የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት
前往频道在 Telegram
ይህ የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት የቴሌግራም ቻናል ሲሆን የሰንበት ት/ቤቱ መልዕክት : ትምህርት እና ወቅታዊ መረጃዎችን ማስተላለፊያ ነው መልዕክትም ካሎት በዚህ ሊንክ ይላኩልን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @Tgfkt
显示更多1 277
订阅者
无数据24 小时
+37 天
-130 天
数据加载中...
吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+11
在0个频道中
五月 '26
+16
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+24
在2个频道中
Get PRO
三月 '26
+22
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+15
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+25
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+35
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+21
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+60
在1个频道中
Get PRO
九月 '25
+17
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+14
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+20
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+22
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+22
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+28
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+35
在1个频道中
Get PRO
二月 '25
+52
在2个频道中
Get PRO
一月 '25
+61
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+91
在1个频道中
Get PRO
十一月 '24
+52
在1个频道中
Get PRO
十月 '24
+63
在2个频道中
Get PRO
九月 '24
+88
在1个频道中
Get PRO
八月 '24
+56
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+34
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+45
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+62
在1个频道中
Get PRO
四月 '24
+40
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+67
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+59
在1个频道中
Get PRO
一月 '24
+40
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+24
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+51
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+40
在1个频道中
Get PRO
九月 '23
+16
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+2
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+6
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+11
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+17
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+2
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+4
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+43
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+30
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+5
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+30
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+15
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+2
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+2
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+7
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+3
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+5
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+3
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+6
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+5
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+7
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+13
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+3
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+5
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+4
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+5
在0个频道中
Get PRO
七月 '210
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+5
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+5
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+7
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+13
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+6
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+11
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+574
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 17 六月 | 0 | |||
| 16 六月 | 0 | |||
| 15 六月 | 0 | |||
| 14 六月 | 0 | |||
| 13 六月 | +1 | |||
| 12 六月 | +3 | |||
| 11 六月 | +2 | |||
| 10 六月 | +1 | |||
| 09 六月 | 0 | |||
| 08 六月 | 0 | |||
| 07 六月 | 0 | |||
| 06 六月 | +2 | |||
| 05 六月 | 0 | |||
| 04 六月 | 0 | |||
| 03 六月 | +1 | |||
| 02 六月 | +1 | |||
| 01 六月 | 0 |
频道帖子
ደብረ ምጥማቅ
➡️ ግብጽ በምትገኘው በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በተሠራችው ደብረ ምጥማቅ ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ ድንግል ማርያም ከግንቦት ፳፩ ጀምሮ እስከ ፳፭ ቀናት በተከታታይ በመገለጧ ሕዝበ ክርስቲያን በዓሏን ያከብራሉ፡፡
➡️ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ምድረ ግብጽና ኢትዮጵያ በተሰደደች ጊዜ በአሁኑ ጊዜ ደብረ ምጥማቅ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ ዐርፈው ነበር:: ጌታችንም ቦታውን ባርኮ የእርሷ መገለጫ እንዲሆን ቃል ኪዳን ገብቶላት ስለነበር ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት በዓት ሆነ:: በደብረ ምጥማቅም እመቤታችንም ቅድስት ድንግል ማርያም :-
ብርሃን ተጎናጽፋና በሠራዊት መላእክት ታጅባ ተገልጣለች፤ በዚያን ጊዜም ሱራፌል ማዕጠንታቸውን ይዘው ሰገዱላት፤ እንዲህ እያሉም አመሰገኗት፤ አብ በሰማይ አይቶ እንዳንቺ ያለ አላገኘም፤ ባንቺም ሰው ሆነ፡፡›› (መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፳፩ ገጽ. ፫፻፲፰)➡️ ሰማዕታትም እንደየክብራቸው ማዕረግ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ሊሰግዱ ረቂቃን በሆኑ ፈረሶቻቸው ተቀምጠው ወደ እርሷ ቀረቡ፤ በመጀመሪያ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሁሉም ቀድሞ ከሰገደላት በኋላ ሌሎቹም በተመሳሳይ መልኩ ሰገዱላት፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዮስ በዱሪ ፈረስ ተቀምጦ ወደ እርሷ በመምጣት ሰገደላት፡፡ ጻድቃን በአንድነት ቀርበው ለክብሯ ሰገዱላት፤ ቀጥሎም በንጉሥ ሄሮድስ በግፍ የተገደሉት ሕፃናት ለእርሷ ሰገዱ፤ በደስታና በፍቅርም ተጫወቱ፡፡ በዚያ የተሰበሰቡትም ክርስቲያኖች፣ እስላሞችና አረማውያን ይህን በአዩ ጊዜ ደስታ ሞልቶባቸው በተለየ ዓለም ያሉ ይመስላቸው ነበር፡፡ (መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፳፩ ገጽ. ፫፻፲፰) አባ ጽጌ ድንግልም በደብረ ምጥማቅ በታላቅ ክብር ለምእመናን የታየችው የአምላክ እናት የድንግል ማርያምን መገለጥ በማኅሌተ ጽጌ ድርሰቱ እንዲህ በማለት ገልጾታል፤
‹‹አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ፣ ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ፣ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ፣ ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሁ መዓልተ፣ ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ፤ የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ በደብረ ምጥማቅ ለአምስት ቀናት ያህል በተገለጽሽ ጊዜ ማርያም ምን ያህል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው፡፡›› (ማኅሌተ ጽጌ)➡️ በደብረ ምጥማቅ ከተሰበሰቡት ሕዝብ መካከል እናትና አባታቸው፣ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ባልንጀሮቻቸው የሞቱባቸው ሰዎች ቅድስት ድንግል ማርያም እንድታሳያቸው በለመኗት ጊዜ እንደ ቀደመ መልካቸው አድርጋ ታሳያቸው ነበር፡፡ አንዳንዶች ደግሞ መሀረባቸውን ወደ ላይ በሚወረውሩት ጊዜ እርሷ የወደደቻቸው እንደሆነ በእጅዋ ተቀብላ መልሳ ትጥልላቸዋለች፤ ሁሉም ለበረከት ይካፈሉታል፡፡ እነርሱም ወደ ቤታቸውም ለመሄድ በሚፈልጉ ሰዓት ተሰናብተውና በተባርከውም ይሄዳሉ፡፡ (መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፳፩ ገጽ. ፫፻፲፱) ➡️ የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች እመቤታችን ድንግል ማርያምን ያዩባቸው ቀናት አረማውያኑ ያመኑበት፣ የበደሉት በምልጃዋ ቸርነትን ምሕረትን ያገኙበት፣ ያመኑት ደግሞ የተባረኩበት ዕለታት ነበሩ፡፡ ሕዝቡ እርሷን ተመኝተው ያጡት ወይንም ጠይቀው ያልተፈጸመላቸው ምንም ነገር አልነበረም:: ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ጻድቃን፣ ሰማዕታት፣ ደናግል፣ መነኮሳት መላእክትና ሊቃነ መላእክትም ለድንግል ማርያም ሲሰግዱ ይታዩ ነበር:: ➡️ ከዚህ በኋላ በዘመናት ይኖሩ የነበሩ ቅዱሳን የአምላክን እናት ለማየት ብዙዎች ተመኝተዋል፤ የመልክአ ማርያም ደራሲ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ የአምላኩን እናት ቅድስት ድንግል ማርያምን ፊቷን ለማየት ሽቶ
‹‹ሰላም ለመልክእኪ ዘተሠርገወ አሜረ ዘያበርህ ወትረ ፍቅርትየ አንቲ እንተ ታበድሪ ፍቅረ አርእዪኒ ገጸ ዚኣኪ ማርያም ምዕረ ዘኢይሰምዖ ካልእ እንግርኪ ነገረ፤” ዘወትር የሚያበራ ፀሐይን ጌጥ ላደረገ መልክሽ ሰላምታ ይገባል፤ ፍቅርን የምትመርጪ (የምታስቀድሚ) አንቺ የምወድሽ ማርያም ሌላ የማይሰማው ነገርን እነግርሽ ዘንድ አንድ ጊዜ ያንቺን ፊት ግለጪልኝ (አሳይኝ)›› (መልክአ ማርያም)በማለት ተማፅኗታል።ነቢዩ ዳዊት
‹‹ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኲሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር፤ የምድር ባለጠጎች አሕዛብ ሁሉ በፊትሽ ይማለላሉ›› በማለት ትንቢትን እንደተናገረላት በርካታ ቅዱሳን ሰዎች ቅድስት ድንግል ማርያምን ተገልጻላቸው ለማየት ተመኝተዋል፤ ልመናቸው ተሰምቶላቸው የአምላክ እናት ተገልጻላቸው ፊቷን ለማየትን ክብሯን ለመግለጥ ቅዱሳን አባቶች፣ ጻድቃን ሰማዕታት በቅተዋል፡፡ ይህም የሆነው በፍጹም ልቡናቸው በመማፀናቸውና በፍጹም ትጋት የጌታቸውን እናት ሲያገለግሉ በመኖራቸው እንደሆነ የጻድቃኑ ገድል ምስክር ነው፡፡ እነርሱም ሌት ከቀን ምኞታቸው ይሳካላቸው ዘንድ በጸሎት ይማፀኑ ነበር፡፡
(መዝ. ፵፬፥፲፪)
➡️ እመቤታችን ድንግል ማርያምም ጸሎታቸውን ሰምታ ያሰቡትን ትፈጽምላቸው ነበር፤ ምኞታቸው ከተሳካላቸው ቅዱሳን አባቶች መካከል አባ ይስሐቅ አንዱ ነው፤ ይህ ቅዱስ አባትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በፍጹም ልቡናው ይወዳት ስለነበር ለሰባት ዓመታት አምላኩን ክብርት እናቱን ያሳየው ዘንድ በጸሎቱ ተማጸነ፡፡ ዘወትር ከሠርክ ጸሎት በኋላ ሌሎች መነኮሳት ለመኝታ ወደየ በዓታቸው ሲሄዱ አባ ይስሐቅ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕሏ ፊት ቆሞ ሦስት መቶ ስግደትን እየሰገደ ይማፀን ነበር፡፡ ከስግደቱም ጋር ‹‹ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ አርእየኒ እመከ አሐተ ሰዓተ፤ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለአንዲት ሰዓት እናትህን አሳየኝ››እያለ ይጸልይ ነበር፡፡ በእንደዚህም ሁኔታ ለሰባት ዓመት ከቈየ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በታላቅ ግርማ ተገለጸችለት፤ የልቡም መሻት ምን እንደሆነ ጠየቀችው፤ አባ ይስሐቅም የርሷን ገጽ ያዩ ዐይኖቹ ሌላ ነገርን ማየት እንደማይሹ ነገራት፤ ከተወደደ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ እንድታማልደውም ተማጸናት፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያምም ልመናውን ተቀበለች፤ ከዚያም በኋላ የዕረፍቱ ቀን ከሦስት ቀን በኋላ መሆኑን አሳወቀችው፤ ባርካውም ወደ ሰማይም በክብር ዐረገች፤ ይህ ቅዱስ አባት ይስሐቅም እርሷን ካየ በሦስተኛው ቀን ዐረፈ፡፡ (መጽሐፈ ስንክሳር ታኀሣሥ ፳፩ ገጽ.፬፻፺፪) እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ ተገልጣ የሕዝቡን ምኞት እንደፈጸመችላቸው የእኛንም በጎ መሻት ትፈጽምልን፤ አሜን፡፡ ወቅታዊ ትምህርት ክፍል
| 2 | እንኳን ደስ አላችሁ
የአባታችን የአምላካችን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ህንፃ ቤተ ክርስትያን ሊመረቅ ነው።
የጥምቀት ቤታችን የታቦት ማደርያችን የሆነው የአባታችን ቤት ገዳመ ኢየሱስ አዲሱ ቤተ መቅደስ ብፅአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ግንቦት 12 ከ ቀኑ 7:00 ቅዳሴ ቤቱ ተባርኮ ግንቦት 13 ታቦተ ህጉ ወጥቶ የሚከብር ይሆናል።
በዚህ የደስታ ቀን ሁላችሁም በቦታው በመገኘት የአባታችንን ቤት እንድንመርቅ አደራ እንላለን።
የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት | 1 050 |
| 3 | ዓለም ማየት ነበር ማየት ነበር ዓለም
ምኞትና ሳቁ
የሰማይ ከዋክብት ፀሐይ ከጨረቃም
ከዚህ ቀኑ በልጠው ችለው አልደመቁ
ሐሩር ነበር ሰሙ መቃጠል ነው ቅኔው
በዘመን ትንግርቱ
አንድ አንቺ ወርቅ ሆነሽ ደመና አስናቅሽለት
ጋርደሽ ከመከራ ፈተሽ ከእስራቱ
የአዳም አስራቱ...
ለሰማያት ንጉሥ የሰማይ ንግሥቱ
የብርሃናት መብረቅ
በቀንሽ ብልጭታ በልደትሽ ፋና
በመዳኑ ተስፋ ጨለማው ቀን ሆነ ስለአንቺ ሲመረቅ
አዳም በደለኛው አዳም የቀጠፍከው
እርቃን ገላህ ታየ አፍረህ የሸፈንከው
ከንቱ ሙከራ ነው
ልፋት ሲሆንብህ አያድንህ ነገር
በእጅህ የከለልከው
ያልከኝ ጥንተ ጠላት እይ ኃፍረትህን ና
አላቀረቀርኩም ላልደፋ አንገቴን
እንደትላንትና
እናቴን ወልጄ በርሷ ከድኖ ነውሬን
መሀሪ አምላኬ አድርጎኛል ቀና
እናቴ ሆይ እሰይ እናቴ ሆይ እሰይ
እንኳን መጣሽልኝ እንኳንም ወለድኩሽ
ትውልድ ከ'ነ ዘሬ ለተማረረብኝ
ከእርግማን እድሌ በአንቺ አለፍኩብሽ
ለተወለድሽልኝ መልካም ልደት ለአንቺ
የጌታዬ እናት መኖር ትርጉም ሆነ
ሕይወቴ ስትመጪ
ለተወለድኩብሽ መልካም ልደት ለእኔ
የጌታዬ እናት ቃልኪዳኔን አየሁ የተገባልኝን የነፍስ መድኅኔን
ገነት መኖር ነበር መኖር ነበር ገነት
ምኞትና ዓለሜ
አሁን ሆኖ አየሁ መሽቶ ተስፋ ያ'ረኩት
የዓመታት ሕልሜን
ዓለም ማየት ነበር ማየት ነበር ዓለም
የምኞት ቀለሟ
በጭንቅ በምጥ ወልዳም ሲተቿት ሲኖሩ
ከአንድ አንቺ በስተቀር ማንም
አላከመም የነፍስ ሕመሟን
ወየው ነበር ሰሟ ፀፀት ነበር ቅኔው
በዘመን ትንግርቷ
አንድ አንቺ ወርቅ ሆነሽ እሰይ አሰኘሻት
መልተሽው መሻቷን
የሔዋን አስራቷ...
ለዓለማት ንጉሥ የዓለም እናቱ
ማትጠገብ ዜማ
ሲስረቀረቅ ከሩቅ የልደትሽ ድምፁ
በይፋ ሲሰማ
በመዳኗ ተስፋ ጨለማዋ ነጋ አንቺን ተሸልማ
ሔዋን በደለኛ ሔዋን ቃል ያጠፍሽው
እርቃን ገላሽ ታየ አፍረሽ የሸፈንሽው
ከንቱ ሙከራ ነው ልፋት ሲሆንብሽ
አያድንሽ ነገር በእጅሽ የከለልሽው
ያልከኝ ጥንተ ጠላት እይ ኃፍረትህን ና
አላቀረቀርኩም ላልደፋ አንገቴን
እንደትላንትና
እናቴን ወልጄ በእርሷ ከድኖ ነውሬን
መሀሪ እግዚአብሔር አድርጎኛል ቀና
እናቴ ሆይ እሰይ እናቴ ሆይ እሰይ
እንኳን መጣሽልኝ እንኳንም ወለድኩሽ
ትውልድ ከ'ነ ዘሬ ለተማረረብኝ
ከእርግማን እድሌ በአንቺ አለፍኩብሽ
ለተወለድሽልኝ መልካም ልደት ለአንቺ
የጌታዬ እናት መኖር ትርጉም ሆነ
ሕይወቴ ስትመጪ
ለተወለድኩብሽ መልካም ልደት ለእኔ
የአምላኬ እናት ቃልኪዳኔን አየሁ
የተገባልኝን
የነፍስ መድኅኔን
ምስጉን ነህ ኢያቄም ቡርክት ነሽ ሐና
ፀሐዬን አየሁት ብርሃኔ ደመቀ ባስገኛቿት ፋና
እመ ብዙኃን ሆይ ተወልደሽ ወልደሽን
ደምቆ ሞገሳችን
የሰሎሞን አክሊል መጎናፀፍያችን
እንደ ንጉሥ ከብሮ አበራ ገፃችን
እፁብ ተደንቀናል
ከደጅ አስቀርቶ ቤት የማያስገባ
ከሊባኖስ ሃገር አየን የሚማርክ
ግሩም ውብ አበባ
አበባዬ ሆይ...
ውበቴ ነይ ውጪ የግንቦት ሙሽራ
ከአድማስ ወዲያ ብሉይ
ከአድማስ ወዲህ ሐዲስ
በአንቺ አብረቅርቆ አየሽ ወይ ሲያበራ?
ትንቢት እንዲፈፀም ከምሥራቅ ፈንጥቀሽ
ቃሉ እንዳይታበይ ሌ'ቱን አንፀባርቀሽ
ስለ እኛ ደስታ ስለ ኢያቄም ስለት
ስለ አዳም ተስፋ ስለ ሐና ጸሎት
ስለ መልካም ብስራት ስለ ጌታ ልደት
እሰይ እንኳን በራሽ.....!!
(ልደት ክብሩ)
"አሀቲ ይእቲ ለእማ ወኅሪት ይእቲ ለእንተ ወለደታ"
"ለእናቷ አንዲት ናት ለወለደቻትም የተመረጠች ናት"
ለድኀነታችን መጀመሪያ ለሆነው ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደቷ በዓል እንኳን አደረሳቹ!!!
(ኪነ ጥበብ ክፍል) | 1 654 |
| 4 | 没有文字... | 1 189 |
| 5 | ክብረ ሃይማኖት ትጣራለች
የክብረ ሃይማኖት ልጆች የሆናችሁ ከእውቀቷ የቀሰማችሁ በህይወት በጥበብ ያሳደገቻችሁ በህይወታችሁ ላይ አሻራ የጣለችላችሁ በሙሉ ኑ የነገዋን የሰንበት ትምህርት ቤቷን ሁኔታ እንወያይ እንመካከር አንድ ላይ አገልግለን ያሳደገችንን የእናታችንን ቤት ወደተሻለ ነገር እናሳድጋት
( እሁድ በፍፁም መቅረት አይቻልም) | 1 662 |
| 6 | AASSU STRACTURE ATIBIYA (1).pptx | 1 189 |
| 7 | የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ
ሰላም እንደምን አመሻችሁ ውድ የክብረ ሃይማኖት ልጆች ሚያዝያ 25 የሚኖረን ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች መካከል አንዱ የሆነው አዲሱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅር በተመለከተ ውይይት ይኖረናል
በውይይቱም...
👉 ሰንበት ትምህርት ቤቶች በሙሉ ተመሳሳይ መዋቅር ይኑራቸው የሚለው እና ተግባራዊ ሊደረግ የታሰበው መዋቅር ሲሆን የምናነሳ ሲሆን ይህ መዋቅር በአገልግሎት ዘመን በአባላት ብዛት በሰንበት ትምህርት ቤቶች በመማር ማስተማር እና ሰንበት ትምህርት ቤቷ ባፈራቻቸው ክህነት ያላቸው አባላት እና በዝማሬ አገልጋይ መሰረት ባደረገ 4 ደረጃ ያለው መዋቅር ተዘጋጅቷል የወደፊቷን የሰንበት ትምህርት ቤት መዋቅር ከአራቱ አንዱ ስለሚሆን በመዋቅር ዙርያ ውይይት ይኖረናል
👉 በጠቅላይ ቤተ ክህነት ፀድቆ በወረደው መሰረት የሰንበት ትምህርት ቤቶች የምርጫ ዘመን በተመሳሳይ ጊዜ ይሁን ስለተባለ አዲስ አበባ ላይ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በሙሉ በያዝነው በዚኛው ዓመት የዓመራር ምርጫ የሚያደርጉ ይሆናል። በዚህም መሰረት 2017 ዓ.ም የአመራርነት ዘመናቸውን የሚጨርሱ የነበሩ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የምርጫ ዘመን የሚከለስ በመሆኑ እና በ 2018 ዓ.ም ሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤቶች ግዴታ የምርጫ ዘመናቸው ወጥ መሆን ስላለበት ያለው አመራር ባለበት እንዲቀጥል ተደርጓል ይህ በእንዲ እንዳለ በ 2019 ዓ.ም የአመራርነት ጊዜያቸውን የሚጨርሱ ልክ እንደኛ ያሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶችም በ2018 ዓ.ም ምርጫ እንዲያከናውኑ እና የምርጫ ወቅት ተመሳሳይ እንዲሆን ተደርጓል በዚህም ላይ ሃሳብ አንስተን አስመራጭ ኮሚቴ እንመርጣለን
ማስታወሻ:- ለሰንበት ትምህርት ቤቶች የተዘጋጀው የመዋቅር ይዘት ዓላማ እና ምድባት በተመለከተ ጠቅለል ያለ ፅሑፍ ከዚ በታች በ powerpoint ስለሚለቀቅ እዩት
👇👇👇👇👇👇 | 1 141 |
| 8 | ክርስትናና የሕክምና ሙያ (part 1)
ጥቂት የማይባሉ ክርስቲያኖች ህክምናን በተለይ ደሞ ዘመናዊ ህክምና ቦታ መሄድን በእግዚአብሔር አለማመን የሚመስላቸው አሉ ይህ በልማድ የመጣ አስተሳሰብ እንጂ በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ሆነ በአባቶች ትምህርት የሌለ ሊቀር የሚገባው አስተሳሰብ ነው ፡፡ በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ህክምናና እና ሃይማኖት እርስ በእርስ የሚጋጩ ነገሮች ሳይሆኑ የሚመጋገቡም ጭምር ናቸው ህክምናና እና ክርስትና የሁለቱም ዋነኛ ዓላማ ለሰው ልጆች ጤንነት መስጠት ነው (የሃይማኖት ዘለዓለማዊው ላይ የበለጠ ቢያተኩርም) የክርስቲያኖች ሰውነት የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ነው የዚህን ቤተመቅደስ ጤንነት መጠበቅ አማራጭ ሳይሆን ግዴታው ነው፡፡
1ኛ ቆሮንቶስ 6:19-20: ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
ህክምና ከሃይማኖት ጋር የሚጋይጋጭ ብቻ ሳይሆን በርካታ የቤተክርስቲያን አባቶች በዚህ ትልቅ ሙያ ላይ የተሰማሩም ጭምር ናቸው፡፡ ለምሳሌ ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊው ሳይቀር የዚህ ታላቅ ሙያ ባለቤት ነበር ። ስለዚህ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይለናል
"ቆላስይስ4:14: የተወደደው ባለ መድኃኒቱ ሉቃስ ዴማስም ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
ይህ የጥበብ ሙያ በጥበብ መጽሀፍ ውስጥ ክብር የሚያስፈልገው እንደሆነ በግልጽ ተቀምጧል
...ሲራክ 38:1 -7 እሱን እግዚአብሔር ስለ መረጠው ጌትነቱ እንደ እጁ ሥራ ነውና ባለመድኃኒትን አከብረው።..... እግዚአብሔር መድኃኒትን ከምድር ፈጥሯልና አዋቂ ሰው ባለመድኃኒትን አይንቀም። ..በኃይሉ ይከብሩ ዘንድ እግዚአብሔር ለሰዎች ጥበብን ሰጣቸው።... በመድኃኒቱ ያድናቸዋል በሽታቸውንም ያርቅላቸዋል።
በግልፅ እንደምናየው ክርስትና ህክምናን ክብር የሚገባው ሙያ እንደሆነ የህክምና ባለሙያነት እራሱ የእግዚአብሔር ፍጥረትን በጥበብ መረዳት የጠቢባን ስራ እንደሆነ
አይደለም ባለመድኃኒቱ መሆኑ ይቅርና ባለ መድኀኒትን ለማክበር እራሱ አዋቂነትን እንደቅድመ ሁኔታ በማስቀመጥ የሙያውን ታላቅነት ይመሰክራል ።
የቤተክርስቲያን አባቶች ህክምና ላይ መስራት ብቻ ሳይሆን የህክምና ተቋማትን ሳይቀር እስከ ማሰራት የደረሱ አሉ በተለይ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በርካታ የሀክምና ተቋማትን ፓትሪያሊክ በነበረባት ቁስጥንጥንያ አሰርቷል እርሱ ብቻ ሳይሆን ባስሎዮስ ዘቂሳርያም በቂሳርያ በጣም ትልቅ ሃኪም ቤት እሰርቶ የማስተዳደሩን ኃላፊነት ለእንድ የዚያው አገረ ስብከት ጳጳስ አደራ ሰጥቷል። መጽሃፍ ቅዱስም ሆነ ቅዱሳን አባቶቻቸን ታሪክ የምንመለከተው ክርስትና የህክምና ደጋፊ ሆኖ የተቀመጠ ብቻ ሳይሆን በህክምናው ዘርፍ ላይ ቅዱሳን አባቶቻችን የሀክምና ባለሙያ ከመሆን ጀምሮ የህክምና ተቋማትን እስከ ማስገንባት ትገኛለች አሁንም ድረስ ያሉ ሊቃውንቶቿ የህክምና ባለሙያዎች እና የህክምና ተቋማት ሰሪዎች ናቸው ለአብነትም በሃገራችን የአባ ገብረኪዳን በባህርዳር የሚያሰሩትን የህክምና ተቋም መመልከት ይቻላል።
የሁለቱም ዓላማ በራሱ የሚስማማ በመሆኑ ሃይማኖት በራሱ የህክምናን ጥበብ የሚያቃል ተደርጎ መታየቱ ባለመድኃኒት ጋር መሄድን የእግዚአብሔርን ማዳን አለማመን እንደሆነ የሚያስብ ክርስቲያን እራሱን መፈተሽ አለበት ይህ ማለት ግን የስጋ በሽታዎች ሁሉ መፍትሔያቸው የህክምና ቦታ ነው ማለት በራሱ ሌላ ስህተት ውስጥ ሊጥለን ይችላል ። መጽሃፍ ቅዱስ ህክምናን ብቻ ሳይሆን የቤተክርስቲያን አባቶችንም ሳይቀር ለስጋዊ ህመማችን መድኃኒት አርጎ ሰጥቶናል ከምስጢራተ ቤተክርስቲያን አንዱ ቀንዲል (ቅብዓ ቅዱስ) ዓላማቸው ክርስቲያኖች ከተያዙት ደዌ በዚህ በቅዱስ ቅባት የሚፈወሱበት ነው ከዚህ ባለፈም ሁሉም የቤተክርስቲያን አገልግሎቶች መንፈሳዊ ተግባራት ድኅነተ ነፍስን ብቻ ሳይሆን ድኅነት ስጋንም ጭምር የሚያስገኙ መሆናቸውን መገንዘብ ይኖርብናል፡፡
ያዕቆብ 5:14: ከእናንተ የታመመ ማንም ቢኖር የቤተ ክርስቲያንን ሽምግሌዎች ወደ እርሱ ይጥራ፤ በጌታም ስም እርሱን ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት።
ስለዚህ ሁለቱንም መንገድ መጠቀም ሳይጣሉ መጠቀም አለብን ምንም እንኳን በራሱ ህክምና ከሃይማኖት ጋር ባይጋጭም አንዳንድ አካላት የራሳቸውን ክፉ ዓላማ ለማስፈጸም ሲሉ በሕክምና ስም የሚያስገቧቸው ሐሳቦች አሉ። ከእነዚህም ውስጥ ሦስቱን ማለትም
፨ ውርጃን (Abortion)
፨ ወሊድ መቆጣጠሪያን calendar method ጭምር
፨ Euthanasia (ታማሚው የማይድን ሆኖ ከታመነ እና በጣም እየተሰቃየ ከሆነ በፍቃዱ መግደል)
እንደዚህ አይነት ነገር ሲያጋጥሙት አንድ ክርስቲያን በምን አይነት መንገድ መፍታት እንዳለበት እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ አንፃር ለመመዘን እንሞክራለን ።
ምንጭ:
-ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱና ትምህርቱ
-thesis on ethical repercussion on abortion and related issues by fr Anastasios
✍ ያሬድ አካሉ
ወቅታዊ ትምህርት ክፍል | 736 |
| 9 | #ክብረ_ሃይማኖት | 1 030 |
| 10 | ትንሣኤከ ለእለ አመነ
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
በዓለ ትንሣኤ በደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤተክርስቲያን በዚህ መልኩ ተከብሯል :: 👇
#ክብረ_ሃይማኖት
📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ ቲክቶክ
📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ ቴሌግራም
📌 የፌስቡክ አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ ፌስቡክ
📌 የዩቲዩብ ቻናል
👉 ይህን ይጫኑ ዩቲዩቡ | 688 |
| 11 | በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
<<እርሱ፡ግን፡ስለ፡መተላለፋችን፡ቈሰለ፥ስለ፡በደላችንም፡ደቀቀ፤የደኅንነታችንም፡ተግሣጽ፡በርሱ፡ላይ፡ ነበረ፥በርሱም፡ቍስል፡እኛ፡ተፈወስን።>>
ት ኢሳ 53÷5
ውድ በአገልግሎት የምትመስሉን ወንድሞችና እህቶች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ እያልን የእዳ ደብዳቤያችንን ሊያጠፉ በቀራኒዮ አደባባይ እራሱን ስለኛ ካሳ አድርጎ ያቀረበ ሞታችንን በህይወት የቀየረ የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሳኤ ስናከብር በደሙ የመሰረታትን ቅድስት ቤተ ክርስትያንን ለመጪው ትውልድ አባቶች እንዳስረከቡን እንድናስረክብ በአገልግሎታችን እንድንበረታ እና እንድንጠነክር አምላከ ፊልጶስ ወባኮስ ይርዳን።
መልካም በዓል
የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት | 630 |
| 12 | #በዓለ_ስቅለት
#ክብረ_ሃይማኖት | 574 |
| 13 | #በዓለ_ስቅለት
#ክብረ_ሃይማኖት | 409 |
| 14 | በዓለ ስቅለት
በዓለ ስቅለት በደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤተክርስቲያን በዚህ መልኩ ተከብሯል :: 👇
#ክብረ_ሃይማኖት
📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ ቲክቶክ
📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ ቴሌግራም
📌 የፌስቡክ አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ ፌስቡክ
📌 የዩቲዩብ ቻናል
👉 ይህን ይጫኑ ዩቲዩቡ | 282 |
| 15 | የስቅለት ዕለት የሚደመጡ ዝማሬ
ውድ የክብረሃይማኖት አባላት በስቅለት ዕለት ከምናዳምጣቸው ዝማሬዎች መካከል በወንድማችን ዲ/ን አብነት መላኩ የተዘመሩ ቀና በሉ እና ኦ የማይሞተው ሞተ የተሰኙ ዝማሬዎች በዩቲዩብ ገፃችን ተለቋል ::
መዝሙሩን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ተጠቀሙና የተለመደውን ስራ ሁላችንም እንስራ
https://youtu.be/tVqfrgVrwZw?si=nkk08Fw-UqqsTPd2
#ክብረ_ሃይማኖት
📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ ቲክቶክ
📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ ቴሌግራም
📌 የፌስቡክ አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ ፌስቡክ
📌 የዩቲዩብ ቻናል
👉 ይህን ይጫኑ ዩቲዩቡ
https://youtu.be/tVqfrgVrwZw?si=nkk08Fw-UqqsTPd2 | 346 |
| 16 | የሰሙነ ሕማማት ሥርዓት(በሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ)
ሰሙነ ሕማማት አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ሁሉ ቤዛ ሆኖ ተላልፎ መሰጠቱን የምናስታውስበት ሳምንት ነው።
ይህንን ምክንያት በማድረግ የሥርዓት ለውጥ ሲደረግ ሲመለከቱ ግራ የሚጋቡና ሥርዓተ አምልኮውን በሚገባ ከመከታተል ይልቅ ሥርዓት የጣሱ እየመሰላቸው የሚጨነቁ ስላሉ ልናደርገው የሚገባንን እጽፍላችኋለሁ።
1,በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብሎ ፊትንና መላ ሰውነትን በትዕምርተ መስቀል {በመስቀል ምልክት} ማማተብ አይከለከልም።
ከካህን እጅ ቡራኬ አንቀበልም በካህኑ እጅ ያለውን መስቀል አንሳለምምና ማማተብም የለብንም በሚል ፍልስፍና ካልሆነ ማማተብ ክልክል ነው ተብሎ የተጻፈበት ቦታ የለምና።
2 . የሚከለከል ጸሎት የሌለ መሆኑን አውቃችሁ ያስለመዳችሁትን ጸሎት በትጋት ጸልዩ።
መሥዋዕት ካለመሠዋታችን ቅዳሴ ካለመቀደሳችን በቀር በዚህ ሳምንት ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ጀምሮ እስከ ሊቃውንት ድርሳናት ድረስ በቤተ ክርስቲያን የማይጸለይ ጸሎት የለምና።
3 ሰላምታ መስጠት ከጸሎተ ሐሙስ ዕለት በቀር አልተከለከለም
፤ እሱም ቢሆን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በይሁዳ ሰላምታ ተላልፎ መሰጠቱን ለማስተዎስ እንጅ ሌላ የተለየ ምክንያት ስለሌለው በመርሳት ወይም በሌላ ከድፍረት በተለየ ምክንያት ሰላምታ ያቀረበላችሁን ሰው ልታስደነግጡና ትልቅ ኃጢአት እንደሠራ አድርጋችሁ ልታስጨንቁት አይገባም።
4 . “በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ" ብሎ መጻሕፍትን ማንበብ ወይም ሌላ ሥራን መጀመርይቻላል።
ስመ እግዚአብሔር መጥራት የምንከለከልበት ጊዜ መቸም የለምና።
5 . የጌታችንን ሕማሙንና ሞቱን የሚያስታውሱ መጻሕፍትን በማንበብና በመስማት ጊዜአችንን መወሰን ይገባናል።
6 . በዚህ ሳምንት ተድላ ደስታን ሲያደርጉ መገኘት ከአይሁድ ጋር እንደ መተባበር የሚያስቆጥር ስለሆነ አብዝቶ በመብላትና በመጠጣት፣ ያማረውንና ጌጠኛውን ልብስ በመልበስ፣ ባልና ሚስት በምንጣፍ በመገናኘት እንዲሁም በልዩ ልዩ ምክንያት ከምናደርጋቸው ተድላ ደስታዎች መራቅ ይገባናል።
ቅዱሳን በዘመናቸው ሁሉ ባሰቡት ጊዜ የሚያስጨንቃቸውን የክርስቶስን መከራ እያሰብን ለጥቂት ጊዜም እንኳን ቢሆን የክርስቶስን መከራ በሰውነታችን ማሰብ ይገባናል።
የተቻለው እንደ ጴጥሮስ የራሱን ኃጢአት እያሰበ እንደ ማርያም መግደላዊት የክርስቶስን ሞት እያዘከረ ሊያለቅስ ይገባዋል። በወዲያኛው ዓለም ከማልቀስ የሚያድነን ዛሬ የራሳችንን ኃጢአት አስበን የክርስቶስን ሞት አዘክረን የምናለቅሰው ለቅሶ ነው እንጅ ዛሬ ከተደሰትን ደስታችንን በዚህ ዓለም ማድረጋችን አይደለምን?
7 . በተቻለን መጠን በቤተ ክርስቲያን መዋል ይገባናል፤ ሕማማተ መስቀልን የሚያስታውሱ መጻሕፍት የሚነበቡበት ሳምንት ስለሆነ ነው።
ነገር ግን በልዩ ልዩ ምክንያት በቤተ ክርስቲያን መዋል እንኳን ባይቻላችሁ ባላችሁበት ቦታ ሁናችሁ እየዋሻችሁ በሐሰት የከሰሱትን፣ እየቀማችሁ ልብሱን የገፈፉትን፣ ሰው እየደበደባችሁ በጅራፍ የገረፉትን፣ በወንድሞቻችሁና በእኅቶቻችሁ ላይ እየፈረዳችሁ በክርስቶስ ላይ የፈረዱበትን፣ በሰዎች ላይ እየተዘባበታችሁ የተዘባበቱበትን፣ በሳቅና በሽንገላ ሰውን እየሸነገላችሁ ሽንገላ በተሞላበት ሰላምታ ጌታውንና መምህሩን አሳልፎ የሰጠ ይሁዳን ልትመስሉ አይገባም።
ይልቁንም በአይሁድ እጅ ተላልፎ ቢሰጥም ንጹሓ ባሕርይመሆኑን በማመን እስከ ቀራንዮ የተከተሉትን ደቀመዛሙርት ልትመስሉ ይገባል። እግራችሁ በመቅደሱ ውስጥ ባይቆምም ልባችሁን ከመቅደስ ልታወጡት አይገባም። እያዘናችሁ ባላችሁበት ቦታ ዋሉ።
8 . በቤታችሁም ሆነ በቤተ ክርስቲያን አብዝታችሁ ስገዱ።
ስለሁላችንም ቤዛ የሚሆን ክርስቶስ በፊታችን መስቀል ተሸክሞ ሲወድቅ እያያችሁት ትቆማላችሁን? አይሁድ ገፍተውት አንድ ጊዜ ወደ ምድር በወደቀ ጊዜ ለወደቀው መውደቅ ዘመናችንን ሙሉ ብንወድቅ ብንነሣ ውለታ መክፈል እንችል ይመስላችኋል? ቅዱሳን ሳያቋርጡ ሲሰግዱ የሚኖሩት ክርስቶስ በፊታቸው በአይሁድ እጅ እየተገፋ መስቀሉን እንደተሸከመ ሲወድቅ በዓይነ ሕሊናቸው ስለሚያዩት ነው። በስንክሳር ተጽፎ የምናገኘው ዜና ሞታቸው እየሰገዱ ሳሉ ሞት ነፍሳቸውን ከሥጋቸው ለይቶ እንደሚወስዳትና ለስገደት ታጥቀው እንደተንበረከኩ እንደሚገኙ ይነግረናል። የተሰቀለውን ክርስቶስን የሚያስብ ሰው ለሰውነቱ ዕረፍትን አይሻም።
9 . ከሁሉም ሰው ጋር ፍቅርን አድርጉ። ሰውን ለመውደድ ምክንያት አታብጁ።
ክርስቶስ አሳልፎ የሰጠውን ይሁዳን “ወዳጄ” ብሎ ሲጠራው አትሰሙትም? እግዚአብሔርን አንተን ያለ ምክንያት እንደ ወደደህ አንተም ያለ ምክንያት ሰውን መውደድ ልመድ። ክርስቶስ አንተን ጠላቱ ሆነህ ሳለ ፍቅርን ካላጎደለብህ ለጠላትህ ፍቅርን አታጉድልበት።
ክርስቶስ ይሁዳን "ወዳጀ” ብሎ ከጠራው አንተም ይሁዳዎችህን ወዳጀ ብለህ ጥራቸው። አውቃለሁ ጠላትን መውደድ መራራ ሐሞትን ከመጠጣት በላይ መራራ ነው። ነገር ግን እኔም ለይሁዳዎቻችን ፍቅርን እንስጥ ማለቴ መራራ ሐሞት የጠጣ ክርስቶስን እንድንመስለው ነው።
10. ለሁሉም መስጠት በምትችሉት መጠን ስጡ እንጅ አትቀበሉ።
ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነውና በመስጠታችሁ ብፁዓን ተብለው ወደ እግዚአብሔርመንግሥት ከሚገቡት ትቆጠራላችሁ።
ምናልባትም የምትሰጡት ገንዘብ ባይኖራችሁ ዕዳ አይሆንባችሁም ቢሆንም ገንዘብ ለሰጧችሁ ባለጠጎች የምትሰጡት ጸሎት ሊኖራችሁ ይገባል። ከምንጊዜውም የበለጠውን ስጦታ የተቀበልንበት ሳምንት መሆኑን እያሰባችሁ አንዳች የምሰጡት ሥጋዊም ሆነ መንፈሳዊ ስጦታ የሌላችሁ ባዶዎች እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ።
ከሁሉ በላይ የሆነውን ስጦታ የጌታን ሥጋና ደም እነሆ ተቀብለናል።
ክርስቶስ መድኃኒነ መጽአ ወሐመ በእንቲአነ ወበሕማማቲሁ ቤዘወነ !!
( ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የሊቃውንት ጉባዔ ሰብሳቢ የዐራቱ ጉባዔያት ምስክር መምህር)
ወቅታዊ ትምህርት ክፍል | 1 631 |
| 17 | ፕሮግራማችን ጀምራል ላይቭ ላይ ነን 👇
https://vt.tiktok.com/ZS98pC9h5FqNG-fta5Z/
#ክብረ_ሃይማኖት
📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ ቲክቶክ
📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ ቴሌግራም
📌 የፌስቡክ አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ ፌስቡክ
📌 የዩቲዩብ ቻናል
👉 ይህን ይጫኑ ዩቲዩቡ | 542 |
| 18 | እየጠበቅናችሁ ነው !
ፕሮግራሙን መሳተፍ የማትችሉ በቲክቶክ ገፃችን ላይቭ ላይ ጠብቁን
ቲክቶክ ገፅ👉 ቲክቶክ | 539 |
| 19 | 🌿ሆሳዕና በአርያም 🌿
ሆሣዕና ማለት መድኃኒት ወይም አቤቱ አሁን አድን ማለት ነው፡፡ በዐቢይ ጾም ስምንተኛ ሳምንት የሚከበር በዓል ሲሆን ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ዓበይት በዓላት አንዱ ነው። ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሑዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ከትንሣኤ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው።
“አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልል በዪ፤ እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም በአህያይቱም ግልገል በውርንጫይቱ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል፡፡” (ዘካ. ፱÷፱)
በማለት በነቢያት የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደብረ ዘይት ቤተ ፋጌ በአህያ ውርንጫ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም መግባቱን በማሰብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዓሉን በድምቀት ታከብረዋለች፡፡
በወንጌሉም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ወደ ኢየሩሳሌም ደብረ ዘይት ቤተ ፋጌ በደረሰ ጊዜ ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ጠርቶ “
በፊታችሁ ወደአለችው መንደር ሂዱ ያን ጊዜም የታሰረች አህያ ከውርንጫዋ ጋር ታገኛለችሁ፤ ፍቱና አምጡልኝ”
አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም የሰው ንብረት ዘርፈን እንዴት እናመጣለን? ብለው መፍራታቸውን የተረዳው ጌታችንም “
ምን ታደርጋላችሁ? የሚላችሁ ቢኖር ጌታቸው ይሻቸዋል በሉ፤ ያን ጊዜ ይሰዱአችኋል”
አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ሄደው ጌታችን ኢየሱስ እንዳዘዛቸው አደረጉ፡፡
ልብሳቸውንም በአህያውና በውርንጫይቱ ላይ አድርገው ጌታችንም በእነርሱ ላይ ተቀመጠ፡፡ ሕዝቡም ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉለት፤ ዘንባባ እና የዛፎችንም ጫፍ ጫፍ እየቆረጡ
“ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም” እያሉ ይጮሁ ነበር፡፡ (ማቴ. ፳፩÷፩-፲፩)
ልብሳቸውን ማንጠፋቸውም ለክብሩ መግለጫ ነው፡፡ እንዲህ ባለ ክብርና ምስጋና ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ ከተማዋ በዝማሬና በአመስጋኞች ጩኸት ተናወጠች፡፡
የሕዝቡ ጩኸትና ደስታ ያበሳጫቸው ፈሪሳዊያንና አይሁድ የሚያመሰግኑትን ዝም እንዲያሰኝ ጌታችንን ቢጠይቁትም
“እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ያመሰግኑኛል
ብሎ መልሶላቸዋል፡፡ በነቢዩ ዳዊት
ከሚጠቡ ሕፃናትና ከልጆች ምሥጋናን አዘጋጀህ” (መዝ. ፰÷፪)
ተብሎ የተነገረው ትንቢት እንዲፈጸም የአርባ የሰማንያ ቀን የዓመት የሁለት ዓመት ሕፃናትም አመስግነውታል፡፡ አዋቂዎችም ሕፃናትም “ሆሣዕና በአርያም” እያሉ ማመስገናቸው “መድኃኒት መባል ለአንተ ይገባሃል” ማለታቸው ነው።
በበዓለ ሆሣዕና ከሚነሳው ታሪክ ውስጥ የአህያዋና የውርንጫዋ ጉዳይ ነው፡፡ ጌታችን ኪሩቤል በሚሸከሙት ዙፋን የሚቀመጥ አምላክ ሲሆን ትሁት ሆኖ በአህያ ላይ ተቀመጠ፡፡ አህያዋን ከነውርንጫዋ “ፈታችሁ አምጡልኝ” ማለቱ የሰውን ልጅ ከኃጢአት እሥራት ለመፍታት የመጣ አምላክ መሆኑን ያመለክተናል፡፡ ደቀ መዛሙርቱም አህዮቹን ፈተው ማምጣታቸው ሥልጣነ ክህነታቸውን ያመለክታል፡፡ “በምድር የፈታችሁት በሰማይ የተፈታ ይሁን” እንዲል፡፡
በአህያ ላይ ልብሳቸውን ማንጠፋቸው የምትመች የማትቆረቁር የወንጌልን ሕግ ሰጠኸን ሲሉ ነው፡፡ በአህያ የተቀመጠ ሰው በፈረስ እንደተቀመጠ ሰው ፈጥኖ አያመልጥም። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከፈለጉኝ አያጡኝም ሲል በአህያ ተቀምጧል፡፡
ከኢየሩሳሌም እስከ ቤተ መቅደስ ፲፮ ምዕራፍ ነው፡፡ ፲፬ቱን በእግሩ ሄዶ ሁለቱን በአህያዋ፣ በውርንጫይቱ ደግሞ ሦስት ጊዜ ቤተ መቅደሱን ዞሯል፡፡ ይህም የሦስትነቱ ምሳሌ፣ አሥራ አራቱን በእግሩ መሄዱ አሥርቱ ትእዛዛትን፣ አራቱ ደግሞ የአራቱ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ ኖኅ፣ ክህነተ መልከ ጼዴቅ፣ ግዝረተ አብርሐም እና ጥምቀተ ዮሐንስን ያመለክተናል፡፡
ከግለሰብ ደጅ የተፈታችን አህያ “ጌታዋ ይፈልጋታል” ብሎ ያስፈታት በፈጣሪነቱ ወይም ስለፈጠራት ገንዘቡ ስለሆነች ነው፡፡ አህያን ያልናቀ አምላክ እኛም ከኃጢአት ርቀን ብንፈልገው ማደሪያዎቹ ሊያደርገን ፈቃዱ ነው፡፡ የአህያዋን መፈታት የፈለገ ጌታ እኛም ወደ ካህናት ቀርበን ኃጢአታችንን ተናዘን ከበደል እሥራት እንድንፈታ ይፈልጋልና፡፡
ሆሣዕና ከረቡዕ ጀምሮ የሚታሰብ ታላቅ የቤተ ክርስቲያን የበዓል ቀን እንደሆነ ይታወቃል። በዋዜማዎቹ ዕለታት ከቅዱስ ያሬድ ድርሰት ከሆነው ከጾመ ድጓ
ሆሣዕና በአርያም፣ ሆሣዕና ለወልደ ዳዊት …በማለት ይዘመራል፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ ሕዝቡ ዘንባባ ይዘው
ቡርክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር፤ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረክ ነው።’’ (መዝ. ፻፲፯፥፳፮)
በማለት ስለተቀበሉት ይህን በማሰብ ቤተ ክርስቲያናችን ዘንባባ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ታድላለች፤ በቤተ ክርስቲያን በአራቱም ማዕዘናት ከአራቱም ወንጌል ዕለቱን የሚመለከቱ ምንባባት ይነበባሉ፡፡ ከቅዱስ ማቴዎስ (ማቴ. ፳፩፥፩-፲፯)፤ ከቅዱስ ማርቆስ (ማር. ፲፩፥፩-፲)፤ ከቅዱስ ሉቃስ (ሉቃ.፲፱፥፳፱-፴፰)፤ ከቅዱስ ዮሐንስ (ዮሐ. ፲፪፥፲፪-፳)።
በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሐት ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሐት የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወቅታዊ ትምህርት ክፍል | 445 |
| 20 | ዘሆሳዕና
ማቴ ም. ፭ ቁ. ፲፩ - ፴፩
“እርሱም መልሶ፥ “ያዳነኝ እርሱ፦ አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለኝ” አላቸው። "አይሁድም፥ “አልጋህን ተሸክመህ ሂድ ያለህ ሰውዬው ማነው?” ብለው ጠየቁት። "ያ የተፈወሰው ግን ያዳነው ማን እንደሆነ አላወቀም፤ ጌታችን ኢየሱስ በዚያ ቦታ በነበሩት ብዙ ሰዎች መካከል ተሰውሮ ነበርና። ከዚህም በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ያን የዳነውን ሰው በቤተ መቅደስ አገኘውና፥ “እነሆ፥ ድነሃል፤ ግን ከዚህ የባሰ እንዳያገኝህ ዳግመኛ እንዳትበድል ተጠንቀቅ” አለው። ያም ሰው ሄዶ ያዳነው ጌታችን ኢየሱስ እንደሆነ ለአይሁድ ነገራቸው። ስለዚህም አይሁድ ጌታችን ኢየሱስን ያሳድዱትና ሊገድሉትም ይሹ ነበር፤ በሰንበት እንዲህ ያደርግ ነበርና። ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፥ “አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል፤ እኔም እሠራለሁ” አላቸው። ስለዚህም አይሁድ ሊገድሉት በጣም ይፈልጉ ነበር፤ “ሰንበትን የሚሽር ነው” በማለት ብቻ አይደለም፤ ደግሞም እግዚአብሔርን “አባቴ ነው ይላል፤ ራሱንም ከእግዚአብሔር ጋር ያስተካክላል” በማለት ነው እንጂ
ከዚህም በኋላ ጌታችን ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አላቸው፥ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ ወልድ ከራሱ ብቻ ምንም ሊያደርግ አይችልም፤ አብ ሲያደርግ ያየውን ነው እንጂ፤ ወልድም አብ የሚሠራውን ያንኑ እንዲሁ ይሠራል። አብ ልጁን ይወዳልና የሚሠራውንም ሥራ ሁሉ ያሳየዋል፤ እናንተም ታደንቁ ዘንድ ከዚህ የሚበልጥ ሥራን ያሳየዋል። አብ ሙታንን እንደሚያስነሣቸው፥ ሕይወትንም እንደሚሰጣቸው እንዲሁ ወልድም ለሚወድዳቸው ሕይወትን ይሰጣል። አብ ከቶ በማንም አይፈርድም፤ ፍርዱን ሁሉ ለወልድ ሰጠው እንጂ። ሰዎች ሁሉ አብን እንደሚያከብሩ ወልድን ያከብሩ ዘንድ፤ ወልድን የማያከብር ግን የላከውን አብን አያከብርም። "እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ በላከኝም የሚያምን የዘለዓለም ሕይወትን ያገኛል፤ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይሄድም። “እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ ሙታን የእግዚአብሔርን ልጅ ቃል የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል፤ እርሱም አሁን ነው፤ የሚሰሙትም ይድናሉ። “ለአብ በራሱ ሕይወት እንዳለው: እንዲሁም ደግሞ ለወልድ በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጠው። የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ነውና ይፈርድ ዘንድ ሥልጣንን ሰጠው።
“በመቃብር ያሉ ሁሉ ቃሉን የሚሰሙባት ጊዜ ትመጣለችና ስለዚህ አታድንቁ። “መልካም የሠሩ ለሕይወት ትንሣኤ፥ ክፉ የሠሩም ለፍርድ ትንሣኤ ይነሣሉ። እኔ ከራሴ አንዳች አደርግ ዘንድ አልችልም፤ እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ እንጂ፤ ፍርዴም እውነት ነው፤ የላከኝን ፈቃድ እንጂ የእኔን ፈቃድ አልሻምና....
መልዕክታት
ዕብ ም. ፱ ቁ. ፲፩ - ፍጻሜ
፩ ጴጥ ም.፬ ቁ. ፩ - ፲፪
ሐዋ.ሥራ ም. ፳፰ ቁ. ፲፩ - ፍጻሜ
ምስባክ
መዝሙር 8:2-3
እም አፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሓተ
በእንተ ጸላኢ
ከመትንስቶ ለጸላኢ ወለገፋኢ
ትርጉም
ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ
ስለ ጠላትህ
ጠላትንና ቂመኛን ለማጥፋት
ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ | 351 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
