ch
Feedback
የግጥም ምሽት በቴሌግራም

የግጥም ምሽት በቴሌግራም

前往频道在 Telegram

ይህ ቻናል ከተለያዩ መጽሐፍት የተቀነጨቡ ግጥሞች የሚቀርቡበት እንዲሁም ወርሃዊ የግጥም ውድድሮች የሚካሄዱበት ነው ግጥም ለምትወዱ ሁሉ...የራሳችሁን ሙከራም የምታቀርቡበት ነው ለማንኛውም አስታየት @Nirvana134 እንዲሁም @simba23 ላይ አለን ፧ @yegetem32

显示更多
5 931
订阅者
无数据24 小时
-87 天
-4030 天
帖子存档
°°°° ስውር ቁጣ © ሲራክ ወንድሙ . ዋ!....ሲባል በድራር - ዋ!... ሲባል በዜማ ፥ ዋ!... ሲባል ዋ!... ስትይ - ዋይታሽን ሳልሰማ፥ ፍቅርሽ ሞቷል ብለው - በእምባሽ መንኜ ፥ ሰማዩ ላይ ታየው - ደመናውን ሆኜ ። @siraaq ............... @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

የሰው ዶሮ """"""""""""" "እህ" ብለው ያወሯት ጊዜ ቆጥራ ቆጥራ "ዷ" ብላ ገደለች፤ "ፐ" ብለው ያወሯት ውበቷ ደብዝዞ ሰው አላስደመመች! "ቂቂቂ..." ያሉባት እንባን አስረገፈች ሳቅን አኮስምና፤ "እዬዬ" ይሉባት አበርትታ አቆመች ሰውን አጠንክራ! እኔ ይሄን አይቼ የቃልን ንግስና፤ ቃል አይወጣም ከአፌ እኔም ፈራሁና! እኔም በኔው ዳና፥ በህይወት ጎዳና፥ ነገር ሆድ ቢብሰኝ ቃልን ከአንደበቴ ከምላሴ አለቅም፤ የሰው ዶሮ መጥቷል እንደ ብትን ጥሬ ካ'ፍ ካ'ፍ የሚለቅም! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

°°°°እማሆይ ፍልስፍና ©ሲራክ ከዳተኛው ልቤ - መካድ የለመደ 'እግዜር የለም' አለ አንቱን በወደደ --------//////_________ @yegetem32 @yegetem32

°°°ምኞት ደመና ነው! © ሲራክ የትነት ወዝ ገላ - የሰማዩ ግርግም ፥ ምኞት ደመና ነው - የጤዛ ጥርቅም። @yegetem32 @yegetem32

#ልፋ_ሲለኝ ____ ____ ያንቺን ሀሳብ ደ'ፍቼ የኔን ሀሳብ ተ'ግቼ፤ለብቻዬ ስቀር ላግኝሽ ጥራለው በካቻምናው ልቤ፤በኮሶ ሳላሽር ።።።።።።።።።።።።።።።፡።። ደረቴን ነፍቼ በሄድኩበት ሁሉ፤ስላንቺ ሳወጋ ልቧን ከኔ ውጪ፤በጦሩ ሚ'ወጋ "የለም" ይላል ያጣሽ ልቤ፤ላይፈይድ'ለት ነገር ቸልሶ እንደ ማጥፋት፤ከረመጡ 'ያደር ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ✍ሳሙኤል አለሙ @yegetem32 @yegetem32

መተናነስ """"""""""" ጊዜ ሲጥል ክፉ ከሁሉ ዝቅ ዝቅ ከአፈሩ አላውሶ፤ ቀን ሲጎድል ክፉ የእፍረትን ካባ እሬት አስቅምሶ፤ ዘመን ሲዋጅ ክፉ ቀና ቀና አያደርግ ዓይንን አሰብሮ ከአንገት አስጎንብሶ፤ አስቀምጦ ይገኛል እንኳን ከአዳም ልጅ ከግዑዝ ፍጥረቱ ቁልቁል አሳንሶ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

#አንድ_ቦታ ____ ____ ያንተ ያላት የትም አትሄድም አለች አለች ይላሉ አንድ ቦታ ከፍቶኝ ስውል ጊዜ ለምን አትመጣም መቀመጧን ትታ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ደፍረሽ ባትመጪም በሰመመን አለም ይራብ ይጥማልኝ እንጂ ወዳንቺ መጣለው እግሬ እስኪ ቀጥን አንድ ያደረገንን ወንዝ ፈልጋለው ስፈልግ ስፈልግ... ከእልፍ መንገዶች ባንዱ ሲመታኝ እንቅፋት ወንዙን ሳያገኙ ደርሶ መልስ መንቃት ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ብቻ ግን... ንገሯት ንገሯት መሽኮርመሙ ይቅር አንድ ቦታ ውላ በባይተዋር ከ'ምታድር እኔን ከሷ የከተበውን ብዕር ስታደርገው ፈራ ተባ በስርዝ ድልዝ ውስጥ ሌላዋ እንዳትገባ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ✍ሳሙኤል አለሙ Join us👇👇 @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

የቅርብ ሩቅ """""""""""""' ፈጣሪን ፍለጋ ስንል ቆላ ደጋ ከደብሮች ደብር አሰሳ ስንዳክር ሆኖልን ቅንነት የዋህነት ፍቅር እሩቅ የመሰለን ተቀምጦ ተገኘ ከልቦናችን ስር! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

# ኤፍሬም_ስዩም እንደፃፈው # ኑ_ግድግዳ_እናፍርስ_2008 # የማርያም_ንግስ_እለት ። . አዳፋ ነጠላ በቀጠነ ገላ ፥ ነፋስ የሚጥለው የነተበ ጫማ. ጥቁር ያዘን ቀሚስ ፥ ኑሮ ያጨቀየው ለብሳ የተገኘች ......... ከቤተክርስቲያን አፀድ ፥ ቆማ ከዋርካ ስር አንዲት ምስኪን ባልቴት .....ትለማመን ነበር , አደራሽን ማርያም አደራሽን ማርያም እበላው የለኝ መሶቤ ተራቁቷል እለብሰው የለኝም ጀርባዬ በርዶታል። , ወድቃ እየተነሳች እምባ እያፈሰሰች ተስፋዋ ማርያምን ትለማመን ነበር ከቤተክርስቲያን ጓሮ ቆማ ከዋርካ ስር። , የደብሩ አለቃ ካባ ላንቃ ለብሶ ምጣህቱን ደርቦ ልክ የሌለው ቦርጩ ወደፊት ተስቦ የንግሱን ምዕመን ወደፊቱ ስቦ ጮክ ብሎ ያወራል ጮክ ብሎ ያስተምራል። , 1 የመቅደሱ ቀለም ሊታደስ ይገባል 2 የካህናት ደመወዝ ሊጨመር ግድ ይላል 3 ደጀ ሠላም ወንበር እጅጉን ያንሰናል ...... . እናም....... በዚህ ታላቅ ደብር ይህ ችግር ስላለ ለማርያም የሚሆን እጃቹ የት - አለ? እያለ።..... ህዝቡን ያስተምራል ህዝቡን ይደልላል።...... ለንግሱ የመጡ..... ባለ ብዙ ብሮች ብዙ ባለጠጎች.... ጥለት የለበሱ ፥ በሽቶ የራሱ ቆመው የነበሩ....እፊት ከመቅደሱ ቀለም እንዲቀባ እንዲታደስ ደብሩ ለደጀ ሠላሙ ደግሞም ለወንበሩ በሺ .....የሚቆጠሩ ብሮች ወረዋሩ.... . የደብሩ አለቃ ግንባር በጣም ውዛ የሚወረወረው ብሩም በጣም በዛ። . የዛች የምስኪን ነፍስ ያች ታላቅ መቅደስ ቆማ ከዋርካ ስር ተስፋዋ ማርያምን ትለማመን ነበር:: , ኣደራሽን ማርያም አደራሽን ማርያም እበላው የለኝም መሶቤ ተራቁቷል እጠጣው የለኝም ማድጋዬ ጎድሏል እለብሰው የለኝም ጀርባዬ በርዶታል አንቺ ነሽ ተስፋዬ የኔስ ተስፋ ሞቷል ወድቃ እየተነሳች እምባ እያፈሰሰች። , , ግና ግን ለዛሬ ፥ ለክብርሽ እንዲሆን ተቀበይ ስጦታ ውሰጂ አምሃዬን የሟች ባሌን ማስታወሻ የኣንገት ሃብሌን:: @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

ድክመቴ """"""""""" ከብርታቴ ሸርተት፥ ከአስተሳሰብ ወረድ፥ ከክብረቴ ቅልል፥ እንዴ ቂል እንደ ጅል፥ ብሆንብሽ እቴ፤ ሰርክ አንቺ ነሽ ክፉ ፍቅርሽ ነው ሽንቁሬ ፥አንቺው ነሽ ድክመቴ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yehager_tibeb @yehager_tibeb

መዝገብ ""''''''''''''''''' እያት መዝገብህን በና አመድ ስትሆን ሲለቁባት እሳት አይምሮህን ገዝታው ለሷ ስትሯሯጥ ኖረህ ስትሳሳት ተመልከታት አሁን ስትቋጭ ለጥፋት እያት መዝገብህን ያንተ ህይወት ትርጉም የምነትህ ማህተብ፤ ስትዋደቅላት ጭካኔህን አይቶ ሰይጣኑ ሲያማትብ! ሲደነቅ ሲገረም በአያሌ ተግባርህ እምነትህን ትተህ አሳት ስታላምድ፤ እያት መዝገብህን ኃጥያትህን ፅፋ ስትሆን ዶግ አመድ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yehager_tibeb @yehager_tibeb

"ጥጋብ እና ሚዛን" እዛ ማዶ ጋራ፣ ምን ይንኮሻኮሻል፣ ፍየል ተደብቆ፣ ያንን ቦርጩን ያሻል፣ እዚህ ማዶ ዋሻ፣ ዝምታው በርትቷል፣ በጉ ተደብቆ፣ ምራቁን ይውጣል፣ የሚለውን ቀመር፣ የበጉን ረሀብ፣ የፍየሉን ሲሳይ፣ ይሄኛው ልዩነት፣ ለምን መጣ ብለን፣ መነሻውን ስናይ፣ ፍየል ማለት ተግባር፣ ጎርሶ አጣጥሞ፣ ጠግቦ የሚያገሳ፣ በግ ማለት አባባል፣ ለህሊናው ብሎ፣ ሆዱን የሚረሳ፣ የሚል ተረት ይዘን፣ ለከሰረ ውጤት፣ ነፍስን ከስጋ ጋር፣ ከምናወዳድር፣ እስኪ ምን አለበት፣ ህሊናም ቅን ሆኖ፣ ሆድም ጠግቦ ቢያድር፣ ብለን ስንጠይቅ፣ የሚሰራው ጠፍቶ፣ የተፈጥሮን ሒሳብ፣ በግ በደግነቱ፣ ለህሊናው ብሎ፣ ሆዱን እየረሳ፣ ምግብ ትቶ ሲራብ፣ ቆጡን እያሳዩ፣ ፍየሎች ወሰዱት፣ የብብቱን ጥጋብ፡፡ መርዕድ ተስፋዬ 03/06/2008ዓ.ም @yehager_tibeb @yehager_tibeb Join👆👆👆👆

ሎዛ """""" ሎዛ ሳትሆን እንደዋዛ፤ ኳሶቹን ጠልዛ፤ ከመረቡ ግርጌ፥ ከመረቡ ራስጌ፥ ስንቱን አገባችው የሰው አፍ አሲዛ! ሎዛ የሀዋሳ ንግስት የታደለች ለዛ፥ ብርታት እምነት ወኔ በአንድ ላይ ደብልቃ ፥በአንድ ላይ ጠምዛ፤ ወግ ማረጓን አየች እንደ ወንድ በርትታ ሴትነቷን ይዛ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

የትል ትዕግስት """""""""""""'""'''''' እኔ ደቂቅ ፍጡር በደረት ተሳቢ አካሄዴ ሁሉ የተንቀረፈፈ፤ ቅዱስ ያሬድ ብልጡ ውድቀቴን በሙሉ በአንክሮ አይቶ ተምሮ አተረፈ፤ በትንሽነቴ ንቆኝ አላለፈ! በዚች እሽክርክሮሽ ተመልከት ያሬድን ከትል አስተሳሰብ ትዕግስትን ይወርሳል፤ በውጤቱ ማምሻ በጥዑመ ዜማ ፈጣሪ ይወደሳል! ተመልከታት ትሏን የትዕግስቷ ልኬት በታሪክ ይወሳል፤ ቅዱስ ያሬድ ሲባል የቅጠል ትል ታሪክ መች በዋዛ ይረሳል፤ ጌታ አስተምሮቱ በትልም ይገዝፋል! ተመልከት እራስክን ተስፋ ቤትህ ወድቆ ትዕግስት በማጣትህ እምነትህ ይፈርሳል፤ በውድቀትህ ማግስት ነክሽ ነካ እያለ ሰይጣን ይደግሳል! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @Run_Viva_Run @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32

ሥሚማ """""""""" ወረት ነው አልልም ሁሉን አይቻለሁ ደጉንም ክፉውንም አስተናግጃለሁ ድንገት እንዲህ ሲሆን ስሚኝ ግራ ገባኝ ኩራት ክብሬን ገፎ እሆነው ሲያሳጣኝ ሽምድምድ አድርጎ ብርታቴን ሲነሳኝ ልቤ መረታቱን መንፈሴ ሲነግረኝ በወጣትነቴ ደግሞ ሊፈትነኝ ልንገርሽ ስሚማ አንቺን አስከጀለኝ ✍ በቃሉ @Deviee2 @yegetem32 @yegetem32

#የአምስት_ሚሊዮን_እራት_ቻሌንጅ ።።። ህልሜ አለሜ ከቤቴ ስወጣ እራቱን አልሜ፣ ከደጃፍ ላይ ቆመሽ ማን ነህ አትበይኝ ሚሊዮን ነው ስሜ፣😂 ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ለእራቱ እየተዘጋጀን ነው።ለዛ ከዛሬ ጀምሮ ስሜ ማን ነው? .."ሳሙኤል"እንዳትሉ😂 @Samuelalemu5 @yegetem32 @yegetem32

ሂዱ """"" ረሀቤን ይዤ፥ ችግር ተጠርዤ፥ ድህነቴን ይዤ፥ እንቅልፌን ስተኛ፤ ከብቶች እያገደ፥ በአፉ እያሽሟጠጠ፥ ስቆ አልፎኝ ነበር፥ ጎረምሳው እረኛ፤ ሊረዳኝ ሳይከጅል ፥እንደ ችግርተኛ! ሆዴን ማስታገሻ፥ አንድ ዳቦ ስሻ፥ ገንዘብ ይሉት ጠፍቶኝ፥ ስኖር እንዳመሌ፤ ከቁብም ሳይቆጥረኝ ከቡና ተክል ላይ ቡና ይለቅም ነበር፥ አንድ ሽማግሌ! ለአንድ እንጀራ ጠፍቶኝ እርሀቤን ታቅፌ፥ ቁጭ ስል ከቤቴ፤ ችላ ብላኝ ነበር እንጀራም የሌለው ፥ሰፌድ ሰፊ እሜቴ! ሰው ከሰው ሲጣላ፥ ከአንዱ አንዱ ሲባላ! ሰውም በችግሩ፥ ደሀውም ሀብታሙም እኩል ሲማረሩ፤ ምንተዳዬ ብለው ከአንገት ቀና አላሉ፤ አራሽ ከመሬቱ ፥ዶክተር ምርምሩን! ታድያ ምን አግብቶኝ ስትሰናበቱ "ለምን? እንዴት?" ብዬ እኔ እምቆረቆር፤ ስታረዝ ስጠማ ያኔ በችግሬ የት ሄዳቹ ነበር? ታድያ ምን አግብቶኝ እንዳትሄዱ ብዬ 'ምገባው ከምልዱ፤ እንዳለው ኖራለሁ እኔም ከችግሬ በሉ እናንተም ሂዱ! ቻው.... አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) @yegetem32 @yegetem32 @yegetem32