ch
Feedback
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

前往频道在 Telegram

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

显示更多

📈 Telegram 频道 Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council 的分析概览

频道 Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council (@eiasc1) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 11 287 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 8 059,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 961

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 11 287 名订阅者。

根据 27 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -74,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 17.17%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.89% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 938 次浏览,首日通常累积 1 116 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

凭借高频更新(最新数据采集于 28 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

11 287
订阅者
-224 小时
-267
-7430
帖子存档
ለክልል መጅሊስ ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽነሮች የስልጠናና ምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ ተጀመረ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 28 /2018 ዓ.ል| ሙሀረብ 20/1448 ዓ.ሂ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዳማ | ​የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን ከ"ጋይድ ላይት ኮንሰልቲንግ" ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የአቅም ግንባታና የእርስ በእርስ ልምድ ልውውጥ መድረክ በአዳማ ከተማ ተጀምሯል። ለሦስት ቀናት በሚቆየው በዚህ መርሐ ግብር ላይ ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡ የመጅሊስ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽነሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። የአቅም ግንባታ ስልጠናውንና የምክክር መድረኩን በይፋ ያስጀመሩት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንትና የዑለማእ ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ የተከበሩ ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ናቸው። ​ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው በ2017 ዓ.ም "ምርጫችን በመስጂዳችን" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ሀገራዊ የመጅሊስ ምርጫ በምሁራን ዘርፍ በርካታ አዳዲስ ምሁራንና ባለሙያዎች የመጅሊስ የአመራር መዋቅሮችን መቀላቀላቸውን አስታውሰዋል። ​ፕሬዝደንቱ የአቅም ግንባታ ስልጠናው ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርገው በመጅሊሱ ውስጥ መስተካከል ያለባቸውን ክፍተቶች ለመድፈን ስህተቶችን ለማረምና ዘመኑን የዋጀ አሰራርን ለማስረጽ ትልቅ በር የሚከፍት መሆኑን ገልጸው ይህ ስልጠና በተለያዩ ክልሎች መካከል ያሉ መልካም ተሞክሮዎችን በመጋራት የጋራ አቅምን ለመገንባት መልካም አጋጣሚ መሆኑን ተናግረዋል። የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት በመልክታቸው መጨረሻ በስልጠናው የተገናኙት ባለሙያዎች ተቋሙን ወደ ላቀ ደረጃ እንዲያሸጋግሩ ጥሪ አቅርበው ለሥራቸው ስኬታማነት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል። በዚህ የስልጠና መረሀ ግብር ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሸይኽ ኤልያስ አወል የስልጠናውን ዋና ዓላማና አስፈላጊነት በሰፊው አብራርተዋል። ተቋሙን ዘመናዊ ለማድረግ አዲስና ሰፊ የሰው ኃይል አደረጃጀት የተፈጠረ ሲሆን፣ የሐጅና ዑምራ ኮሚሽን በገለልተኝነትና ራሱን ችሎ መቋቋሙ ለዚህ ስኬት ዋነኛው የለውጥ መነሻ መሆኑ ገልጸዋል። ኮሚሽኑ በደረጃው እንዲደራጅ የሚያስችለው ማቋቋሚያ ደንብ፣ መመሪያና መተዳደሪያ ደንብ ተዘጋጅተው በጠቅላይ ምክር ቤቱ እንዲጸድቁ መደረጉን መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ገልጸዋል። ​ የተጀመረው አገራዊ የለውጥ አጀንዳ ግቡን እንዲመታና የሕዝበ ሙስሊሙን ተጠቃሚነት እንዲያረጋግጥ ሁሉም ክልሎችና አጋር አካላት በኅብረትና በጋራ እንዲሠሩ ጥሪ ቀርበዋል። በመጨረሻም በክልል መጅሊሶች ደረጃ የሚስተዋሉ የፋይናንስ አያያዝ፣ የንብረት አስተዳደርና የኦፕሬሽን አሠራር ክፍተቶችን በዘላቂነት ለመሙላት ዘመኑን የዋጀ አሰራርን ለማስረፅ እንዲህ ያሉ የስልጠና መድረኮች ወሳኝ መሆናቸው አስታውሰዋል። ​ይህ መድረክ ተሳታፊዎቹ በስልጠናው የሚያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር፣ በየክልሎቻቸው የሚገኙትን የመጅሊስ መዋቅሮች የአሠራር ጥራትና ታማኝነት ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል። በስልጠናው የመክፈቻ ስነስረአት ላይ የተከበሩ ኡስታዝ አብዱልቃድር ማህ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሐጅ እና ዑምራ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ምክትል ኮሚሽነር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤትን ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ይከታተሉ | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

ኢማም አል ሻፊኢ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ ከኒዳዑል ኢህሳን አል ኸይሪያ ዓለም አቀፍ ተራዕዶ ድርጅት ጋር በመተባበር በተያዩ የሸሪዓ የዕውቀት ዘርፎች ያሠለጠናቸውን ስድስት መቶ ሠልጣኞችን አስመረቀ። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 25 /2018 ዓ.ል| ሙሀረም 17 /1447 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዳማ | ኢማም አል ሻፊኢ ኢስላማዊ ዩንቨርስቲ ከኒዳዑል ኢህሳን አል ኸይሪያ ዓለም አቀፍ ተራዕዶ ድርጅት ጋር በመተባበር ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተመለመሉ ኢማሞችን፣ ዱዓቶችንና ቃዲዎችን በተያዩ የሸሪዓ የዕውቀት ዘርፎች አሰልጥኖ አስመረቀ። የኢማም አል ሻፊኢ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ መስራችና የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር ኢማም አል ሻፊኢ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፎ እዚህ በመድረሱ መደሰታቸውን ገልጸው ለዚህ ስኬት አስተዋጽኦ ለነበራቸው ባለ ድርሻ አካላት ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል። በተያዩ ሸሪዓዊ ዕውቀቶች የአቅም ግንባታ ክህሎት ሥልጠና ያጠናቀቁ የዛሬ ተመራቂዎች በስልጠናው ያገኙትን ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር ሕዝበ ሙስሊሙን እንዲያገለግሉም ፕሬዝደንቱ አዳራ ብለዋል። የጠቅላይ ምክር ቤቱ የዑለማ ጉባዔ የፈተዋ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ሸይኽ ጀይላን ኸድር በበኩላቸው ጉባዔው በተያዩ የሸሪዓ ዕውቀት ዘርፎች የሰለጠነ የሰው ኃይል ለመፍጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ ታጁዲን ኸድር በምርቃት መርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት ኢማም አል ሻፊኢ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ በሸሪዓ ዘርፍ በመጀመሪያ ዲግሪ የሰለጠነ የሰው ኃይልን እያፈራ የሚገኝ አንጋፋ የሸሪዓዊ ትምህርት ተቋም ነው። ዩኒቨርስቲው እየሰጠ ያለውን ተከታታይ ስልጠና አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማ ጉባዔ አባልና የትምህርትና ካሪኩለም ዘርፍ ኃላፊ ተባባሪ ፕሮፌሰር አብደላ ኸድር ናቸው። የኢማሙ አል ሻፊኢ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንት ፕሮፌሰር ሙሀመድ ከማል ቲልሞ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በሀገራችን ያለውን የኢልም ሽግግር ከማስቀጠል ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰው ዩንቨርስቲው ከመደበኛ ስራው ባሻገር ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የመህበረሰብ ክፍሎች ከሃያ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ድጋፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሆነ ተናግረዋል። ዋና መቀመጫውን አዳማ ከተማ አድርጎ ለዓመታት በርካታ ተማሪዎችን በተለያዩ ኢስላማዊ ትምህርቶች በማስተማር ላይ የሚገኝ ዩንቨርስቲው በዘንድሮው የትምህርት ዘመንም በአራት ፋኪሊቶዎች 300 ወንዶችን እና 205 ሴት ሰልጣኞችን በዲግሪ መርሀ ግብር ተቀብሎ እያስተማረ ይገኛል። በስልጠናው ከፍተኛ ውጤት ላስመዝገቡ ሶስት ሰልጣኞች ነጻ የዑምራ ሽልማት የተሰጣቸው ሲሆን በምርቃት መርሀ ግብሩ ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የዑለማእ ጉባዔ ዘርፍ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ ጁነይድ ሐምዛ ዩሱፍን ጨምሮ የዩንቨርስቲው እንዲሁም የፌዴራል እና የክልል መጅሊስ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ታላላቅ ዑለማዎች፣ ዑስታዞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤትን ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ይከታተሉ | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የዓረብኛ ቋንቋ በሀገሪቱ ስርዓተ ትምህርት ውስጥ እንዲካተት የባለበድርሻ አካላት የተቀናጀ ስራ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 23 /2018 ዓ.ል| ሙሀረም 15 /1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ | የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ጥናትና ምርምር ፎረም በቅንጅት "ዓረብኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ትላንትና ዛሬ፣ ብሩህ ተስፋዎችና ተግዳሮቶች" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጁት የዓረብኛ ቋንቋን ታሪካዊና አሁናዊ ፋይዳ የሚዳስስ የፓናል ውይይት ተካሄደ። ​ውይይቱን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በንግግር አስጀምረውታል። ፕሬዝደንቱ በንግግራቸው የዓረብኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በበርካታ ዘርፎች ደማቅ አሻራ አሳርፏል ብለዋል። ​ቋንቋው የሚናውን ያህል ተገቢ ትኩረት አልተሰጠውም ያሉት ፕሬዝደንቱ ዓረብኛ ቋንቋ በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ካለው የላቀ ፋይዳ አንጻር በኢትዮጵያ ስርዓተ ትምህርት ውስጥ እንዲካተት ጠቅላይ ምክር ቤቱ አቅዶ እንደሚሰራ ገልጸዋል። ​ ​በውይይቱ ላይ ረዳት ፕሮፌሰር ዑስታዝ ሙሐመድ ሰዒድ "የዓረብኛ ቋንቋ ታሪካዊ የጉዞ ለውጥ በኢትዮጵያ እና ሀገራዊ ፋይዳው"፣ ዶ/ር አብደላህ ኸድር "ተቋማዊ ትግበራዎች እንዲሁም ረዳት ፕሮፌሰር አብዱልዓዚዝ ሁሴን "ዓረብኛ በኢትዮጵያ ስርዓተ ትምህርት የፖሊሲ ማዕቀፍ ውስጥ የሚሉ ሶስት ጥናታዊ ጽሁፎችን አቅርበዋል። ​ተሳታፊዎች በቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፎች ላይ ውይይት በማድረግ መፍትሔ የሚሹ ተግዳሮቶች እና የወደፊት አቅጣጫዎችን አቅርበዋል። ተሳታፊዎች ቋንቋው ተገቢ ትኩረት ተሰጥቶት ተደራሽ እንዲሆን ከማድረግ አንጻር ክፍተቶች እንዳሉ እንዲሁም ከግብዓት እጥረት እና ከተቋማዊ ድጋፍ ማነስ አንጻር ይስተዋላሉ ያሏቸውን ክፍተቶችም አንስተዋል። ​ ኢትዮጵያ ከአረብ ሀገራት ጋር ያላትን ታሪካዊና ሁለንተናዊ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እና ወጣቱ ትውልድ በዓለም አቀፍ መድረክ ያለውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የቋንቋው መስፋፋት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም ጠቅሰዋል። እንደ እንግሊዘኛ ቋንቋ ሁሉ ዓረብኛ ቋንቋም በሀገሪቱ ስርዓተ ትምህርት ውስጥ እንዲካተት ለማድረግ የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረትና ተቋማዊ እገዛ ወሳኝ እንደሆነም ተመላክቷል። ​በውይይት መድረኩ ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንቶች፣ የሥራ አስፈጻሚ አባላት፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ ዑለማዎችና ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። •••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤትን የሕዝብ ግንኙነት እና ሚዲያ ዘርፍ ይከታተሉ | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

በዓረብኛ ቋንቋ ታሪካዊና አሁናዊ ፋይዳ ዙሪያ ያተኮረ ውይይት ሊያካሂድ ነው። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 22 /2018 ዓ.ል| ሙሀረም
+1
በዓረብኛ ቋንቋ ታሪካዊና አሁናዊ ፋይዳ ዙሪያ ያተኮረ ውይይት ሊያካሂድ ነው። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 22 /2018 ዓ.ል| ሙሀረም 14 /1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ | ​ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ሙስሊሞች ጥናትና ምርምር ፎረም ጋር በመተባበር በዓረብኛ ቋንቋ ላይ ያተኮረ ውይይት ማዘጋጀቱን የጠቅላይ ምክር ቤቱ የዑለማ ጉባዔ አባልና የትምህርትና ካሪኩለም ዘርፍ ኅላፊ ተባባሪ ፕሮፌሰር አብደላ ኸድር ገለፁ። ​ውይይቱ "የዓረብኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ትላንትና ዛሬ ብሩህ ተስፋዎችና ተግዳሮቶች" በሚል መሪ ሃሳብ እንደሚካሄድ የገለጹት ኃላፊው በውይይት መድረኩ ዓረብኛ ቋንቋ በሀገራችን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ባህላዊ እና ኪነ ጥበባዊ ዘርፎች ላይ ያሳረፈው የታሪክ አሻራ ይዳሰሳልም ብለዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የታሪክ፣ የቋንቋ እና የባህል ተመራማሪዎች፣ ምሁራን እና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች የሚገኙ ሲሆን ጉዳዮ ይመለከተኛል የሚሉ አካላት ሰኔ 23/2018 ከጠዋቱ 2፡30 በሸራተን ሆቴል ተገኝተው በጎ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል። •••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍን ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የሶማሌ ክልል ሸሪዓ ፍርድ ቤት የፌዴራል የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አዋጅ መፅደቅን አስመልክቶ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 19/2018 ዓ.ል| ሙሀረም 11/1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ጅግጅጋ | የሶማሌ ክልል የሸሪዓ ፍርድ ቤት አስተዳደር የፌዴራል የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች የሕግ ረቂቅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅደቁን አስመልክቶ ለህዝበ ሙስሊሙ እና ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ። ​ፍርድ ቤቱ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ለክቡር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ ለኢትዮጵያ ኡለማዎች ምክር ቤት፣ ለመላው ህዝበ ሙስሊም፣ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና ለተከበሩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የተሰማውን ልባዊ ደስታና የምስጋና መልዕክት አስተላልፏል። ​የሶማሌ ክልል የሸሪዓ ፍርድ ቤት ይህንን አዋጅ ታሪካዊ ስኬት ሲል የገለጸው ሲሆን ይህም የሸሪዓ ፍርድ ቤቶችን አወቃቀርና አሠራር ለማጠናከር ተቋማዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ እንዲሁም በሕገ-መንግሥቱና በሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ፍትሕን ለማስፈን፣ መብቶችን ለማስከበርና ማኅበረሰብን በታማኝነት ለማገልገል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር አስገንዝቧል። ​በተጨማሪም ፍርድ ቤቱ ይህ የሕግ ረቂቅ እንዲጸድቅ የሚመለከታቸው አካላት በተለይም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና የኡለማዎች ምክር ቤት ላደረጉት ከፍተኛ ጥረትና ትብብር ምስጋና አቅርቧል። ይህ የተገኘው ውጤት በሀገሪቱ ያለውን ብሔራዊ የጋራ ትብብርና የዜጎችን ሃይማኖታዊ መብቶች መከበር መጀመሩን የሚያሳይ መሆኑም መግለጫው ተጠቅሷል። ​የሶማሌ ክልል ፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ሸይኽ አሕመድ ሙሐመድ አደም ይህ ታሪካዊ ስኬት በሀገራችን ፍትሕ፣ መረጋጋትና ልማት እንዲሰፍን ለሚደረገው ጉዞ አዲስ ምዕራፍ እንዲሆን በመግለጫው መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል። •••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

"ጠቅላይ ምክር ቤቱ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት እንዲሰፋ ድጋፍ ያደርጋል" - ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 18/2018 ዓ.ል| ሙሀረም 10/1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ | የኢትየጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርት ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን ዘመን ባንክ “ዚ-ቀመር” የተሰኘ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ባስጀመረበት መድረክ ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ንግግር አድርገዋል፡፡ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንቱ በንግግራቸው ለባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ፣ ለሥራ አመራር አባላት፣ ለባለአክሲዮኖችና ለጠቅላላው የባንኩ ሠራተኞች የእንኳ ደስ ያላችሁ መልካም ምኞታቸውን ገልፀው ዘመን ባንክ “ዚ-ቀመር” አገልግሎት መጀመሩ የፋይናንስ ተደራሽነትን ከማሳደግ ባለፈ ለህዝበ ሙስሊሙ አማራጭ የፋይናንስ አገልግሎት ዕድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ህዝበ ሙስሊሙ በፋይናንሱ ዘርፍ በንቃት እንዲሳተፍና ተጠቃሚ እንዲሆን በር የከፈተ ነው ያሉት ሸይኽ አብዱልከሪም ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለዚህ ዘርፍ ዕድገትና ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ያደርጋልም ብለዋል፡፡ •••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ፀደቀ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 18/2018 ዓ.ል| ሙሀረም 10/1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ | ላለፉት 25 አመታት አገልግሎት ላይ የነበረውን ​የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 188/1992 ሙሉ በሙሉ የሚተካው አዲሱ ረቂቅ አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቋል:: የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ሕግ የማርቀቅ ሥራው ሲከናወን የቆዬ ሲሆን ረቂቁ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት በተዋቀረ ባለ 7 አባላት የዳኞችና የባለሙያዎች ኮሚቴ የተዘጋጀ ነው። ​ኮሚቴው የውጭ ሀገራት ተሞክሮዎችን፣ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተገኙ ጠቃሚ ግብዓቶችን እንዲሁም የህዝብ አስተያዬቶችን በማካተት ረቂቁን አዘጋጅቶ ለፓርላማው የህግ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በመምራት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል:: በአዲስ መልክ የተዘጋጀው ይህ አዋጁ የፍርድ ቤቶቹን የዳኝነት ሥልጣን፣ አደረጃጀትና አሠራር፣ የዳኞች አሿሿምና በጀት እንዲሁም የፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባኤን በአዲስ መልክ ማቋቋምን ጨምሮ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችን በዝርዝር አካቷል። የአዋጁ መጽደቅ ህዝበ ሙስሊሙ ከመልካም አስተዳደር ጋር በተያያዘ ሲያነሳ ለነበረው የረጅም ጊዜ ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ ነው:: ይህ አዋጅ እንዲፀቅ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋን ጨምሮ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አመረሮች፣ ረቂቁን ያዘጋጁ የኮሚቴ አባላት፣ የፓርላማው የህግ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል። ማሻሻያውን ተከትሎ የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ለህዝበ ሙስሊሙ ተገቢ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ህዝበ ሙስሊሙ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል። •••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

የሜኒሶታ ኢስላሚክ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ የሀጅ ልዑካን ቡድን በሳውዲ አረቢያ ላስመዘገበው ከፍተኛ ድል ደማቅ የእውቅና መርሃ ግብር አካሄደ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 17 /2018 ዓ.ል| ሙሀረም 9 /1447 ዓ.ሒ                            بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ                 ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አዲስ አበባ | የሜኒሶታ ኢስላሚክ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፣ በሳውዲ አረቢያ የሀጅና ዑምራ ሚኒስቴር በተዘጋጀው የ1447 ሂጅሪያ የሀጅ አገልግሎት አሰጣጥ ውድድር ላይ “የአልማዝ (Diamond)” ሽልማት ላስመዘገበው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን እና ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባደማቅ የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር አከናወነ። ​ በዚሁ መርሃግብር ላይ ዓሊሞች ፣ ዲፕሎማቶች የዩኒቨርሲቲው የስራ ኃላፊዎች፣ የዕውቅናው ተሸላሚዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በዕለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የክብር ዶክተር ሼይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ፣የኢትዮጵያ የሀጅ ልዑካን ቡድን በሳውዲ አረቢያ መንግስት ከተሳተፉ በርካታ ሀገራት መካከል ተወዳድሮ ከፍተኛውን እና ደማቅ የሆነውን የ“አልማዝ (Diamond)” ደረጃ ሽልማት ማሸነፉ የሀገሪቱን ገፅታ በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። ይህም ስኬት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትና ባለድርሻ አካላት ከመቼውም ጊዜ በላይ ተቀናጅተውና ሌሊት ከቀን ሰርተው ስራቸውን በብቃት መወጣታቸውን የሚያሳይ መሆኑ ጠቁመዋል። ይኽ ውጤት አሏህ እርዳታ የተገኘ በመሆኑ ውጤቱ ቀጣይነት እንዲኖረው ከመቼውም ጊዜ በተሻለ መስራትና አሏህን መማፀን ያስፈልጋል ብለዋል። በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የሀጅና ዑምራ ዘርፍ ሀላፊ ዶክተር መሀመድ ሷሊህ የኢትዮጵያ ልዑክ ያገኘው ሽልማትም የዚህ የጋራ ትብብር ውጤት ሲሆን፣ መስተንግዶው ለአሠራር መመሪያዎች ተገዢ መሆናችንንና ለኢትዮጵያውያን ሐጃጆች የተሰጠውን ልዩ እንከብካቤ ያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል። የሜኒሶታ ኢስላሚክ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ፕሬዚዳንት ዶክተር ማሕሙድ ሁሴን አብደላ በበኩላቸው ፣ እንዲህ ያሉ ሀገራዊና ሀይማኖታዊ ስኬቶችን ማበረታታትና ዕውቅና መስጠት ለቀጣይ የተሻሉ ስራዎች መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልፀዋል። ዩኒቨርሲቲው እውቀትን ከሥነ-ምግባር ጋር አጣጥመው የሚያስኬዱ ብቁ ትውልዶችን የማፍራት ታላቅ ዓላማ ሰንቆ እየሠራ እንደሚገኝም ተገልጿል። ዩኒቨርሲቲው ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር በመተባበር ለሀገርና ለወገን የሚጠቅሙ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። ​በዕለቱ ለተሳካው የሀጅ አገልግሎት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የልዑካን ቡድን አባላት፣ ተቋማትና ግለሰቦች የደረጃው ማረጋገጫና የምስጋና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ ተሸላሚዎቹም የተሰጣቸው ዕውቅና ወደፊት ይበልጥ በታማኝነትና በቁርጠኝነት ለማገልገል ትልቅ ጉልበት እንደሚሆናቸው ገልጸዋል። •••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1

በኢትዮጵያ ያለውን ኢስላማዊ የፋይናንስ ስርዓት ለማጠናከር እና የልማት ስራዎችን ለማፋጠን የሚያግዝ ውይይት ተደረገ። ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሰኔ 16/2018 ዓ.ል| ሙሀረም 08/1448 ዓ.ሒ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ባኩ | በኢትዮጵያ ኢስላማዊ የፋይናንስ ሥርዓትን ለማጠናከር እና ማኅበረሰብ ተኮር የልማት ሥራዎችን ለመደገፍ የሚያስችሉ ተስፋ ሰጪ ውይይቶች ተደረጉ። ​ውይይቱ በአዘርባጃን ባኩ ከተማ በተካሄደው የ2026 የኢስላሚክ ልማት ባንክ (IsDB) ዓመታዊ ስብሰባ ጎን ለጎን ነው። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከኢስላሚክ ልማት ባንክ ጋር የትብብር ሰነድ በመፈራረም በትምህርት እና በማህበራዊ ልማት ዘርፍ በቅንጅት እየሰሩ የሚገኝ ሲሆን የጠቅላይ ምክር ቤቱ የፕሮጀክት አስተዳደር ኃላፊ ኢንጂነር አንዋር ሙስጦፋ ከኢስላሚክ ልማት ባንክ ተለዋጭ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሳሚ አል-ሱዋይለም ከተመራው ልዑክ ጋር በልማት ስራዎች ዙሪያ መክረዋል። ​ውይይቱ በኢትዮጵያ ያለውን ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ልማት ለማገዝ ተግባራዊ ሊሆኑ በሚችሉ የመፍትሔ ሃሳቦች ላይ ያተኮረ ነው። በተለይም ተቋማዊ አቅምን በመገንባት እንዲሁም የውጭ የትምህርት እድልን በመፍጠር እና መልካም ተሞክሮዎችን በመለዋወጥ የህዝበ ሙስሊሙን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ አቅምን ማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎችን በጋራ መሥራት በሚቻልባቸው ሐሳቦች ዙሪያ ሰፊ ጊዜ ወስደው ተወያይተዋለ። ​የጠቅላይ ምክር ቤቱ ስልታዊ አጋር የሆነው የኢስላሚክ ልማት ባንክ ኢንስቲትዩት በኢትዮጵያ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብና ከወለድ ነፃ የፋይናንስ ሥርዓቱ ይበልጥ እንዲጎለብት አስፈላጊውን ሙያዊና ተቋማዊ ድጋፍ ለማድረግ ፍላጎት እንዳለው በውይይቱ ተነስቷል። ​በኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣው ከወለድ ነፃ የባንክና የፋይናንስ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን በመቅሰም ተወዳዳሪነቱን እንዲያሳድግ እንደሚሰራም በውይይቱ የተነሳ ሲሆን ኢንጂነር አንዋር ኢስላሚክ ባንኩ እያደረገ ላለው ሁለንተናዊ ድጋፍ ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል። •••••••••••••••••••••••••• የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ይከታተሉን | Follow us፡ ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council ቴሌግራም | t.me/eiasc1 ትዊተር | https://x.com/eiasc1