African Leadership Excellence Academy
前往频道在 Telegram
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤ በንድፈ-ኃ
显示更多2 789
订阅者
无数据24 小时
+177 天
+10130 天
帖子存档
የትውልድ እና የሃገራዊ ዳግም መነሳት አይቀሬነት እና የመዋቅራዊና ስትራቴጂያዊ እድል ሚና፡ ከግለሰብ እስከ ሃገር
Understanding the Power and the role of luck: From individual's to that of a nation level analysis
By Zadig Abreha
ዛሬ ምሽት
በአፍሌከስ የፌስቡክ እና የዩቲዩብ ገጾች👇
Facebook: https://web.facebook.com/aflexacademy.gov.et
YouTube: https://www.youtube.com/@AfricanLeadershipExcellenceAca
ዕድል🔸 የአጋጣሚ ጉዳይ ሳይሆን፡ ጊዜን ከመጠበቅ፣ አውድን ከመረዳት፣ ከዝግጁነት እና አመቺ ሁኔታዎችን ከመጠቀም የሚመጣ ነው ❗️
እድለኞቹ (ግለሰቦች፣ ተቋማት፣ ከተሞች፣ ሃገራት ........ )
ፍራንሲስ ፉኩያማ 'Why Nations Fail❓' በሚለው መጽሃፉ📖 እድል ለሃገራት ግንባታ እና ውድቀት ያለውን አስተዋጽዖ በሰፊው ተንትኖታል
እኛ (ኢትዮጵያውያን🇪🇹) ምን እድሎች ነበሩን❓ ምን እድሎች አሉን❓ ወደፊትስ ምን እድሎች ይጠብቁናል ❓
እድል ከአጋጣሚ በላይ ብዙ ትርጉም ያለው ሁነት ነው ❗️
👆ብዙ አዳዲስ ነገሮች የሚማሩበት ስልጠና በአፍሌክስ ፕሬዝደንት በዛዲግ አብርሃ
ዘመኑ ሁለት ቅራኔዎችን እያስተናገደ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ዛዲግ "በአንድ ወገን በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ እንደዚህ ዘመን ሀብት የተፈጠረበት ፣ በሌላ መልኩ ደግሞ ፍትሐዊ ያልሆነ የሀብት ክፍፍል የተንሰራፋበት 10% የሚሆኑ ባለሀብቶች 70% የሚሆነውን የዓለም ሀብት የተቆጣጠሩበትና የዓለምን ፖለቲካ እና ኢኮኖሚ የሚዘውሩበት ዘመን ላይ እንገኛለን:: ይህ ደግሞ አፍሪካ የካፒታሊስት ስርዓት ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት የሚያሰናክል ነው" ሲሉ እንቆቅልሹን በማስረጃ አስረድተዋል::
የዚህን ዘመን ሌላ መለያ ባህርይ ያስታወሱት አቶ ዛዲግ "ዘመኑ ስትራቴጂያዊ ውይይት የሚደረግበት ነው" ይላሉ:: "የቆየው ስርዓት ሲነቃነቅ እና አዲስ ስርዓት ለመወለድ በር ሲያንኳኳ ስትራቴጂያዊ ውይይት አስፈላጊ ሆኖ ይከሰታል:: በምዕራቡ ዓለም ተፀንሶ የተወለደው ካፒታሊዝም አስፈላጊነቱ ጥያቄ ውስጥ ገብቷል:: ራሱን አድሶ ፣ አፈር ልሶ ካልተነሳ አደጋ ውስጥ ነው:: ዕድሜውን ጨርሷል:: አፍሪካም የካፒታሊዝምን መሰረተ ልማት ገንብታ ወደ ስራ ካልገባች ከዓለም የኢኮኖሚ ምህዋር ስለምትገለል ስትራቴጂያዊ ውይይት የግድ ነው" ብለዋል::
አውሮፓ ካፒታሊዝምን የመሰረተችው እና ለዓለም ያበረከተችው ለዘመናት መካከል በተደረገ የተቋም ግንባታ እንደሆነና ቻይና እና ህንድም ከቅኝ ግዛት ሰንሰለት ራሳቸውን አላቀው ፣ ከወደቁበት ተነስተው የዓለምን ሁለተኛ እና አምስተኛ ኢኮኖሚ የገነቡት ተቋም ላይ በመስራታቸው እንደሆነ አቶ ዛዲግ ገልጸዋል::
"አፍሪካ ያገኘችውን የሽግግር እድል ሳታባክን በሶምሶማ ወይም በማራቶን ሳይሆን በፈጣን ዝላይ ራሷን የሚመስል የካፒታሊዝም መሰረተ ልማት መገንባት አለባት" የሚሉት አቶ ዛዲግ
ገርበብ ብሎ የተከፈተው ዕድል ሊዘጋ የሚችልበትን ስጋቶችም ጠቅሰዋል " የሰው ሰራሽ አስትውሎት በአፍሪካ ያለውን ርካሽ የሰው ጉልበት መተካቱ ፣ በአፍሪካ ወጣቶችን የሚያካትት እና የሚያስተናግድ ስርዓት አለመገንባቱ እንዲሁም ያልተቀናጀ እና ያልተዋሀደ ስትራቴጂ የዕድል መስኮቱን ሊዘጉት ይችላሉ" ብለዋል::
"የዓለምን 20% የተፈጥሮ ማእድን በጉያዋ የያዘችው አፍሪካ መሰረተ ሰፊ የሆነ የማይታይ የካፒታሊዝም መሰረተ ልማት መገንባት እንዴት ተሳናት?" የሚል ጥያቄን ያነሱት አቶ ዛዲግ "በ2023 በተደረገ ጥናት ከ500 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ አፍሪካዊያን ህጋዊ ማንነታቸውን የሚያረጋግጡበት ዲጂታልም ሆነ የወረቀት መታወቂያ የላቸውም:: ያፈሩትን ሀብት አስመዝግበው የሚጠቀሙበት እና የሚያስተላልፉበት ስርዓት የለም:: የተንዛዛ የቢሮክራሲ አሰራር ከመደበኛው ስርዓት እንዲሸሹ እና ኢ-መደበኛው ጋር እንዲጠጉ አድርጏል" በማለት ማነቆዎችን አብራርተዋል::
በአፍሪካ የካፒታሊዝም ስርዓት ግንባታ ስኬታማ የሚሆነው ሰዎች መብታቸው በህግ አውቅና ሲሰጠው እና ንብረታቸው ጥበቃ ሲደረግለት እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ዛዲግ ለአፍሪካ ችግር መፍትሄ የሚፈልቀው ከራሷ ማጀት እንጂ ከአውሮፓውያን ሳሎን እንዳልሆነም ገልጸዋል::
+2
“የአፍሪካ ካፒታሊዝም ስርዓት ሽል ሆኖ ተፀንሶ መወለድ ካለበት ከልጆቿ ማህፀን እንጂ ከምዕራቡ ዓለም የኪራይ ማህፀን አይደለም” ዛዲግ አብርሃ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም (አፍሌክስ):- የአፍሪካ ካፒታሊዝም ስርዓት ሽል ሆኖ ተፀንሶ መወለድ ያለበት በአህጉሪቷ ማህፀን ውስጥ እንጂ ከምዕራቡ ዓለም በሚገኝ የኪራይ ማህፀን መሆን እንደሌለበት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ::
አቶ ዛዲግ ለብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት አመራሮችና ባለሙያዎች እየሰጡት ባለው ስልጠና ላይ እንደጠቀሱት አፍሪካ ከምዕራቡ ዓለም የምትኮርጃቸውም ሆነ የምትወርሳቸው የኢኮኖሚ ፣ የማህበራዊ እና የፖለቲካ ስርዓቶችና ሞዴሎች ከጫፍ ሳይደርሱ እንደሚጨነግፉ ተናግረዋል::
"አፍሪካ የቀደመ ታሪኳን ፣ የዛሬውን እድሏን እና መፃኢ ተስፋዋን ተጠቅማ ምን አይነት የካፒታሊዝም ስርዓት ብትመሰርት ይህን የግርታ ዘመን ትሻገረዋለች?" የሚል መጠይቅን ያነሱት አቶ ዛዲግ የአፍሪካን እድል እና ስጋት በስፋት ተንትነዋል::
"የሰው ልጅ በዘመኑ እና በታሪኩ ገጥሞት የማያውቅ እድልና ስጋት ከበሩ ቆመዋል:: ይህ በአምስት መቶ ዓመት አንዴ የሚገኝ የበስተቀረ ዘመን የትራንስፎርሜሽን ጊዜ ነው:: ይህ ገርበብ ብሎ የተከፈተው የሽግግር መስኮት ካልተጠቀምንበት ይዘጋል:: አፍሪካም ይህን ዘመን እንዳታጣ የራሷን ሀብትና እውቀት ማዕከል ያደረገ የካፒታሊዝም ስርዓትን ማዋለድ አለባት" ብለዋል አቶ ዛዲግ::
አቶ ዛዲግ አያይዘውም ከድህነት ለማምለጥ የሚደረገውን እልህ አስጨራሽ ትግል የሚያስተጓጉለው ድህነት ውስጥ ነን ወይ? የሚለውን ጥያቄ በአግባቡ መልሶ በጋራ ተማምኖ ስትራቴጂ አዘጋጅቶ ወደ ተግባር ለመግባት መቸገር እንደሆነ አስረድተዋል።
“ድህነት መልከ ብዙ ነው የሀብት እጥረት ብቻ አይደለም፤ በተደጋጋሚ የተነገረን እና አምነን የተቀበልነው እውነታ ነው” የሚሉት አቶ ዛዲግ “ጋኑ እና መክፈቻ ቁልፉ እንዲገናኙ የኢኮኖሚ እና የስርዓት ማነቆዎችን ለይቶ መስራት ተገቢ ነው” ብለዋል።
ድህነት መልካም ወዳጅ ሳይሆን ክፉ ባላጋራ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተው የጠቀሱት አቶ ዛዲግ “ድህነት ካልተሸነፈ እና ካልተቋረጠ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ደጋግሞ እየጎበኘ አንገት ያስደፋል፤ እየገነባን ያለነውን የሰላም እና የዴሞክራሲ ስርዓት ወደ ኋላ ይመልሳል፤ የውሳኔ ስርዓታችንን አዛብቶ ፍትህን ያጓድላል” ሲሉ ተናግረዋል።
ግለሰቦች፤ ተቋማት እና ሀገራት ራሳቸውን ከድህነት ማነቆ አላቀው ወደ ብልጽግና የሚሸጋገሩባቸውን ሳይንሳዊ መንገዶችን ካደጉ ሀገራት ጋር በትይዩ መልክ ያቀረቡት አቶ ዛዲግ “ከድህነት መውጫው መንገድ ራስን፤ ተቋምን እና ሀገርን ለመቀየር ዝግጁ መሆን ነው” ያሉት አቶ ዛዲግ “ከድህነት የሚያወጣን አንደኛው በር ራሳችን የምናዘጋጀው ፍኖተ-ካርታ ነው። ራስን የድህነት ሰለባ አድርጎ ከመቁጠር እና ከመብሰልሰል በአሸናፊነት ስነ-ልቦና ተሞልቶ ችግር መፍቻ መሰረታዊ ክህሎቶች ላይ መስራት፤ ዕውቀትን እንደ አንድ መሳሪያ በመቁጠር ተግቶ መማር፤ አቅምን ማዕከል ያደረገ ቁጠባ ውስጥ መግባት፤ ዘመን ወለድ ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ ራስን ለማሰልጠን መትጋት ያስፈልጋል” ብለዋል።
ከድህነት በማምለጥ የበለጸገ ማህበረሰብ እና ሀገር መሆን የሚቻልባቸውን ስትራቴጂያዊ መንገዶችን በስፋት የተነተኑት አቶ ዛዲግ፤ ድህነትን በዘላቂነት ለማሸነፍ ተቋማት ሰፊ ድርሻ እንዳላቸው አስታውሰው በትምህርት እና ጤና ላይ የሚሰሩ አካታች እና ተወዳዳሪ ተቋማት፤ የመሰረተ ልማት ተደራሽነት፤ ፈጠራ እና የአቅም ግንባታ ስራዎች ከድህነት ለመውጣት የሚያስችሉ እንደሆኑ ተጠቅሷል።
“ድህነትን ለማሸነፍ መሰረታዊ ሽግግር ይፈልጋል፤ በሀገራችን ብልጽግናን የሚያረጋግጥ ስርዓት መገንባት ቅድሚያ የሚሰጠው ሀገራዊ ተግባር ሆኖ ተጀምሯል፤ መሪዎች ብቃትን ፍትሀዊነትን እና ዘላቂነትን በትምምን መልኩ ተቋማዊ እንዲያደርጉ እየተሰራ ነው” ብለዋል አቶ ዛዲግ።
+2
“በድህነት ማነቆ ውስጥ ያሉ ለማምለጥ አይሞክሩም፤ በአንገታቸው ላይ ያለው ሸምቀቆ ስለማይታያቸው አይፈቱትም” ዛዲግ አብርሃ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም (አፍሌክስ):- በድህነት ማነቆ ውስጥ ያሉ ሰዎች ካሉበት ድህነት ውስጥ ለመውጣት እንዳይሞክሩ በአንገታቸው ላይ ያለው ሸምቀቆ ጠፍንጎ ስለያዛቸው እና ስለማይታያቸው ለመፍታት እንደሚቸገሩ የአፍሌክስ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ።
ፕሬዚደንቱ ለብሔራው መታወቂያ አገልግሎት አመራሮች እና ባለሙያዎች ስለ ድህነት ማነቆ እና ማምለጫ መንገዶች ስልጠና ሲሰጡ እንደገለጹት ድህነትን ማሸነፊያ አንዱ እና ዋነኛው መንገድ በድህነት ውስጥ መሆንን ማወቅ እና መረዳት ቀዳሚው ተግባር ቢሆንም በድህነት ውስጥ ያሉ ብዙዎች ግን አብረውት ተስማምተው እየኖሩ እንደሆነ ስለማይረዱ እና በአንገታቸው ላይ ያለው ሸምቀቆ ስለተሰወረባቸው የሸምቀቆውን ውል አግኝተው ለመፍታት እንደሚቸገሩ ተናግረዋል።
+3
“ኢትዮጵያ ከንፈር የሚመጠጥላት እና የሚታዘንላት ሀገር አይደለችም” ዛዲግ አብርሃ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 19 ቀን 2017 ዓ.ም (አፍሌክስ):- ኢትዮጵያ ከንፈር የሚመጠጥላት እና የሚታዘንላት ሳትሆን የምትታፈር እና የምትከበር ሀገር መሆኗን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ::
አቶ ዛዲግ ለብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት አመራሮች እና ባለሙያዎች ስለ ‘ህልም ሀያልነት’ ስልጠና ሲሰጡ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ታሪክ የሚያኮራ እንጂ የሚያሳፍር እንዳልሆነ ጠቅሰው "ሀገራችን በቀደመው ታሪኳ የአፍሪካ የነፃነት ቀንዲል ነበረች አሁን ደግሞ የአህጉሪቷ ቁጥር አንድ ተፅእኖ ፈጣሪ ናት ይህ ደግሞ የሚያስከብር እንጂ የሚያሳፍር አይደለም" ብለዋል::
"ከሞራል ርዕይ አንፃር አድዋ ቋሚ ምስክራችን ፣ የፍትህ መስታወታችን፣ ህያው ቅርሳችን ነው:: ከታሪክ እይታም ቢሆን ጠንካራ መሰረት ያለን ህዝቦች ነን:: ላመንበት ዓላማ መሰዋትም መለያችን ነው:: የነበሩንን ጠንካራ ጎኖች እያጎላን ፣ የሌለንን እየሞላን የመጣን ፣ ነገን በብሩህ ተስፋ እየጠበቅን የምንገኝ ህዝቦች በመሆናችን ከንፈር የሚመጠጥልን አይደለንም" ሲሉ አቶ ዛዲግ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል::
የኢትዮጵያ ህልም በግንባታ ሂደት ላይ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ዛዲግ "ያለፈውን በጎ ትውስታ፣ ኩራት እና ትህትና አሁን ካለን እምቅ አቅም ጋር አዋህደን ከእርዳታ ተቀባይነት ወደ እርዳታ ሰጭነት የሚያሸጋግረንን ህልም ቀርፀናል" ብለዋል::
የኢትዮጵያ ህልም ለመጀመሪያ ጊዜ በሰነድ እና በትርክት መልክ የቀረበው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደሆነና 'ኢትዮ ኤይድ' በሚል ስንዴ ወደ አፍሪካ ሀገራት በእርዳታ እንደተላከ ያስታወሱት አቶ ዛዲግ ይህም የኢትዮጵያን ህልም መዳረሻ በግልፅ የሚያመላክት እንደሆነ ተናግረዋል::
"ኢትዮጵያውያን በህልም ዙሪያ ውይይትና ክርክር የማድረግ ባህላችን ደካማ ነው" ያሉት አቶ ዛዲግ ብሄራዊ ህልም በጋራ ቢታለም ከመወቃቀስ እንድናለን ባይ ናቸው::
አቶ ዛዲግ በስልጠናው ላይ ብሄራዊ ህልም የሚሰራባቸውን መንገዶች ያብራሩ ሲሆን የህልም የጋራ ባለቤትነት ላይ ሀሳብ ሲሰጡም "ሀገራዊ ህልም ከትናንት ትውስታችን፣ ከቁስላችን ፣ ከስቃያችን ፣ ከድላችን እና ከስኬታችን ተቀድቶ ከነገ መዳረሻችን ጋር ይቀናጃል ፣ የግለሰብ ሆኖ ተጀምሮ የሀገር ሆኖ ይደመደማል ብለዋል" አያይዘውም ብሄራዊ ህልም እንደ ሀገር ሮጠን ልንደርስ ያሰብንበትን ስፍራ የሚያመላክት ፣ ማንነታችንን የሚቀርፅ እና አንድነታችንን የሚያዋልድ እንደሆነ አብራርተዋል::
"ህልም በቁርጠኝነት ፣ በተጠያቂነት እና በእቅድ የምንፈፅመው ለትውልዳችን የምናልመው የህይወት ግባችን ነው" የሚሉት አቶ ዛዲግ የሀገራትን የህልም መነሻ እና መድረሻ ታሪካዊ ዳራ በስፋት አንስተዋል:: የአሜሪካን፣ የህንድን ፣ የቻይናን እና የደቡብ ኮሪያን ከኢትዮጵያ ጋር በንፅፅር ያቀረቡ ሲሆን ህልማቸውን ለማጋራት እና ለማሳካት ያከናወኗቸው ተግባራት በአስተማሪነት ቀርበዋል::
የማርቲን ሉተር ኪንግ 'ህልም አለኝ' የሚለው ታሪካዊ ንግግር የአሜሪካንን ህልም ቅርፅ እንዳስያዘ ፣ ማርከስ ማርቬይ ለጥቁር ህዝቦች የኢኮኖሚ እና የመንፈሳዊ ነፃነት ያደረገው ትግል እና ያሳካው ህልም ፣ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ስለ አፍሪካዊነት አልመው የቀድሞውን የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የመሰረቱበት ህልም ፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካውያን የነፃነት ተምሳሌት ሆና ወደ ተቋም ባለቤትነት እንድትሸጋገር እና ትናንትን ከነገ እንድታገናኝ እንዳስቻላት በስልጠናው ላይ ተገልጿል::
ስልጠናው ለአራት ተከታታይ ቀናትም እንደሚቀጥል ታውቋል::
ሂውማኖክራሲ ቅድሚያ የሚሰጠው ለአሰራር እና ስርዓት ሳይሆን ሰው ተኮር አገልግሎት ላይ ነው
ሂውማኖክራሲ ተልዕኮን በባለቤትነት ወስደው የሚፈጽሙ ሰራተኞችን ነው
ሂውማኖክራሲ የግብረ-መልሱ ስርዓት በተገደበ ጊዜ ሳይሆን ከተልዕኮ አፈጻጸም ጋር በተገናኘ በቅጽበት ውስጥ ነው
ሂውማኖክራሲ የመንግስት ሰራተኞች በትብብር ሰርተው ችግራቸውን እንዲሻገሩ ዕድል ይፈጥራል
ሂውማኖክራሲ ተጠያቂነትን ወደ ቡድን አውርዶ ቡድኖች በጋራ እንዲሰሩ ያደርጋል።
ሂውማኖክራሲ ውሳኔ እንዲሰጡ የሚፈቅደው ለችግሩ ቅርብ ለሆኑ ሰዎች ነው
የአፍሪካ አመራር ልእቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብር ስለ ሂውማኖክራሲ ምን አሉ?
ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ፣ የዲስትሪክት ዳይሬክተሮች እና ባለሙያዎች 'መንገድ እና የኢትዮጵያ ማንሰራራት' በሚል ርዕስ ላይ በሰጡት ስልጠና ስለ ሂውማኖክራሲ ይህን ብለዋል:-
ሂውማኖክራሲ መሪዎችን የሚመለከተው እንደ አሰልጣኝ እንጂ እንደ መሪ አይደለም
ሂውማኖክራሲ የሚያተጋው አዳዲስ ሀሳብ የሚያመነጩትን፤ አዳዲስ ውጤት የሚያስመዘግቡትን፤ ራሳቸውን እያስተማሩ የሚጓዙትን፤ ለትብብር ቅድሚያ የሚሰጡትን ነው
ሂውማኖክራሲ የሚፈልገው በምናብ የሩቁን አቅርበው የሚያልሙ የመንግስት ሰራተኞችን ነው
ሂውማኖክራሲ የሚያከብረው ተጠሪነቴ ለአለቃዬ ነው የሚሉትን ሳይሆን ተጠሪነቴ ለተልዕኮዬ ነው የሚሉትን ነው
ሂውማኖክራሲ የሚያከብረው እኔ የተቀጠርኩት ለመታዘዝ ነው የሚሉትን ሳይሆን እኔ ችግር ፈች ነኝ የሚሉትን ነው
ሂውማኖክራሲ የሚያከብረው ተስማምተው በትምምን የሚሰሩትን እንጂ ሀላፊነት የሚሸሹትን አይደለም
ሂውማኖክራሲ የመንግስት ሰራተኛን ችግር ፈች ያደርጋል
ሂውማኖክራሲ ድብቅ አቅምን እና እምቅ ችሎታን ወደ ተጨባጭ ውጤት ይቀይራል።
ሂውማኖክራሲ የሚፈልገው ስልጣን እና ተዋረድን ሳይሆን ከህሎትን ከቆምንለት ዓላማ ጋር እንድናዋህድ ነው
በዓለም አቀፍ ደረጃ ከቢሮክራሲ ወደ ሂውማኖክራሲ እየተደረገ ያለውን ሽግግር በስፋት የጠቀሱት አቶ ዛዲግ " ሂውማኖክራሲ ከንድፈ ሀሳብ በላይ የሆነ ለሰው ልጆች የዘመናት ጥያቄ እና ትግል ምላሽን ይዞ የመጣ የሰውነት ውሀ ልክ ነው:: አገልግሎት ሰጭን ከተቀባይ ጋር በአንድ ዓላማ የሚያሰልፍ ሰዎች ያላቸውን እምቅና ድብቅ አቅም ጎልቶ እንዲወጣ የሚያደርግ ሳይንስ እና ጥበብ ነው"
"ሂውማኖክራሲ ብዙ ሰዎች ሀሳብ እንዲያዋጡ ያበረታታል" የሚሉት አቶ ዛዲግ የላቀ የእርስ በእርስ ግንኙነት ፣ አይበገሬነት ፣ ፍትሀዊነት ፣ ተፅዕኖ ፈጣሪነት እና መተማመን የሂውማኖክራሲ ተጨባጭ ውጤቶች ተደርገው እንደሚወሰዱም ተናግረዋል::
ሰባቱን የሂውማኖክራሲ አዕማዶች ያብራሩት አቶ ዛዲግ " የሰው ልጅ በዕጣ-ፈንታው ላይ ባለቤት መሆን ይፈልጋል:: ሂውማኖክራሲ በባህርይው ህዝብን ከእቅድ ጀምሮ እስከ ውሳኔ ሰጭነት በባለቤትነት ያሳትፋል:: የሚሰራውም የሚያገለግለውም በመመሪያ እና በህግ ብቻ ሳይሆን ሰውነትን ከአሰራር ጋር አሰናስሎ ነው" ብለዋል::
"ሂውማኖክራሲ የሰውን ልጅ በክብር ያስቀመጠ ብቻ ሳይሆን ማህበራዊ ትስስርን በመፍጠር ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ጥልቅ መተማመንን በማዳበር የጋራ ርዕይን ከህዝብ ወደ መንግስት እና ከመንግስት ወደ ህዝብ ያሻግራል" የሚሉት አቶ ዛዲግ ሂውማኖክራሲ በዲሲፕሊን የተገራ ነፃነትን እየፈቀደ ፈጠራን እንደሚያበረታታም ገልፀዋል::
የመንግስትተቋማት የሰው ልጅን ክብር እያስጠበቁ የተደበቀውን እምቅ አቅም እና ችሎታ ለመጠቀም በሚያስችል መልኩ መቀረፅ እንዳለባቸው የሚጠቅሱት አቶ ዛዲግ የመንግስት አስተዳደር የሰውን ልጅ ክብር መጠበቂያ መሳሪያ መሆን እንዳለበትም ጠቁመዋል::
የኢትዮጵያ ማንሰራራት እውን የሚሆነው በታሪኳ ለመጀመሪያ ግዜ በጀመረችው ሰው ተኮር አገልግሎቶች ውስጥ እንደሆነና ቢሮክራሲ ያሳነሰውን የሰው ልጆች ክብር በሂውማኖክራሲ በመተካት ወደ ብልፅግና የሚደረገውን ጉዞ ማሳለጥ እንደሚገባም በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ተነስቷል::
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ይስራ ሃላፊዎች ለአቶ ዛዲግ አብርሃ ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል::
+3
“ቢሮክራሲ የሰውን ልጅ አሳንሶታል:: ሂውማኖክራሲ ግን ክብር አጎናፅፎታል:: የሰው ልጅ ትንሽ ሆኖ እንዲኖር አልተፈጠረም ” ዛዲግ አብርሃ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም (አፍሌክስ):- የአገልግሎት ተቋማት የሚቋቋሙት ፣ የሚቆዩት እና ዘመናትን ተሻግረው የሚቀጥሉት ለሰው ልጆች ክብር እስከሰጡ ብቻ እንደሆነ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ::
ፕሬዚደንቱ ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ፣ የዲስትሪክት ዳይሬክተሮች እና ባለሙያዎች 'መንገድ እና የኢትዮጵያ ማንሰራራት' በሚል ርዕስ በአካል እና በበይነ-መረብ ሲሳተፉ ለነበሩ ሰልጣኞች ለአራት ቀናት ሲሰጡት የነበረው ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል::
አቶ ዛዲግ በማጠቃለያው ስልጠና ላይ እንደጠቀሱት፣ በዚህ በግርታ ዘመን የመንግስት የአገልግሎት ተቋማት ቅድሚያ መስጠት ያለባቸው ለሰው ልጆች ክብር እና ሰው ተኮር አገልግሎት መሆኑን ጠቅሰው ፣ "ሰውነትን ያስቀደመ አገልግሎት ተሻጋሪ ነው:: ተቋማት ለሰዎች አዳጊ ፍላጎት እጅ መስጠት አለባቸው" ብለዋል::
አቶ ዛዲግ አያይዘውም " ከሰው ልጆች ጥቅምና ፍላጎት ጋር አብረው የሚያድጉ እና የሚቀየሩ አገልግሎቶች እና ተቋማት ያስፈልጉናል:: ህዝባችን ለዘመናት ሲናፍቀው የነበረው የሰው ተኮር የአገልግሎት ጥያቄን የሚመልስ አሰራር በመጀመሩ የሰው ልጅ የሚገባውን ክብር እያገኘ ነው" ብለዋል::
+2
በመትከል ማንሰራራት በሚል መሪ ቃል የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ
ሱሉልታ፤ ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ም (አፍሌክስ)፡- የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ (አፍሌክስ) አመራርና ሰራተኞች "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአካዳሚው ቅጥር ግቢ ውስጥ አካሂደዋል።
የችግኝ ተከላው በአገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለው የ2017 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አካል መሆኑ ተገልጿል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የአካዳሚው የአስተዳደር እና ቢዝነስ ልማት ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ከአካዳሚው ቅጥር ግቢ ጀምሮ በአገር እና በአለም አቀፍ ደረጃ ለአየር ንብረት ጥበቃ ትልቅ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ምክትል ርዕሰ አካዳሚው አክለውም፣ አፍሌክስ እንደ አመራር ልማት ማዕከልነቱ በአገር አቀፍ ደረጃ ለሚከወነው ለዚህ መርሃ ግብር አቅጣጫ በመስጠትና በማስተባበር ረገድ ትልቁን ድርሻ የሚወስደው አመራር እንዲኖር በሚወጣው ሚና ላይ ትኩረት ሰጥተው ተናግረዋል።
የአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች በችግኝ ተከላው መርሃ ግብር ላይ በንቃት የተሳተፉ ሲሆን፣ ይህ እንቅስቃሴ የአፍሌክስን የአካባቢ ጥበቃ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
የአስተዳደር እና ቢዝነስ ልማት ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ(ዶ/ር) አሰራር የማዘመን፣ ዲጂታላይዜሽን የማስፋፋት፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ፈትሾ የማስተካከል፣ ጠንካራ ተቋማዊ ቅንጅት የመፍጠር ፣ምርታማነትን የመጨመር እና ከትምህርት ጥራት ጋር በተያያዘ ሀሳቦችን የሰጡ ሲሆን፤ እያንዳንዱ አመራርና ሰራተኛ በሚሰራው ስራ ላይ ሃላፊነት በተሞላበት መንፈስ ተግባሩን ማከናወን እንደሚገባው አሳስበዋል።
የአመራር ልማት ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ መሰረት ደስታ በበኩላቸው በሴክተር ሪፎርም በኩልም ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን እና ኢንፎርሜሽንና መገናኛ ቴክኖሎጂ (ICT) በጣም ተስፋ ሰጪ ውጤት ማምጣታቸውን ጠቅሰው በማህበራዊ ዘርፍም በትምህርት እና በጤና የተገኘው እመርታ ለቀጣይ ዓመት መንደርደሪያ እና የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በድምሩ ሲታይ በ2017 በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፎች የላቀ ስኬት መመዝገቡን መረጃዎችን ዋቢ አድርገው ያስቀመጡት ወ/ሮ መሰረት በግብርናው ዘርፍ፣ በማዕድን እና በቡና ወጪ ንግድ፣ በተኪ ምርት እና በሌሎች ዘርፎች በታሪክ ከፍተኛ ውጤት መምጣቱን አንስተዋል። አመራሩና ባለሙያው ምሉዕ የሆነ ምስል እንዲኖረው እና እንደ አመራር ልማት ተቋም ምን ይጠበቅብናል የሚለውን ለማየት ሰፊ ውይይቶችን በማድረግ እና እርስ በእርስ ሀሳብ በመለዋወጥ ሪፖርቱን እና ዕቅዱን ማዳበር እንደሚቻል ተናግረዋል።
የአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች በሰጡት አስተያየት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፍ አስደናቂ እመርታዎች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ ግልጽ ያልሆኑ እና ማብራሪያ በሚፈልጉ ጉዳዮች ዙሪያ ጥያቄ አንስተው በአካዳሚው ምክትል ርዕሰ አካዳሚዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
+3
በመንግስት የ2017 ዓ.ም በጀት አመት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና በ2018 ዓ.ም በጀት አመት የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሄደ።
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ም (አፍሌክስ)፡- የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አመራርና ሰራተኞች በመንግሰት የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና የ2018 በጀት አመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አድርገዋል።
ሪፖርቱን እና እቅዱን ያቀረቡት የአመራር ልማት ዘርፍ ተወካይ አቶ ጥላሁን አረጋ እንደገለጸት እንደ ሀገር የ2017 በጀት ዓመት በርካታ የፖሊሲ ለውጦች የተደረገበት ዓመት እንደነበርና በተለይም በማክሮ ኢኮኖሚ ዘርፍ በተደረጉ ማሻሻያዎች በርካታ ውጤቶች እንደተመዘገቡ ጠቅሰው በ2017 በጀት አመት በርካታ ትላልቅ ፕሮጀክቶች የተጠናቀቁበት ነበር ያሉት አቶ ጥላሁን በ2018 በጀት ዓመት በመንግስት የሚሰሩ የልማት ስራዎች ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ አዝማሚያዎች ማዕከል ያደረጉ እንደሚሆኑና በመጭው 2018 በጀት ዓመት የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በ9 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።
የሀገራችን የመካከለኛ ዘመን እቅድ በ2018 በጀት ዓመት የሚጠናቀቅ በመሆኑ ቀሪ ተግባራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት ዓመት ጭምር እንደሆነ ያመላከቱት አቶ ጥላሁን እንደ ሀገርና እንደ ተቋም የታቀዱትን እቅዶች በተጨባጭ ለመፈፀም እንዲቻል በቀጣይ የማስፈፀም አቅምን በመፈተሽ የአቅም ግንባታ ስራዎች መስራት ፣የሰውና ሃይል ግንባታ ስራዎችን በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል።
+4
ችግሮቻችንን መፍታት የምንችለው በጦርነት ሳይሆን በመግባባት ሊሆን እንደሚገባ ተገለፀ።
ዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ሀምሌ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
መከላከያ ሰራዊት ለተለያዩ አላማዎች የሚገነባ ቢሆንም የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት ትርፋማ እንደሚያደርግ
በህግና ትምህርት ዘርፍ አማካሪ ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረ ማሪያም ገልፀዋል።
ፕሮፌሰሩ ይህንን የገለፁት ማዕከላዊ ዕዝ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ የነበሩ የዕዙ ገፅታዎች የተሰነዱበት "ሚስጥረ ዕዛችን " የተሰኜ መፅሀፍ የተመረቀ ሲሆን የይዘት ግምገማ በተደረገበት ወቅት ነው።
ኢትዮጵያ የምትቀጥለውና የምትበለፅገው በጦርነት ሳይሆን በተለያዩ መስኮች ተሰማርቶ ለውጥ ማምጣት ሲቻል ነው ያሉት ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማሪያም በመፀሀፉ ውስጥ ሰላምን የሚያቀናቀኑ ፣የኢትዮጵያን ያለፉ ገፅታዎች በመዳሰስ የውትድርናን ባህሪና የዕዙ ተልዕኮን የመፈፀም አቅም በመተንተን ለሰላም የሚበጀውን መንገድ የሚያሳይ መሆኑን በመግለፅ አድናቆታቸውን ገልፀዋል።
የምንገኝበት ዘመን ዕድልም መከራም ይዞ የመጣ ዘመን ነው ያሉት የአፍሪካ ልህቀት ማዕከል ፕሬዝዳንት ዶክተር ዛድግ አብረሀ ናቸው።
በመፅሀፉ ይዘት ግንዛቤያቸውን ባስቀመጡበት ወቅት ቴክኖሎጅው ያመጣውን በጎም ሆነ መጥፎ እድሎችን መቀበልና መመከት የሚያስችል ሰራዊት መገንባት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ ትናንት ያጣቻቸውን ሀብቶቿን በመጠየቋ ያልተዋጠላቸው አካላት በየአቅጣጫው እያዋከቡ ይገኛሉ ያሉት ዶክተር ዛድግ ኢትዮጵያ አሁን ላይ የመጨረሻው ውጤታማ የታሪክ እጥፋት ላይ ትገኛለች። ስለሆነም የኢትዮጵያ ህዝብና መከላከያ ሰራዊቱ ታሪካዊ ሀላፊነቱን ለመወጣት አሁን ያለበትን ጥንካሬ ሊያስቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።
ፕሬዚደንቱ የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥን ታሪካዊ መሰረት በሰፊው ያቀረቡ ሲሆን 'የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ትናንት ፣ ዛሬ እና ነገ' በሚለው ንፅፅራዊ ገለፃቸው ስር "ቀደም ባሉት ዓመታት በሜሶፖታሚያ እና ግብጽ አገልግሎቱ እንደተባረከ እና እንደተቀደሰ እንዲሁም ከፈጣሪ እንደተሰጠ የአደራ ተግባርና መንፈሳዊ ግዴታ ይቆጠር ነበር" የሚሉት አቶ ዛዲግ በጥንታዊት ቻይና የነበረው ደግሞ " የሞራል ልዕልናን መሰረት ያደረገ የአገልግሎት አሰጣጥ እና የመንግስት ሰራተኞች ምልመላ እና ፈተና ነበር" ሲሉም አብራርተዋል::
አቶ ዛዲግ በቀደምት ግሪክ እና ሮም የነበረውን የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ሲያስታውሱም ፣ ህዝብን ማገልገል የዜግነት ግዴታ እንደነበርና ሁሉም ዜጋ በተራ ያገለግል እንደነበር ጠቁመው "በሮም ኢምፓየር ውስጥ የሀይማኖት ተቋማት ፣ ሆስፒታሎች እና ትምህርት ቤቶች አገልግሎትን በሙያዊ መንገድ ይሰጡ ነበር" ብለዋል::
በመካከለኛው ዘመን የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ በንጉሳውያን እጅ ስር ወድቆ የነበረ ቢሆንም የካቶሊክ እምነት ተቋማት በፅህፈት ሙያ ሰፊ ተሳትፎ እንዳደረጉም በገለፃው ላይ ተጠቅሷል::
ከ1500-1800 በነበረው ዘመን መንግስት የአገልግሎት ዘርፉን እየተቆጣጠረ እንደመጣና በተማከለ ስርዓት ውስጥ ቢሮክራሲ ተወለደ የሚሉት አቶ ዛዲግ ፣ ከቅኝ ግዛት ጋር በተያያዘ ቅኝ ገዥዎች ቢሮክራሲን እንደተጠቀሙበት እና በ19ነኛው ክፍለ ዘመን የተቀጣጠለው የኢንዱስትሪ አብዮት ግን የህዝብ አገልግሎቱን ይበልጥ ተፈላጊ እንዳደረገውም አቶ ዛዲግ ተናግረዋል::
የቀደመው ዘመን የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ አገልግሎቱን እንደ ግዴታ መውሰዱ ፣ የስልጣን ተዋረድ መብዛቱ ፣ ሙያን መሰረት ያደረገ አሰራር መፈጠሩ ፣ ቁጥጥርን ማዕከል ማድረጉ ማሳያዎች እንደነበሩ ተጠቅሷል::
"የአሁኑ ዘመን የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ፋታ በማይሰጡ ችግሮች የተወጠረ ነው:: ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ፈጣን የእድገት ባቡር ላይ ተሳፍሯል" የሚሉት አቶ ዛዲግ "በተለመደው አካሄድ አዲሱን ችግር መሻገር አንችልም" ባይ ናቸው::
ከመፃኢው ጊዜ አንፃር የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ "ሰውነት ተኮር ነው" የሚሉት አቶ ዛዲግ "የግል ዘርፉን ለመምሰል ከመሞከር ይልቅ በላቀ መልኩ ዓላማን መሰረት አድርጎ መትጋት ያስፈልጋል:: ከቁጥጥር ስርዓተ ወደ መተሳሰብ እና ትብብር እንዲሁም አሻራን ማዕከል ወዳደረገ ተልእኮ ፈፃሚነት መሸጋገር ግዴታ ነው" ሲሉ ተናግረዋል::
“የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ከቁጥጥር ቀንበር ነፃ ወጥቶ ወደ ትብብር ቀጠና መግባት አለበት” ዛዲግ አብርሃ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም (አፍሌክስ):- የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን ከቁጥጥር እና ክትትል ስርዓት ተላቆ ወደ ትብብር መንፈስ መሸጋገር እንዳለበት ተጠቆመ::
የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ፣ የዲስትሪክት ዳይሬክተሮች እና ባለሙያዎች 'መንገድ እና የኢትዮጵያ ማንሰራራት' በሚል ርዕስ በአካል እና በበይነ-መረብ ለሚሳተፉ ሰልጣኞች እየሰጡት ባለው ስልጠና ላይ እንደገለፁት ፣ የሀገራችን የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ፋታ በማይሰጡ ዘርፈ ብዙ ችግሮች የተወጠረ እና በክትትል እና ቁጥጥር ላይ የተመሰረተ የአመራር ዘይቤን የሚከተል በመሆኑ ከትብብር እና ጤናማ ፉክክር ራሱን ያቀበ እንደሆነ ተናግረዋል::
ዘመኑን ለመዋጀት ችግሮችን ፈጠራ በተሞላበት መንገድ የሚፈታ ፣ አሰራር እና ስርዓትን የሚለውጥ ፣ ወሰን እና ድንበርን ተሻግሮ አገልግሎት የሚሰጥ ፣ ችግርን የሚሸሽ ሳይሆን ተጋፍጦ የሚያሸንፍ ፣ ቁጥጥርን ሳይሆን መተማመንን እና አካታችነትን የሚቀበል የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል::
+2
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከያንግ ሲ.ኢ.ኦ ፎረም ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ
ሱሉልታ - ሐምሌ 10/2017 - (አፍሌክስ) - የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ (አፍሌክስ) በግሉ ዘርፍ ከሚሰራው ያንግ ሲ.ኢ.ኦ ፎረም እና በግንባታና ኢንጂነሪንግ ስራዎች ላይ ከተሰማራው አሚጎስ ኢንስቲቲዩት ጋር በጋራ ለመስራት ትብብር መስርቷል።
ትብብሩ አካዳሚው የአመራር ልማት ስራውን ከመንግስት እና ሲቪል ማህበረሰብ በተጨማሪ በግሉ ዘርፍም እንዲያሰፋ ያስችለዋል።
ከያንግ ሲ.ኢ.ኦ ፎረም ጋር የተደረሰው ስምምነት ከያዛቸው ቁልፍ ተግባራት መካከል በየአመቱ በእንግሊዝ የሚካሄደውን የአፍሪካን ኢኮኖሚ የተመለከተ የቢዝነስ ፎረም ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት በጋራ መስራት ዋነኛው ነው።
የዚህ ፎረም ወደ ኢትዮጵያ መምጣት አፍሪካውያን ስራ ፈጣሪዎች መድረኩን በቅርባቸው እንዲያገኙት ከማስቻሉም በላይ፣ ለኢትዮጵያ የኮንፈረንስ ቱሪዝም እድገት አስተዋጽዖ ያበረክታል እንዲሁም አፍሪካውያን ባለሀብቶች በሀገሪቱ ኢንቨስት እንዲያደርጉ በር ይከፍታል።
ይህ ተግባር አፍሌክስ የአፍሪካ ጉዳዮች በአፍሪካ ውስጥ በሚካሄዱ መድረኮች እንዲፈቱ ለማስቻል ከያዘው ዓላማ ጋር አብሮ የሚሄድ መሆኑ ተመላክቷል።
+1
ሱሉልታ - ሐምሌ 10/2017 - (አፍሌክስ) - የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ (አፍሌክስ) በግንባታና ኢንጂነሪንግ ስራዎች ላይ ከተሰማራው አሚጎስ ኢንስቲቲዩት ጋር በጋራ ለመስራት ትብብር መስርቷል።
አፍሌክስ በግንባታ እና ኢንጂነሪንግ ስራዎች ላይ ከተሰማራው አሚጎስ ኢንስቲቲዩት ጋር በጋራ ለመስራት ከተስማማባቸው ጉዳዮች መካከል፡- የአካዳሚውን የኃይል ምንጭ ወደ ጸሀይ ኃይል መቀየር፣ ከአካዳሚው ቅጥር ግቢ ውስጥ የጉድጓድ ውሃ በማውጣት ለአካባቢው (ሱሉልታ) ማህበረሰብ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ማቅረብ፣ ለአካባቢው መንገዶች በጸሀይ ኃይል የሚሰሩ የመንገድ መብራቶችን ማስገባት፣ እና የተጀመሩ የስማርት ፋርም ስራዎች አስፈላጊውን ቴክኖሎጂ በመተግበር ማስፋፋት ይገኙበታል።
የአፍሌክስ የቢዝነስ ልማት እና አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) አካዳሚው የአካባቢውን ማህበረሰብ የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ለሚያከናውናቸው ተግባራት ይህ ስምምነት ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል።
