486
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
ውድ ተማሪዎችና ወላጆች
ከነገ ረቡዕ ጥቅምት 24 2014 ዓ.ም ጀምሮ ፈተና የሚሰጠው በመጀመሪያዎቹ ሁለት ክፍለጊዜዎች ስለሆነ ቀሪውን ጊዜ መደበኛ ትምህርት ይቀጥላል።
ስለዚህ ተማሪዎች ሙሉ ቀን ትምህርት ቤት የሚውሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆችና ተማሪዎች፣
የመጀመሪያው ሳምንት ትምህርት በግማሽ ቀን ይጠናቀቃል ማለታችን ይታወቃል።
ሆኖም ከረቡዕ ጀምሮ የመሉ ቀን ትምህርት መጀመር አስፈላጊ ሆኖ ሰለተገኘ ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገው እንዲመጡ እናሳስባለን።
ስለምንጊዜውም ትብብራቸሁ እናመሰግናለን!
የቪዥን አካዳሚ አስተዳደር!
በቪዥን አካዳሚ በ2014 የትምህርት ዘመን ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ በቅድሚያ እንኳን አደረሳችሁ እያልን:-
✍የ2014 ዓ.ም የትምህርት መርሐ ግብር ሰኞ ጥቅምት 01 የሚጀምር መሆኑን እያሳወቅን በዕለቱ ከጠዋቱ 1፡30 ጀምሮ በተመዘገበችሁበት ግቢ በመገኘት ትምህርታችሁን እንድትጀምሩ እያሳወቅን፣የ2014 የትምህርት ዘመን ከት/ት ቢሮ በተሰጠዉ መመሪያ መሠረት ፈረቃው ቀርቶ ከሰኞ እስከ አርብ ለሙሉ ቀን የሚሰጥ መሆኑን እንገልጻለን።
✍በመሆኑም ኮቪድ-19ኝን ለመከላከል የወጣውን መመሪያ አሟልተችሁ፤ የት/ቤቱን ዩኒፎርም በመልበስና ሌሎችንም የት/ቤቱን የሥነሥርዓት ደንብ በሟሟላት መምጣት ይጠበቅባችኋል።
👉የመጀመሪያው ሣምንት ትምህርት በግማሽ ቀን የሚጠናቀቅ መሆኑንም አውቃችሁ ልጆቻችሁን ከ6:30 ጀምሮ እንድትወስዱ እናሳስባለን።
የቪዥን አካዳሚ አስተዳደር!
ውድ ወላጆችና ተማሪዎች፥
ከት/ቤቱ አጠቃላይ መረጃዎችን ለማግኘት የሚያስችልዎት ቻናል- Vision Academy https://t.me/joinchat/Fm01fl0TN-w0MmRk የሚለው ነው። ማስፈንጠሪያውን በመጫንእንድትቀላቀሉ በአክብሮት እናሳስባለን ።
ለቪዥን ነባር ተማሪዎች ወላጆች!
የመጨረሻውን የምዝገባ ቀን ስለማሳወቅ፤
የ2014 የትምህርት ዘመን የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሀምሌ 28 እስከ ነሐሴ 15 የተከናወነ ሲሆን ጥቂት ተማሪዎች ያልተመዘገቡ በመኖራቸው ለመጨረሻ ጊዜ እስከ ነሐሴ 25/2014 ተራዝሞ እየተደረገ የሚገኘው ምዝገባ የማብቂያው ቀን ማክሰኞ መሆኑን አውቃችሁ እንድታስመዘግቡ እያሳሰብን፤ ከነሐሴ 25 በኋለ የሚመጣን የነባር ተማሪን ምዝገባ የማናስተናግድ ሲሆን፤ ባለው ክፍት ቦታ አዲስ ተማሪዎችን እንመዘገባለን። የአዲስ ተማሪዎችም ምዝገባ ነሐሴ 30/2014 የሚያበቃ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።
የት/ቤቱ አስተዳደር!
የመማሪያ መፃህፍት ለመግዛት ሲመጡ ለምዝገባ የከፈሉበትን ደረሰኝ(ሰሊፕ) ካልየዙ ስለማይስተናገዱ ይህንኑ ይዘው እንዲመጡ እናሳስባለን፡፡
ቀን 14/12/2013 ዓ.ም
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆች
✅ጥቂት ነባር ተማሪዎች ለ2014 የት/ት ዘመን በተሰጠው የጊዜ ገደብ አልተመዘገቡም፡፡
ለነባር ተማሪዎቻችን ዕድሉን ለመስጠት ለመጨረሻ ጊዜ እስከ ነሐሴ 25 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ብቻ የምንመዘግብና በክፍት ቦታዎች አዲስ ተማሪዎችን የምንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
✅ከ1ኛ-12ኛ ክፍል የመንግስት መጽሐፍ ያቀረብን ስለሆነ ከነሐሴ 20 ቀን 2013 ጀምሮ ከመብራት ኃይል ዋና ግቢ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ት/ቤቱ
ለቪዥን አካዳሚ ነባር ተማሪዎች
የነባር ተማሪ ምዝገባ ማብቂያ ቀን ነሐሴ 15 / 2013 ዓ.ም መሆኑን በድጋሚ እያሳወቅን ከነሐሴ 15 በኋላ የሚመጣ የነባር ተማሪን ምዝገባ ለማስተናገድ የምንቸገር መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የት/ቤቱ አስተዳደር
ቪዠን አካዳሚ
የ2014 ዓ.ም ነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 28 - ነሐሴ 15 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ የሚካሄድ መሆኑን አውቃችሁ ልጆቻችሁን እንድታስመዘግቡ እየገለጽን በምዝገባ ወቅት፡-
ሁለት የተማሪው ጉርድ ፎቶግራፍ እና
የ2013 የትምህርት ዘመን ማጠቃለያ ሪፖርት ካርድ ይዞ መቅረብ የሚጠበቅ ሲሆን ምዝገባው የሚካሄደው በዋናው ግቢና በሰሚት 1ኛ ደረጃ ግቢ መሆኑን እየገለጽን ፣ ልጆቹ በሚማሩበት አካባቢ ምዝገባውን በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ እንድታደርጉ እናሳውቃለን፡፡
የትምህርት ቤቱ አስተዳደር!
ለወላጆች በሙሉ!
የ2013 ዓ.ም የተማሪዎች ውጤት መግለጫ ካርድ ማክሰኞ ሐምሌ 27 2013 ዓ.ም ከ7፡00 ሰአት ጀምሮ ስለሚሰጥ በየግቢያችሁ በመገኘት እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡
ለወላጆች በሙሉ!
የ2013 ዓ.ም የተማሪዎች ውጤት መግለጫ ካርድ ማክሰኞ ሐምሌ 27 2013 ዓ.ም ከ7፡00 ሰአት ጀምሮ ስለሚሰጥ በየግቢያችሁ በመገኘት እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡
ሐምሌ 19 ቀን 2013 ዓ.ም
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆች በሙሉ!
ጉዳዩ፡- ለሁለተኛ ጊዜ የተደረገ የስብሰባ ጥሪን ይመለከታል፦
ሐምሌ 18 ቀን 2013 ዓ.ም የተጠራው የቪዥን አካዳሚ ወላጆች የመጀመሪያ ስብሰባ መካሄድ ስላልቻለ ሐምሌ 25 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ገርጂ መብራት ኃይል በዋናው ግቢ ይደረጋል፡፡የመወያያ አጀንዳዎቹም፡-
1. የትምህርት ሥራ ሪፖርት ማቅረብ
2. የወ.ተ.መ.ህ ሪፓርት ማቅረብ
3. የ2014 ዓ.ም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ማቅረብ ሲሆን በዕለቱ በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኙ በአክብሮት ጥያቄያችንን እናቀርባለን፡፡
ቪዥን አካዳሚ!ሐምሌ 19 ቀን 2013 ዓ.ም
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆች በሙሉ!
ጉዳዩ፡- ለሁለተኛ ጊዜ የተደረገ የስብሰባ ጥሪን ይመለከታል፦
ሐምሌ 18 ቀን 2013 ዓ.ም የተጠራው የቪዥን አካዳሚ ወላጆች የመጀመሪያ ስብሰባ መካሄድ ስላልቻለ ሐምሌ 25 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ገርጂ መብራት ኃይል በዋናው ግቢ ይደረጋል፡፡የመወያያ አጀንዳዎቹም፡-
1. የትምህርት ሥራ ሪፖርት ማቅረብ
2. የወ.ተ.መ.ህ ሪፓርት ማቅረብ
3. የ2014 ዓ.ም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ማቅረብ ሲሆን በዕለቱ በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኙ በአክብሮት ጥያቄያችንን እናቀርባለን፡፡
ቪዥን አካዳሚ!
ለ3ኛ ክፍል ወላጆች
ለውጤት መግለጫ ካርድ ዝግጅት የሚሆን የተማሪዎችን ሙሉ ስም እድሜና ፆታ ላኩልን ባልነው መሰረት አብዛኛው ወላጅ ልኮልናል።
መረጃውን ያላካችሁ ወላጆች ነገ ረቡዕ ሐምሌ 21 2013 ዓ.ም በስራ ሰአት ለቢሮ እንድታሳውቁ እናሳስባለን።
ሐምሌ 19 ቀን 2013 ዓ.ም
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆች በሙሉ
ጉዳዩ፡- ለሁለተኛ ጊዜ የተደረገ የስብሰባ ጥሪን ይመለከታል
ሐምሌ 18 ቀን 2013 ዓ.ም የተጠራው የቪዥን አካዳሚ ወላጆች የመጀመሪያ ስብሰባ መካሄድ ስላልቻለ ሐምሌ 25 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ገርጂ መብራት ኃይል በዋናው ግቢ ይደረጋል፡፡የመወያያ አጀንዳዎቹም፡-
1. የትምህርት ሥራ ሪፖርት ማቅረብ
2. የወ.ተ.መ.ህ ሪፓርት ማቅረብ
3. የ2014 ዓ.ም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ማቅረብ
ሲሆኑ በዕለቱ በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኙ በአክብሮት ጥያቄያችንን እናቀርባለን፡፡
ቪዥን አካዳሚ
ሐምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆች በሙሉ
ጉዳዩ፡- የስብሰባ ጥሪን ይመለከታል
ሐምሌ 18 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ የቪዥን አካዳሚ ወላጆች ጠቅላላ ስብሰባ ገርጂ መብራት ሀይል በዋናው ግቢ ይደረጋል፡፡
የመወያያ አጀንዳዎቹም፡-
1. የትምህርት ሥራ ሪፖርት ማቅረብ
2. የወተመህ ሪፓርት ማቅረብ
3. የ2014 ዓ.ም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ማቅረብ
ሲሆኑ በዕለቱ በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኙ በአክብሮት ጥያቄያችንን እናቀርባለን፡፡
ቪዥን አካዳሚ
ከ1-12 ለዋናው ግቢ ወላጆችና ተማሪዎች በመሉ፦
ቀደም ብሎ በተላከው የማጠቃለያ ፈተና ፕሮግራም ላይ የተደረገ ማሻሻያን ማብራሪያን ይመለከታል፥
የ4ኛው ሩብ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ቀጥሎ በተዘረዘረው መርሐ-ግብር መሠረት የሚከናወን መሆኑን አውቃችሁ ልጆች በቀሩት ጥቂት ቀናት ውስጥ እራሳቸውን በተገቢው መንገድ እንዲያዘጋጁ እንድትረዷቸው እናሳስባለን።በመሆኑም፦
A. ከ1ኛ-4ኛ ክፍል በሁለቱም ፈረቃ የሚማሩ ተማሪዎች ከዓርብ:ሐምሌ 09 እስከ ቅዳሜ:ሐምሌ 10/2013 ዓ.ም ድረስ ፈተና ይወስዳሉ። ዓርብ ዕለት የሚሰጠው ፈተና ለሙሉ ቀን የሚሰጥ ስሆን የቅዳሜ ፈተና ለግማሽ ቀን ብቻ ይካሄዳል።
B. ከ5ኛ-7ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ሰኞ:ሐምሌ 12 እና ሐሙስ:ሐምሌ 15/2013ዓ.ም ፈተና ይወስዳሉ። ሐምሌ 9 ዐርብ እና ሐምሌ 10 ቅዳሜ ቤት ሆነው ለፈተና ይዘጋጃሉ።
C. ከ9ኛ-11ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ደግሞ ሰኞ ሐምሌ 12፥ ሐሙስ ሐምሌ 15 እና ዐርብ ሐምሌ 16/2013 ፈተና ይሰጣል።
ማስታወሻ፡
✅ ከ5ኛ-11ኛ ክፍል ላሉት ተማሪዎች ፈተናው የሚሰጠው ለግማሽ ቀን መሆኑን አውቃችሁ ከ 6:30 ጀምሮ ተማሪዎችን መውሰድ ትችላላችሁ።
✅ዩኒፎርም ይለበሳል።
✅ዐርብ:ሐምሌ 16/2013 ዓ.ም ከ1ኛ-4ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎች የፈተና ውጤት የሚመለስበት ቀን ሲሆን
✅ቅዳሜ :ሐምሌ 17/2013 ዓ.ም ለይ ከ5ኛ-7ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎች ፈተና የመመለሻ ቀን ይሆናል።
✅ ሰኞ ሐምሌ 19/2013 ዓ፥ ም ከ9-11 ክፍል ፈተና ይመለሳል።
✳️ስለ ቀና ትብብራችሁ ከልብ እናመሰግናለን!
ቪዥን አካዳሚ!
