ነውር አትጠየፍም ልጄ ቆሽሿል ፥ ተበላሽቷል ብላ ፊቷን አታዞርም ። ሥላሴም የሰውን በኃጢአት መቆሸሽ ሳይፀየፉ በቸርነታቸው ጎቦኝተው ለንስሐ ያደርሱታል ። ይህንን የፅድቅ አየር የምንምገው ያማረውንም ብርሃን የለበስነው ስለ ፅድቃችን ሳይሆን በሥላሴ ቸርነት ነውና ስለዚህም ሥላሴን በሴት አንቀፅ #ቅድስት እንላቸዋለን ። አኔድም ሴት ልጆቿን ፈጭታና ጋግራ ትመግባቸዋለች ሥላሴም እንደዛው ናቸው ። በዝናብ አብቅለው በፀሐይ አብሥልው ፍጥረታትን ሁሉ ይመግባሉ ። ስለዚህ ሥላሴ እንደ እናት ሁሉንም ይመግባሉና በሴት አንቀጽ #ቅድስት ይባላሉ ። @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

📢 Advertising in this channel You can place an ad via Telega․io. It takes just a few minutes. Formats and current rates: Vie
📢 Advertising in this channel You can place an ad via Telega․io. It takes just a few minutes. Formats and current rates: View details

#ጸሎተ_ሃይማኖት (የሃይማኖት ጸሎት) ነአምን በ፩ዱ፡ አምላክ እግዚአብሔር አብ አኃዜ ኲሉ ገባሬ ሰማያት ወምድር ዘያስተርኢ ወዘኢያስተርኢ።  ሁሉን በያዘ ሰማይንና ምድርን የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ በአንድ አምላክ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን።  መቅድም  ሀ. ስሙ  1. ጸሎተ ሃይማኖት  2. የኒቅያ የሃይማኖት መግለጫ (ውሳኔ ሃይማኖት፤ አንቀጸ ሃይማኖት) Nicene Creed  3. የኒቅያ ቁስጥንጥንያ ውሳኔ ሃይማኖት Nicene-Constantinopolitan Creed ለ.  ለምን አስፈለገ? 1. « መለኮታዊውንና ሐዋርያዊውን እምነት ጠቅልሎ ያስቀመጠ ስለሆነ።» ቅዱስ አትናቴዎስ   2. ስለ እግዚአብሔር ባሕርይ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረውን ግልጥ በማድረግ ከክህደት ምእመናን ለመጠበቅ ነው።  3. እያንዳንዱ ቃልና ሐረግ የክርስቲያንን እምነት የሚያጠነክር ስለሆነ ነው።  4. ቤተ ክርስቲያን ልትሆነውና ልታደርገው የሚገባትን ነገር የሚያመለክት ነው።  ሐ. በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ያለው ልዩ ቦታ  1. በመላው የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ተቀባይነት ያለው አንቀጸ ሃይማኖት ነው።  2 የክርስቶስን አምላክነት የመንፈስ ቅዱስ አምላክነት  በማብራራት ቤተ ክርስቲያንን ከታላቅ አደጋ የታደገ ነው።    3. በኒቅያ በ325 ዓ.ም ላይ   እንደገና በ381 ዓ.ም ላይ በቁስጥንጥንያ በተከናወነው ኢኩሜኒካል ጉባኤ ላይ ተጨማሪ አንቀጾች ( መንፈስ ቅዱስን የሚመለከቱ) ገብቶለት ቤተ ክርስቲያንን በቀጥተኛ ሃይማኖት (ኦርቶዶክስ) የመራ ነው።  መ. በቤተ ክርስቲያን የአምልኮ ሕይወት ያለው ቦታ 1. በጸሎት ማለትም በቅዳሴ ጊዜ በካህናትና በምእመናን ይደገማል።  2. የሚጠመቁ ሰዎች እምነታቸውን የሚገልጡት ጸሎተ ሃይማኖትን አሰምተው በመድገም ነው። (የክርስትና አባትና እናት ስለሕፃኑ ፈንታ ሁነው በጸሎተ ሃይማኖት እምነታቸውን መመስከር አለባቸው።   3. የክርስትና መለያ ምልክት ስለሆነ በምኩራብ የእምነት መግለጫ የሆነው « እስራኤል ሆይ ስማ (ሼማ)በሚለው የአይሁድ አንቀጸ ሃይማኖት ትይዩ ሊታይ የሚችል ነው።  መ. ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ያለው ግንኙነት  1. ጸሎተ ሃይማኖት በተደነገገ ወቅት ገና የመጽሐፍ ቅዱስ ቀኖና ገና አልተቋጨም ነበር።  2. ጸሎተ ሃይማኖት ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን የያዘ ስለሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ ቀኖና ለመወሰን ማለትም የትኞቹ መጻሕፍት በቅዱሳት መጻሕፍት ቁጥር መግባት እንዳለባቸው ለመወሰን አገልግሎአል።  @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

#ፀሎት ፀሎት ማለት ምን ማለት ነው? #ጸሎት ማለት ፦ጸለየ፣ለመነ፣ ጠየቀ አማለደ፣ ማለደ ካለው የግዕዝ ቃል የወጣ ቃል ነው፡፡ ጸሎት ማለት ጠቅለል አድርገን ስንመለከተው ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር
#ፀሎት ፀሎት ማለት ምን ማለት ነው? #ጸሎት ማለት ፦ጸለየ፣ለመነ፣ ጠየቀ አማለደ፣ ማለደ ካለው የግዕዝ ቃል የወጣ ቃል ነው፡፡ ጸሎት ማለት ጠቅለል አድርገን ስንመለከተው ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር እግዚአብሔርን ማመስገን መለመን፣ መጠየቅ፣ መማለድ፣ መማፀን ነው፡፡ “ጸሎት ብሂል ተናግሮ ምስለ እግዚአብሔር፡፡” አባታችን አዳምም ከመላእክት ተምሮ በየሰዓቱ ይጸልይ ያመሰግን ነበር፡፡ ዲያብሎስ በእባብ አድሮ ወደ አዳም በመጣ ጊዜ ጸሎት እያደረገ ስለነበር ዲያብሎስን ድል ነሥቶታል ሔዋንን ግን ሥራ ፈትታ እግሯን ዘርግታ ስለአገኛት ድል ነስቷታል፡፡ ጸሎት ሰማእታት ከነደደ እሳት፣ ከተሳለ ስለት፣ ከአላውያን መኳንንት፣ ከአሕዛብ ነገሥታት ከዲያብሎስ ተንኮል እና ሽንገላ ዲያብሎስ በእነርሱ ላይ ከአጠመደው አሽከላ የዳኑበት ጋሻ ነው፡፡ ኤፌ.6፥10 21 ጸሎት፣ ሰው አሳቡን ለእግዚአብሔር የሚገልጥበት እግዚአብሔርም የሰውን ልመና ተቀብሎ ፈቃዱን የሚፈጽምበት ረቂቅ ምስጢር ነው፡፡ የጸሎት መሠረቱ “ዕሹ ታገኛላችሁ ለምኑ ይሰጣችኋል ደጁ ምቱ ይከፈትላችኋል” የሚለው የጌታችን ትምህርት ነው።/ማቴ: 7፥7/ @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

#በእንተ_ፆም ጾም ‹‹ጾመ›› ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲኾን ትርጕሙም መተው፣ መጠበቅ፣ መከልከል ማለት ነው፡፡ ጾም ከምግብ መከልከል ብቻ ሳይኾን ከክፉ ተግባር ዅሉ መቆጠብ ጭምር ነው፡፡ ሠለስቱ ምዕትም፡- ‹‹ጾምሰ ተከልኦተ ብእሲ እመብልዕ በጊዜ ዕውቅ በውስተ ሕግ፤ ጾምስ በታወቀው ሰዓት፣ በታወቀው ዕለት ሰው ከምግብ የሚከለከለው መከልከል ነው›› በማለት የጾምን ትርጕም ያስረዳሉ /ፍትሐ ነገሥት፣ አንቀጽ ፲፭/፡፡ ጾም በብሉይ ኪዳንም ኾነ በሐዲስ ኪዳን የታወቀ፣ በነቢያት የነበረ፣ በክርስቶስ የጸና፣ በሐዋርያት የተሰበከ እና የተረጋገጠ መንፈሳዊ ሕግ፤ ፈጣሪን መለመኛ መንፈሳዊ መሣሪያ ነው፡፡ ጾም ሰው ሠራሽ ሕግ ሳይኾን ልዑል እግዚአብሔር የመሠረተው፣ ከእግዚአብሔር ለሰው ልጅ የተሰጠ የመጀመሪያው ትእዛዝ ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒችን ኢየሱስ ክርስቶስም እከብር አይል ክቡር፣ እነግሥ አይል ንጉሥ፣ እጸድቅ አይል ጽድቅ የባሕርዩ የኾነ አምላክ ነው፡፡ ለእኛ አርአያ ቤዛ ሊኾነን፣ እናንተም ብትጾሙ ብትጸልዩ አጋንንትን ድል ትነሳላችሁ ሲለን፣ ጾምን ለመባረክ ለመቀደስ፤ በመብል ምክንያት ስተን ስለ ነበር ስለ እኛ ኀጢአት እና በደል ሲል ዐርባ ቀንና ሌሊት ጾሟል፡፡ ጌታችን ሲጾም ዐርባውን መዓልት እና ሌሊት ሙሉ ምንም እኽል ውኃ አልቀመሰም፡፡ ሊቀ ነቢያት ሙሴም እንደዚሁ ጽላተ ሕጉን ከእግዚአብሔር ሲቀበል እኽል ውኃ አልቀመሰም ነበር፡፡ ምክንያቱም አምላካችን ‹‹በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ያደርጋል፤ ከእኔ የበለጠም ያደርጋል›› ብሏልና፡፡ አባቶቻችን ጻድቃንም ከዐሥረኛው ማዕረግ (ከዊነ እሳት) ላይ ሲደርሱ በእርሱ መንፈስ (በመንፈስ ቅዱስ) ኃይል ታግዘው ከእኽል ውኃ ተከልክለው ይጾማሉ፡፡ ይህም በሥጋዊ ዓይን ሲመዘን ፈጽሞ የሚከብድ ነው፡፡ ሃይማኖት ከሳይንስና ከአእምሮ በላይ ነውና፡፡ በዚህም  ሃይማኖት የሚቀበሉት እንጅ የሚጠራጠሩት የሚፈላሰፉት እንዳልኾነ እንረዳለን፡፡ @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

#ጾመ_ሰብአ_ነነዌ ‹‹ጾመ ሰብአ ነነዌ፤ የነነዌ ሰዎች ጾም›› የሦስት ቀን ጾም የጾሙት በነነዌ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ከተማዋም (ነነዌ) በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ የምትገኝ ስትኾን መሥራቿም ናምሩድ ነው (ዘፍ.፲፥፲፩-፲፪)፡፡ ጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ለአሦር መነሻ የሆነች፤ እጅግ ሰፊና ያማረች፤ የቅጥሯ ርዝመትም ፲፪ ኪሎ ሜትር የሚሸፈን ነበር፡፡ በከተማዋ ንጉሡ ሰናክሬም ብዙ ሕንጻዎችን ገንብቶ ነበር (ዮናስ ፬፥፲፩)፡፡ በዚያ ዘመን የነበሩ የነነዌ ሰዎች ኃጢአታቸው በዝቶ እግዚአብሔር ሊያጠፋቸው ሲል ዮናስ የስሙ ትርጓሜ ‹ርግብ› የሆነ በዳግማዊ ኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት የነበረ ነቢይን ቸርነትና ምሕረቱ የማያልቅበት እግዚአብሔር መክሮ፣ ዘክሮ እንዲመልሳቸውና ንስሐ እንዲገቡ ነቢዩ ዮናስን ወደ ነነዌ ሕዝብ ላከው (ሉቃ.፲፩፥፴)፡፡ ይህ ነቢይ መኖሪያው በገሊላ በጋትሔፌር ድንበር ከተማ ነበረ፤ አባቱም አማቴ ይባላል፡፡ በዚያን ጊዜ ኢዮርብዓም ሶርያውያንን አባሮ የእስራኤልን ድንበር እንዲመልስ ነቢዩ ዮናስ ትንቢትን ተናገረ (፪ኛነገ.፲፬፥፳፭፤ ዮናስ ፩፥፩)፡፡ ነቢዩ ኤልያስ ያስነሣው የሰራጵታዋ መበለት ሕፃን ነቢዩ ዮናስ እንደ ሆነ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል (፩ኛነገ.፲፯፥፲፱)፡፡ መድኃኒታችን ክርስቶስም የዮናስን ከዓሣ ሆድ መውጣት የራሱ ትንሣኤ ምሳሌ አድርጎ ነግሮናል (ማቴ.፲፪፥፲፱-፵፪፤ ሉቃ.፲፩፥፴-፴፪)፡፡ እግዚአብሔር አምላክም ‹‹ሔደህ በነነዌ ላይ ስበክ›› ባለው ጊዜ ነቢዩ ዮናስ ‹‹አንተ መሐሪ ነህ፤ ልትጠፉ ነው ብዬ ተናግሬ ብትምራቸው ሐሰተኛ ነቢይ እባላለሁ›› ብሎ ላለመታዘዝ እስራኤልን ለቆ በመርከብ ወደ ተርሴስ ሸሸ፡፡ እግዚአብሔርም ታላቅ ነፋስን አስነሥቶ መርከቧ በማዕበል እንድትመታ አደረገ፡፡ ከዮናስ ጋር በመርከቧ ተሳፍረው የነበሩ ነጋድያንም ያላቸውን ሀብት ወደ ባሕሩ መጣል ሲጀምሩ ነቢዩ ዮናስ ጥፋቱን ተገንዝቦ ‹‹ማዕበሉ በእኔ ምክንያት የመጣ ስለሆነ ንብረታችሁን ሳይሆን እኔን ወደ ባሕር ጣሉኝ›› ብሎ ተማጸናቸው፡፡ እነርሱም ‹‹ስለዚህ ሰው ነፍስ እንዳንጠፋ፣ ንጹሕም ደም በእኛ ላይ እንዳይደረግብን አይሆንም›› አሉ፡፡ ወደ ባሕሩ ለመጣል ዕጣ በተጣጣሉ ጊዜም ዕጣው በዮናስ ላይ ስለ ወጣ ነጋድያኑ ዮናስን ወደ ባሕሩ ጣሉት፡፡ ወዲያውኑ ከእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዘ ታላቅ ዓሣ አንበሪ ዮናስን በአፉ ተቀብሎ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት አሳድሮ ወደ ነነዌ አደረሰው፡፡ እግዚአብሔር የቅል ተክልን ምሳሌ በማድረግ ቅጠሉ በመድረቁ ዮናስ ባዘነ ጊዜ ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብናአ እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ሆኑ ያሳዝኑኛል›› በማለት ነቢዩ ዮናስም ውሸታም ላለመባል መኮብለሉ ስሕተት መሆኑን አስረድቶታል፡፡ ዮናስም ነነዌ መሬት ላይ መድረሱን ባወቀ ጊዜ ከእግዚአብሔር መሸሽ አለመቻሉን ተረዳ፤ የነነዌ ሰዎችንም ‹‹ንስሐ ግቡ›› እያለ መስበክ ጀመረ፡፡ የነነዌ ሰዎችም ንስሐ በገቡ ጊዜ እግዚአብሔር ይቅር ብሎ ከጥፋት አድኗቸዋል፡፡ ሐሰት እንዳይባልም እሳቱ እንደ ደመና ሆኖ ከላይ ታይቶአል፡፡ የታላላቁ ዛፍ ቅጠል እስኪጠወልግ ድረስ አድርቆ ለሕዝቡ አሳይቷቸዋል፡፡ ንስሐቸው በከንቱ እንዳልቀረ አስረድቷቸዋል (ትንቢተ ዮናስ)፡፡ ታኅሣሥ ፭ ቀን የሚነበበው የመጽሐፈ ስንክሳር ክፍል ‹‹ወበልዐ አሐደ ኀምለ›› በማለት ንስሐ ያልገቡ አንድ አገር ያህል ሰዎች በእሳቱ እንደ ጠፉ ይነግረናል፡፡ ጾመ ነነዌ የሦስት ቀን ሱባኤ ነው፤ በሦስት ቀናት ጾምና ጸሎት ንስሐ የገቡ የነነዌ ሰዎች ከጥፋት እንደ ዳኑ ሁሉ፣ በብሉይ ኪዳን አስቴር ሦስት ቀን ጾማ፣ ጸልያ በእስራኤል ላይ የመጣውን መቅሠፍት እንዲመለስ አድርጋለች (አስ.፬፥፲፭-፲፮)፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከበዓል ስትመለስ ሕፃኑ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ላይ ጠፍቶአት ከሦስት ቀን ፍለጋ በኋላ በቤተ መቅደስ አግኝታዋለች (ሉቃ.፪፥፵፮)፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለሄሮድስ በሰጠው ምላሽ መልስ ሦስት ቀን የሱባኤ ፍጻሜ መሆኑን ገልጿል (ሉቃ.፲፫፥፴፪)፡፡ ጾመ ነነዌ የእግዚአብሔርን ቸርነትና መሐሪነት የምናስታውስበት ጾም ነው፡፡ ይኸውም እኛ ፍጡራኑ በበደልን ጊዜ ፈጽሞ ከማጥፋት ይልቅ ምክንያት ፈልጎ እንድንድን ያደርገናል፡፡ ዮናስ ለስብከት ፈቃደኛ ባይሆን እንኳን እግዚአብሔር በተለየ ጥበቡ እንዲሔድ አድርጎታል፡፡ በእርግጥ እግዚአብሔር ሌላ የሚልከው ነቢይ አጥቶም አይደለም፤ እርሱንም ጭምር ሊያስተምረው ስለ ፈለገ እንጂ፡፡ የነነዌ ሰዎች የተነሳሕያን ምሳሌ ናቸው፡፡ ይህም ማለት ሰው ጥፋቱን አምኖ ንስሐ ከገባ እግዚአብሔር ይቅር ማለቱን አይተውም፡፡ ለዚህም ነው ዮናስን ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ  ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ሆኑ ያሳዝኑኛል›› ያለው፡፡ ቀደምት የቤተ ክርስቲያን አባቶቻችን ይህን እና ሌሎች አጽዋማትን እንድንጾም የወሰኑልን ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ሕጉ የተዘጋጀልን እንደ ነነዌ ሰዎች እኛም ጾመን፣ ጸልየን ከኃጢአታችን እንነጻ ዘንድ ነው፡፡ ዛሬ ዓለማችን በኃጢአት ማዕበል እየተናወጠች ባለችበት ወቅት እኛም እንደ ነነዌ ሰዎች ከበደላችን ብንመለስ እና ንስሐ ብንገባ ቸሩ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረት የባሕርይ ገንዘቡ ስለ ሆነ ‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ይቅር እላችኋለሁ፤›› ይለናል፡፡ ስለሆነም በነቢዩ ዮናስ ላይ የተደረጉ ተአምራትንና ካለመታዘዝ የሚመጣ ቅጣት ቀላል አለመሆኑን በማስተዋል፣ ለነነዌ ሰዎች የወረደውን ምሕረት በመገንዘብ ለእግዚአብሔርም ሆነ ለሃይማኖት አባቶች እና ለወላጆቻችን መታዘዝ ይገባናል፡፡ ስንጾምም እግዚአብሔር አምላካችን መዓቱን በምሕረት፣ ቍጣውን በትዕግሥት መልሶ በኃጢአት ለጠፋው ዓለም ይቅርታውን ይልካል፡፡ በመጾማችን ራሳችን ከመዓትና ከመቅሠፍት ከመዳናችን ባሻገር በእኛ በደል ምክንያት አገራችን፣ ዕፀዋቱና እንስሳቱም ሳይቀር ከድርቅና ከቸነፈር ይተርፋሉና፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

#ጥር_21_የእመቤታችን_በዓለ_ዕረፍት ! አስተርእዮ ማርያም አስተርእዮ ማለት መታየት፣ መገለጥ ማለት ነው። ቃሉ አስተርአየ ታየ፣ ተገለጠ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው። ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገባው ቃል ኪዳን መሠረት በሥጋ የተገለጠበት(የታየበት) ፣ አንድነት ሦስትነቱም የተገለጠበት ወቅት በመሆኑ ከልደት በዓል እስከ ጥር መጨረሻ በሙሉ ዘመነ አስተርእዮ በመባል ይታወቃል። የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር “አስተርእዮ ማርያም” ተብሏል። ልቡናዋ በይኩነኒ የጸና ንጽሐ ሥጋ ፣ ንጽሐ ነፍስ ፣ ንጽሐ ልቡና አስተባብራ የያዘች ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በቃል መነገሩ በልብ መታሰቡ ከፍ ከፍ ይበልና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ተንሥኢ ወንዒ”  የነፍሴ ደስታ የኾንሽ ውድ እናቴ ሆይ ተነሥተሽ ወደ እኔ ነዪ (መኃ ፪፥፲) ብሏታል። ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ ቅዱስ ዳዊት “ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር” መዝ.፹፮፥፫ እግዚአብሔር ማህጸንሽን ከተማ አድርጎ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የኖረብሽ ሆይ ስለ አንቺ የተነገረው የተደረገው ነገር ዕጹብ ድንቅ ነው እንዳለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት ሆና ማረፏ ይደንቃል። ታላቁ የቤተክርስቲያናችን አባት ቅዱስ ያሬድ ሞቷ የሚያስደንቅ መሆኑን «ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል» በማለት ገልጾታል። ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሞትና ትንሣኤ በነገረ ማርያም አበው እንደሚያስረዱት ዕረፍቷ በጥር ፳፩ እሑድ ነው ። አባቶቻችን በጾመ ፍልሰታ ውዳሴ ማርያም ቅዳሴ ማርያም ሲተረጉሙ የእረፍቷን ነገር እንዲህ ብለው ይተርካሉ። የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉ ስድሳ አራት ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ በእሑድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላእክቱን አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት። ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁን? አለችው። በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት። እሊህን ከማርክልኝስ ይሁን አለችው። ቅድስት ሥጋዋን ከቅዱስ ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በዝማሬ መላእክት አሳረጋት። ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት በደመና ጠቅሶ ካለችበት አድርሶ እመቤታችሁን ስጋዋን በክብር አሳርፉ አላቸው። ሐዋርያት በአጎበር አድርገው ወደ ጌቴሰማኒ ይዘው ሲሄዱ አይሁድ ቀድሞ ልጇን ተነሳ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ይኖራሉ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን በእሳት እናቃጥላታለን ብለው ተነሱ። ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ተራምዶ አጎበሩን ጨበጠው። መልአክ መጥቶ በሰይፍ ሁለት እጁን ቀጣው ከአጎበሩ ተንጠልጥሎ ቀረ። በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት እጁ ተመልሶለታል። ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ጨምሮ በደመና ነጥቆ ከገነት አግብቶ ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖራት። ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው በነሐሴ መባቻ ጾም ጀመሩ ሁለት ሱባዔ ሲፈጸምም እሑድ አምጥቶ ሰጥቷቸው ቀብረዋታል በሶስተኛው ቀን ማክሰኞ “ከመ ትንሳኤ ወልዳ” እንደ ልጇ ተነሥታለች። ቅዱስ ቶማስ አልነበረም ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ሲመጣ ስታርግ አገኛት ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ ዛሬም ደግሞ ያንችን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁን ብሎ “ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ” ከሀዘኑ የተነሳ ሊወድቅ ወደደ እመቤታችንም አይዞህ አትዘን እሊያ ትንሳኤየን ዕርገቴን አላዩም አንተ አይተሃል ተነሣች ዐረገች ብለህ ንገራቸው ብላ የያዘችውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው። ከዚህ በኋላ ሂዶ የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ አላቸው አግችተን ቀበርናት አሉት ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር ተው ይህ ነገር አይመስለኝም አላቸው። ቅዱስ ጴጥሮስ አንተ እንጅ ልማድህ ነው አንተ ብቻ ተጠራጥረህ አትቀርም ሰውን ሁሉ ስታጠራጥር ትኖራልህ ብሎ ተቆጥቶ ወደ መቃብሩ ሂዶ ቢከፍተው አጣት ደንግጦ ቆመ ሐዋርያው ቶማስም አታምኑኝም ብየ እንጅ እመቤታችንስ ተነሣች ዐረገች አላቸው የያዘውንም ሰበን ሰጣቸው ለበረከትም ተካፍለውታል። በዓመቱ ሐዋርያት ቅዱስ ቶማስ ትንሣኤሽን ዕርገትሽን አይቶ እኛ ሳናይ ብለው ጾም ጀመሩ በ፲፮ኛው ቀን እመቤታችንን መንበር አድርጎ ቅዱስ ጴጥሮስን ካህን ዘይትራድኦ ቅዱስ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ በዚያው ላይ ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ቤተክርስቲያንም ይህንን መታሰቢያ አድርጋ በየዓመቱ ታከብረዋለች። ሰአሊ ለነ ቅድስት የኃጥአንን ለቅሶና ሐዘን አይተሽ ስለእነርሱ ድኅነት(መዳን) ዕረፍትሽን በሀሴት የተቀበልሽ እመቤታችን ሆይ ሐዋርያት በሱባዔ ትንሣዔሽን ለማየት በቅተዋልና እኛም በዓለ ዕረፍትሽን አክብረን ልጅሽ በሰጠሽ ቃል ኪዳን በቀኙ እንቆም ዘንድ ለምኝልን። አሜን! @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

#በስመአም_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን !                                                                   የጊዜያት ባለቤት እግዚአብሔር አምላክ ሆይ የጨለማውን ግርማ ገፈህ ብርሃንህን እንድንመለከት ስላደረከኝ አመሰግንሃለሁ። በመኝታዬም ስለጠበከኝ ከሞት ስለሰወርከኝ እጅ መንሳቴን አቀርባለሁ ። ቸር አረኛዬ ትጉህ የማታንቀላፋ ነህና ሌሊቱን ከእኔ ጋር ሆነህ እንደጠበኸን ይህንን ማለዳ  ባርከህ ቀድሰህ የሰላም ውሎ እንድንውል ቀኝህ ትርዳኝ ። መንገዴን  ሁሉ ከፊት እያሆንክ ምራኝ ። መንገዴን ሁሉ ከፈት እየሆንክ ምራኝ ። ከደካማ ፍጡርነቴ የተነሳ በኋላዬም ምን እንዳለ አላውቅምና አንተ ጠብቀኝ ። በዙራያዬ ሁሉ ጠላት ያስቀመጠብኝን እንቅፋትና መሰናክል አስወግድልኝ ። በመልካም እሳቶች አስስጊጠኝ ከፈተና ያተነሣ እንኳን  ብወድቅ አንሳኝ እንጅ አትተወኝ ። በዚህች ብሩክት እለትም በስራዬ ፤ በንግዴ ፤ በመንገዴ ፤ በክብራ ፤ በአገልግሎቴ ሁሉ የጥፋት መረብን ዘርግቶ ሰላሜንና በረከቴን ሊያሳጣኝ የተዘጋጀውንና ያሚያሴርብኝን ጠላት(ዲያብሎስን )እቅዱንና ሥራውን ሁሉ አፍርስህ ሰላምን አጎናጽፈኝ ።  በዚህ እለት ኀጢያትን እቅጄ በድፍረት እንዳልፈጽም ፤ በመዘንጋትም እንዳልተገብር አድርገኝ ።ደም ከሚፈስበት ፤ ፍርድ ከሚዛባበት ፤ ደሀ ከሚበደልበት ፤ በማታለልና በማጭበርበር ከሚከበርበት ፤ ጣዖትና ስይጣን ከሚመለክበት ሥራና ባታ ሁሉ ፈጽመህ ጠብቀኝ ። ደካማው ልጅህ እጆቼን ዘርግቼ መንገዴን እንድትመራኝ በቀረብሁ ጊዜ ኅጢያቴንና በደሌን አይተህ ሳትጠያፈኝ ተቀብለህ ምራኝ ። እለቱን ሁሉ ፈቃድህን ማድረግ እንድችል በቃልህ አስተምረኝ ።መንፈስ ቅዱስ ሕይወቴን ይቆጣጠር ።ትናንትን  እንደጠበኸኝ  እንደመገብከኝ  ከክፉም እንደሰወርከኝና እንደሰወርከኝ ዛሬም እንደፍቃድህ ጠብቀኝ ። አንተ ያልከው ይሆን ዘንድ ግድ ነውና በከንቱ ከመጨነቅና ከመተከዝ ተስፋም ከመቁረጥ ሰውረኝ                     ለዘላለሙ አሜን ! @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf

ሥርየተ ኃጢአት ፦  “ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኃጢአት” (ጸሎተ ሃይማኖት) ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ባወጡት አንቀጸ ሃይማኖት ላይ ካሰፈሩት አንቀጽ አንዱ በጥምቀት ሥርየተ ኃጢአት እንደሚገኝ “ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኀጢአት፣ ኀጢአትን በምታስተሠርይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን” የሚለው ነው፡፡ እነዚህ አባቶች በቅዱስ መጽሐፍ የሰፈረውን በአንዳንድ የቤተክርስቲያን የውስጥ ጠላቶች አማካይነት ወደ ቤተክርስቲያን ሾልኮ የገባን የስህተት ትምህርት ለማጥራት፣ እምነትን ለማጽናትና ምእመናንን ከውዥንብር ለመታደግ አንቀጸ ሃይማኖትን ወስነዋል፡፡ ይህ የአበው ውሳኔ መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ያደረገ መሆኑን ከብዙ ማስረጃዎች የምንገነዘበው እውነታ ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል፡ በድንቅ አጠራሩ ለአገልግሎት የተጠራው ቅዱስ ጳውሎስ ከኃጢአቱ ይነጻ ዘንድ “አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ” መባሉን አስተውሉ (የሐዋ. ሥራ 22፡16)፡፡       ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በበዓለ ሃምሣ ተሰብስበው ለነበሩት በትምህርቱ ልቡናቸው በተነካ ጊዜ “ምን እናድርግ?” ብለው ሲጠይቁት የመለሰላቸው “ንስሐ ግቡ ኃጢአታችሁ ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ” ብሏቸው ነበር (የሐዋ. ሥራ 2፡37-38)፡፡ ይህ ታዲያ ከሌላ በረት ለመጡ በጎች እንጂ በበረቱ ተወልደው በበረቱ ላደጉት በጎች አይደለም፡፡ “በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ” ማለቱ የእርሱን የባሕርይ አምላክነት ለመግለጽ እና ዓለም እንዲቀበለው ለማስተማር እንጂ ጥምቀት መፈጸም የሚገባው በሥላሴ ስም መሆኑን ጌታችን ራሱ አስተምሯል (ማቴ 28፡19)፡፡       “ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለስርየተ ኃጢአት” በሚለው ንባብ ውስጥ ያለችው “ስርየተ ኃጢአት” የምትል ‘ነባር’ ኃጢአትን አመላካች ሐረግ የምታመለከተው ካደጉና ከጎለመሱ በኋላ ተምረው፣አምነው፣አመክሮ (የፈተና ጊዜ) አልፈው ለጥምቀተ ክርስትና የበቁ ንዑሰ ክርስቲያኖችን እንጂ ሕጻናትን ወይም ጥንተ አብሶን አያመለክትም፡፡ ክርስቶስን መምሰል ፦ “ጥምቀት ክርስቶስን በሞቱ የምንመስልበትና በትንሣኤው የምንተባበርበት ነው” (ሮሜ 6፡3-4) ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን? እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደተነሣ እንዲሁ እኛ በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን” (ሮሜ. 6፡3-4) በማለት በጥምቀት ክርስቶስን እንደምንመስለው ተናግሯል፡፡ ማጥመቅ በፈሳሽ ውኃ ነው፤ ጥልቅ ውኃ በማይገኝበት ጊዜ ግን ውኃ በሞላበት ገንዳ ይፈጸማል፡፡ ይህም ካልሆነ ውኃ ቀድቶ የተጠማቂውን መላ አካል ውኃው እንዲያገኘው በማድረግ በእጅ እየታፈኑ ያጠምቁታል፡፡          በጥምቀት ጊዜ የተጠማቂው አካል በውኃ እንዲጠልቅ መደረጉ “ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን” (ሮሜ. 6፡4) የሚለውን በገቢር ለመግለጽ ነው፡፡ እንዲሁም ተጠማቂው ከውኃ ውስጥ ብቅ ማለቱ “በጥምቀት ደግሞ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር ሥራ በማመናችሁ ከእርሱ ጋር ተነሳችሁ” (ቆላ. 2፡12) ያለውን እንዲሁ በድርጊት ለማሳየት ነው፡፡ አጥማቂው ካህን “አጠምቀከ/ኪ በሥመ አብ አጠምቀከ/ኪ በሥመ ወልድ አጠምቀከ/ኪ በሥመ መንፈስ ቅዱስ” እያለ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ እያደረገ ድርጊቱን ሦስት ጊዜ መፈጸሙ በሥላሴ አንድነትና ሦስትነት አምኖ መጠመቁን ለማጠየቅ ሲሆን እንዲሁም የጌታን ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በመቃብር አድሮ መነሳቱንና ተጠማቂዎችም ኋላ በትንሣኤ ዘጉባኤ “ንቃ መዋቲ” የሚለው አዋጅ ሦስት ጊዜ በሚታወጅበት ጊዜ በቀዋሚ አካል በምትናገር አንደበት ከራስ ጠጉራቸው እስከ እግር ጥፍራቸው ከቁጥር ሳይጎድሉ ከሰውነታቸው ሳይከፈሉ ወንድ በአቅመ አዳም ሴት በአቅመ ሔዋን መነሳታቸውን ለማዘከር ነው፡፡ ስለዚህ ጥምቀት “ከክርሰቶስ ጋር ከሞትን ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንድንኖር እናምናለን” (ሮሜ. 6፡8) በሚለው የሐዋርያው ቃለ ትምህርት መሠረት ጥምቀት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በሞቱ የምንመስልበት በትንሣኤውም የምንተባበርበት ታላቅ ምሥጢር ነው፡፡         የክርስቶስ አካል መሆን ፦ “ጥምቀት የክርስቶስ አካል መሆናችን የሚረጋገጥበት ነው” (ገላ 3፡27) በዘመነ ብሉይ የአብርሃም ወገኖች የአብርሃም ልጆች መሆናቸው ይረጋገጥ የነበረው በግዝረት ነበር፡፡ ግዝረት በኦሪቱ የእግዚአብሔር ሕዝብ መለያ ነበር፡፡ ያልተገረዘ ሁሉ ከሕዝቡ ተለይቶ እንዲጠፋ የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ነበር (ዘፍ. 17፡14)፡፡ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በአምሳልነት ሲፈጸም የኖረው ግዝረት በዘመነ ሐዲስ በጥምቀት መተካቱን  “በክርስቶስ ገዛሪነት የኃጢአትን ሕዋስ ሰንኮፍ ቆርጦ በመጣል ሰው ሰራሽ ያይደለ ግዝረትን የተገዘራችሁበት፤ በጥምቀት ከእሱ ጋር ተቀበራችሁ ከሙታን ለይቶ ባስነሣው በእግዚአብሔር ረዳትነትም በሃይማኖት ከእሱ ጋር ለመኖር በእስዋ ተነሣችሁ” (ቆላ. 2፡11-12) በማለት አበክሮ ያስገነዝባል፡፡         ግዝረት ለሕዝበ እግዚአብሔር የአብርሃም የቃል ኪዳን ተሳታፊዎች የመሆናቸው መለያ ምልክት እንደነበር ሁሉ ጥምቀት ደግሞ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ለሚያምኑ ሁሉ የጸጋው ግምጃ ቤት ከሆነችው ቅድስት ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኘው ጸጋ ተሳታፊ ያደርጋቸዋል፡፡ በጥምቀት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አንድ እንሆናለን፡፡ “ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና” (ገላ. 3፡27) በማለት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው በጥምቀት ከእግዚአብሔር ጋር አንድ እንሆናለን፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔር ያደሰውን አዲሱን ሰውነት የምንለብሰውና የክርስቶስ ተከታዮች የምንሆነው በጥምቀት ነው፡፡ በቀጣይ ፦ የጥምቀት አከፋፈል (ዓይነቶች) @Eotc_Books_By_Pdf @Eotc_Books_By_Pdf