ch
Feedback
የአካባቢ ወጣቶች መዝሙራት

የአካባቢ ወጣቶች መዝሙራት

前往频道在 Telegram

የተመረጡ የማህበራት እና የካሴት መዝሙራትን የሚያገኙበት፣ ወቅታዊና አሁናዊ መረጃዎችን የሚጋሩበት እንዲሁም የተለያዩ መፅሀፍትንና ትረካዎችንና የመሳሰሉትን የሚያገኙበት ድንቅ ቻናል ተቀላቀሉን ብዙ ያተርፉበታል። ለአስተየትዎ @Natnael1201

显示更多
2 018
订阅者
-224 小时
+17 天
+730 天

数据加载中...

吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+8
在0个频道中
八月 '26
+54
在0个频道中
Get PRO
七月 '26
+49
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+20
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+31
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+25
在1个频道中
Get PRO
三月 '26
+11
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+24
在1个频道中
Get PRO
一月 '26
+28
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+35
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+36
在2个频道中
Get PRO
十月 '25
+31
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+37
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+65
在1个频道中
Get PRO
七月 '25
+34
在1个频道中
Get PRO
六月 '25
+47
在5个频道中
Get PRO
五月 '25
+48
在3个频道中
Get PRO
四月 '25
+75
在1个频道中
Get PRO
三月 '25
+50
在1个频道中
Get PRO
二月 '25
+58
在4个频道中
Get PRO
一月 '25
+103
在1个频道中
Get PRO
十二月 '24
+110
在2个频道中
Get PRO
十一月 '24
+69
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+63
在1个频道中
Get PRO
九月 '24
+96
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+48
在1个频道中
Get PRO
七月 '24
+61
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+29
在1个频道中
Get PRO
五月 '24
+39
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+41
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+35
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+69
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+54
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+87
在1个频道中
Get PRO
十一月 '23
+72
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+54
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+50
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+50
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+38
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+26
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+31
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+20
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+29
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+63
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+97
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+86
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+49
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+53
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+98
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+82
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+113
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+80
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+152
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+103
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+66
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+46
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+116
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+116
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+76
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+125
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+98
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+86
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+105
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+86
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+86
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+355
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
05 九月0
04 九月+1
03 九月+4
02 九月+2
01 九月+1
频道帖子
ሥርዐተ ቅዱስ ወንጌል ካህናት ወንጌልና ኪዳን ሲያነብቡ ጥምጥማቸውን ያወልቃሉ፤ አክሊላቸውንም ያወርዳሉ ይኸውም ለአክብሮተ ወንጌል ነው:: ወንጌል በሚነበብበት ጊዜ መቆም እንጂ መቀመጥ ፈጽሞ ክልክል
ሥርዐተ ቅዱስ ወንጌል ካህናት ወንጌልና ኪዳን ሲያነብቡ ጥምጥማቸውን ያወልቃሉ፤ አክሊላቸውንም ያወርዳሉ ይኸውም ለአክብሮተ ወንጌል ነው:: ወንጌል በሚነበብበት ጊዜ መቆም እንጂ መቀመጥ ፈጽሞ ክልክል ነው። ካህኑ አንብቦ ሲጨርስ ራሱ ተሳልሞ ከንፍቅ ካህን ጀምሮ እንደ የማዕረጋቸው ያሳልማቸዋል ካህናቱ ከተሳለሙ በኋላ ምዕመናን ይሳለማሉ ኾኖም በሚሳለሙበት ጊዜ ሴቶች ክንብንባቸውን ከራሳቸው ላይ አውርደው መሳለም ይገባቸዋል፤ ንጉሥም ቢሆን እንኳ ዘውዱን ማውረድ አለበት::
❝ነአምን በቃለ ወንጌል ቅዱስ — ቅዱስ በሆነው በወንጌልህ ቃል እናምናለን❞
— እያሉ እጅ እየነሡ ክንብንባቸውን እያወረዱ ይሳለማሉ በቃለ ወንጌል ማመናቸውን ይመሰክራሉ:: ክብረ ወንጌል በቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ቅዱስ ወንጌል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ቅድሚያ የሚሰጠው ከፍ ያለ ክብር ያለው እንደሆነ የታወቀ ነው:: ስለ ክብረ ወንጌል የማይነገርበት ሥርዐት እና አምልኮ ቤተክርስቲያን የላትም:: በቅድስት ቤተክርስቲያን ቅዱስ ወንጌልን የማያሳትፍ ጸሎት፣ ቁርባን፣ መሥዋዕትና አገልግሎት የለም:: ማኅሌትና ሰዓታት ሲቆም፤ ጸሎተ ፍትሕት ሲደረስና ጸሎተ ተክሊል ሲከናወን በእነዚህ ሁሉ መስቀል ተይዞ ወንጌል ይነበባል:: በአጠቃላይ ቅዱስ ወንጌል የማይነበብበት የአገልግሎት ዘርፍም ሆነ የጸሎት ክፍል ቤተክርስቲያን የላትም። ይህም ለቅዱስ ወንጌሉ ያላትን ክብር ከፍ አድርጎ ያሳያል:: ቅዱስ ወንጌል ለሥርዐት፣ ለአምልኮት፣ ለሕግጋትና ለአገልግሎት መሠረት በመኾኑ ከሌሎቹ ሥርዓቶች የበለጠ ክብር ይሰጠዋል። ለምሳሌ:- በቅዳሴ ጊዜ ወንጌል ሲነበብ የደከመ/የታመመ እንኳን ቢሆን በዚያች በንባብ ቅጽበት ውስጥ ድካሙንም ሕመሙንም እንደምንም ችሎም ቢሆን ቆሞ እንዲያደምጥ ይታወጃል:: አዋጁን የሚያውጀው ገባሬ ሠናዩ ዲያቆን:-
❝ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ቅዱስ ወንጌል ቆማችሁ አድምጡ!❞
— የሚለው አዋጅ ከታወጀ በኋላ የተቀመጠ ካለ ቀጥ ብሎ ሕሊናውን ሰብስቦ ይቆማል:: (እዚህ ጋር ዲያቆኑ ወንጌሉን «አድምጡ» እንጂ «ስሙ» አይልም። በሁለቱ ቃላት መካከል ያለውን ልዩነት ልብ በሉ!) ዲያቆኑ ቁሙ ወአጽምዑ ማለቱ የንፍሐተ ቀርን፤ ካህኑ ወንጌል ማንበቡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፍርድ ቀን «ንዑ ኀቤየ፥ ሑሩ እምኔየ» ብሎ ፍርድ የማስተላለፉ ምሳሌ ነው:: በዚህ ጊዜ የሚደወለው ደወል የግርማ መዓቱ፤ ወንጌል ከተነበበ በኋላ መጋረጃ መዘጋቱ ሑሩ እምኔየ ብሎ ኀጥአንን የማሰናበቱ ምሳሌ ነው። (የቅዳሴ አንድምታ) ወንጌል ከተነበበም በኋላ ንፍቅ ካህን ወንጌል መስማት ክብሩ ምን ያህል እንደሆነ ሲናገር እንዲህ ይላል:-
❝ክቡር የሚሆን የወንጌልህን ቃል እንሰማ ዘንድ እንሳለመውም ዘንድ ደስ ይለን ዘንድ ለዚህ የበቃን ያደረግኸን ሁሉን የያዝህ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ላንተ ምስጋና ይገባሃል! ዳግመኛም ክቡር የሚሆን የወንጌልህን ቃል በልቡናችን ትጽፍ ዘንድ እንለምናለን እንማልድሃለን❞
— ብሎ ይማጸናል:: የቅዱስ ወንጌል ክብሩ የሚጀምረው መጽሐፉን ከማክበር ሲሆን ይኸውም አቅም ያለው ደብር የመጽሐፉን ገበታ (የውጭውን ሽፋን) በወርቅ እና በብር ያስጌጡታል አቅም የሌለው ደብር ደግሞ በወርቃማ ሱቲ (በከበረ ልብስ) ያለብሱታል:: ይህ ሁሉ ታዲያ ክብሩን ለመግለጥ ነው:: ምእመናን ቅዱስ ወንጌልን እንዴት ባለ ሁኔታ መስማት እንደሚገባቸው ሥርዓተ ቅዳሴው ሲናገር:-
❝የሰማያዊውን ንጉሥ የከበረ የወንጌሉን ቃል ለመስማት ከመጀመሪያቸው እስከ መጨረሻቸው ድረስ ከማመስገን ከመቀደስ በቀር ማድነቅና ጸጥታ ሊሆን ይገባል:: የምድራዊ ንጉሥ ደብዳቤ ሲነበብ አንድ ሰው እንኳን ለመናገር የማይደፍር ከሆነ፤ ቢናገርም ቅጣትና ግርፋት የሚያገኘው ከሆነ የሰማያዊው ንጉሥ ደብዳቤ የምትሆን ወንጌል ሲነበብ የሚናገር ምን ያህል ቅጣት ያገኘው ይሆን?❞
— በማለት ወንጌል ሲነበብ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ እንደሚገባው ሥርዐተ በቅዳሴያችን ያስጠነቅቃል:: ጸሎተ ወንጌል ከተፈጸመ በኋላ ንፍቅ ዲያቆን መብራት ይዞ በፊት፥ ንፍቅ ካህን ማዕጠንት ይዞ በኋላ ሆኖ ሁለቱም በቅድስት በቀኝ በኩል ዞረው በሰሜን የመቅደሱ በር ይገባሉ:: ሠራዒ ዲያቆን በቅድስቱ ላይ ሆኖ ፊቱን ወደ ምዕራብ መልሶ ቃጭል እየመታ:- «ጻዑ ንዑሰ ክርስቲያን» ይላል። ይህንንም የሚያውጅበት ምክንያት «ንዑሰ ክርስቲያን» የሚባሉት የክርስትና ሃይማኖትን በማጥናትና ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በመከታተል ላይ ያሉት ገና ያልተጠመቁ አዲስ ክርስቲያኖች ሲሆኑ እንዲወጡ መታዘዛቸው ለመቊረብ ስለማይችሉ ነው። የጥንቱ ትምህርተ ወንጌል ሰዓት ወንጌል ከተነበበ በኋላ ኤጲስ ቆጶስ ካለ ወንጌሉን በእጁ ይዞ በክፍሎቹ የተነበበውን ለሕዝቡ ተርጉሞ ማስተማር ይገባዋል። ኤጲስ ቆጶስ ከሌለ ትርጓሜን የሚችል የተማረ ካህን እንዲያስተምር ታዝዟል (ፍትሐ ነገሥት ፲፪)። ትምህርቱ ግን ሳይበዛ ከዐሥራ ዐምስት ደቂቃ ባልበለጠ ወንጌሉንና ምስባኩን እንዲሁም የተነበቡትን መልእክታት በማቆራኘት ምስጢረ ቁርባንን ማዕከል በማድረግ አጭር ትምህርተ ወንጌል መስጠት ይገባል:: በዘመናችን ግን ወንጌል ከተነበበ በኋላ «ፃዑ ንዑሰ ክርስቲያን» ከመባሉ በፊት ትምህርተ ወንጌል መስጠት ከቆመ ዓመታት ተቆጥረዋል:: ለዚህ ብዙ ምክንያቶች መጠቀስ የሚችሉ እንደሆነ ቢገባኝም ሆኖም ግን የጥንቱን (የቀደመውን) የአባቶቻችንን ሥርዓት መሸራረፍም ሆነ ማዛነፍ ተገቢ አይደለም። እዚህ ጋር ቤተክርስቲያን የተመሠረተችው ለሁለት ዐቢይ ተልእኮ መሆኑ መታወቅ አለበት፤ ይኸውም ለቅዳሴና ለወንጌል ነው:: እነዚህ ሁለቱ የማይነጣጠሉ ሰምና ወርቅ፤ ድር እና ማግ፤ ጥርስ እና ከንፈር ሆነው የሚኖሩ የድኅነታችን ወሳኝ ጸጋዎች ናቸው:: ይልቁንም ወንጌል ደግሞ የጸጋዎች ሁሉ መግቢያ በር ነው። ሰው ሳይማር አይጠመቅም፤ ሳይጠመቅ አይቆርብም፤ ስለዚህ ጥምቀትም ቁርባንም የሚገኙት ከወንጌል ትምህርት የተነሣ ነው:: «ፃዑ» ከመባሉ በፊት ትምህርት የሚሰጥበት ምክንያት ለሁለት ዓላማ ነው። አንዱ ከሌላ ቤተ እምነት ወይም ከአምልኮተ ጣዖት የመጡ ለምሥጢረ ጥምቀት ደጅ የሚጠኑ ንዑሳነ ክርስቲያንን አስተምሮ ለመሸኘት ሲሆን፥ ለቍርባን የተዘጋጁ ምእመናን ደግሞ ፈሪሃ እግዚአብሔር ባልተለየው ልቡና፣ ትሕትና በተዋሐደው ስብእና ቀሪውን ሥርዐት እንዲከታተሉና በፍርሃትና በረዓድ ሆነው ወደ ቅዱስ ቁርባን እንዲቀርቡ ለማነቃቃት እንዲሁም ለማስጠንቀቅ ነው:: ይልቁንም እዚህ ላይ ትምህርት መስጠቱ ልዩ ጥቅም አለው። ይኸውም አንደኛ ምእመኑ በቁመት ብዛት ሰውነቱ ሳይዳከም ልቡናው ሳይደክም በትኩስ ተመስጦ በሞቀ መንፈሳዊ ኀይል ትምህርቱን በሚገባ ነቅቶ ተግቶ ይሰማል:: ሁለተኛው «ወንጌል መስማት» የከበረ የቅዳሴው አካል የድኅነት ማዕከል እንደሆነ በሚገባ እንዲገነዘብ ስለሚረዳ። እናስተውል! ዲ/ን ኃይለራጉኤል

2
❝ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወአስተበርክ ክሡተ ቅድመ ማኅበራንኪ እሉ እንዘ እቀውም ድርገተ ፈጻሚተ መፍቅድ ማርያም እስእለኪ ስእለተ ጸግውኒ እግዝእትየ ለዓለመ ዓለም ሕይወተ እምእደ እኩያን አጽራርየ አድ
❝ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወአስተበርክ ክሡተ ቅድመ ማኅበራንኪ እሉ እንዘ እቀውም ድርገተ ፈጻሚተ መፍቅድ ማርያም እስእለኪ ስእለተ ጸግውኒ እግዝእትየ ለዓለመ ዓለም ሕይወተ እምእደ እኩያን አጽራርየ አድኅንኒ ሊተ❞ ... .. . [በእነዚህ የአንቺ ማኅበር በሚሆኑ ጉባኤያተኞችሽ መካከል በአንድነት እየቆምኩ በሥዕልሽ ፊት እሰግዳለሁ፤ በግልጽም እንበረከካለሁ፡፡ የልቤን መሻት የምትፈጽሚልኝ ማርያም ሆይ እለምንሻለሁ፤ እመቤቴ ሆይ፥ ለዘለዓለሙ ሕይወትን ስጪኝ፥ ከክፉ ጠላቶቼ እጅም አድኚኝ።]
354
3
♡ የልቤ ዜማ ♡       የልቤ ዜማ ነሽና ሰላም ነው ያንቺ ምስጋና ሞገሴ ነው ስምሽ ለኔ ስላለሽ ማርያም ከጎኔ በመገፍት ብኖር እምነቴን አፀናለሁ በጣቶችሽ  ተይዤ አዲሱ ቀን አያለሁ [፪]          ስማፀን ደጅሽ መጥቼ           ተመለሰኩ ተረጋግቼ        እንደምን አንቺን እረሳለሁ          በምልጃሽ ተፈውሻለሁ የጠላቶቼን አራስ የሚቀጠቅጠው የአብራክሽን ፍሬ ተስፍዬን አበራው [፪]       የድኅነት ምክንያት አርጎሻል      ለአዳም ዘር ትምክህት ሆነሻል             የልቤ ብርሃን ፍና           አዛኝት ባንቺ ልፅናና የአፌን እንጉርጉሮ ምስጋናዬ ወርሶታል እግሬ ከእረግረግ ወጥቶ በሰገነት ተተክሏል [፪]          ሐዜኔን የምሻገረው        ስምሽን እየጠራሁ ነው         አገኘው ደስታ ሰላም         ጠርቼ ብዬ ማርያም  በአብረቅራቂው ፍቅር በዓለሙ ውስጥ ስኖር ለሙውጣት ዳክራለሁ ማርያም ማርያም እላለሁ [፪]            ሰምተሻል ልመናዬን          ወጣሁኝ ያኑን ጥልቁን         እሳቱን ባንቺ አልፌአለሁ          በምልጃሽ ደግፌ አለ ዘማሪ ዲያቆን እንዳለ ደረጀ ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
326
4
የበዓሉ መጠሪያ ስሞች 1. ደብረ ታቦር የተባለው ጌታ ክብሩን የገለጠበት ስፍራ ደብረ ታቦር ስለሆነ በዚሁ በዓሉ ስያሜውን አግኝቷል። 2. ቡሔ ይባላል ፦ ቡሄ ብርሃን ማለት ነው በደብረታቦር ቧ ብሎ የተገለጠውንየጌታችንን የፊቱን ብርሃን ጸዳል፤ የልብሱንም እንደ ነጭ በረዶ ጸዓዳ መሆን ያስረዳል፡፡ 3. ቡሔ ማለት መላጣ (ገላጣ) ማለት ነው፡፡ይኸውም በበዓሉ ዋዜማ ልጆች ‹‹ ቡሔ በሉ፤ ቡሔ መጣ ፣ ያ መላጣ፣ ቅቤ ቀቡት እንዳይነጣ›› ይላሉ እዚህ ላይ ቡሄ ያለው ዳቦውን ነው፡፡ 4. "ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት›" እንደሚባል ወቅቱበሃገራችን የጸዓተ ክረምት ዋዜማ ስለሆነ የክረምቱ አፈናው ተወግዶ /ተጋምሶ/ የብርሃን ወገግታ የሚታይበት ፤ በዶፉና በጎርፉ ተሸፍና የነበረች መሬት የምትገለጥበት በመሆኑ ነው፡፡ 5.  ቡሔ (ቡሔእየ) ተብሎ ይተረጎማል ይኸውም የደብረታቦር እለት እርሾ ሳይገባበት ተቦክቶ የሚጋገረውን ኅብስት ያሳያል፡፡ 6. ችቦ የመብራቱ ፣ የሙልሙል ዳቦ የመጋገሩና የጅራፍ ማጮኽ ምክንያት መብራት የሚበራው 12 ለ13 ዋዜማ ሌሊት በ3 ሰዓት ነው የጌታችን ክብሩ በተገለጠበት ጊዜ ብርሃኑ የሌሊቱን ጨለማ ገፍቶት እስከ አርሞንዔም ደርሶ ነበርና በዚያ አካባቢ የነበሩ እረኞች በሁኔታው ተገርመው ቀንም መስሎኣቸው ሌሊቱም ተዘንግቷቸው በዚያው ቆይተው ነበርና ቤተሰቦቻቸው ምን አግኝቷቸው ይሆን በማለት መብራት አብርተው (ችቦ ይዘው)፣ የሚመገቡትን ይዘው/ሙልሙል/ልጆቻቸውን ፍለጋ ወጥተዋል እረኞችም ያሉበትን ቦታ ለቤተሰቦቻቸው ጅራፍን በማጮኸ አመልክተዋቸዋልና ይህን ለማሰብ ነው፡፡ ዋናው ምሥጢሩ ግን፡- የችቦው ብርሃን የጌታ ክብር መገለጡን፣ የጅራፋ ጩኸት ሐዋርያትን ያስደነገጣቸው የአብ የምስክርነቱ ቃል ምሳሌ ሲሆን፣ ኅብስቱ ጌታችን በመስቀል ላይ መሥዋዕት የመሆኑ (የሥጋወደሙ) ምሳሌ ነው፡፡ •  ከላይ እናዳየነው ጅራፋ መጮኹ የአብ የምስክርነቱ ቃል ምሳሌ ነው ይኸውም በታቦር ተራራ ላይ እንደሆነም ተገልጧል ስለዚህ ዛሬም ምሳሌነቱን ለማጉላት ጅራፍ የማጮኹን ሥርዓት በተራራ ማድረግ የተሻለ ነው፡፡ ከዚህ በተረፈ ግን  ሥርዓቱን ባልጠበቀ መልኩ ማክበሩ ሃይማኖታዊ ትውፊት የለውም ይልቁንም ሰውን ለማስደንገጥ ተብሎ በአስደንጋጭ ነገሮች  ሰውን ማስደንገጥ የበዓሉን ሥርዓት ማሳደፍም ከመሆኑም በላይ ከሃይማኖተኛ ሰው የማይጠበቅ የሰውን መብትና ክብር መንካት ነው ጌታችን በብርሃን ንስሓ እንመላለስ ዘንድ ዓይነ ልቡናችንን ብሩህ ያድርግልን፡፡                          ✔️መ/ር ነቢዩ ኤልያስ
740
5
ዘክረምት☘️ እግዚአብሔር፦ የበልግ ዝናምን ይሰጣችሁ ዘንድ እግዚአብሔርን ለምኑት። በረከትን ለእናንተ ያዘንባል። ክረምትን በየዓመቱ የምታስገባ አቤቱ ዕውቀትን ስጠን። ሰማይን በደመና የሚጋርድ ለሥጋ ሁሉ ምግብን የሚሰጥ ነው። በምድር ሁሉ ዝናምን ያወርዱ ዘንድ ደመናትን የሚያዝዛቸው ነው። ለቸሮች ቸር ለይቅር ባዮች ይቅር ባይ የሆነ [እግዚአብሔር] በምድር ላይ ዝናምን ያወርዳል። [አቤቱ አንተ] ለነገሥታት ሰላምን ትሰጣለህ ለአብያተ ክርስቲያናትም ጸጥታን ትሰጣለህ። በኖኅ ጸሎት ይቅር በለን። አንተ ሕይወትን የፈጠርክ በረከትን የምትሰጥ ነህ። አንተ የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ ነህ። ከፍጥረት ሁሉ ሰውን ከፍ ከፍ ያደረግህ ከዕለታት ሁሉ ሰንበትን ያከበርክ አንተ ነህ። ወደ ምድረ በዳ ብሄድም ኀይሌ እግዚአብሔር ነው። ብወድቅና ብፍገመገም በመስቀልህ እነሣለሁ። (#በግእዝ፦ ሰአልዎ ለእግዚአብሔር የሀብክሙ ዝናመ ጸደይ። ያዝንም ለክሙ በረከተ። ዘአንተ ታርኁ ክረምተ በበዓመት ሀበነ እግዚኦ አእምሮ። ዘይገለብቦ ለሰማይ በደመና ዘይሁብ ሲሳየ ለኵሉ ዘሥጋ። ዘይኤዝዞሙ ለደመናት ያውርዱ ዝናመ ውስተ ኵሉ ምድር። ኄር ለኄራን መሓሪ ለመሓርያን ያወርድ ዝናመ በዲበ ምድር። ትሁብ ሰላመ ለነገሥት ወኅድዐተ ለአብያተ ክርስቲያናት። በጸሎቱ ለኖኅ ተሣሀለነ። አንተ ውእቱ ገባሬ ሕይወት ወሃቤ በረከት። አንተ ኬንያሁ ለኵሉ ፍጥረት። እምኵሉ ፍጥረት ሰብአ ዘአዕበይከ ወእምኵሉ ዕለት ሰንበተ ዘአክበርከ። እመኒ ሖርኩ ውስተ በድው ኀይልየ እግዚአብሔር እመኒ ወደቁ ወተንተንኩ እትነሣእ በመስቀልከ)። ክረምት፦ የዝናም ኮቴው ተሰማ። ዝናም በሚዘንብ ጊዜ የተራቡት ይጠግባሉ። ዝናም በሚዘንብ ጊዜ ችግረኞች ደስ ይላቸዋል። (#በግእዝ፦ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም። ሶበ ይዘንም ዝናም ይጸግቡ ርኁባን። ሶበ ይዘንም ዝናም ይትፌሥሑ ነዳያን)። ምጽአት፦ ወልድ ከሰማይ ኀይላት ጋር በሚያስደነግጥ ግርማ በመጣ ጊዜ። የዕለታት ሁሉ በኵር የሆነች እሑድ ትሰለጥናለች። ያን ጊዜ ጨረቃ የለም፣ ፀሐይም የለም፣ ክረምት የለም በጋም የለም። (#በግእዝ፦ አመ ይመጽእ ወልድ በግርማ መደንግፅ ምስለ ኀይለ ሰማያት ትሰፍን እሑድ ርእሰ ኵሎን ዕለታት። አሜሃ አልቦ ወርኅ ኢ ፀሐይ ኢ ክረምት ወኢ ሐጋይ)።                     🍏ዘዘወትር🍏 እግዚአብሔር፦ ክረምትን ለምድር ያዘጋጃል። በተራሮች ላይም ሣርን ያበቅላል። ደመናትም ቃሉን ይሰማሉ። [አቤቱ] አንተ ነዳያንንና ባዕለ ጸጎችን ትመግባቸዋለህ። ለሙት ልጆች አባት ነህ። ስለችግረኞች ሕዝብ ብለህ የምድርን ፍሬን ባርክ ለዘርና ለመከር አድርስ። የክርስቶስ ጥበቡ ድንቅ፣ ነገሩ መልካም፣ ቃሉ ያማረ ነው። ውሃን በደመና ሲያቁር ደመናው አይቀደድም። እግዚአብሔር ምክሬ እንደ ምክራችሁ ሐሳቤ እንደ ሐሳባችሁ አይደለም አለ። በምድር ላይ ዝናምን የማዘንብ በተራሮች ላይ ሣርን የማበቅል እኔ ነኝ። ለእንስሳት ምግባቸውን እሰጣቸዋለሁ። ይህንን ሁሉ እጄ ፈጥሮታልና። ከአብ በስተቀር የወልድን ሐሳብ የሚያውቅ የለም። ከወልድ በቀርም የአብን ሐሳብ የሚያውቅ የለም። አቤቱ አንተ የማትጎድል መዝገብ ነህ። አንተ ክብራችንና ጌጣችን ነህ። አንተ የመድኀኒታችን አክሊል ነህ። (#በግእዝ፦ ያስተዴሉ ክረምተ ለምድር ወያበቍል ሣዕረ ውስተ አድባር። እስመ ደመናትኒ ይሰምዑ ቃሎ። አንተ ትሴስዮሙ ለነዳይ ወለባዕላይ ለዕጓለ ማውታ አብ። ባርክ ፍሬሃ ለምድር አብጽሕ ለዘርዕ ወለማዕረር በእንተ ነዳያን ሕዝብከ። ጥዑም ቃሉ ወሠናይ ነገሩ መንክር ጥበቢሁ ለክርስቶስ። ዘየዐቍሮ ለማይ በደመና ወኢይሰጠጥ ደመናሁ። ይቤ እግዚአብሔር ኢኮነ ምክርየ ከመ ምክርክሙ ወኢኮነ ኅሊናየ ከመ ኅሊናክሙ። አነ ውእቱ ዘአወርድ ዝናመ ዲበ ምድር ወአበቍል ሣዕረ ውስተ አድባር እሁቦሙ ሲሳዮሙ ለእንስሳ እስመ እደውየ ገብሮ ለዝንቱ ኵሉ። አልቦ ዘየአምር ኅሊናሁ ለወልድ ዘእንበለ አብ ወአልቦ ዘየአምር ኅሊናሁ ለአብ ዘእንበለ ወልድ። አንተ ውእቱ ዘኢይቀብል መዝገብ። አንተ ውእቱ ክብርነ ወትርሲትነ። አንተ ውእቱ አክሊለ መድኀኒትነ)። ምስጋና፦ በየዘመኑ እንዴት እንደሠራ አይቼ እግዚአብሔርን እያመሰገንሁ ከገዳም ወጣሁ። (#በግእዝ፦ ወፃእኩ ውስተ ገዳም እንዘ እሴብሖ ለእግዚአብሔር ርእይየ ኵሎ ዘከመ ገብረ በበመዋዕሊሁ)። ተፈጥሮ፦ ደመናት በእውነት በአቅማቸው ውሃዎችን ያካፋሉ። (#በግእዝ፦ ይነፈንፋ ጽድቀ ደመናት ማያተ በአቅሞሙ)።             🍒ዘተረስዐ ዘልደት ሰንበት🍒 ነገረ ማርያም፦ እግዚአብሔር ማርያምን ዘመንሽ ዘመኔ ነው መጠንሽ መጠኔ ነው አላት። (#በግእዝ፦ ወይቤላ እግዚአብሔር ለማርያም አዝማንየ አዝማንኪ አምጣንየ አምጣንኪ)። © በትረ ማርያም አበባው ካሣ
500
6
[መሐረነ አብ የምህላ ጸሎት].mp3
816
7
▽▽▽መሐረነ አብ = አብ ሆይ ማረን▽▽▽ ➧፩➧መሐረነ አብ ➝ሃሌ ሉያ ➝ተሣሃለነ ወልድ ➝ሃሌ ሉያ ➝መንፈስ ቅዱስ መሓሪ ተዘከረነ በሣህልከ (፫ ጊዜ በል) ➧፪➧ለከ ንፌኑ ስብሐተ ወለከ ናዐርግ አኰቴተ። ➧፫➧መሐረነ መሓሪ ኀጢአተነ አስተሥሪ። ➧፬➧ወአድኅነነ ➝ወተማኅጸን ነፍሰነ ወሥጋነ ➝ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር። ➧፭➧አምላክነ ➝ወመድኀኒነ ➝ኢየሱስ ክርስቶስ ተሣሃለነ። ➧፮➧በብዝኀ ምሕረትከ ➝ደምስስ አበሳነ ➝ወፈኑ ሣህለከ ላዕሌነ። ➧፯➧እስመ እም ኀቤከ ➝ውእቱ ሣህል ➝ሃሌ ሉያ መሐረነ አብ መሓሪ። ➧፰➧ወተሣሃለነ ➝ሀብ ሣህለከ መሓሪ ➝ኢታጥፋነ ተዘኪረከ ዘትካት። ➧፱➧በምሕረትከ ➝እስመ መሓሪ አንተ ➝ወብዙኅ ሣህልከ ለኵሎሙ እለ ይጼውዑከ። ➧፲➧ይጼውዑከ በጽድቅ ➝ሰማዒ ወትረ ➝ከሃሊ ዘውስተ አድኅኖ። ➧፲፩➧ከሃሊ ➝ዘውስተ አድኅኖ ➝ለአምላክነ ጻድቅ እስመ ጽድቅ ቃሉ። ➧፲፪➧ንስአሎ ለአብ ➝ይፈኑ ለነ ሣህሎ ➝እስመ አብ የአክል ለዘሰአሎ። ➧፲፫➧ሃሌ ሉያ ➝ስብሐት ሎቱ ይደሉ ➝ሃሌ ሉያ አኰቴት ሎቱ ይደሉ። ➧፲፬➧ሃሌ ሉያ ➝ለክርስቶስ ለእግዚአ ኵሉ ➝ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ። ➧፲፭➧ወይዕዜኒ ➝መኑ ተስፋየ ➝አኮኑ ➝እግዚአብሔር ➝ውስተ እዴከ እግዚኦ አመኀፅን ነፍስየ። ➧፲፮➧ኀበ አምላከ ምሕረት ➝አመኀፅን ነፍስየ ➝ኀበ ንጉሠ ስብሐት ➝አመኀፅን ነፍስየ ➝በእግዚእየ ወአምላኪየ ➝አመኀፅን ነፍሰየ ➝እም ኵሉ ምግባረ እኩይ አድኅና ለነፍስየ። ➧፲፯➧ሀቡ ➝ንስአሎ ➝ናስተምሕሮ ➝ለአምላክነ ጻድቅ እስመ ጽድቅ ቃሉ። ➧፲፰➧ዘይክል ኵሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ ➝አምላከ ነዳያን ረዳኤ ምንዱባን ➝ንሕነ ኀቤከ ተማኅፀነ። ➧፲፱➧ዘይክል ኵሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ ➝አምላከ ነዳያን ናዛዜ ኅዙናን ➝ንሕነ ኀቤከ ተማኅፀነ። ➧፳➧ዘይክል ኵሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ ➝አምላከ ነዳያን ወተስፋ ቅቡጻን ➝ንሕነ ኀቤከ ተማኅፀነ። ➧፳፩➧ወበከመ ዐቀብከነ እም ነግህ እስከ ሠርክ ዕቀበነ እግዚኦ እም ሠርክ እስከ ነግህ። (፫ ጊዜ በል) ➧፳፪➧አይቴ ውእቱ አምላኮሙ ከመ ኢይበሉነ አሕዛብ ምህላነ ስማዕ ቃለ አብ። ➧፳፫➧አይቴ ይእቲ ትምክሕቶሙ ከመ ኢይበሉነ አሕዛብ ምህላነ ስምዒ ማርያም። ➧፳፬➧ኤሎሄ ኤሎሄ ዘአመ ትቤ በጽራሕከ ተማኅፀነ ምህላነ ስማዕ አምላክነ። ➧፳፭➧ተሣሃልከ እግዚኦ ምድረከ ሃሌ ሉያ ፤ ስማዕ ጸሎተነ ወስእለተነ ፤ ወስረይ ኵሎ ኀጢአተነ ፤ ስማዕ ፤ ጸሎተነ ወስእለተነ ፤ ዘሰማዕኮ ጸሎቶ ወስእለቶ ለዕዝራ ፤ ተወከፍ ምህላነ ሰላመከ ሀበነ፤ እማዕከሌነ ኢትርኀቅ። ➧፳፮➧ወሚጥ መዐተከ እምኔነ ፤ ሃሌ ሉያ ንዒ ኀቤየ እንቲኣየ ፤ ሠናይት ርግብየ መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል ወኵሉ ነገራ በሰላም። ➧፳፯➧አርእየነ እግዚኦ ሣህለከ ሃሌ ሉያ ፤ ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲኣነ ሐረድዎ ወገመድዎ ፤ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብአ ነገሥት ፤ ረገጸ ምድረ ፤ አንሥአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ ፤ በሰላም ዐደወ ፤ መንግሥተ ክብር ወረሰ ➧፳፰➧መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ሰአል ወጸሊ በእንቲኣነ አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩ ለንጉሥ ዐቢይ። ➧፳፱➧ገብርኤል አብሠራ ለማርያም ወይቤላ ትወልዲ ወልደ ወይነግሥ ለቤተ ያዕቆብ ለዓለም ወአልቦ ማኅለቅት ለሰላሙ። ➧፴➧ ባርከኒ አባ እንሣእ በረከተከ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ገብረ-መንፈስ-ቅዱስ አባ ባርከኒ እንሣእ በረከተከ። (ብፁዕ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘዔለ ገዳማተ እም ኀበ እግዚኡ ይንሣእ ዕሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሓ ወበሰላም።) ➧፴፩➧ማኅደረ ሰላምነ ቅድስት ደብተራ እሞሙ ለሰማእት ወእኅቶሙ ለመላእክት ንዑ ንስግድ ኵልነ ኀበ ማርያም እምነ። (መስቀል ብርሃን ለኵሉ ዓለም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን መድኀኔ ዓለም ወሀቤ ሰላም ሰላመከ ሀበነ።) ➧፴፪➧ለዓለም ወለዓለመ ዓለም ሃሌ ሉያ ሰላመ አብ ወሰላመ ወልድ ወሰላመ መንፈስቅዱስ የሀሉ ማዕከሌክሙ። ►►►►እግዚኦታ ይቀጥላል . . .►►► ➥➥መ/ር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ (ከድሬዳዋ)
763
8
◦•●◉ በታማኝነቱ የተመሰገነ ◉●•◦ በታማኝነቱ የተመሰገነ ለእመቤታችን ጠባቂ የሆነ ዮሴፍ አረጋዊ ይባርከን ፀሎትህ ምሳሌ ሆኖናል ብርሃን ህይወትህ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ማዕረግ ቅድስና ታላቅ ስለሆነ ከእስራኤል አባቶች እጣው ለአንተ ሆነ ጌታን ለማሳደግ በቅተሀል በፀጋ በአተረፍከው መክሊት በተሰጠህ ዋጋ/2/ ◦•●◉።።።።።።።አዝ።።።።።።።◉●•◦ በረሃብ በስደት ልብህ አልተፈታ ለፈጠረ ሕፃን ታምነሃል ለጌታ ተጋድሎህን አልገታ ድካም ሽምግልና በረታ ጉልበትህ በአምላክ እንደገና/2/ ◦•●◉።።።።።።።አዝ።።።።።።።◉●•◦ የዳዊት ልጅ ዮሴፍ እጅግ አስተማርከን ጠባቂ እና አባት ሆነህ በሌት በቀን የድንግልን ሀዘን ሰቆቃ ስደት ተካፍለህ ወስደሃል ታላቅ በረከት/2/ ◦•●◉።።።።።።።አዝ።።።።።።።◉●•◦ የሰማዩን ኪዳን የአብን አደራ በትንሿ ቤትህ ጠበክም ሳትፈራ በዓለም ስደተኛ የሆነው ሕፃን አደገ በቤትህ ታላቁ መድህን/2/
642
9
+2
መልክዐ ፍልሰታ እና እትአመነኪ ማርያም-በገብረ ሥላሴ
643
10
🍀🍀🍀🍀🍀🍀 መዝሙር ዘሰንበት 🍁🍁🍁🍁🍁🍁 ከሐምሌ ፳፬ እስከ ሐምሌ ፴ (በ፫/ሙ) ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ፤ምህሮሙ ወይቤሎሙ አክብሩ ሰንበትየ፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ፤ በሰንበት አጋንንተ አውጽአ ወበቃሉ እለ ለምፅ አንጽሐ ፤በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ በሰንበት ወረቀ ምድረ ወገብረ ፅቡረ ወበምራቁ አሕየወ ዕውረ፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ዘይኤዝዞሙ ለደመናት ያውርዱ ዝናመ ውስተ ኵሉ ምድር፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ያውርዱ ዝናመ ውስተ ኵሉ ምድር ውስተ ፍና ኀበ ይትፈቀድ መካን፤ በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ውስተ ፍና ኀበ ይትፈቀድ መካን ከመ ኅቡረ ይትፈሣሕ ዘይዘርዕ ወየዓርር ፤በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ማ፦ምድር ርእየቶ ወአእኰተቶ ፤ባሕርኒ ሰገደት ሎቱ። አመላለስ፦ ምድርኒ ርእየቶ ወአእኮተቶ/2/ ባሕርኒ ሰገደት ሎቱ/4/ ትርጉም፦ በሰንበት ወደአይሁድ ምኲራብ ገባ ሰንበቴን አክብሩ ብሎ አስተማራቸው በሰንበት አጋንንትን አወጣ በቃሉ ለምፃሞችን አነጻ በሰንበት ምራቁን ወደምድር እንትፍ አለ ጭቃም አደረገ በምራቁ ዕውሩን አዳነ በምድር ሁሉ ላይ ዝናምን ያወርዱ ዘንድ ደመናዎችን የሚያዛቸው እሱ ነው በሚያስፈልግበት ስፍራ ሁሉ። የሚዘራም የሚያጭድም አንድ ላይ ይደሰቱ ዘንድ። ምድር አየችው አመሰገነችው ባሕርም ሰገደችለት። https://t.me/maheberat
611
11
​​​​👆የቀጠለ እኒኽም ቅዱሳን ይኽንን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን የሚቆለምም ልብንም የሚያቀልጥ ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርን የሚበጣጥስ መሳሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፡፡ ከቅዱሳኑም አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋር ማቃጠሉና መፍላቱ ጸጥ አለ፡፡ ወንድሞቻችን ሆይ እንግዲህ በጭንቃቸው ጊዜ ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ይህ መልአክ ከሰማእታትና ከጻድቃን ጐን እንደማይለይ እወቁ ለኃጥአንም ኃጢአታቸውን ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላቸዋል፡፡ እኛም የዚህ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓሉን እያከበርን አማላጅና ወዳጅ እናድርገው። በዚህም በሚመጣውም ዓለም ሊረዳን ይችላልና፡፡ ዳግመኛም መስፍኑ ሐሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ 14 የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል ሰባቱን በራሱ በቂርቆስ አካል ማለት ሁለቱን በጆሮዎቹ ሁለቱን በዐይኖቹ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ አንዱን በልቡ ይቸነክራቸው ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የህፃኑን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ ይጨምሩ ዘንድ አዘዘ፡፡ አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህንን መከራ ከእርሱ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡ ሕዝቡም ይህንን ሁሉ ተአምር ባዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡ ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ብዙ መከራ ከተቀበሉ በኋላ ጥር 15 በሰይፍ ተመትተው ስማትነትን ተቀብለዋል። የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እየሉጣ ተራዳኢነት ጸሎት አይለየን። ከዚህ በኋላ ሕፃኑን አስፈልገው ቢጠይቁት ነቢዩ ዳዊት የተናገረው ኃይለ ቃል መንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት፤ ‹‹የአሕዛብ ጣዖታት የወርቅና የብር የሰው እጅ ሥራዎች ናቸው፡፡ የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ›› መዝ. ፻፴ በማለት ሲዘልፏቸው አገር ገዥው ሰምቶ ተቆጣና የብረት ጋን አስመጥቶ ውኃ ሞልቶ ከዕቶን እሳት ላይ ጥዶ ልዩ ልዩ ማገዶዎች በመጨመር ነበልባሉ ከመጠን በላይ ሆነ፡፡ የብረት ጋኑም ድምፅ እንደ ክረምት መብረቅና ነጎድጓድ እስኪያስፈራ ድረስ አስነድዶ ሕፃኑን ከነእናቱ ወስዳችሁ ጨምሩአቸው ብሎ አዘዘ፡፡ በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ በጣም ፈራች፡፡ የእግዚአብሔር ሥራ እፁብ ድንቅ ግሩም ረቂቅ ነው፡፡ ገና አፉን ያልፈታ የሦስት ዓመት ሕፃን ‹‹እናቴ ሆይ! ገድላችን እንፈጽም ዘንድ ጨክኝ በርቺ›› አላት፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም ‹‹ልጄ የነፍስ አባት ሁነኝ›› አለችው፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ከዘመናቸው ሳይደርስ፣ ታሪካቸውን ሳይማር የሠለስቱ ደቂቅን ታሪክ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ‹‹አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል›› ቢላት ፍርሃቱ ሊለቃት ባለመቻሉ፣ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ! የወይኑን ፍሬ ስትሻ ግንዱን ታጠፋለህን? እንደዚህስ ሁሉ እኔን አድነህ እናቴን ታጠፋታለህን?›› ብሎ በጸለየጊዜ መንፈስ ቅዱስ አደረባትና መንግሥተ ሰማያትን በዓይነ ሥጋ እንድታይ አደረጋት፡፡ ከዚህ በኋላ ፍርሃቱ ለቀቃትና ‹‹ልጄ ሆይ! ከዛሬ ጀምሮ መምህሬ፣ አባቴ፣ መካሪዬ እልሃለሁ እንጂ ልጄ አልልህም›› ብላ በጭካኔ ከልጅዋ ጋር ወደ ፈላው የብረት ጋን ገባችበት፡፡ በዚህ ጊዜ ሕፃኑ ቂርቆስ አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል ያለውን ቃል ለመፈጻም እግዚአብሔር አምላክ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው፡፡ መልአኩም በትእምርተ መስቀል እሳቱን ቢባርከው እንደ በረዶ ቀዝቅዞላቸዋል፡፡ በመልካቸውም እንደ ፀሐይ አበራ፡፡ ከእግር ጥፍራቸው እስከ ራስ ጠሩራቸው አንድም ሳይጎዳቸው በደህና ወጡ፡፡ በመጨረሻም ሕፃኑ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ እንዲህ አለ፡፡ ይህን ያህል ገድል ተጋድዬ ምን ዋጋ ትሰጠኛለህ ቢለው፣ ጌታ በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ዳግመኛም ሥጋህ በምድር ላይ እንዳይፈርስ እንዳይበሰብስ በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርሃለሁ አለው፡፡ ስለሆነም በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያናችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለእናታችን ለቅድስት ኢየሉጣ እና ለሕፃኑ ለቅዱስ ቂርቆስ ያደረገውን ይህን ታላቅ ተአምር ድንቅ ሥራ በማሰብ ከዋዜማው ጀምራ እግዚአብሔርን ስታመሰግን ትውላለች ታድራለች፡፡ የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከት ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይኑር አሜን፡፡
600
12
​​ሐምሌ 19 ቅዱስ ገብርኤል እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!! በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው። የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል እንዲህ ተርከውታል፡፡ በዘመነ ሰማእታት ከሐድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች ሰማእትነትን ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ። እየሉጣም የሦስት ዓመት ህፃን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኮንን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሰሩባት ወደእርሱ አስቀረባት እና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኮንን ሆይ ዕድሜው ሦስት አመት የሆነው ህፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ አለችው፡፡ ህፃኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደእርሱ አስመጣው ህፃኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ህፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው፡፡ ህፃኑም መልሶ አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፡፡ መጻሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና አለው፡፡ እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስካስደነገጣቸው ድረስ ንጉሱን መኳንንቱንና ጣኦታቱን ረገማቸው፡፡ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ፡፡ መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በያይነቱ በሆነ ስቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት፡፡ እግዚአብሔርም ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር፡፡ ብዙዎች አህዛብም ይኸንን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማእትነት አረፉ፡፡ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ፡፡ በህፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው፡፡ መስፍኑም በውስጡ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አንጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም እንዳዘዛቸው ካአደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፡፡ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮኸል ወላፈኑም እንደጸሐይ ነጸብራቅ በሩቁ ይጋረፋል፡፡ የፍላቱም ኃይል በ14 ክንድ ያኽል ከፍታ ወደ ላይ ይዘላል፡፡ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት በዚህ ጊዜ ህፃን ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡ በዚያም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጼም አይደርብሽ አናንያንና አዛርያን ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከእቶነ እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ፡፡ እናት ሆ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለመዳን ስትይ በማያልፈው ዘላለማዊ እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ይኽስ አይሆንም ይቅርብሽ፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናት ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እርሱ እኛንም ከጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን ልጆቹንና ሚስቱን በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባሳጣው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ እግዚአብሐር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ እግዚአብሔርም እንደወደደ አደረገ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይኽንን መከራ ልንታገስ ይገባናል፡፡ ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላክ ሆይ ይችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይኽን እንዳታደር ግን ቸርነትህ ትከለክልኸለች አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለኽ ልታዝ መለኮታዊ ባሕሪህ አይደለም፡፡ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም በአንድ ጠብቁት ብለኽ ታዝዛለኽ እንጂ፡፡ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይኽንን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡ አቤቱ ዲያብሎስም ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማው በማለት እንዳይደነፋ ለእናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከእየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታኽ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቸዋለሁና አለችው፡፡
491
13
በዘባነ ኪሩብ በዘባነ ኪሩብ ለሚቀመጠው በእሳት ድንጋዮች ቅጥሩን ላጠራው ዘምሩ ለእግዚአብሔር ለጌታ ዘምሩ የተከበረ ነው በሰማይ በምድሩ /2×/ /አዝ/ ኢሳይያስ ሲያየው በእጅግ አፈረ የተፈራ ነው የተከበረ የሰማይ ደጆች ተንቀጠቀጡ ለቅዱስ ስሙ ክብርን ሲሰጡ /አዝ/ ያልተቀደሰ ለምጽ ያነደደው እንዴት ይችላል ሊያመሰግነው በል ፍቀድልኝ ፍቅር ነህና ልግባ መቅደስህ ላቅርብ ምስጋና /አዝ/ ዙፋንህ ታየኝ ትምክህቴ ሆይ ስትመሰገን በሰማይ ላይ ሲያመሰግንህ ያልተደሰተ ባይተዋር አልሁን አልወጣ ከአንተ /አዝ/ ቅኔ የሞላበት ያንን ሰገነት ልቀላቀለው ተመኘሁ በእውነት ልዘምርልህ ባይገባኝም ዝም የሚል ልሳን አልሰጠኸኝም    ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
621
14
አጎንብሼ ሄጄ አጎንብሼ ሄጄ ቀና ብዬ መጣው በዮሐንስ ጠበል ጤናዬን አገኘው ጌታን ያጠመቁ ክቡራን እጆቹ ተዓምር ይሰራሉ ዛሬም ለልጆቹ አዝ አልጋዬን አዝዬ በደስታ ዘለልኩኝ በመጥምቁ ጠበል በእጁ ተዳሰስኩኝ የመራኝን በትር ከእጄ ላይ ጥያለሁ በሰባኪው ጸሎት በምልጃው ድኛለሁ አዝ ለዓለም ያልተቻላት በእምነቱ ለቆኛል አበቃልህ ያሉኝ እጅግ ተደንቀዋል በለምጽ የነደድኩት ታደስኩ እንደገና አዲስ አካል ይዤ ቆምኩኝ ለምስጋና አዝ ያለፍኩባት ሰፈር በእምባ ተሞልቼ እልልታዬን ሰማች ድኜ ተደስቼ የንዕማን ቁስል ተራግፏል ከላዬ መሞቴን የማይወድ አሰበኝ ጌታዬ አዝ አባናና ፋርፋን አስንቁአል ጠበል ዮርዳኖስ በእምነት ለወረዱ ሁሉ ዮሐንስ በመንፈስ ሲያጠምቅ አይቻለሁ በእጁ ተፈውሼ ምስክር ሆኛለሁ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
567
15
በማህፀን ቅኔ በማህፀን ቅኔ ለማርያም ተሰማ በተራራማ አገር በኤፍሬም ከተማ ዮሐንስ ይናገር በረሃ ያደገው ድንግል ስትናገር ምን እንዳዘለለው የእናቱ ማህፀን የቅኔ እርስት ሆነች ድንግል የአምላክ እናት ፊቱ ስለቆመች በሀሴት ዘለለ ዘመረ በደስታ ከድንግል ሲወጣ ታላቁ ሰላምታ አዝ።።።።።። በድንግል ማህፀን ስላየ ጌታውን ከመወለድ ቀድሞ ሰማነው መዝሙሩን ትንቢቱ ሲፈፀም በሆዷ ሲነግስ ሰገደ ለአምላኩ የስድስት ወር ፅንስ አዝ።።።።።። ጀመረ ስብከቱን ገና ሳይወለድ ተፈጥሮ መች ቻለ ነብዩን ለማገድ አፉ ተከፈተ በታላቅ ምስጋና በእናቱ ማህፀን ድምፅን አሰማና አዝ።።።።።። የዮሐንስ እናት ኤልሳቤጥ ገረማት ልጇ በማህፀን ቅኔን ሲቀኝባት ድምጿን ከፍ አረገች አለም እንዲሰማ ሞላት መንፈስ ቅዱስ በመዝሙር በዜማ አዝ።።።።።። የዮሐንስ እናት ኤልሳቤጥ ገረማት ልጇ በማህፀን ቅኔን ሲቀኝባት ድምጿን ከፍ አረገች አለም እንዲሰማ ሞላት መንፈስ ቅዱስ በመዝሙር በዜማ
512
16
እግዚአብሔርን አመስግኑ ስራው ግሩምድንቅ ነው በሉ እግዚአብሔርን አመስግኑት እግዚአብሔርን አመስግኑት ሥራ ግሩም ድንቅ ነው በሉት እግዚአብሔርን እመስግኑት ስራህ ግሩም ድንቅ ነው በሉት ❴አዝ❵ ሠማይን ያለ ምሰሶ ምድርንም ያለ መሰረት ያጸናው እርሱ ነው ሥራህ ድንቅ ነው በሉት ❴አዝ❵ የባህርንም ጥልቀት የመጠነ ዳርቻዋን የወሰነ እግዚአብሔርን አመስግኑ ሥራ ግሩም ድንቅ ነው በሉት ❴አዝ❵ ማእበል ንፋሱን የሚገስጽ ፍጥረቱ ለስሙ የሚታዘዝ ትጉህ እረኛ ድካም የሌለበት እግዚአብሔርን ሥራህ ድንቅ ነው በሉት ❴አዝ❵ ንጹሐ ባህርይ ነው ሁሉን የሚገዛ የነገስታት ንጉስ አልፋና ኦሜጋ ዘለዓለም እርሱ ነው የማይለወጥ እግዚአብሔር ስራህ ድንቅ ነው በሉት ❴አዝ❵ ጥበብን የሚሰጥ ጥበበኛ ፍርድ የማያጎድል እውነተኛ ዳኛ እንደ እርሱ ያለ ከቶ አይገኝም እግዚአብሔር ግሩም ነው ለዘልዓለም
511
17
ኪዳነምሕረት እናቴ ኪዳነምህረት እናቴ ሚስጥረኛየ ጓዳዬ የጎደለኝን ታውቂያለሽ ካፌ ሳይወጣ ሳልነግርሽ/2/ አዝ አልፏል መናኛው ኑሮ ምልጃሽ ውሀውን ቀይሮ መልካሙ ወይን ደረሰ እንባዬ ባንቺ ታበሰ /2/ አዝ ልዘምር ልቁም ከፊትሽ ልምጣ ልንበርከክ ለክብርሽ ብርቅ ከሀገር ከቤቴ ከቶ አረሳሽም እናቴ/2/ አዝ አልልም መቼ ነው ቀኑ የኔ መጎብኛ ዘመኑ እንደሚፈፀም አምናለሁ ሁሉን በጊዜው አያለሁ /2/ አዝ የልቤን ችግር  ላዋይሽ ከስእልሽ ፊት ቆሜ እንባዬ ቀድሞኝ ዝም አልኩኝ ሳልነግርሽ ስለምታውቂ /2/ ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ
513
18
​​​​ሰኔ ፲፪ የቅዱስ_ሚካኤል ዓመታዊ በዓል! እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ። 👉 በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው “በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ድረስልኝ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡ ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
525
19
❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️ የሰኔ 12 የሀያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ማኅሌት አማርኛ ትርጉም(ክፍል ፪) 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 መልክዓ ሚካኤል ለእስትፋስከ ከተባለ በኃላ ዚቅ ወከሢቶ ረከበ ኀበ ይብል እዜንዎሙ ለነዳያን ፈነወኒ: ወእከስት ሎሙ ግዕዛነ ለጼውዋን: ወእፈውስ ሎሙ ለቁሱላነ ልብ: ወእሰምዮ ለባሕራን ኅሩየ: ዝኬ ዘተነግረ በመዋዕለ ትካት: ለ፳ኤል ኅብስተ መና ዘአውረደ በገዳም: ወርእየቱ ከመ ተቅዳ ወከመ አያያተ መዓር ጥዑም ፈድፋደ።  የዐማርኛ ትርጕም ደብዳቤውን ገልጦም ”ለችግረኞች እረዳቸው ዘንድ ላከኝ” የሚል ጽሑፍ አገኘ። ለምርኮኞችምነጻነትን እሰጣቸው ዘንድ።የልብ ቁስለኞችንም አድን ዘንድ፤ባሕራን የተመረጠ ብዬ እሰይመዋለኹ።ይኽ በጥንት ዘምን የተነገረ ነው።ለእስራኤል መና ከደመና በምድረ በዳ ያወረደ ርሱ ነው።መልኩም እንደ ድንብላልና እጅግ እንደሚጣፍጥ የማር ወለላ ነበር። ወረብ "ወከሢቶ ረከበ"/፪/ ኀበ ይብል እዜንዎሙ ለነዳያን ፈነወኒ/፪/ ወእስብክ ሎሙ ግዕዛነ ለጼውዋን ወእስምዮ ለባሕራን ኅሩየ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም ደብዳቤውን ገልጦም ”ለችግረኞች እረዳቸው ዘንድ ላከኝ” የሚል ጽሑፍ አገኘ።ለምርኮኞችም ነጻነትን እሰጣቸው ዘንድ።ባሕራን የተመረጠ ብዬ እሰይመዋለኹ። መልክዐ ሚካኤል፦ ሰላም ለአጻብኢከ መጽሐፈ እለ ለክዑ፤ዕጒለ አባግዕ እምኖሎት በጊዜ ተመልዑ፤ሚካኤል አንተ ለንጉሠ ነገሥት ካህነ ምሥዋኡ፤አሣዕነ መድኃኒት ለእገርየ አጻብኢከ ይቅጽዑ፤ከመ በፍናውየ የኀዝ ለሰላም ቅብዑ።  የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል ሆይ በትጉሃን እረኞች ትጋት የተነሣ ደቂቀ አባግዕ በበረከቱ ጊዜ መጻሕፍትን ላዘጋጁ ጣቶችህ ሰላም እላለሁ። ጠባቂው መልአክ ሆይ የነገሥታት ንጉሥ የሚሆን የእግዚአብሔርየመሥዋቱ ካህን ነህና።በምሄድበት ጎዳና በሰላም እራመድ ዘንድ።በጥበብ የበለጸጉ ጣቶች ለእግሮቼ የሕይወት ጫማን ያዘጋጁልኝ። ዚቅ ቅዱሳት አጻብኢከ ለጽሒፈ መጽሐፍ እለ ተቀንያ: ወብጹዓት አዕይንቲከ ምስጢረ መለኮትዘርእያ: ሚካኤል መልአክ ወሐዋርያ።  የዐማርኛ ትርጕም መልአክና አስተማሪ የኾንክ ሚካኤል መጽሐፍን ለመጽሐፍ የቀኑ/የለዘቡ እጣቶችኽ የተለዩ ናቸው፤የመለኮት ምስጢርን ያዩ ዐይኖችኽም ምስጉኖች ናቸው። ወረብ ምስጢረ መለኮት ዘርእያ አዕይንቲከ/፪/ ሚካኤል መልአክ መልአክ ወሐዋርያ ሚካኤል መልአክ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል መልአክ ኾይ መልአክ ነኽ፤ ዳግመኛም ሚካኤል መልአክም ሐዋርያ ነኽ መልክዐ ሚካኤል፦ አምኃ ሰላም አቅረብኩ ለመልክዕከ ኲሉ:ለለአሐዱ አሐዱ ዘበበክፍሉ: ሚካኤል ክቡር ለልዑል መልአከ ኃይሉ:  ተወኪፈከ አምኃየ እምኑኃ ሰማያት ዘላዕሉ:  ዕሴተ ጸሎትየ ፈኑ ወአስብየ ድሉ።  የዐማርኛ ትርጕም  ሚካኤል ሆይ ለእያንዳንዱ በየክፍሉ ለተነገሩ መልኮችህ ሁሉ የምስጋና እጅ መንሻ አቀርባለሁ።ልዑሉ መልአክ ሆይ እግዚአብሔር ኃይሉን የሚገልጽብህ ኃያል መልአክ ነህና የምስጋናዬን እጅ መንሻ ተቀብለህ።ከላይ ከኢየሩሳሌም ሰማያዊት የጸሎቴን ዋጋ እጥፍ ድርብ አድርገህ ላክልኝ። ዚቅ  መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል: ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ: አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩለንጉሥ ዓቢይ።  የዐማርኛ ትርጕም  የሰላማችን አለቃ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ስለ እኛ ለምንልን፤ ልመናችንን ወደ ገናናው ንጉሥ ዙፋን አሳርግ ወረብ  መልአከ ሰላምነ/፬/ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ሰአል በእንቲአነ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም  የሰላማችን አለቃ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ስለ እኛ ለምንልን አንገርጋሪ  አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእነ: ሚካኤል አርመመ ወገብርኤል ተደመ: ፀሐይ ጸልመ ወወርኅደመ ኮነ: ወሪዶ እመስቀሉ አብርሃ ለኲሉ።  የዐማርኛ ትርጕም  ጌታችንን አይሁድ በሰቀሉት ጊዜ ሚካኤል ዝም አለ፤ገብርኤል ግን ተቆጣ፤ፀሓይ ጨለመ፤ጨረቃም ደምን ኾነ ከመስቀሉ ወርዶ ለኹሉ አበራ። አመላለስ  ወሪዶ እመስቀሉ/፪/ እመስቀሉ አብርሃ ለኲሉ/፬/  የዐማርኛ ትርጕም  ከመስቀሉ ወርዶ ለኹሉ አበራ። ወረብ  አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእነ/፪/ ሚካኤል አርመመ ወገብርኤል ተደመ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም  ጌታችንን አይሁድ በሰቀሉት ጊዜ ሚካኤል ዝም አለ፤ገብርኤል ግን ተቆጣ። እስመ ለዓለም፦ ይቤሎሙ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ: አዓርግ ሰማየ አቡየ ወአቡክሙ: ኀበ አምላኪየ ወአምላክክሙ: ዘንተ ይቤሎሙ ዓርገ ውስተ ሰማያት: ካዕበ ይመጽእ በዘዚአሁ ስብሐት: ሠርጎሙ ለሐዋርያት ብርሃኖሙ ለእለ ውስተ ጽልመት: መድኃኔነገሥት ክብሮሙ ለመላእክት ኖላዊሆሙ ለአሕዛብ ለከ ስብሐት  የዐማርኛ ትርጕም  ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን “ወደ አባቴና አባታችኹ ሰማይ እኼዳለኹ” አላቸው። ይኽን ብሏቸው ወደ ሰማያት ወጣ።ዳግመኛም በራሱ ምስጋና ይመጣል።የደቀ መዛሙርቱ ሽልማታቸው ነው፤በጨለማ ውስጥ ላሉትም ብርሃናቸው ነው፤የነገሥት አዳኝ የመላእክት ክብራቸው፣ጠባቂያቸው ነው። ዓዲ እስመ ለዓለም-  እምድኅረ ተንሥአ እሙታን ዓርገ ውስተ ሰማያት በስብሐት አምላከ ምሕረት: ወተቀብልዎ አዕላፋ አዕላፋት: ወሚካኤል ሊቀ መላእክት በንፍሐተ ቀርን እምኀበ እግዚአብሔር: ስብኩ ትንሣኤ ውስተ ኲሉ ምድር።  የዐማርኛ ትርጕም  የይቅርታ አምላክ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ በክብር ወደ ሰማያት አረገ፤የአእላፍ መላእክትም ተቀበሉት፤ሚካኤልም በመለኸት ድምፅ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፤በዓለም ኹሉ መነሣቱን አስተምሩ። https://t.me/maheberat
438
20
❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️ የሰኔ 12 የሀያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ማኅሌት አማርኛ ትርጉም(ክፍል ፩) 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 ሥርዓተ ነግሥ:-  ስምዐኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉አቤቱ ጸሎቴን ስማኝ ምስጋና አቀርባለኹ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉ጩኸቴም በፊትኽ ይድረስ ምስጋና አቀርባለኹ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ 👉ፊትኽን ከእኔ አትመልስ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉በችግሬ ጊዜ ጆሮኽን ወደ እኔ አድምጥ ምስጋና አቀርባለኹ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ 👉በምጠራኽ ጊዜም ፈጥነኽ ስማኝ ምስጋና አቀርባለኹ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል። 👉 ለዘለዓለሙ ምስጋና አቀርባለኹ። ያ ማለት ያለ ልዑል እግዚአብሔርን እናመስግነው ማለት ነው። በአንዲት ቃል ዓለምን ኹሉ የፈጠረ አምላክ ፈጽሞ የተመሰገነ ነው።    መልክዐ ሥላሴ፦ ሰላም ለጒርኤክሙ ስቴ አንብዐ ሰብእ ዘኀሠሠ፤ብዑላነ ሞገስ ሥላሴ ኢታንድዩኒ ሞገሰ፤እመ ትትኃየዩኒሰ ኢትኅድጉኒ ጽኑሰ፤ሚካኤልኑ ለአውጽኦ ስጋየ ጌሠ፤ወእመ አኮ ገብርኤል ወሀበኒ ነፍሰ።  የዐማርኛ ትርጕም  የሰውን እንባ መጠጥ ለፈለገ ጉሮሯችኹ ሰላም ይገባል።ባለሟል ባዕለጸጎች ሥላሴ ከበሟልነት አታሳጡኝ፤ቸል ቸል ብትሉኝ ስንኳ ችግረኛ እንደኾንኩ አትተውኝ፤ሚካኤል ሥጋዬን ለማውጣት ገሠገሠን?ያም ባይኾን ገብርኤል ነፍስን ሰጠኝ። ዚቅ  ኢይጽሕቅ ዘይመክሮ ወኢየኀሥሥ ዘይመክሮ:አልቦቱ ጥንት ወኢተፍጻሜት: ኢየኀልቅመንግሥቱ ወአልቦ ዘይክል መዊዐ ኀይሉ:ወአልቦ ኁልቊ ለሠራዊተ መላእክት እለ ይትለአክዎ: አንተ ውእቱ አቡሃ ለጥበብ: ገባሬ ኲሉፍጥረት ወገባሪሃ ለሕግ።  የዐማርኛ ትርጕም  የሚመክረው አይለምንም፤የሚመክረውም አይፈልግም።መጀመሪያና መጨረሻ የለውም።መንግሥቱም አያልቅም።ኀይሉን ማሸነፍ የሚችልም የለም።ለሚላኩት የመላእክት አለቆችም ስፍር ቁጥር የላቸውም።የጥበብ አባቷ አንተ ነኽ፤የፍጥረት ኹሉ ሠሪ አንተ ነኽ፤የሕግ ሠሪዋም አንተ ነኽ።    ነግሥ  ሰላም ለልሳንከ መዝሙረ ቅዳሴ ዘነበልባል፤ ወለድምፀ ቃልከ ሐዋዝ ቀርነ መንግሥቱ ለቃል፤ሞገሰ ክብሩ ሚካኤል ለተላፊኖስ ባዕል፤አልቦ ዘይትማሰለከ በልማደ ምሕረት ወሣህል፤እንበለ ባሕቲታ እኅትከ ማርያም ድንግል። የዐማርኛ ትርጕም  ነበልባላዊ የኾነ የምስጋና መዝሙር ለሚሰጥ አንደበትኽ ሰላም ይገባል።የቃል የመንግሥቱ መለኸት ያማረ ለቃልኽ ድምፅም ሰላም ይገባል።የተላፊኖስ ሀብታም የክብሩ ሞገስ ሚካኤል ኾይ በምሕረትና ይቅርታ ልምድ የሚመሳሰልኽ የለም።ብቸኛዋ እኅትኽ ማርያም ድንግል ናት እንጅ ዚቅ  አመ ይነፍህ ሚካኤል ቀርነ በደብረ መቅደስየ: አሜሃ ይትነሥኡ ሙታን: ይትፌሥሁ መላእክት በዕርገቱ: በፍሥሃ ወበሰላም አዕኮትዎ ለንጉሠ ስብሐት።  የዐማርኛ ትርጕም  ሚካኤል በመቅደሴ ተራራ መለኸትን በነፋ ጊዜ ያን ጊዜ ሙታኖች ይነሣሉ፤ወደ ሰማይ በማረጉም መላእክት ይደሰታሉ፤የምስጋና ንጉሥን በደስታና በፍቅር አመሰገኑት።    መልክዐ ሚካኤል፦ ሰላም ለዝክረ ስምከ ምስለ ስመ ልዑል ዘተሳተፈ፤ወልደ ያሬድ ሄኖክ በከመ ጸሐፈ፤ ሶበ እጼውእ ስመከ ከሢትየ አፈ፤ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል በከመ ታለምድ ዘልፈ፤ለረዲኦትየ ነዓ ሠፊሐከ ክንፈ።  የዐማርኛ ትርጕም  ሚካኤል ኾይ የያሬድ ልጅ ሄኖክ እንደጻፈው።ከልዑል ስም አጠራር ጋር ለተባበረ ስም አጠራርኽ ሰላም እላለኹ።የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ኾይ የተቸገሩትን የተጨነቁትን ዘወትር እንደምትረዳቸው ኹሉ እኔንም ለመርዳት ክንፍኽን ዘርግተኽ ፈጥነኽ ድረስልኝ። ዚቅ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ አቢተነ በመድኃኒትከ: ጸግወነ ንጸውዕ ስመከ: ኖላዊነ ኄር ትጉሕ ዘኢትነውም ሰላመከ ሀበነ።  የዐማርኛ ትርጕም ምስጋና ምስጋና በመድኀኒትኽ አሳድረን፤ስምኽን እንጠራ ዘንድ ስጠን፤የማታንቀላፋ ትጉ ቸር እረኛ ሰላምኽን ስጠን። ወረብ ሀበነ ሰላመከ ንጸውዕ ስመከ/፪/ ዘኢትነውም ትጉሕ "ኖላዊነ ኄር"/፪//፪/  የዐማርኛ ትርጕም የማታንቀላፋ ትጉ ቸር እረኛ፤ ስምኽን እንጠራ ዘንድ ሰላምኽን ስጠን።    መልክዐ ሚካኤል፦ ሰላም ለልሳንከ በነቢበ ጽርፈት ዘኢተሀበለ፤በእንተ ሥጋሁ ለሙሴ አመ ምስለ ሰይጣን ተበሀለ፤ሚካኤል ክብርከ እምክብረ መላእክት ተልዕለ፤ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ፤በብሂለ ኦሆ ፍጡነ አስምዐኒ ቃለ።  የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል ኾይ ስለ ሙሴ ሥጋ ከዲያብሎስ ጋር ክርክር በተደረገ ጊዜ የዘለፋ ቃል ላልተናገረ አንደበትኽ ሰላም እላለሁ።ክቡሩ መልአክ ኾይ ክብርኽ ከመላእክት ኹሉ ክብር ከፍ ያለ ነውና። በሥነ ሥዕልኽ ፊት ቁሜ ልመናዬን በማቀርብበት ጊዜ ኹሉ። “አይዞኽ አለኹልኽ” በማለት ፈጥነኽ ድምፅኽን አሰማኝ። ወረብ ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ/፪/ "በብሂለ ኦሆ"/፪/ ፍጡነ አስምአኒ ቃለ/፪/  የዐማርኛ ትርጕም በሥነ ሥዕልኽ ፊት ቁሜ ልመናዬን በማቀርብበት ጊዜ ኹሉ። “አይዞኽ አለኹልኽ” በማለት ፈጥነኽ ድምፅኽን አሰማኝ። ዚቅ አመ ይነፍሕ ሚካኤል ቀርነ በደብረ መቅደስየ: አሜሃ ይትነሥኡ ሙታን: ይትፌሥሁ መላእክት በዕርገቱ: በፍሥሃ ወበሰላም አዕኮትዎ ለንጉሠ ስብሐት።  የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል በመቅደሴ ተራራ መለኸትን በነፋ ጊዜ ያን ጊዜ ሙታኖች ይነሣሉ፤ወደ ሰማይ በማረጉም መላእክት ይደሰታሉ፤የምስጋና ንጉሥን በደስታና በፍቅር አመሰገኑት።    መልክዐ ሚካኤል፦ ሰላም ዕብል ለአስናኒከ ዘመንፈስ፤ ዘኢይረክቦን ጥረስ፤ሚካኤል ረዳኢ ለእለ ውስተ ባሕር ወየብስ፤እስመ ረሰይከ ካህነ ምሥዋኡ ክርስቶስ፤መፍትው ሊተ ትተንብል ቀሲስ። የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል ኾይ መሰበር ማፋጨት ለማያገኛቸው ረቂቃን አስናኖችኽ ሰላም ይገባል።ረዳቴ መልአክ ኾይ በባሕር ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ በየብስ ላይ ለሚመላለሱ ፍጥረታት ኹሉ ረዳታቸው አንተ ነኽ።ስለዚኽም ኢየሱስ ክርስቶስ በመሠዊያው ላይ ካህን አድርጎ ሾሞኻልና። አንተ ቀሲሱ ሚካኤል ለኔ ለአገልጋይኽ ምሕረትን ትለምን ዘንድ ተገቢ ነው። ዚቅ ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕረ ምስሌሁ: ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ: ዮም ሰማያዊ በምድር አስተርአየ።  የዐማርኛ ትርጕም ባሕራንም ከርሱ ጋራ ወደ ባሕር የኼደ ሚካኤልን አየኹት መረዳቱን ግን አልቻልኩም፤ ሰማያዊ ዛሬ በምድር ታየ። ወረብ ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕረ/፪/ ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ ስዕንኩ/፪/ ባሕራንም ከርሱ ጋራ ወደ ባሕር የኼደ ሚካኤልን አየኹት፤ መረዳቱን ግን አልቻልኩም፤ሰማያዊ ዛሬ በምድር ታየ።    መልክዐ ሚካኤል ሰላም ለእስትንፋስከ ቁሱላነ ነፍስ ለአጥዕዮ፤ ዘይነፍሕ ፄና አንህዮ፤ሚካኤል ነዓ ኲናተከ በተረስዮ፤ለገቢር ከመ ቀዳሚ ለአርዌ አመፃ ደርብዮ፤እስመ ኢኃደገ እንከ ዘትካት እከዮ። የዐማርኛ ትርጕም ሚካኤል ኾይ የነፍስ ቁስለኞችን ለማዳን መድኃኒተ ፈውስን እፍ ለሚለው እስትንፋስህ ሰላም እላለሁ።ድል አድራጊው መልአክ ሆይ ያ የቀድሞው አመፀኛው አውሬ (ዲያብሎስ) የጥንት ተንኮሉን ሊተው አልቻለምና።የጦር መሣሪያህን ታጥቀህ።መጥተህ ድምጥማጡን አጥፋው።
343