Halal Branding and Marketing PLC ®
前往频道在 Telegram
🟢 Our Services 🟢 ➜Brand Design ➜Logo Design ➜Flyer Design ➜Business Card ➜Banner Design ➜Broucher Design ➜Letterhead Design ➜Social Media Poster ⚪️For More Information⚪️ •Phone Number: 0978065466
显示更多320
订阅者
+224 小时
+37 天
-330 天
帖子存档
የነብዩ ﷺ ግመል
ስሟ " ﺍﻟﻘﺼﻮﺍﺀ " ( #አል_ቀሱዋእ) ትባላለች.ስያሜዋን ያገኘችው የጆሮዋ ጫፍ በጥቂቱ የተቆረጠ በመሆኑ ምክንያት ነው።ውልደቷ የ #በኒ_ቁሸይር ጎሳ መንደር ነው። በጥቁርና በነጭ መልኮች መካከል (ወደ ነጭ ያደላች ) የሆነች ግመል ናት። በጥንካሬዋ፥በፍጥነቷ፥በቅልጥፍናዋና በትጋቷ ወደር ያልተገኘላት፤ የሠይድ አባ በክር ስጦታ የሆነች እድለኛ ናት-ግመሏ። ሠይድ አባ በክር ሁለት ግመላቶችን ገዝቶ ወደ ነብዩ ﷺ በመምጣት "እናትና አባቴ መስእዋት ይሁንልሁና ከሁለቱ ግመሎች አንዷን መርጣችሁ ውሠዱ" አላቸው።ዳልቻ መልክ ያላትን መረጡ።
🪧 በመልእክተኛው ﷺ እጅግ የተመረጠች ናት።(በነገራችሁ ላይ ነብዩ ﷺ #ሶስት ግመሎች ናቸው ያሏቸው። ከሶስቱ ስለ ምርጧና የጀነት ስለሆነችው እያወራን ነው)
ከሁሉቱ ግመሎች ይልቅ ታዛዥ ናት፤ ለነብዬ የተለየ ፍቅርና ታዛዥነት አላት - ለዚህም ነው መመረጧ። አንድም ግመል በፍጥነት እሷን ቀድሞ አያውቅም. አንዴ ምን ተፈጠረ መሠላችሁ...
🪧 አንድ አዕራቢይ(የገጠር ሠው) የሆነ ግለሠብ የነብዬን ግመል ይቀድማታል። ግርምት ተፈጠረ፤አንድም ግመል ቀድሟት አያውቅም። በቅልጥፍና የሚግደዳደራት አካል በመፈጠሩ ሁሉም አፈጠጠ። ነብዬምﷺ እንዲህ አሉ " አሏህ ይህንን ደንግጓል ፤ በዱንያ ላይ አንድም ነገር ከፍ አይልም በአንፃሩ ግዜውን ጠብቆ ዝቅ የሚል ቢሆን እንጂ!! "
🪧 ይህቺው አፍቃሪ ግመል ከነብዬ ﷺ ህልፈት በሁዋላ ደግም አልሆነች። ፍፁም ጤናዋ ራቃት፤ማንንም በጀርባዋ ለመሸከም፥ማንንም ለማጓጓዝ ፍቃደኛ አልሆን አለች። በሀዘን ኩርምት፥ጭምት አለች።ከዛም ብሳ ደግሞ ከሞቱ በሁዋላ እህል ውሀ መቅመስ አልቻለችም። ለአንድ ወር ያህል አፏን ከምግብና ከእህል ከልክላ ሠነበተች። እጅግም ከማልቀሷ ብዛት ሁለት አይኖቿ ታወሩ ወዳጄ እያነገርኩህ ያለሁት ስለ ሚስቶቻቸው አልያም ስለ ባልደረቦቻቸው አይደለም፤ #ቀሱዋእ ስለተባለች የነብዩ ግመል ነው፤ ወዲህ በል!! ) ይህም ብቻ አይደለም በሀዘን ፥በለቅሶ፥በረሀብ፥ በጥማት ብዛት ተቆሳቁላ "ያለ ነብዬ ፥ ህይወት ለምኔ!" በማለት በ #14 አመቷ በናፍቆት እንደተንገበገበች ይህቺን ጠፊ አለም ተሠናበተች!!
ــــــــــــــــــــــــــــــــ
@nurmesjidgondar
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
