______🌺የፍቅር ሀይል🌺_____
ፍቅርና አምነት(ፍቅር ባጋጣሚ(
ክፍል 13
ብሌን የስማችውን መልካም ዜና እያብስለስለችና ለቶማስ ብትነግርው እንደማይፍቅድላት እያስበች እቤት ደርስች ......እቤት ደርሳ የውጭውን በር ስትከፍት ያየችውን ማመን አቃታት ,,,,,, የቶማስ መኪና ግቢ ውስጥ ቆማለች ,,
ብሌን በጣም ግራ ገባት እንዴት ሊሆን ቻለ ሄጃለው ብሎኝ አለነበር? ለምንስ ተመለስ ?እቤት ሲያጣኝ ለምንስ አልደወለም ? እያለች እራሷን በጥያቄ አፍጠጠችው ግራ ገባት ውደ ቤት ቀስ ብላ ምን እንድምትል እያስበች ውደ በሩ ተጠጋች,
ቶማስ ይሄድበት የነበርው ስራ ለነገ ተዘዋውሯል ስለዚህ ዛሬን እርፍት አድርጉና ነገ በጠዋት ተነስተን እንሄዳለን ሲባል ጊዜ የሆነ ሀሳብ ድቅን ሲልበት ወደ ቤቱ ተመለስ ነገር ግን ብሌንን እቤት አላገኛትም ነበር ስልኩም ባትሪ ዘግቶበት ስለነበር እቤት ገብቶ ስልኩን ቻርጅ እያደርገ ሶፍ ላይ ጋደም ብሎ ነበር...
ብሌን ቀስ ብላ የሳሎኑን በር ከፍተችው ፊት ለፊት ሶፍ ላይ ቶማስን አየችው ,,ሀኒ,አለች በፍርሀት ድምፅ ,ቶማስ ሲያያት እፊቷ ላይ የሚታየውን ፍርሀት ተመለከተ ከድምፃም ተርዳ,ሊያስጨንቃት ስላልፍለገ ከተኛበት ተነስቶ ,,እናቴ,,ጠፍሽብኝ እኮ የት ሄደሽ ነው ?እያለ ወደሷ ተጠግቶ አቅፎ ሳማት ,,
ብሌን ደንግጣለች ,ሀኒ ,በስላም ነው ምነው ተመለስክ ?ምን ተፍጠር?ችግር አለ?ለምንስ አልደወልክልኝም?እያለች የፍቅር አይን እያየችው ጥያቄዋን አዘነበችው.,ቶማስ ለነገ እንደተባለና የተመለስውም እሷና እሱ ቀድመው ሄደው ዛሬን እንዲዝናኑ ና ነገ ከስራ መልስ ትንሽ ተዝናንተው እንዲመለሱ ፍልጎ ነበር ,ቶሎ ወደ ቤት የተመለስው ,ሲያጣት ያልደወለው ስልኩ ባትሪ ስላልነበርው እንደሆነም ነገራት,,
ቶማስ ለስራ የሚሄደው ውብና ማርኪ ወደ ሆነችው ሀዋሳ ከተማ ነበር ብሌንን ይዞ ሄዶ ዘና ማለት ይፍልግም ስለነበር ይሄንን አጋጣሚ በስበብ መጠቀም ስለፍለገ ነበር ወደ ቤት ቶሎ የተመለስው ,
ብሌን ለስራ ካንዴም ሁለቴ ሀዋሳ ሄዳ ታውቃለች ለመዝናናትና ዞር ዞር ብሎ ለማየት ግን እድሉ አልነበራትም ሄዳ ብትዝናና ግን ደስ ይላታል የቶማስ ሀሳብንም ደግፍዋለች ቢያንስ ለሁለት ቀን ዘና እንላለን ከቻልኩም ስለ መጣው እድል እነግረዋለው ብላ አስበች , ሀኒ , ታዲያ ለምን አንሄድም አለችው እርግጠኛ ነሽ እንሂድ አለ ቶማስ ደስ እያለው ,አወ እንሂድ ምን እንስራለን አለች ብሌን ,ሁለቱም ተጣድፍው መቀየርያ ልብስ ይዘው ጉዟቸውን ወደ ውቧና ምርጣ ከተማ ሀዋሳ አደርጉ.,
ብሌን ድሮ ለስራ ስትሄድ ባዛር ሲኖር በሚኒባስ ብዙ ሆነ ስለሚሄዱ አብዛኛውን መንገድ በእንቅልፍ ነበር የምታሳልፍው ዛሬ ግን በባሏ መኪና የምትፍልገውን ዘፍን እየስማች እየሳቀችና እየተደስተች መንገዳቸውን ቀጥለዋል መንገድ ላይ ያማራት ነገር ካየች ቆመው ከፍለጉ ገዝተው ካልፍለጉም አይተው በቃ በደስታ ጉዟቸውን ቀጥለዋል ምግብ ከአዲስ አበባ ሳይወጡ ስለበሉ አልራባቸውም መንገድ መንገዱንም የሚበላ እየገዙ እየበሉ ስለነበር ምንም አላስፍለጋቸውም ,,
ጉዟቸው በደስታ ቀጠለ የሀዋሳ መዳርሻ የሆኑትን ትናንሽ ከተማዎች አልፍው ሻሽመኔ ደርሱ ሻሽመኔም ውብ ሀገር ነች እዛ ሲደርሱ ስአቱም እየመሽ ነበር መብላትም ፍልገው ስለነበር ወደ አንዱ እሪስቶራንት አመሩ መኪናቸውን አቁመው እየተፍለቀለቁ ከመኪና ወርደው ወደ ውስጥ ገብ የሚፍልጉትን በልተው ጠጥተው ትንሽ ካርፊ በኃላ ጉዟቸውን ቀጠሉ,,
ሻሸመኔ ለሀዋሳ ቅርብ ናት ብዙም ሳይቆዬ ፍንትው ወደ አለችው ደማቋ ከተማ ሀዋሳ ደርሱ (ሀዋሳን እኔን ስለምወዳት ነው መስለኝ ገፀታዋን ብገልፅ አልጠግባትም ሀዋሳ ምርጥ ሀገር ናት ለኔ ) ሀዋሳ እንደደርሱ በጣም ተደሰቱ የት ማርፍ እንዳለባቸው አሰብ ብዙም ሳያቅማሙ ወደ "OSS international hotel " አመሩ ሆቴሉ ልዬ ነው " ከውጪ እስከ ውስጥ እጅግ ያምራል በቃ ውብ ነው(ዋውው ብታዬት ደግሞ ትደስታላችሁ ከለዊ እሪዞርት ግን አይበልጥም እመስክራለው)"፦
እዛ ገብተው እቃቸውን እስቀምጠው ሻወር ወስደው ትንሽ ካርፍ በኃላ ወደ ፍቅር ሀይቅ ተያይዘው ወጡ ምሽት ላይ ፍቅር ሀይቅ አካባቢ ትእይንት ይኖራልና በስአቱም ደስ የሚል ትዕይንት ነበር እሱ ሲያዬ አምሽተው እዛው የአሳ እራታቸውን በልተው ወደ ክላሳቸው ከመሄዳቸው በፊት ወደ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አደርጉ ',,..ገብርኤልን አመስግነው ተመልስው ወደ OSSጉዟቸውን አመሩ ,,,,
ክፍላቸው እንደደርሱም ሁለቱም ደክመው ስለነበር አልጋቸው ላይ ወደቁ ፍፁም ደሰተኛ ፍፀም ስላም በፍታቸው ላይ ይነበባል ብሌን በዚህ ደስታ መሀል ለቶማስ የመጣልኝን መልካም እድል ብነግርውስ ብላ አስበች ደስታ ማድፍርስ ይሆናል ብላ ዝም አለች ,,,,,,
ቶማስ ብሌን ልትነግርው የፍለገችው ነገር እንዳለ ስለተርዳ እንድትነግርው ወደ ድርቱ አስጠግቶ በማከፍና ፀጉሯን በማሻሸት እንድትነግርው ጠየቃት ....
______ይቅጥላል
ከወድዱት ላይክ አና ሼር ያድርጉ
COMMENT
@DEMO_NS👤