ch
Feedback
🇪🇹የሕግ ጉዳይ

🇪🇹የሕግ ጉዳይ

前往频道在 Telegram

Law Related Issue, Ethiopia Legal Info, 👇 #ከጠበቃና የሕግ አማካሪ ጋር ለመማከር @TalkToLawyer We offer you Reliable services with a very high sense of responsibility. https://www.facebook.com/lawsocieties EthiopianLawFamily@gmail.com

显示更多
8 525
订阅者
+124 小时
+327
+6330
帖子存档
ሠንጠረዥ “ሀ” ከመቀጠር በሚገኝ ገቢ ላይ ተፈጻሚ የሚሆኑ ምጣኔዎች
ሠንጠረዥ “ሀ” ከመቀጠር በሚገኝ ገቢ ላይ ተፈጻሚ የሚሆኑ ምጣኔዎች

በኢትዮጵያ_የፍትሐ_ብሔር_ሥነ_ሥርዓት_ሕግ_መሠረት_የመጨረሻ_አስተያየቶችና_የመዝጊያ_ክርክሮች.docx0.50 KB

ስለ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የይግባኝ የዳኝነት ስልጣን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሚከተሉትን ጉዳዮች በይግባኝ የማየት ስልጣን ይኖረዋል፡- 👉የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመጀመሪያ ደረጃ ስልጣኑ ውሳኔ የሰጠባቸው፣ 👉የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በይግባኝ ሰሚነት ስልጣኑ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከሰጠው ውሳኔ የተለየ ውሳኔ የሰጠባቸው፣ 👉የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ጉዳዮችን በተወካይነቱ በመጀመሪያ ደረጃ ስልጣኑ አይቶ ውሳኔ የሰጠባቸው፣ 👉የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ጉዳዮችን በተወካይነቱ በይግባኝ ሰሚነት ስልጣኑ የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሰጠው ውሳኔ የተለየ ውሳኔ የሰጠባቸው፣ 👉በሌሎች ህጎች የተጠቀሱ ጉዳዮችን፡፡ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 9 ንዑስ አንቀጽ (1-5)

አንድ ተከሳሽ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎለት ክስ የቀረበበት ስለመሆኑ እውቋል የሚል ግምት ሊወሰድ የሚገባው አገር አቀፍ ስርጭት ባለው ጋዜጣ ጥሪ የተደረገለት መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ እንጂ በአንድ ክልል ብቻ ተደራሽ በሆነ ጋዜጣ ብቻ ጥሪ መደረጉን መጥሪያ እንዳደረሰው ማረጋገጫ አድርጎ በመውሰድ እና መጥሪያ ደርሶታል የሚል ግምት በመውሰድ ጉዳዩን ተከሳሹ በሌለበት አይቶ ውሳኔ መስጠት በሕገ-መንግሥቱ ለተከሰሱ ሰዎች የተረጋገጠላቸውን መሠረታዊ መብት የሚጥስ ስለመሆኑ ። @የሰ/መ/ቁ፦ 173967 ቅፅ.24

በኤሌክትሪክ አደጋ ምክንያት ለሚደርስ ጉዳት ተገልጋዮች ከአገልግሎት ሰጪው እውቅና እና ፈቃድ ውጭ በራሳቸው በሚዘረጉት የኤሌክትሪክ መስመር ለሚደርሰው ጉዳት አገልግሎት ሰጪው ተቋም ተጠያቂ አይሆንም። እንደ ኤሌክትሪክ አደጋ ባሉ የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ የአደጋውን መንስኤ ለማወቅ በፖሊስ የሚደረግ የባለሙያ (Forensic) ምርመራ ከፍተኛ የማስረጃነት ዋጋ (High Probative Value) አለው። ይህንን የባለሙያ ምርመራ ውጤት ያለ በቂ ምክንያት ወደ ጎን በማለት ውሳኔ መስጠት መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው። አገልግሎት ሰጪው ኃላፊነት የሚኖርበት እሱ ራሱ በዘረጋውና ባለቤት በሆነበት መስመር ላይ ለሚደርስ ጉዳት ብቻ ነው። በተገልጋዮች ጥፋት ለሚደርስ አደጋ ተቋሙ ካሣ የመክፈል ግዴታ የለበትም። የኤሌክትሪክ ኃይል ባለቤት መሆን ብቻውን ኃላፊነትን አያስከትልም፤ ኃላፊነት ሊኖር የሚችለው ተገቢው ጥንቃቄ ካልተደረገ እና ጥፋት ከተፈጸመ ብቻ ነው። ሰ/መ/ቁ.175142 (ግንቦት 24 ቀን 2012 ዓ.ም)

የተሻሻለው176_2014_የሒሳብ_መዝገብ_አያያዝ.pdf7.10 MB

"የፍትሕ ተቋማት" 6 ተቋማትን ያካትትል:: 1. ፍርድ ቤቶችን 2. የዐቃቤ ሕግ ተቋማትን (ፍትሕ ሚ/ር፣ ፍትሕ ቢሮ) 3. የፖሊስ ተቋማትን 4. ማረሚያ ቤቶችን 5. የጥብቅና ተቋማትን 6. የተከላካይ ጠበቆች ተቋማትን -አንቀጽ 18(2)፣ 23 *በዚህ አዲሱ Code (ዐዋጅ ቁ. 1410/2018) የጥብቅና ሙያ የፍትሕ ሥርዓቱ የተፈጥሮ/የባሕርይ አካል እንደሆነ በግልጽ በማረጋገጥ ማንኛውም ምድራዊ ኃይል ጠበቃን ነጋዴ ነው ብሎ ሊጠራው እንደማይችል አሥምሮአል:: ስለሆነም በጠበቆች ላይ የሚፈጸም ጥቃት በፍትሕ ተቋማት/በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የተፈጸመ ጥቃት ነው::👴🏽🧓🏾 ሀይሉ ሀሰና

+6
HOF 2018 (1).pdf17.05 MB

+9
2012-all-decided-federartion-files-combined-compressed (1).pdf12.96 MB

ለተከታታይ አምስት (5) ቀናት ከስራ የቀረ ሰራተኛ ያለማስጠንቀቂያ ከስራ ሊሰናበት ነው። ከእረፍትና ልዩ ልዩ ፍቃዶች ውጭ አንድ ሰራተኛ ለአምስት (5) ተከታታይ ቀናትና ከዚያ በላይ ከስራ የቀረ ሰ
+1
ለተከታታይ አምስት (5) ቀናት ከስራ የቀረ ሰራተኛ ያለማስጠንቀቂያ ከስራ ሊሰናበት ነው። ከእረፍትና ልዩ ልዩ ፍቃዶች ውጭ አንድ ሰራተኛ ለአምስት (5) ተከታታይ ቀናትና ከዚያ በላይ ከስራ የቀረ ሰራተኛን ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ውልን ማቋረጥ የሚያስችል አዲስ የህግ ትርጉም ተሰጥቷል፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከዚህ በፊት በሰበር መዝገብ ቁጥር 249795 ላይ አንድ ሰራተኛ በተከታታይ ከአምስት (5) ቀናት በላይ ከሥራ ከቀረ አሰሪው ለእያንዳንዱ ቀን ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ የሥራ ውልን ማቋረጥ እንደማይችል ጠቅሶ የሕግ ትርጉም ሰጥቶ ነበር። ሆኖም ሰበር ሰሚ ችሎቱ አሁን ላይ አሰሪው ለእያንዳንዱ ቀን ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ ከስራ ማሰናበት የለበትም የሚለውን የሕግ ትርጉም ሽሮታል። በምትኩ ከእረፍቶችና ልዩ ልዩ ፍቃዶች ውጭ አንድ ሰራተኛ ለአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናትና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ከቀረ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ውሉን ማቋረጥ ይቻላል በሚል ትርጉም ተሰጥቷል። ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው። ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

+1
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኤላክትሮኒክ ፊርማ ዯንብ 582/2018

👉 ቃብድ ✍️ ቃብድ ማለት ተዋዋይ ወገኖች ውላቸው እንዲጸናላቸው ያላቸውን ፍላጎት ለማሳየት እና ሽያጩን ለማረጋገጥ አንዱ ወገን ለሌላኛው የሚሰጠው የማስያዣ ገንዘብ ነው። በኢትዮጵያ የውል ሕግ ሥርዓት ውስጥ ቃብድ ከመደበኛ የውል አፈጻጸም ለየት ያሉ የሕግ ውጤቶች አሉት። 1. የቃብድ የሕግ ውጤት በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1885 እንደ ፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1885(1) እና (2) ድንጋጌ፣ በቃብድ የታሰረ የሽያጭ ውል ከሌሎች ውሎች የሚለየው በሚከተሉት ነጥቦች ነው፦ ተቃራኒ ስምምነት እስካልተደረገ ድረስ፣ ቃብድ የሰጠው ወገን የሰጠውን ቃብድ በመተው፣ ቃብድ የተቀበለው ወገን ደግሞ የተቀበለውን ቃብድ እጥፍ አድርጎ በመመለስ ውሉን በፈቃዳቸው ማፍረስ ይችላሉ። በቃብድ የታሰረ ውል እንደ ሌሎች መደበኛ ውሎች በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1776 መሠረት በግዴታ እንዲፈጸም በሕግ አይገደድም። ይልቁንም ተዋዋዮቹ ቃብዱን በመተው ወይም እጥፍ በመመለስ ከውሉ የመውጣት የመውጫ ቀዳዳ ይሰጣቸዋል። የቅድመ ክፍያ እና የቃብድ ልዩነት 👇👇👇✍️✍️✍️ ተከራካሪዎች የከፈሉት ገንዘብ ቃብድ ሳይሆን ለሽያጭ ዋጋው ማሟያ የተደረገ የቅድመ ክፍያ ከሆነ፣ የቃብድ ሕግ እጥፍ መመለስ ወይም ትቶ መቅረት ተፈጻሚ አይሆንም። ቃብድ ለተዋዋይ ወገኖች ውሉን የመተው መብት የሚሰጥ ቢሆንም፣ የሚከፈለው ገንዘብ ቃብድ መሆኑንም ወይም የቅድመ ክፍያ መሆኑ በግልጽ መታወቅ አለበት። ከጠበቃና የሕግ አማካሪ ሚኪያስ መላክ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service

የደቦ ፍርድ ከጎዳና እስከ ዲጂታል አደባባይ ለሕግ የበላይነት የፈጠረው ስጋት✍️✍️✍️
በሀገራችን እየተለመደ የመጣው #የደቦ_ፍርድ (Mob Justice) ከጎዳና እስከ ዲጂታል መድረኮች ፍትሕን ከችሎት አውጥቶ አደባባይ ላይ በመጣል የሀገርን ገጽታና የዜጎችን ደኅንነት ከፍተኛ አደጋ ላይ ጥሎ ይገኛል፡፡ በማንኛውም ሥልጡን ማኅበረሰብ ውስጥ ፍትሕ የሚሰጠው በሕግ በተቋቋሙ የፍርድ አካላት እንጂ በቲክቶክ የዲጂታል ፍረጃ ወይም በጎዳና ስሜታዊ ስብስብ አይደለም፡፡ አለሕግ ስንል፤ አወ ሕግ ስላለ ነው፡፡ ሕግ ባለበት ሀገር ደግሞ ፍትሕ የማግኘት መብት የሁሉም ሰው ነው፡፡ በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 37 መሠረት፣ የዳኝነት ሥልጣን የፍርድ ቤት እንጂ የቲክቶክ መንደር ወይም የሰፈር ቡድን አይደለም፡፡ ችሎት ማለት ዝም ብሎ አዳራሽ ወይም ወንበር አይደለም፤ ችሎት የሥልጣን፣ የጥበብ እና የውሳኔ መፍለቂያ ነው። በሕግ ቋንቋ ችሎት ማለት፡- 1. ክርክር የሚሰማበትና የሚደመጥበት፣ 2. ማስረጃ የሚመዘንበትና እውነታው የሚመረመርበት፣ 3. በዳኞች አማካኝነት የመጨረሻ ሕጋዊ ውሳኔ የሚሰጥበት የተቀደሰ ሥርዓት ነው፡፡ በሕገ-መንግሥታችን አንቀጽ 20 መሠረት፣ ማንኛውም ሰው ጥፋተኛነቱ በሕግ እስካልተረጋገጠ ድረስ እንደ ንጹሕ የመቆጠር መብት አለው፡፡ ሆኖም ዛሬ ወንጀለኛን ማጋለጥ በሚል ሰበብ፤ የግል ቂም በቀልንና ጥላቻን ለመወጣት የሚደረጉ የዲጂታል ስም ማጥፋት ዘመቻዎች ንጹሕ ዜጎችን ለከፋ ሥነልቦናዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እየዳረጉ ነው፡፡ በተለይ በቲክቶክ እና መሰል መድረኮች ላይ ፎሎወር እና ላይክ ለማግኘት ብቻ ፖሊስ ምርመራ ሳይጀምር ሰዎችን ማዋረድና እንደወንጀለኛ መቁጠር እንዲሁም ለጥቃት ማጋለጥ በራሱ ከባድ ወንጀል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡ ብዙዎች በቡድን ስንሆን አንጠየቅም ብለው ሊያስቡ ይችላሉ፤ ይህ ግን ትልቅ የሕግ ስህተት ነው፡፡ በወንጀል ሕጋችን መሠረት በቡድን/በደቦ ነው የፈጸምኩት የሚል ምክንያት ከቅጣት አያድንም፡፡ • የጸጥታ አካላት ተጠርጣሪዎችን ሲይዙ የሚያሳዩት ከሥነምግባር ውጭ የሆነ አያያዝ ማኅበረሰቡ ሕግን በእጁ እንዲያጠናቅቅ በዝምታ የሚሰጥ ግብዣ ይመስላል፡፡ ሕግ የሚከበረው ሕግን አክብሮ በማስከበር ነው፡፡ • ወንጀለኛን ለሕግ አሳልፎ መስጠት እንጂ፣ በእራሳችን እርምጃ መውሰድ እና ራስን እንደ ዳኛ አድርጎ መቁጠር ሌላ የከፋ ወንጀል ነው፡፡ ዛሬ በሌላው ላይ የሚፈረደው የደቦ ፍርድ፣ ነገ የእኛንም በር ማንኳኳቱ አይቀርም፡፡ መደብደብ፤ መግደል፤ ማኅበራዊ ሚዲያዎች/በዲጂታል ስም ማጥፋት እና ለአሉታዊ ነገር ግለሰቦችን ማነሳሳት በቡድን/በደቦ በዘመቻ ስለተፈፀመ ተጠያቂነትን አያስቀርም 1. በኢፌዴሪ ሕገመንግሥት አንቀጽ 15 ፤20 ፤ 24 እና 37 መሰረት ማንኛውም ሰው በሕግ ካልተደነገገ በስተቀር ሕይወቱን አያጣም፡፡ ጥፋተኛነቱ በሕግ እስካልተረጋገጠ ድረስ እንደ ንጹሕ ይቆጠራል፡፡ ክብሩና መልካም ስሙ የመከበር መብት አለው፡፡ ክርክሩ ወይም ጉዳይ ለፍርድ ቤት ቀርቦ ለማስወሰን መብት አለው፡፡ 2. በወንጀል ህጋችን አንቀጽ 538 እና ተከታዮቹ መሰረት በሰው ሕይወትና አካል ላይ የሚፈጸሙ በቡድን የታገዙ ጥቃቶች ከባድ ቅጣት ያስከትላሉ፡፡ 3. የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅ 958/2008 መሰረት በዲጂታል መድረክ የሰውን ስም ማጥፋትና የሐሰት መረጃ ማሰራጨት በጽኑ እስራት ያስቀጣል፡፡ 4. የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ አዋጅ 1185/2012 መሰረት በማስረጃ ያልተደገፈ ማንኛውም ሰው ወንጀለኛ እያሉ መሰየም ዘመቻ ከባድ የወንጀል ተጠያቂነት አለው፡፡ ያለ ሕግ የበላይነት ፍትሕ የለም፤ ያለ ፍትሕ ደግሞ ሰላም የለም! የፍርድ ቤት መዶሻን በእጃችን ከመያዝ እንቆጠብ። መንግሥት የሕግ ማስከበር ቁርጠኝነቱን በተግባር ሊያሳይ፣ ማኅበረሰቡም ለሕግ ተገዥነቱን ሊያረጋግጥ ይገባል፡፡ በዚህች ምድር ስንኖር ያለ ሕግ ፍትሕ የለም፤ ያለ ሕግ የበላይነት ፍትሕ የለም፤ ያለ ፍትሕ ደግሞ ሰላም የለም! በእውነት ዓምድ እንቁም! ሚኪያስ መላክ በፌዴራል ማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ አለሕግ alehig.com አለ ሕግ 0920666595 ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service WhatsApp👉 #+251920666595 Telegram👉 @MikiasMelak https://t.me/AleHig

የውጭ ሀገር መንጃ ፈቃድ ቅያሬ አገልግሎት ለማግኝት
የውጭ ሀገር መንጃ ፈቃድ ቅያሬ አገልግሎት ለማግኝት

የተጨማሪ እሴት ታክስ ደረሰኝ ሳያውቁ ጊዜው ካለፈብዎ; ወይም ሲያሳውቁ በመሀል የረሱት ደረሰኝ ካለ ምን ማድረግ እንዳለብዎ ህጉ የሚለውን እናካፍልዎ? በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/201
የተጨማሪ እሴት ታክስ ደረሰኝ ሳያውቁ ጊዜው ካለፈብዎ; ወይም ሲያሳውቁ በመሀል የረሱት ደረሰኝ ካለ ምን ማድረግ እንዳለብዎ ህጉ የሚለውን እናካፍልዎ?
በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2016 እና በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 570/2017 መሠረት፣ የታክስ ደረሰኝን ለማስታወቅ ጊዜው ካለፈብዎት እንደ ጉዳዩ ዓይነት የሚከተሉትን እርምጃዎች መውሰድ ይችላሉ፦ 1. የግብአት ታክስ ተቀናሽ (Input Tax Credit) ለማግኘት ከሆነ ደረሰኙን ያላሳወቁት ግዥ ፈጽመው የከፈሉትን ታክስ ለማቀናነስ (ለመቀነስ) ከሆነ፣ አዋጁ የጊዜ ገደብ ፈቅዶልዎታል። በአዋጁ አንቀጽ 29 ንዑስ አንቀጽ 7 መሠረት፣ በማናቸውም ምክንያት በአንድ የሂሳብ ጊዜ ውስጥ ተቀናሽ ሊደረግ የሚገባውን የታክስ መጠን (የግብአት ታክስ) ሳያሳውቁ የቀሩ እንደሆነ፣ ተቀናሽ ሊጠየቅበት ከሚገባው የሂሳብ ጊዜ መጨረሻ ጀምሮ ባሉት 12 ወራት ውስጥ በሚቀርብ ቀጣይ የታክስ ማስታወቂያ ላይ ደረሰኙን በማካተት ተቀናሽ እንዲደረግልዎ መጠየቅ ይችላሉ። 2. የሽያጭ (የውጤት ታክስ) ደረሰኝ ለማስታወቅ ከሆነ የሽያጭ ደረሰኝ መቁረጥ ወይም ማስታወቅ ዘግይተው ከሆነ፣ የታክስ ግዴታው ስለማይቀር ማስታወቂያውን በአፋጣኝ ማቅረብ ይኖርብዎታል። ማንኛውም የተመዘገበ ሰው ለእያንዳንዱ የሂሳብ ጊዜ የታክስ ማስታወቂያውን ወሩ በተጠናቀቀ በሚቀጥለው ወር የመጨረሻ ቀን ድረስ የማቅረብ ግዴታ አለበት። ይህ ጊዜ ካለፈ ግን የሚከተሉት ሁኔታዎች ይፈጠራሉ፦ • አስተዳደራዊ ቅጣት እና ወለድ፦ ታክስን በወቅቱ አለማሳወቅ ወይም ዘግይቶ መክፈል በታክስ አስተዳደር አዋጅ መሠረት የአስተዳደራዊ ቅጣት እና ወለድ ያስከትላል። • የታክስ ባለሥልጣኑ ውሳኔ፦ የታክስ ባለሥልጣኑ ታክስ ሳይታወቅ በቆየበት ጊዜ ሁሉ የራሱን የታክስ ስሌት ውሳኔ (Assessment) ሊሰጥ ይችላል። 3. የታክስ ተመላሽ (Refund) ጥያቄ ካለዎት የተመዘገበው ሰው ተመላሽ ሊከፈለው በሚገባበት ጊዜ የታክስ ማስታወቂያ የማቅረብ ግዴታውን ካልተወጣ፣ የታክስ ባለሥልጣኑ ማስታወቂያው እስከሚቀርብ ድረስ ተመላሹ ገንዘብ ሳይከፈል እንዲቆይ ሊያደርግ ይችላል። 4. በኤሌክትሮኒክ ፊስካል መሣሪያ (EFD) የሚጠቀሙ ከሆነ መሣሪያው ባለመሥራቱ ምክንያት ግብይቱን በወቅቱ መመዝገብ ካልቻሉ፣ ሁኔታው በተፈጠረ በ24 ሰዓት ውስጥ ለታክስ ባለሥልጣኑ ማሳወቅ እና በእጅ የሚዘጋጅ የታክስ ደረሰኝ መስጠት ይኖርብዎታል። መሣሪያው ወደ ሥራ ሲመለስም ቀደም ብለው ያከናወኑትን ግብይት በመሣሪያው ውስጥ መመዝገብ ይኖርብዎታል። በአጠቃላይ፣ የግብአት ታክስን (የግዥ ደረሰኝን) ለማስታወቅ የ12 ወራት የጊዜ ዕድል ቢኖርዎትም፣ የሽያጭ ደረሰኝን ግን ለቅጣት እና ለወለድ እንዳይዳረጉ በወቅቱ ማስታወቅ ተገቢ ነው።
አዋጁ የግብአት ታክስ ተቀናሽ ለማድረግ የሚሰጠው የ12 ወራት ገደብ እንዴት ይሰላል?
ተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2016 አንቀጽ 29 ንዑስ አንቀጽ 7 መሠረት፣ የ12 ወራት የግብአት ታክስ ተቀናሽ መጠየቂያ የጊዜ ገደብ የሚሰላው በሚከተለው መሠረት ነው፦ 👉 የአቆጣጠሩ መነሻ (Starting Point)፦ የ12 ወራቱ ስሌት የሚጀምረው ተቀናሽ ሊጠየቅበት ከሚገባው የሂሳብ ጊዜ (ወር) መጨረሻ ቀን ጀምሮ ነው። ይህም ማለት ግዥውን የፈፀሙበት ወይም የታክስ ደረሰኙ የደረሰዎት ወር መጠናቀቂያ ቀን ለአቆጣጠሩ መነሻ ይሆናል ማለት ነው። 👉 የጊዜ ገደቡ ርዝመት፦ መብቱ የሚቆየው መነሻ ከሆነው የሂሳብ ጊዜ መጨረሻ ጀምሮ ለሚቆጠሩ ተከታታይ 12 ወራት ብቻ ነው። 👉 አፈፃፀሙ፦ በማናቸውም ምክንያት በወቅቱ ያልተገለጸ የግብአት ታክስ ካለ፣ በእነዚህ 12 ወራት ውስጥ በሚቀርብ ማንኛውም ቀጣይ የታክስ ማስታወቂያ ላይ ደረሰኙን በማካተት ተቀናሽ እንዲደረግልዎት የመጠየቅ መብት አለዎት። ይህንን ስሌት በምሳሌ ለማየት ያህል፣ አንድ ድርጅት በጥር ወር የፈፀመውን ግዥ የግብአት ታክስ በጥር ወር ማስታወቂያ ላይ ሳይጠቀም ቢቀር፣ የ12 ወራት አቆጣጠሩ የሚጀምረው የጥር ወር የሂሳብ ጊዜ ካለቀበት (ጥር 30) ቀን ጀምሮ ነው። ስለዚህ ድርጅቱ እስከ ቀጣዩ ዓመት ጥር 30 ድረስ ባሉት ማናቸውም ወራት በሚያቀርበው የታክስ ማስታወቂያ ላይ ይህንን ደረሰኝ በማካተት ተቀናሽ ማግኘት ይችላል። 12 ወራቱ ካለፉ ግን ተቀናሽ የመጠየቅ መብቱ በሕግ ይታገዳል

ነፃ የንግድ ቀጠና (Free Trade Zone)
ነፃ የንግድ ቀጠና ማለት የሀገሪቱ የጉምሩክ ክልል አካል እንዳልሆኑ ተቆጥረው፣ የውጭ ምርቶች ያለምንም የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ የሚገቡባቸው፣ እሴት ተጨምሮባቸው መልሰው የሚላኩባቸው ወይም ለሀገር ውስጥ ገበያ የሚቀርቡባቸው ልዩ የንግድ ቦታዎች ማለት ነው። ​ይህ ጽንሰ-ሀሳብ በኢትዮጵያ በቅርብ ዓመታት በልዩ ትኩረት እየተተገበረ ያለ ሲሆን፣ ዋና ዋና መገለጫዎቹና ፋይዳዎቹ የሚከተሉት ናቸው፦ ​1. ከቀረጥና ታክስ ነፃ መሆን ​በነፃ የንግድ ቀጠና ውስጥ የሚገቡ ጥሬ እቃዎች፣ ማሽነሪዎችና መለዋወጫዎች የጉምሩክ ቀረጥና ሌሎች ታክሶች (እንደ ተጨማሪ እሴት ታክስ - VAT) አይከፈልባቸውም። ይህም አምራቾችና ነጋዴዎች የመስሪያ ካፒታላቸውን በታክስ ላይ ከማዋል ይልቅ ለምርትና ለንግድ ማስፋፊያ እንዲጠቀሙበት ይረዳቸዋል። ​2. የሎጂስቲክስና የማከማቻ ማዕከልነት ​ቀጠናዎቹ እንደ ትልቅ የንግድ ማዕከል ያገለግላሉ። ለምሳሌ በድሬዳዋ የተከፈተው የመጀመሪያው ነፃ የንግድ ቀጠና፦ • ​ምርቶችን ለማከማቸት (Warehousing)፣ • ​ለማሸግና የንግድ ምልክት ለመለጠፍ፣ • ​ምርቶችን ለመገጣጠም ወይም እሴት ለመጨመር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። ​3. የውጭ ምንዛሬና የወጪ ንግድ (Export) ​የኢትዮጵያ መንግሥት እነዚህን ቀጠናዎች የሚያስፋፋው በዋናነት፦ • ​የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን (FDI) ለመሳብ፣ • ​የወጪ ንግድን በማሳደግ የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ፣ • ​እና ለዜጎች ሰፊ የስራ ዕድል ለመፍጠር ነው። ​4. የቢሮክራሲ ማቅለያ (One-Stop Service) ​በነፃ የንግድ ቀጠና ውስጥ የሚሰሩ ድርጅቶች የንግድ ፈቃድ፣ የጉምሩክ ክሊራንስ እና ሌሎች የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል እንዲያገኙ ይደረጋል። ይህም በኢትዮጵያ የሚታየውን የቢሮክራሲ መጓተት ይቀንሳል። ​5. በኢትዮጵያ ያለውን ልዩነት መረዳት ​ብዙ ጊዜ "ኢንዱስትሪ ፓርክ" እና "ነፃ የንግድ ቀጠና" ይደባለቃሉ። ልዩነታቸው የሚከተለው ነው፦ • ​ኢንዱስትሪ ፓርክ፦ ትኩረቱ "ምርት" ላይ ብቻ ነው። • ​ነፃ የንግድ ቀጠና፦ ከምርት በተጨማሪ ለንግድ፣ ለሎጂስቲክስ፣ ለጅምላ ሽያጭና ለአገልግሎት ክፍት ነው።

#Update በ "ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" ከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ተጨማሪ የ8 ቀን የምርመራ ጊዜ ተፈቀደ። አርቲስቶቹ እና ቲክቶከሮቹ ዛሬ ሚያዚያ 1 ቀ
+1
#Update በ "ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" ከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ተጨማሪ የ8 ቀን የምርመራ ጊዜ ተፈቀደ። አርቲስቶቹ እና ቲክቶከሮቹ ዛሬ ሚያዚያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበዋል። ፖሊስ ባለፉት 12 ቀናት ውስጥ የ150 ምስክሮችን ቃል መቀበሉንና ከተለያዩ ተቋማት ማስረጃዎችን እየሰበሰበ መሆኑን በመግለጽ፣ ቀሪ ምርመራዎችን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል። ፖሊስ እያንዳንዱ ተጠርጣሪ በወንጀል ድርጊቱ ውስጥ የነበረውን ተሳትፎና የጥቅም ትስስር የሚገልጽ ማብራሪያም ለችሎቱ አቅርቧል። በሌላ በኩል የተጠርጣሪ ጠበቆች ደንበኞቻቸው የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆናቸውንና የጤና እክል ያለባቸው መኖሩን በመጥቀስ የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ቢጠይቁም፣ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ፖሊስ ምርመራውን እንዲያጠናቅቅ ተጨማሪ 8 ቀናት ፈቅዷል። በዚህም መሠረት ፖሊስ ክስ ለመመስረት የሚያስችለውን ምርመራ አጠናቆ ለሚያዚያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲቀርብ ትዕዛዝ ተላልፏል። በተጨማሪም የጤና እክል ገጥሟቸዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎች አስፈላጊውን ሕክምና የሚያገኙበት ሁኔታ እንዲመቻች ፍርድ ቤቱ ማዘዙን ኢቢሲ ዘግቧል። ሚያዚያ 1 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia