ch
Feedback
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

前往频道在 Telegram
5 357
订阅者
无数据24 小时
-97 天
+730 天
帖子存档
የሙያ ብቃት ምዘና የብዙ ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ ሁላችንም የየራሳችንን ሃላፊነት መወጣት ይገባናል ተባለ፡፡ (ጳጉሜ 1 ቀን 2017 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህ
+5
የሙያ ብቃት ምዘና የብዙ ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ ሁላችንም የየራሳችንን ሃላፊነት መወጣት ይገባናል ተባለ፡፡ (ጳጉሜ 1 ቀን 2017 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ስትራቴጂክ ካውንስል አባላት በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘት የሙያ ብቃት ምዘና ስራ የመስክ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የምዘና ዘርፍ ሃላፊ እንደገለጹት የምዘና ስራውን የባለስልጣኑ ስትራቴጂክ ካውንስል፣ የቅ/ጽ/ቤት ሃላፊዎች እንዲሁም የምዘና ዘርፍ ባለሙያዎች በየጊዜው የሚገመግሙት መሆኑን ጠቅሰው በግምገምው በምዘና ሂደቱ ላይ ያለውን ጠንካራና ደካማ ጎን በመለየት መፈታት ያለባቸውን ችግሮች እየፈቱ ለመሄድ የሚያስችል መሆኑን ገልጸው ስራዎች እንዴት በተግባር እየተሰሩ መሆናቸውን ለመመልከት የመስክ ጉብኝቱ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ የመስክ ጉብኝቱ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኮንስትራክሽን እና በICT ሙያዎች ላይ የተግባርና የንድፈሃሳብ ምዘና ምልከታ የተደረገ መሆኑን ጠቅሰው ምዘናው በግብዓት የተሟላ እንደነበረና የምዘና ሂደቱ መልካም እንደነበር ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም እንደዚህ ያለው ጉብኝትና የመስክ ምልከታ ቀጣይነት ባለው መልኩ በሁሉም የምዘና ጣቢያዎች ላይ እንደሚደረግና ክትትልና ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

ጳጉሜ 1 - የጽናት ቀን ጳጉሜ 1፣2017 "ጽኑ መሰረት ብርቱ ሀገር" በሚል አገራዊ መሪ ቃል የጽናት ቀን ይከበራል። መሪ ቃሉ በጽናት ላይ የተገነባ ሀገር ጠንካራ እና ለየትኛውም ጊዜያዊ ፈተና የማይበገር ፣ እጅ የማይሰጥ በመጨረሻም ድል አድራጊ መሆኑን ያሳያል። ፅናት ለእኛ ኢትዮዽያውያን እንደ ቡናችን ፣ እንደ አባይ ወንዛችን አንዱ መገለጫችን ነው። በጦርነት አዉድማ ቀደምቶቻችን በአድዋ ፣ በማይጨው፣ አትሌቶቻችን ደግም በስፓርት ሜዳ ፅናትን አሳይተውናል። የቅርቡን እንኳን ብንመለከት በህዳሴ ግድባችን የባዳና ባንዳው ጥምረት እንዳለ ሆኖ ለ 13 ጊዜ ያህል በፀጥታው ምክር ቤት አጀንዳ ስንሆን ፣ ከዉስጥም ከዉጪም የተቀናጁ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን ዛሬ ግድባችንን ጨርሰን የደረስንበት የታሪክ እጥፋት ከመሪ እስከ ህዝብ ያለንን ፅናት ለዓለም ህዝብ ያሳየንበት ነው። በስንዴ አብዮት ፣ በአረንጓዴ አሻራ ጭምር የስኬታችን ዋነኛው ሚስጥር የመሪዎቻችንና መሪውን የተከተለዉ ህዝብ ፅናት ነው ። በጽኑ መሰረት ላይ የተገነባ ከተማ ያለማቋረጥ ወደፊት ይገሰግሳል ፤ የትኛዉም ምድራዊ ሀይል ካለመበት አያስቀረውም፣ በአዲስ ሀይል አዳዲስ ስኬቶችን ይጨብጣል ። በከተማችን በ2017 ዓ.ም የታየው ፣ ዓለምን ያስደነቀው ፣ አዲስ አበባን አዲስ እና አበባ ያደረገው ስር ነቀል መልሶ ማልማት ፣ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻዎች ልማት ፣ የገቢ አሰባሰብ ፣ የሰላምና ፀጥታ ወዘተ በርካታ ተግባራት ፣ እንዲሁ በቀላሉ የተገኘ ውጤት አይደለም፤ ይልቁኑ በፅናት በመጓዝ የተገኘ እንጂ። ፈተና ሳይኖር ቀርቶ አይደለም ፣ በሚሊዮን የሚቆጠር የከተማችን ነዋሪ ተሳትፎ ፣ በፅናት የተቀናጀ የአመራር ሰጪነት የታየበት ተጨባጭ ውጤት ፣ የጠንካራ ፅናታችን ውጤት በመሆኑ በአዲሱ የ2018 ዓመትም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። በዛሬዉ እለት የጽናት ቀንን ስናከብርም ለሀገራችን እና ለከተማችን ሁለንተናዊ ብልጽግና እንደ ከዚህ ቀደሙ የትኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ያለንን የማይናወጥ ጽናት ዳግም በማረጋገጥ መሆን ይኖርበታል። አመሰግናለሁ ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የጽናት ቀን ጽኑ መሠረት ብርቱ ሀገር ኢትዮጵያ ብልጽግናዋን የምታረጋግጠው መሠረቷን ለማጽናት በሚችሉ ብርቱ እጆች ነው፡፡ በሁሉም ዘርፎች በምናደርገው ተጋድሎ የኢትዮጵያን መሠረት እናጸናለን፡፡ ለማና
የጽናት ቀን ጽኑ መሠረት ብርቱ ሀገር ኢትዮጵያ ብልጽግናዋን የምታረጋግጠው መሠረቷን ለማጽናት በሚችሉ ብርቱ እጆች ነው፡፡ በሁሉም ዘርፎች በምናደርገው ተጋድሎ የኢትዮጵያን መሠረት እናጸናለን፡፡ ለማናቸውም ችግሮች የማትበገር፣ ፈተናዎችን ወደ ዕድል የምትቀይር፣ በመጪው ዘመንም ከዓለም ኃያላን ተርታ የምትሰለፍ ብርቱ ሀገር በደምና በላብ እንገነባለን፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አቶ ደረጀ ሙሉጌታ የቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ የታየው የደረጃ መሻሻል ጥሩ የሚባል መሆኑን በመግለጽ ስታንዳርዶችንና አመላካቾችን በመረዳትና ለኢንስፔክሽን ውጤት ትልቅ ትኩረት በመስጠት እንዲሁም በትኩረት በመስራትና ሊስተካከሉ የሚገባቸውን ጉዳዮች በመለየት እና ትኩረትና ጥረት በማድረግ የተቋማቶቻችንን ደረጃ ልናሻሽል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ከቤቱ ለተነሱ ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄዎች ምላሽ የተሰጠ ሲሆን በኢንስፔክሽን ምልከታ የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ተቋማትም የእውቅና ሰርተፍኬት ተሰጥቷቸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9

የት/ት ስራ የብዙ ባለድርሻ አካላትን የነቃ ተሳትፎ፣ በቅንጅት መስራትን እንዲሁም ሀገርን የመገንባት ከፍተኛ የኃላፊነት ስሜትን የሚጠይቅ ዘርፍ እንደመሆኑ በአብሮነት በመስራት የትምህርት ተቋማትን የ
+4
የት/ት ስራ የብዙ ባለድርሻ አካላትን የነቃ ተሳትፎ፣ በቅንጅት መስራትን እንዲሁም ሀገርን የመገንባት ከፍተኛ የኃላፊነት ስሜትን የሚጠይቅ ዘርፍ እንደመሆኑ በአብሮነት በመስራት የትምህርት ተቋማትን የተወዳዳሪነት ደረጃ ማሻሻል ያስፈልጋል ተባለ፡፡ (ነሃሴ 30 ቀን 2017 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የየካ ቅ/ጽ/ቤት የ2017 ዓ.ም የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ውጤት ትንተና ሪፖርት ለባለድርሻ አካላት አቅርቧል፡፡ አቶ አጥላው ዘውዴ የቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ተወካይ ቡድን መሪ ሲሆኑ የ2017 በጀት ዓመት የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ትንተና ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የ2017 ዓ.ም የአጠቃላይ ት/ት ተቋማት የኢንስፔክሽን ውጤት ትንተና፣የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የ2017 ዓ.ም የኢንስፔክሽን ውጤትና ንጽጽር፣የኢንስፔክሽን አፈጻጸም ከት/ት ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ አንጻር፣የስታንዳርዶች አፈጻጸም፣የኢንስፔክሽን ትንተና ዋና ዋና ግኝቶች በኢንስፔክሽን ትግበራ ሂደት የታዩ ጥንካሬዎችና ያጋጠሙ ችግሮች እንዲሁም ምክረ ሀሳቦችን ዝርዝር ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት ከዕቅዱ አንፃር በዋናነት በኢንስፔክሽን ሞዳሊቲዎች በተለያየ እርከን የሚገኙ ት/ቤቶች 35 ቅ/አንደኛ፣30 አንደኛና መካከለኛ፣ 2 አማራጭ እና 3 ኦ-ክፍል በድምሩ 70(100%) ስታንዳርድ ኢንስፔክሽን በማከናወን ዕቅዱን ማሳካት ተችሏል ብለዋል፡፡

የ2017 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች ይከበራል #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance
የ2017 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች ይከበራል #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!! የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን #ፌስቡክ;https://www.fa
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!! የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ለአቅመ ደካሞች አለንላችሁ በማለት የሚሰሩ እጆች ሊበረታቱ እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡ (ነሀሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የጉለሌ ቅ
+7
ለአቅመ ደካሞች አለንላችሁ በማለት የሚሰሩ እጆች ሊበረታቱ እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡ (ነሀሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጠቅላላ ካውንስል ባለስልጣኑ እያስገነባ ያለውን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ያለዉን የአቅመ ደካማ የሕብረተሰብ ክፍሎች የቤት ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ ጉብኝት አደረገ፡፡ ቅ/ጽ/ቤቱ ከዚህም ሌላ የቤቱን ግንባታ ለሚሠሩ ሠራተኞች የቅ/ጽ/ቤ/ቱ ሶሻል ኮሚቴ እና የሠራተኞች ካፌ በጋራ በመሆን የምሳ ግብዣ በማድረግ የማበረታታት ስራ ተሰርቷል፡፡ ግንባታው በአሁኑ ሰዓት በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ በፍጥነት እየተሰራ መሆኑ ታውቋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

አቶ ሰለሞን አለማየሁ የባለስልጣኑ አማካሪ በመርሃ-ግብሩ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት በብዙ ማጋራት ያተርፋል በመሆኑም በስራዎቻችን ላይ በየጊዜው ስንነጋገርና ሃሳብ ስናካፍል ችግሮቻችንን በመለየት መፍትሄ እናመጣለን በመሆኑም ያለንን ሃሳብ እውቀትን መሰረት አድርገን እናጋራ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በቀረበው ሃሳብ ላይ በርካታ ሃሳቦች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡ (ነሀሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ
+5
የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡ (ነሀሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር "የዕውቀት አመራር ስትራቴጂ" በሚል ርዕስ ተካሂዷል፡፡ አቶ ዳባ ጉተታ በባለስልጣኑ የትምህርት ምዘናና ምርምር ጥናት ቡድን ባለሙያ "የዕውቀት አመራር ስትራቴጂ"በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ለዕውቀት መነሻ የሚሆኑት ጥሬ መረጃ፣ የተተነተነ መረጃ (Information)፣የተተነተነ መረጃ ደግሞ ወደ ዕውቀት ደረጃ እንደሚያደርስ የገለጹ ሲሆን የእውቀት አይነቶች በግለሰቦች ውስጥ እምቅ ሆኖ ያለ እውቀት፣የተጻፈና የሚታወቅ እውቀት የእውቀት አመራር ማለት እነዚህን አቀናጅቶ መጠቀም ማለት እንደሆነና ለመጠቀም ደግሞ ኡደትን መከተል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡እውቀትን መፍጠር ፣ መለየት፣ማጥራት፣ ማከማቸት መጠቀምና ማሳውቅ ባለተቋረጠ ሁኔታ መከናወን ያለባቸው የኡደቱ ሂደቶች መሆናቸውን አስገንዝበዋል፡፡

ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አመራሮችና ሰራተኞች መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ፡፡
ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አመራሮችና ሰራተኞች መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ፡፡

በአጠቃላይ በእስካሁን የኢንስፔክሽን አፈፃፀም በቅርንጫፉ ውስጥ ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካከል 253(90.35%) ትምህርት ቤቶች የኢንስፔክሽን አገልግሎት ያገኙ ሲሆኑ የደረጃ አፈፃፀማቸውም 0(0.0%) ደረጃ 1፣147(58%) ደረጃ 2፣ 106(42%) ደረጃ 3 እና 0 (0.0%) ደረጃ 4 መሆናቸውን በሠነዱ ተመላክቷል፡፡ በተሰጣቸው ግብረ መልስ መሠረት የደረጃ ሽግግር በትምህርት ተቋማቱ ላይ ከጊዜ ወደጊዜ መሻሻልን ማሳየቱን በሰነዱ ተገለጸ ሲሆን ማሻሻል ማሳየታቸው መልካም የሆኑ ግኝቶች መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡ በዕለቱ በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን በኢንስፔክሽን ግኝት የተሻለ አፈጻጸም ያመጡ የትምህርት ተቋማት እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የኮልፌ ቀራንዩ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የኢንስፔክሽን ትምህርት ምዘና ዳይሬክቶሬት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ፡፡ (ነሃሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም)የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የኮልፌ ቀ
+3
የኮልፌ ቀራንዩ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የኢንስፔክሽን ትምህርት ምዘና ዳይሬክቶሬት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ፡፡ (ነሃሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም)የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የኮልፌ ቀራንዩ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2017ዓ.ም የትምህርት ቤቶች የኢንስፔክሽን ትግበራ ውጤት ትንተና በማስመልከት በተካሄደው ውይይት መድረክ ላይ የውጤት ትንተናውን ሠነድ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የኢንስፔክሽን ትምህርት ምዘና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ ሀፍቱ ገ/ሚካኤል ቀርቧል፡፡ በሠነዱም እንደተመላከተው የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ ትምህርት ቤቶች ያሉበትን ተጨባጭ ሁኔታ በ4 የትኩረት መስኮች ላይ ባተኮሩ በ3 መለኪያዎች ፣ በ24 እና 28 ስታንዳርዶች፣ 83/80 አመልካቾች እና 259/246 መስፈርቶች መሰረት በማድረግ የትምህርት ግብዓቱንና ሂደቱን በማሻሻል ተማሪዎች የላቀ የትምህርት ውጤት እንዲያስመዘግቡ ለማድረግ በ2017 የኢንስፔክሽን ምዘናን ተግባራዊ መደረጉን ተገልጿል፡፡ በዋነኝነት የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት መማር ማስተማሩ በተገቢው መመራቱን ፣ጥራቱን ጠብቆ እየተከናወነ መሆኑን በመፈተሽ፣እንደ ተቆጣጣሪ አካልም ለማወቅ ፣ለሚመለከተው አካል ግብረ መልስ ለመስጠት፣ ለውሳኔ ሰጪ አካላት የተደራጀ መረጃ ለማቅረብ እና ለቀጣይ መሻሻል ያለባቸውን ነጥቦች ለማመላከት እና ለማሳወቅ ግብረ መልስ እና የተተነተነ ሪፖርት በማዘጋጀት ወሳኝ በመሆኑ የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ትንተና ሰነድ መዘጋጀቱ ተጠቅሷል፡፡

የድጋፍና ክትትል ቡድኑ አባላት እንደገለጹት ባለስልጣኑ በዝግጅት ምዕራፍ የሚደረግለት ክትትልና ድጋፍ ለተግባር ምዕራፍ መነሻ በመሆን ስራዎችን በተገቢው መንገድ ለማከናወን እንደሚረዳ ገልጸው በተሰጠው አስተያያት መሰረት በቀሪ ጊዜያት ስራዎችን ለማከናወን ድጋፍና ክትትሉ የሚያግዘው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የምዘና ዘርፍ ሃላፊ እንደገለጹት የተሰጡት አስተያየቶች ተገቢ መሆናቸውን አንስተው ቀሪ ጊዜያቶችን የተሻለ ስራ ሰርተን ውጤታማ እንድንሆን የሚያግዘን ይሆናል ብለዋል፡፡ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የጥራት ዘርፍ ሃላፊ በማጠቃለያው እንደገለጹት ተቋሙ እንዲሻገር የሚደረግለት ክትትልና ድጋፍ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው የቅድመ ዝግጅት ስራ ለተግባር ምዕራፍ ወሳኝ በመሆኑ በተሰጡን አስተያየቶች መሰረት ከዛሬ ጀምሮ ወስደን ተግባራዊ የምናደርግ ይሆናል ብለዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ባለስልጣኑ ከከንቲባ ጽ/ቤት በመጡ የድጋፍና ክትትል ቡድን አባላት ድጋፍና ክትትል ተደረገለት፡፡ (ነሃሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም)የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከከንቲባ ጽ/ቤት በመጡ
+5
ባለስልጣኑ ከከንቲባ ጽ/ቤት በመጡ የድጋፍና ክትትል ቡድን አባላት ድጋፍና ክትትል ተደረገለት፡፡ (ነሃሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም)የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከከንቲባ ጽ/ቤት በመጡ የክትትልና ድጋፍ ቡድን አባላት በ2018 የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ላይ ድጋፍና ክትትል አድርገዋል፡፡ የድጋፍና ክትትል ቡድኑ ባለስልጣኑ በ2018 የዝግጅት ምዕራፍ ከእቅድ አዘገጃጀት፣ቅንጅታዊ ስራዎች፣መልካም አስተዳደር ስራዎች ብልሹ አሰራርን መለየትና ማክሰሚያ መንገዶቹ ላይ ያከናወናቸው ስራዎች በተመለከተ ፣የቀረቡ ቅሬታዎችና የተፈቱበት አግባብ እንዲሁም ከ90 ቀናት ልዩ እቅድ አንጻር በዝግጅት ምእራፍ የተከናወኑትን ተግባራት በተዘጋጀው ቼክሊስት መሰረት ዝርዝር ጉዳዩችን የመረጃ፣የሰነዶች ምልከታ እንዲሁም ማብራሪያ የጠየቁ ሲሆን ለተነሡት ጥያቄዎች የስራ ክፍል ሃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

የባለስልጣኑ የኮልፌ ቀራንዩ ቅ/ጽ/ቤት የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በ2017 በጀት ዓመት ባደረገው ምዘና 1ኛ በመሆን እው
+2
የባለስልጣኑ የኮልፌ ቀራንዩ ቅ/ጽ/ቤት የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በ2017 በጀት ዓመት ባደረገው ምዘና 1ኛ በመሆን እውቅና ተሰጠው፡፡ (ነሃሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በ2017 በጀት ዓመት ባደረገው የእቅድ አፈጻጸም በከተማው ካሉ ቅርንጫፍ ተቋማት የስነ ምግባር መከታተያ ክፍሎች የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የኮልፌ ቀራንዩ ቅ/ጽ/ቤት የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት 1ኛ በመውጣት የምስክር ወረቀትና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡ ዳይሬክቶሬቱ ለዚህ ውጤት እንዲበቃ አስተዋጽኦ ለነበራቸው የቅ/ጽ/ቤቱ ማኔጅመንትና ስራ እሰኪያጅ ምስጋና ያቀረቡት አቶ ሚርቄ ሚዶ የቅ/ጽ/ቤቱ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የተሰጠው እውቀናና ሽልማት በቀጣይ ስራዎች ላይ አቅም በመሆን የላቀ አፈጻጸምን ለማስቀጠል ስንቅ እንደሚሆንና በቀጣይም በተሻለ መነሳሳት ስራዎችን በጋራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የክትትል እና ቁጥጥር ስራው በዋናነት በአጠቃላይ ቁልፍ ስራዎች በተለይም ሰው ተኮር የ90 ቀን እቅድ፣መሪ እቅድ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የአቻ ፎረም አደረጃጀት እና የወርቃማ ሰኞ አፈጻጸም እና አተገባበር በትኩረት እንደሚታይ ገልጸዋል፡፡እንዲሁም ቁልፍ ጥራዎች በአግባቡ ታቅደው መሄዳቸው በተግባር ምዕራፍ ላይ ትልቅ ጠቀሜታ ስላለው በዚህም መሰረት ማስተካከያዎች፣ ግብረ-መልስ እና ምክረሃሳቦች እንደሚሰጥባቸውም ተናግረዋል፡፡በሌላ በኩል ክትትል እና ቁጥጥር ከሚደረግበት ተግባር ውስጥ ምዘና፣ የእውቅና ፍቃድ እድሳት እና ኢንስፔክሽን ስራዎች ሲሆኑ በተለይም ቅድመ ዝግጅት ስራዎች፣ከአፈጻጸም አኳያ እና ስራዎች ያሉበት ደረጃ ምን እንደሚመስል በክትትልና ቁጥጥር ስራው እንደሚቃኝ ገልጸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc