ch
Feedback
ስልጤ ዞን ኮሚዩኒኬሽን - SILTIE ZONE COMMUNICATION

ስልጤ ዞን ኮሚዩኒኬሽን - SILTIE ZONE COMMUNICATION

前往频道在 Telegram
2 689
订阅者
-124 小时
+27
-1030
帖子存档
በሴቶችና ህፃናት ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ላይ ያተኮረ የ2018 በጀት ዓመት የሴቶች ልማትና ንቅናቄ ሥራዎች አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ለመምከር የተዘጋጀው ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ! (ወራቤ ፣ሐምሌ 24/2018)የስልጤ ዞን የሴቶችና ህፃናት መምሪያ "የሴቶች አቅምና ንቁ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላምና ብልፅግና!"በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት ዓመት የሴቶች ልማትና ንቅናቄ ሥራዎች አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ለመለየት የተዘጋጀው የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ የሴቶች ልማት ህብረት ስትሪንግ ኮሚቴ እና የፆታዊ ጥቃትና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት አስወጋጅ ግብረ ኃይል በዓመቱ የተመዘገቡ ውጤቶችን፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን እና በቀጣይ በሴቶች ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ላይ የሚሰጡ ትኩረቶችን በስፋት ገምግመዋል። የስልጤ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ረዳት የመግስት ተጠሪና የፖለቲካና ርዕዮተ አለም ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሱነሞ ሴቶች በተለያዩ የልማት መስኮች እያሳዩ ያሉት ንቁ ተሳትፎ በኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው ላይ ብቻ ሳይሆን በማህበራዊ መረጋጋት በሰላም እሴት ግንባታና በአጠቃላይ የዞኑ ልማት ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑ ጠቅሷል። በኢኮኖሚ ዘርፍ ሴቶች በቡድን በመደራጀትና የገበያ ትስስር በመፍጠር እንደ ካሮትና ጎመን ያሉ የግብርና ምርቶችን እስከ አዲስ አበባ ድረስ በማቅረብ አበረታች ውጤቶችን እያስመዘገቡ መሆናቸው ገልዋል። የሴቶች የኢኮኖሚ አቅም መጎልበት በቤተሰብ ውስጥ የነበሩ ግጭቶችን በመቀነስ ወደ ፍርድ ቤት የሚደርሱ የክርክር ጉዳዮችን እንዲቀንሱ አስተዋጽኦ ማድረጉም ጠቁሟል። በፖለቲካው ዘርፍም ሴቶች በዘንድሮው የምርጫ ሂደቶችና በተለያዩ የአመራር እርከኖች ላይ ያላቸው ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱና ይበል የሚያስብል ስራ መሰራቱንም አንስተዋል። በማህበራዊ ዘርፍም ከጤና ጥበቃ፣ ከጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች መከላከልና የማህበረሰብ ንቃተ ህሊና ግንባታ ጋር ተያይዘው የተሰሩ ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸው ገልፀዋል። ተቋማት ከታች እስከ ላይ በቅንጅት መስራት እንዳለባቸውና በዋናነትም ተቋማዊ ግድፈቶችን ማጥራት፣ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናቀቅ፣ እሴቶችን መጠበቅና ወደ ላቀ ደረጃ መሸጋገር እንዲሁም አሉታዊ አሰራሮችን መቀነስ ላይ በተገቢው መስራት ይጠበቃል ብለዋል። ሴቶች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የአረንጓዴ አሻራ እና የትምህርት ስራዎችን ማጠናከር ላን ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው ኃላፊው መልዕክት አስተላልፈዋል። የስልጤ ዞን የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ኸይሪያ ስርሞሎ በ2018 በጀት ዓመት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የህፃናትን መብት ለማስጠበቅ አመርቂ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል። ሴቶች በቁጠባ፣ በህብረት ሥራ ማህበራት እና በጓሮ አትክልት ልማት ላይ ያሳዩት ተሳትፎ የቤተሰብን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱንም ጨምረው ገልጿል። ሴቶች በአቅራቢያቸው መቆጠብና ብድር ማግኘት እንዲችሉ ሁሉም የልማት ህብረት አባላት የሆኑ ሴቶች የህብረት ስራ ማህበራት አባል መሆን እንደሚገባቸው አጽንኦት ሰጥቶታል። የሴቶች ተጠቃሚነት ሲረጋገጥ ማህበረሰቡ ይለወጣል ያሉት ወ/ሮ ኸይሪያ የጤና፣ የትምህርት፣ የግብርና እና የፍትህ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩ የሚያስችሉ የቴክኒክና የስትሪንግ ኮሚቴዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል። ሞዴል ቀበሌዎችን ማስፋፋት በአንድ ማዕከል የተቀናጀ አገልግሎት የሚሰጡ ሞዴል ቀበሌዎችንና ወረዳዎችን ቁጥር ማሳደግ ይገባል ብለዋል። "ሞዴል" የተባሉ አካባቢዎች ተሞክሮአቸውን ለሌሎች እንዲያካፍሉና በ2019 የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም አካል በቁርጠኝነት እንዲነሳ ጥሪ አቅርቧል። በሴቶች ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማጠናከር በ2018 በጀት ዓመት የተከናወኑ የሴቶች ልማት ቡድንና የንቅናቄ ስራዎችን የሚያሳይ አጠቃላይ የአፈፃፀም ሪፖርት በመምሪያው ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ መህዲያ ሀምዳላ ቀርቧል። ሪፖርቱ በዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት የተመዘገቡ ውጤቶች ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና በቀጣይ ትኩረት የሚሰጣቸውን የስራ አቅጣጫዎች ላይ ወ/ሮ መህዲያ በዝርዝር አቅርበው ተሳታፊዎች ሰፋ ያለ ውይይት አድርጓል። የሴቶችን የኢኮኖሚ የፖለቲካና የማህበራዊ ተሳትፎ ይበልጥ ለማጠናከር የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን በዘላቂነት ለማስቀጠልና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ሁሉም የአመራር አካላት በቅንጅትና በልዩ ትኩረት እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል። በመጨረሻም የዞኑ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ በ2019 በጀት አመት በሚሰሩ የዘርፉ ተግባራት ላይ ከዞን ከሚመለከታቸው መዋቅሮች ጋር የግብ ስምምነት በመፈራረም መድረኩ ተጠናቋል።

ተግባራትን አቀናጅቶ በመምራት የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከምንጊዜውም በላይ በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል! :- ክብርት ወ/ሮ ነኢማ ሙኒር ወራቤ ሐምሌ 23/2018 ስልጤ ዞን ኮሙኒኬሽን ተግባራትን በተቀናጀ እና በተደራጀ መልኩ በመምራት የዞኑን ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከምንጊዜውም በላይ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ የስልጤ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ ክብርት ወ/ሮ ነኢማ ሙኒር ገለፁ። ክብርት ወ/ሮ ነኢማ ሙኒር ይህንን ያሉት በዛሬው ዕለት የዞኑን የካቢኔ አባላት ያካተተ ጠንካራ የድጋፍና ክትትል ቡድን በማዋቀር ለተመደቡት አመራሮች የቀጣይ ስራዎችን አቅጣጫ የሚያስይዝ ጠንካራ ኦሬንቴሽን በሰጡበት ወቅት ነው። በመድረኩ ላይ በዋናነት ከተነሱት አጀንዳዎች መካከል የመጀመሪያው ከተረጂነት ወደ ሉዓላዊነት የመሸጋገር ሀገራዊ ራዕይ ሲሆን በምግብ ዋስትና እና በምርት እድገት እራስን መቻል ሙሉ የሀገር ሉዓላዊነትን እንደሚያረጋግጥ የገለፁት ኃላፊዋ ማህበረሰቡን ከእርዳታ ጠባቂነት አውጥቶ አምራችና ምርታማ ወደ ሚያደርጉ አሰራሮች መቀየር ቀዳሚ ትኩረት እንደሚሰጠው ገልፀዋል። ክብርት ወ/ሮ ነኢማ አክለውም ከእርዳታ ጥገኝነት በመውጣትና የራስን አቅም ለመገንባት ትኩረት በማድረግ ማህበረሰቡ በውስጡ ያለውን እምቅ አቅም፣ የተፈጥሮ ፀጋዎች እና የሰው ኃይል በአግባቡ በመጠቀም በራሱ የሚቆምበትን መንገድ አጠናክሮ መሄድ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል። ይህንንም ለማሳካት በሁሉም የልማት መስኮች አዳዲስ የፈጠራ ሃሳቦችንና የውስጥ ሀብት የማንቀሳቀስ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን ገልጿል። የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራትን አጠናክሮ መሄድ እንደሚያስፈልግ ያነሱት ክብርት ወ/ሮ ነኢማ በክረምቱ ወቅት የሚከናወኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የበጎ ፈቃድ ስራዎች በሁሉም የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር መዋቅሮች ተቀራራቢ አፈፃፀም እንዲኖራቸው ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል። ክብርት ነኢማ አክለውም አቅመ ደካሞችን ከመደገፍ እስከ አረንጓዴ አሻራ ድረስ ያሉት ተግባራት በእኩል ትኩረት ሊመሩ እንደሚገባም አሳስቧል። የሀገር መከላከያ ሠራዊት ምልመላ እና የኤልኒኖ ክስተት ተፅዕኖዎችን መቋቋም ላይ አመራሩ ትኩረት አድርጎ መሥራት እንደሚገባውም ክብርት ወ/ሮ ነኢማ ሙኒር ገልፀዋል። የሀገርን ሰላምና ደኅንነት የሚያስጠብቅ ጠንካራ የመከላከያ ኃይል ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የዞኑ ማኅበረሰብ የሚጠበቅበትን ድርሻ እንዲያበረክት የማስተባበር ሥራ ይሠራል ያሉት ኃላፊዋ በተመሳሳይ መልኩ የአየር ንብረት ለውጥ ያመጣውን የኤልኒኖ ክስተት ተፅዕኖ ለመቋቋም እና ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን ለመከላከል ቅድመ ዝግጅትና የመፍትሔ ሥራዎችን አጠናክሮ መሄድ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። በመጨረሻም የተዋቀረው የድጋፍና ክትትል ቲም ወደ ተመደበበት መዋቅር በመውረድ እነዚህን አምስት ዋና ዋና አጀንዳዎች መሬት የማውረድ፣ አመራሩንና ህዝቡን የማስተባበር እንዲሁም የተግባር ውጤታማነትን የመከታተል ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንዳለበት ክብርት ወ/ሮ ነኢማ ሙኒር አሳስበዋል።የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የህዝብ ግንኙነት

እንኳን ደስ አላችሁ/አለን!! የስልጤ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ በክልሉ ካሉ መዋቅሮች በአጠቃላይ በ2018 አፈፃፀም 2ኛ ደረጃን እና በ"ኢትዮ ኮደርስ" ኢኒሼቲቭ የላቀ ውጤት በማስመዝገብ 3ኛ ደረጃ በመያዝ የዋንጫና የሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነ! ወራቤ፤ ሀምሌ 23/2018 ስልጤ ዝን ኮሙኒኬሽን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የ2018 ዓ.ም አመታዊ የዕቅድ አፈፃፀም ጉባኤ በዛሬው እለት አካሄዷል። ቢሮው ባካሄደው አመታዊ ጉባኤ የስልጤ ዞን ሳይንስና ኢንፍርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ በክልሉ ካሉ መዋቅሮች 2ኛ ሆኖ በማጠናቀቅ ዘመናዊ ላፕቶፕ፣ ኮምፒውተር፣ የጥገናና የኔትወርክ ኪቶች እንዲሁም የዋንጫና የሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆኖዋል። በሌላም በኩል መምሪያው በክልሉ ካሉ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በ"ኢትዮ ኮደርስ" ኢኒሼቲቭ የላቀ ውጤት በማስመዝገቡ 3ኛ ደረጃን በመያዝ የታብሌትና የሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆኗዋል። በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!! እንኳን ደስ አለን!!

በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በምስራቅ ስልጢ ወረዳ በተጠናከረ መልኩ ቀጥሏል። የበጎነት ተግባር የመደጋገፍ፣ የመረዳዳት እና የማህበራዊ አንድነት እሴቶችን በተግባር የሚያሳይ ተምሳሌታዊ ሥራ መሆኑ ተገልጿል። በዚሁ ወቅት የምስራቅ ስልጢ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሎ ፋኔ፣ "በጎነት ማለት በትንሽ አውጥተን ትልቅ የህሊና እረፍት የምናገኝበት ተግባር ነው።" በማለት ሁሉም ዜጎች የበጎ ፈቃድ ተግባራትን በማጠናከር ለተቸገሩ ወገኖች ደራሽ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል። የክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በምስራቅ ስልጢ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች በተጠናከረ ሁኔታ እየተካሄደ ሲሆን፣ አቅመ ደካሞችን በመደገፍና የአብሮነት ባህልን በማጎልበት የተሻለ ማህበረሰብ ለመገንባት ያለመ መሆኑ ተጠቅሷል። ሀምሌ 19/2018 Via:-ምስራቅ ስልጢ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

በስልጤ ዞን በ2018 በጀት ዓመት በተከናወኑ የፍትህ፣ የህግ ማስከበር እና የታክስ ስርዓትን የመጠበቅ ስራዎች ከ79 ሚሊዮን ብር በላይ የህዝብና የመንግስት ሀብት ማስመለስ እና ማስጠበቅ መቻሉን የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ አስታወቀ። ወራቤ-ሀምሌ 19-2018-(ስልጤ ዞን ኮሙኒኬሽን)! የመምሪያው ሃላፊ አቶ ሬድዋን ኑሪ የ12 ወራት (ዓመታዊ) የፍትህ ስራዎች አፈጻጸምን አስመልክተው ለዞኑ የመንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡት ውጤቶች የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታትና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተቋማዊ ሪፎርሞች የተገኙ ናቸው ብለዋል። አቶ ሬድዋን በመግለጫቸው እንዳመላከቱት በበጀት ዓመቱ በዞኑ የቀረቡ 1,033 የምርመራ መዛግብት (1,257 ተከሳሾችን የሚያቅፉ) ላይ 100 በመቶ ውሳኔ በመስጠት ሙሉ በሙሉ የማጥራት ስራ ተከናውኗል። በፍርድ ቤት ክርክር ሂደትም በመዛግብት 98.03 በመቶ እንዲሁም በተከሳሾች 98.37 በመቶ ጥፋተኛ የማስባልና የማስቀጣት ስኬት የተመዘገበ ሲሆን፣ በከባድ ወንጀሎች ላይ የማስቀጣት ምጣኔው 100 በመቶ መሆኑን ተናግረዋል። የሙስና እና የታክስ ነክ ወንጀሎችን የመከላከል ስራን አስመልክቶ አቶ ሬድዋን ሲያብራሩ፤ ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዘ ከተመዘበረው 9.6 ሚሊዮን ብር ውስጥ 93.4 በመቶው ወይም 9.01 ሚሊዮን ብር በድርድር ማስመለስ ተችሏል። በተጨማሪም በኮንትራክተሮች ያልተከፈለ የሰራተኞች ስራ ግብር እና የኦዲት ጉድለትን ጨምሮ 26.6 ሚሊዮን ብር የታክስ ገቢ 100 በመቶ ለመንግስት ገቢ መደረጉን ገልጸዋል። በፍትሃብሔር ጉዳዮች በችሎት ክርክር፣ በድርድር እና በአፈጻጸም ሂደት በአጠቃላይ 43.8 ሚሊዮን ብር በላይ ለመንግስት ገቢ መደረጉን የጠቆሙት ሃላፊው፤ በዚሁ ሴክተር 345 ነጥብ 32 ሄክታር የገጠር መሬት እና ከ27 ሺህ ካሬ ሜትር በላይ የከተማ መሬት ህገ-ወጥ ወረራ ተከልክሎ ለመንግስት እንዲጠበቅ መደረጉን አብራርተዋል። የዜጎችን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብት ለማስጠበቅ የተከናወኑ ተግባራትን ያስረዱት አቶ ሬድዋን ኑሪ፤ ለ133 አረጋውያን፣ ሴቶች፣ ህጻናት እና አካል ጉዳተኞች ነፃ የህግ ድጋፍ አገልግሎት መሰጠቱን እና በሴቶችና ህጻናት ጥቃት ካሳ ክስ 474 ሺህ ብር በላይ በፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲከፈል መደረጉን ገልጸዋል። በተጨማሪም የወንጀል ስጋቶችን በዘላቂነት ለመቀነስ ለ735 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች የንቃተ-ህግ ትምህርት መሰጠቱን አክለዋል። የመምሪያው ሃላፊ አቶ ሬድዋን ኑሪ በመግለጫቸው ማጠቃለያ፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን በዲጂታል ሲስተም በማስደገፍ፣ አሰራርን በማጠናከር እና ህገ-ወጥ የሰነድ ማጭበርበር ድርጊቶችን በመከላከል ረገድ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ይበልጥ በማስቀጠል በ2019 በጀት ዓመት የተሻሉ ስራዎችን ለመስራት ከሁሉም መዋቅሮች የበጀት አመቱን የ 12 ወር አፈጻጸም በጋራ በተገመገመት መድረግ የጋራ መግባባት እንደተፈጠረበት አረጋግጠዋል።

‎በወራቤ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የዶክተሮች መኖሪያ ቤት ተጎበኘ! ‎ ‎​ወራቤ -ሀምሌ 14በወራቤ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የዶክተሮች መኖሪያ ቤት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ በስልጤ ዞንና በሆስፒታሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተጎበኘ። ‎ ‎​በጉብኝቱ ወቅት የወራቤ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ካሊድ ሸረፋ እንደገለጹት፤ ሆስፒታሉ ለአካባቢውና ለጎረቤት ዞኖች ማህበረሰብ የሚሰጠውን የሕክምና አገልግሎት ጥራት ለማሳደግና ባለሙያዎችን ለማቆየት የመኖሪያ ቤት ችግር ዋነኛ ማነቆ እንደነበር አብራርተዋል። ‎ ‎​የዚህ ዘመናዊ የዶክተሮች መኖሪያ ቤት ግንባታ መጠናቀቅ ስፔሻሊስትና ሱፐር ስፔሻሊስት ሐኪሞች በሆስፒታሉ ተረጋግተው እንዲሠሩ ትልቅ አቅም ይፈጥራል። ‎ ‎ይህም ለሕሙማን የሚሰጠውን አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት በአስተማማኝ ሁኔታ ያሳድገዋል ሲሉ ዶክተር ካሊድ ተናግረዋል። ‎ ‎​የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሴ ሀይረዲን በበኩላቸው፣ የጤና ባለሙያዎችን የሥራና የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ለጤናው ዘርፍ ውጤታማነት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ‎ ‎​መንግሥት የሕክምና ተቋማትን በመሠረተ ልማት ከማደራጀት ጎን ለጎን የጤና ባለሙያዎችን ምቹ ሁኔታ የመፍጠር ሥራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል። ‎ ‎የዞኑ ጤና መምሪያም የሆስፒታሉን መሠረተ ልማቶች ለማሟላትና የባለሙያዎችን ፍልሰት ለመግታት የሚያስችሉ ድጋፎችን አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አቶ ሸምሴ ገልጸዋል። ‎ ‎​የመርሐ ግብሩ የክብር እንግዳ የሆኑት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የሕክምና አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሀብቴ ገብረሚካኤል እንደተናገሩት የሆስፒታሉን ደረጃ የሚመጥን የመኖሪያ ቤት ግንባታ ወደ መጠናቀቁ መድረሱ የሚበረታታ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። ‎ ‎​ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎት የሚረጋገጠው በቁርጠኝነት በሚሠሩና የተረጋጋ የመኖሪያና የሥራ አካባቢ ባላቸው ባለሙያዎች ነው ብለዋል። ‎ ‎ የግንባታው ቀሪ ሥራዎችም በጥራትና በተቀመጠላቸው ጊዜ ተጠናቀቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ጥብቅ ክትትል መደረግ እንዳለበት አቶ ሀብቴ ተናግረዋል። ‎ ‎የወራቤ ከተማ አስተዳደር አቶ ያሲን ከሊል በበኩላቸው የጤናውን ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ ደረጃ ለማጎልበት ታስቦ የተገነባውን የዶክተሮች መኖሪያ ቤት አከባቢ የሚሰሩ የመሰረተ ልማት ስራዎችን ለማከናወን የከተማ አስተዳደሩ በቅርበት እንደሚሰራ ተናግሯል። ‎ ‎​የተገነባው የዶክተሮች መኖሪያ ቤት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የሆስፒታሉን የሕክምና አቅም በአስተማማኝ ደረጃ ያሳድገዋል ተብሎ ይጠበቃል። ‎ ‎