ch
Feedback
DBU Info

DBU Info

前往频道在 Telegram
5 142
订阅者
-724 小时
-217
-6630
帖子存档
photo content

የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 20ኛ ዙር ምርቃት የፋርማሲ ተመራቂ ብሩክ ደግነት በ3.97 GPA የዋንጫና የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነ ====================== የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 20ኛ ዙር
+7
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 20ኛ ዙር ምርቃት የፋርማሲ ተመራቂ ብሩክ ደግነት በ3.97 GPA የዋንጫና የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነ ====================== የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 20ኛ ዙር የምርቃት ሥነ ሥርዓትን ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው የመመረቂያ አዳራሽ አስመርቋል፡፡ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ የፋርማሲ ትምህርት ክፍል ተመራቂ የሆነው ብሩክ ደግነት 3.97 GPA በማስመዝገብ በወንዶች ዘርፍ የዩኒቨርሲቲው የዋንጫና የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል። በሴቶች ዘርፍ ደግሞ ከማኔጅመንት ትምህርት ክፍል የተመረቀችው ትርንጎ ገዛህኝ 3.96 GPA በማስመዝገብ የዋንጫና የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆናለች። ሁለቱም ተሸላሚ ተማሪዎች ይህን ውጤት ያስመዘገቡት በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ለትምህርታቸው ቅድሚያ በመስጠታቸው መሆኑን ገልጸው፣ በተመረቁበት የሙያ መስክ በትጋት በመስራት ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን ለማገልገል እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡ በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር፣ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባልና የዕለቱ የክብር እንግዳ ዶ/ር መሰረት በቀለ፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስማረ መለሰ፣ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የሴኔት አባላት፣ የተመራቂዎች ቤተሰቦች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስማረ መለሰ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት በሙያ ዘመናቸው ቅንነትን፣ ታማኝነትንና ሙያዊ ሥነ ምግባርን እንዲያስቀድሙ ጥሪ አቅርበዋል። በሥራ ገበታ ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በብቃት ለመቋቋም ራሳቸውን በቀጣይነት እንዲያዘጋጁ፣ የማህበረሰቡን ችግሮች በመቅረፍ ረገድም ሃላፊነታቸውን በታማኝነት እንዲወጡ አሳስበዋል

Congratulations! እንኳን ደስ አላችሁ! የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 20ኛ ዙር የተማሪዎች ምረቃ በዓል ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም
+2
Congratulations! እንኳን ደስ አላችሁ! የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 20ኛ ዙር የተማሪዎች ምረቃ በዓል ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ሀገራዊ እውቅና ለማግኘት የትምህርት ፕሮግራሞችን የውስጥ ግምገማ አካሄደ ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖማክስ ኮሌጅ ሀገራዊ እውቅና ለማግኘት የትምህርት ፕሮግራሞችን የውስጥ ግምገማ አካሄደ ፡፡ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግሩን ያረጉት የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ዲን ሙሃመድ አህመድ (ዶ/ር) የውስጥ ግምገማ ለማድረግ ከአስራት ወ/የስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ለመጡት ባለሙያዎች ምስጋና አቅርበው በፕሮግራሙ በማኔጅመንት በአካውንቲንግና ፋይናንስ እና ኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል በ2018 ዓ.ም ሲሰራ የቆየውን ፕሮግራም የውስጥ ግምገማ (ኢንተርናል አክሪዲቴሽን) የሚካሄድበት መርሃ ግብር እንደሆነ በመግለፅ ፕሮግራሞቹ ወደ ኢቲኤ(ETA) ለግምገማ ከመቅረባቸው በፊት ባለሙያዎቹ የሚታዩ ክፍተቶችን በመሙላት ማስመዝገብና የተሻለ ውጤት ለማምጣት እንደሆነ በማብራራት ውይይቱ የተሳካ እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡ የመክፈቻ ንግግሩን ያደረጉት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጌትነት አሸናፊ (ዶ/ር) ፕሮግራሙን አስመልክተው እነደተናገሩት ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ፣በአካውንቲንግና ፋይናንስ፣ በማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ለመጀመሪያው ኢንተርናል ቫሊዴሽን ለውስጥ ግምገማ ለመድረስ ሃላፊነት ወስደው ስራውን ላከናወኑት ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ቀጥለውም የትምህርት ትራትን ለማስጠበቅ፣ተማሪዎች ተመርቀው ሲወጡ የተሻለ እውቀት፣ክህሎትና መልካም አመለካከት እንዲኖራቸውና ተወዳዳሪ መሆን እንዲችሉ በአክሪዲቴሽን ሂደት ውስጥ ማለፍ ግዴታ እንደሆነ አስገንዝበዋል፡፡ በመሆኑም ፕሮግራሙ በ2015 ዓ.ም በአወትካም ቤዝድ ካሪኩለም ተማሪዎችን በመቀበል ሂደት የተጀመረ መሆኑን ገልፀው መረጃዎች (ዶኪሜንቶች) የአክሪዲቴሽንን ሰታንዳርድ በጠበቀ መንገድ መዘጋጀታቸው ለሚገመገሙት ፕሮግራም መልካም አጋጣሚ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ከአስራት ወልደየስ ጤና ካምፓስ የመጡት ገምጋሚ መ/ራን የቀረቡ ስራዎችን በመመልከት፣ ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት ለችግሮቹ መፍትሄ በማስቀመጥ ግምገማ እንዲያደርጉ በማሳሰብ ውይይቱ የተሻለና ውጤታማ እንዲሆን በመናገር የእለቱን መርሃ ግብር ከፍተዋል፡፡ በእለቱም 11 የግምገማ ፅሁፎች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን በቀረቡት ፅሁፎች ዙሪያ ከገምጋሚዎች ጥያቄዎች፣አስተያየቶችና ገንቢ ሃሳቦች ቀርበዋል፡፡በቀረቡት ጥያቄዎች፣ ሃሳብና አስተያየቶች ላይ ፅሁፉን ባቀረቡት ምሁራን ምላሽና ማብራሪያ ተደርጎባቸው የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡

photo content

የመረጃ አረዳድ ላይ የተፈጠረን ክፍተት ለማብራራት የተሰጠ ማሳሰቢያ ======================================= ሰኞ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የኢፊዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት የ11 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ከ ኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ጋር ተያይዞ የተነሳውን ሐሳብ አስመልክቶ በስህተት በመረዳት በትላንትናው እለት “የማስተርስ ትምህርት ወደ 4 ዓመት ሊያድግ ይገባል” በሚል ርዕስ በተለያየዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወር የዋለው መረጃ የአረዳድ ችግር እንጂ ምንም ዓይነት ህጋዊ መሠረት የሌለው መሆኑን እየገለጽን፤ የሁለተኛ ዲግሪ (Master Degree) ትምህርትን በተመለከተ ምንም የተቀየረ ደንብ የሌለ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን ፡፡ ለተጨማሪ መረጃ ከዚህ በታች የሚገኘውን “የኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ደንብ ቁጥር 561/2016” እንድትመለከቱ እናሳስባለን፡፡ የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን FDRE Education and Training Authority-ETA

#በአብክመ ት/ቢሮ የመምህራን ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ ትም/ት ማሻሻያ ማስፈጸሚያ መመሪያ @amhara_education
+9
#በአብክመ ት/ቢሮ የመምህራን ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ ትም/ት ማሻሻያ ማስፈጸሚያ መመሪያ @amhara_education

ደብረ ብርሃን ያሉ ትራፊክ ፖሊሶች መልካም ናቸው እኔ ያየኋቸው ባለፈ ከደብረ ብርሃን ወደ አዲስ አበባ ስሔድ 500 ብር ክፈሉ ተብለን ከፍለን እየሔድን እያለ ጫጫ መውጫ አንድ ትራፊክ ወደ መኪናው ገብቶ ሲጠይቅ 500 መሆኑን ሲሠማ ታሪፉ 370 ብር ነው 130 ብር እኔ እያየሁ መልስ ብሎ ለሁሉም አስመለሰ "ይኸን ጊዜ ተሳስበን ብናሳልፈው አይሻልም እዚህ ውስጥ ቁርስ ያልበላ ይኖራል አዲስ አበባ የታክሲም ይቸግራቸው ይሆናል ብሎን " በሉ በሠላም ግቡ ብሎ ሸኘን። K.A

photo content

I like
I like

photo content

ነጠላ፣ ጋቢ፣ ሳሪያን ቅድ ኮት፣ በርኖስ፣ ተነፋነፍ፣ አራት ወርድ የሴቶች ቀሚስና ራስ ላይ የሚጠመጠም ሻሽ ዋነኞቹ የደብረ ብርሃን የባህል አልባሳት::

photo content
+4

photo content
+9

ሊጠፉ የተቃረቡ የደብረ ብርሃን ከተማ እና አካባቢው ነባር አልባሳትን ከመጥፋት ለመታደግ ታዋቂ ሰዎች በመልበስ አርአያ ሊሆኑ እንደሚገባ ተገለጠ ​የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ በባህላዊ አልባሳት ዙሪያ የተጠና ጥናታዊ ጽሑፍ ይፋ አድርጓል። ​የመምሪያው ኃላፊ አቶ ተክለዮሐንስ ኃይለጊዮርጊስ እንደገለጹት፤ ባህላዊ አልባሳት ለውበትና ለአየር ንብረት መቋቋሚያ ብቻ ሳይሆኑ የማዕረግ፣ የስልጣን፣ የክህነት፣ የሥራ፣ የስልጣኔ እንዲሁም የጥበብ መገለጫዎች ናቸው። ደብረ ብርሃን ጥንታዊ ከተማ እንደመሆኑ የራሱ መለያ የሆኑ የባህል አልባሳት ያሉት ቢሆንም፣ በጊዜ ሂደት እየጠፉ በመምጣታቸው ይህንን ጥናት ማካሄድ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ኃላፊው አስረድተዋል። ​ጥናታዊ ጽሑፉን ያቀረቡት በመምሪያው የባህል እሴቶችና ኢንዱስትሪ ቡድን መሪ አይናለም አሰፋ በበኩላቸው፤ የደብረ ብርሃን ከተማ የባህል አልባሳት የዘወትርና የክት ተብለው እንደሚከፈሉ ገልጸዋል። በዋናነትም ነጠላ፣ ጋቢ፣ ሳሪያን ቅድ ኮት፣ በርኖስ፣ ተነፋነፍ፣ አራት ወርድ የሴቶች ቀሚስና ራስ ላይ የሚጠመጠም ሻሽ ዋነኞቹ የደብረ ብርሃን የባህል አልባሳት መሆናቸውን ጠቁመዋል። ​እነዚህ አልባሳት እንዳይጠፉና ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ አርቲስቶችና ምሁራን በተግባር በመልበስ ምሳሌ ሊሆኑ እንደሚገባ ቡድን መሪዋ አሳስበዋል። ይህ መሆኑ ማንነትና ባህልን ከማስተዋወቅ ባለፈ፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና ለቱሪዝም ገቢ ማመንጫ እንደሚሆን ገልጸው፣ ለዚህም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትብብር ሊሠሩ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። ​በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የታሪክና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የአጼ ዘርዓ ያዕቆብ የባህል፣ የታሪክና ቋንቋ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዘመነወርቅ ዮሐንስ (ዶ/ር)፤ የባህል አልባሳቱ የቀደምት ትውልድን የአስተሳሰብ ልዕልና፣ የስልጣኔና የጥበብ መገለጫዎች መሆናቸውን ገልጸው፣ ይህንን ጥበብ መጠበቅ፣ ማስተላለፍና ማሳደግ እንደሚገባ አሳስበዋል። ​በመድረኩ ላይ የታደሙት አቶ ትዕዛዙ ገብረጻዲቅ ጥናታዊ ጽሑፉ በተለይ በእድሜ የገፉ ሰዎችን ቁጭት የገለጠና ለቀጣዩ ትውልድ አደራ የሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛዋ ተሳታፊ ወይዘሮ እታበዝ ሐጂ በበኩላቸው ያደጉበትን የባህል ልብስ ቀድሞ ባለማወቃቸው ቁጭት ይሰማቸው እንደነበርና ይህ ጥናት ግን የባህል ልብሳቸውን በሚገባ እንዲያውቁ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል። አሚኮ ​ዘጋቢ፦ ለዓለም ለይኩን

የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሰጠው የክረምት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በትምህርት ጥራት ላይ ለውጥ ማምጣቱ ተገለጠ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ላለፉት ሁለት ዓመታት የሰጠው የክረምት ልዩ የአቅም ማጎል
+5
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሰጠው የክረምት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በትምህርት ጥራት ላይ ለውጥ ማምጣቱ ተገለጠ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ላለፉት ሁለት ዓመታት የሰጠው የክረምት ልዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በመምህራን የማስተማር ክህሎት፣ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና በተማሪዎች የማለፍ ምጣኔ ላይ መሻሻል ማምጣቱን የድህረ-ስልጠና የጥናት ውጤት አመለከተ። ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ሚኒስቴር አነሳሽነት በ2016 እና በ2017 ዓ.ም የሰጠውን የዚህን ስልጠና የዳሰሳ ጥናት ግኝት አስመልክቶ ዛሬ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል። ዩኒቨርሲቲው በአማራ ክልል ለደብረ ብርሃን ከተማና ለሰሜን ሸዋ ዞን ለሚገኙ 3 ሺህ 900 በላይ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራንና የትምህርት አመራሮች በሁለት ዙር ስልጠናውን ሰጥቷል። የዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራት ዳይሬክተር ታምራት ቸሩ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ተቋሙ በ2016 ዓ.ም በተፈጥሮ ሳይንስ፣ በፔዳጎጂና በእንግሊዘኛ ቋንቋ 1 ሺህ 41 ሰልጣኞችን ያሰለጠነ ሲሆን፤ በ2017 ዓ.ም ደግሞ በማህበራዊ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂን ጨምሮ 2 ሺህ 934 ሰልጣኞችን በ12 የትምህርት ፕሮግራሞች አሰልጥኗል። በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና ትምህርት አመራር ልማት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ጢሞቲዎስ ሞጃ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ያስፈለገው ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎችን ቁጥር ለማሻሻልና መምህራንን ከአዲሱ የትምህርት ፍኖተ-ካርታ ጋር በአግባቡ ለማስተዋወቅ መሆኑን ገልጸዋል። ለትምህርት ጥራት መሻሻል የመምህራን ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በእውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት ያሉ ክፍተቶችን ለመሙላት ስልጠናው ትልቅ እገዛ ማድረጉንም አክለዋል። የዳሰሳ ጥናቱ ውጤት እንደሚያሳየው ስልጠናው በመምህራን የማስተማር ዘዴና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ከፍተኛ

photo content

Never Give Up!
Never Give Up!

ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አመታዊ የምርምርና ፕሮጀክት ትልመ-ጥናት ግምገማ አካሄደ፡፡ ═══════ ❁✿❁ ═══════ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም፡፡ ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የምርም
+5
ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አመታዊ የምርምርና ፕሮጀክት ትልመ-ጥናት ግምገማ አካሄደ፡፡ ═══════ ❁✿❁ ═══════ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም፡፡ ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ ፕሬዚዳንት ፅ/ቤት ከ ሰኔ15-ሰኔ17/2018ዓ.ም ድረስ በምርምር ህትመት ስነ-ምግባርና ስርፀት ዳይሬክቶሬት ፣በማህበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ስር የሚሰሩ የምርምር ስራዎች አመታዊ የምርምርና ፕሮጀክት ትልመ-ጥናት ግምገማ አካሄደ፡፡ የመክፈቻ ንግግሩን ያደረጉት የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የምርምር ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ ፕሬዚዳንት ሲሳይ ሙላቴ (ዶ/ር) መርሃ ግብሩን አስመልክተው እንደተናገሩት በመርሃ ግብሩ የቀረቡት የምርምር ፕሮጀክት ፕሮፖዛሎች ከባለፉት ኦፕን ዲፌንሶች(ፅብረቃዎች) እጅግ የተሻሉ መሆን እንዳለባቸውና በተቀመጡት ግቦች መሰረት ውጤታማ መሆን እንዲችሉና በማህበረሰብ ጉድኝት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር የሚሰሩ የምርምር ስራዎች ወደ ማህበረሰቡ በማውረድ ችግር መፍታት የሚችሉ ፣የኢንዱስትሪዎችን የአሰራር ስርአትን በማሻሻል ምርታማነትንና ጥራትን ለማስጠበቅ እንዲቻል፣ እንደ ተግባር ዩኒቨርሲቲ ምርምሮች ችግር ፊቺ መሆን እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ ቀጥለውም የሚቀርቡት የምርምር ፕሮፖዛሎች ጥራታቸውን ለመጨመር በውጭና በውስጥ የሚነሱ የግምገማ ሃሳቦች ላይ ትኩረት ሰጥተው በመከታተል የሚስተዋልባቸውን ችግሮች በመለየት በውይይቱ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በማሳሰብ የእለቱን ፕሮግራም ከፍተዋል፡፡ የፕሮግራሙ አስተባባሪ የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር መቅደስ ጌራወርቅ እንደገለፁት በ2019ዓ.ም ሊሰሩ የሚችሉ የምርምር፣ የማህበረሰብ ጉድኝትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምርምሮችና ፕሮጀክቶችን ኦፕን