ch
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

前往频道在 Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

显示更多
1 810
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
📖የእግዚአብሔር ቃል📖 ... ክፍል አራት... ከመጋቢዎቻችን፤ ከነቢያቶቻችን ወይም ከአስተማሪዎቻችን በላይ የምንመለከተው እና የምንከተለው የሐይማኖታችን ሐዋሪያ እና ሊቀ-ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ: በዛሬው ጽሑፌ እርሱ ቅዱሳት መጽሐፍትን እንዴት እንደሚመለከት እናያለን። እኛም ልክ እንደ እርሱ ልንመለከታቸው ይገባናል... ጌታችን ኢየሱስ የቅዱሳት መጽሐፍትን ስልጣን እና ሃይል የገለጸበትን ሁለት የንባብ ክፍል እንመለከታለን: የመጀመሪያው :- “መጽሐፉ ሊሻር አይቻልምና እነዚያን የእግዚአብሔር ቃል የመጣላቸውን አማልክት ካላቸው፥” — ዮሐንስ 10፥35 ከላይ የምናነበው የጌታችንን ንግግር ነዉ: አይሁድ ለጠየቁት ጥያቄ መልስ ስሰጣቸው "መጽሐፍ ሊሻር አይችልም" /the scriptures can't be broken/ በማለት ስለ ቅዱሳት መጽሐፍት ስልጣን ገልጧል። ከላይ ባለው የጌታ ቃል ውስጥ "መጽሐፍ" ተብሎ በአማርኛው ቅጅ የተተረጎመው ቃል በግሪክ γραφή ---("graphe") የሚል ድምጽ ያለው ቃል ነዉ: ይህም የተጻፈውን የእግዚአብሔር ቃል ለመግለጽ ጥቅም ላይ የዋለ ነዉ። ሁለተኛው የንባብ ክፍል ---“እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ፥ ከሕግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍም፥ ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ።” — ማቴዎስ 5፥18 ከላይ ያነበብነው ቃል ሌላው ኢየሱስ የቅዱሳትን መጽሐፍት ስልጣን የገለጸበት ነዉ። በዚህ ንባብ ውስጥ ሁለት ነገሮች ተጠቅሰዋል: የውጣ እና ነጥብ። በግሪኩ ጽሑፍ የውጣ "iota" ፤ ነጥብ ደግሞ "keraia" ናቸው። የመጀመሪያው ቃል "የውጣ" በዕብራይስጥ ፊደላት ውስጥ የትንሿ ፊደል ስም ነዉ፤ ሁለተኛው ቃል "ነጥብ" የተባለው ደግሞ በዕብራይስጥ ጽሑፎች ውስጥ በፊደል ራስ ላይ የሚደረግ ትንሽ ቀንድ የሚመስል ነጥብ ነዉ። አስተውሉ እነዚህ ሁለቱ በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ በጣም ትንንሾቹ ነገሮች ናቸው። ጌታ ግን ከእነዚህ ከትንንሾቹ አንድቱ እንኳ እንደማትሻር በመናገር የቅዱሳት መጽሐፍትን ስልጣን ገልጧል። (.........መጽሐፍ ሊሻር አይችልምና......) -victor 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

📖የእግዚአብሔር ቃል📖 .... ክፍል ሦስት... በክፍል ሁለት ጽሑፌ የቅዱሳት መጽሐፍት ጻሐፊ እና የጽሑፉን ስልጣን ተመልክተናል። ቅዱሳት መጽሐፍት ሁሉ የእግዚአብሔር እስትንፋስ ያለባቸው እንደሆኑ አይተናል። እያንዳንዱ ጽሑፍ የባለቤቱ ስልጣን ያለው በመሆኑ ቅዱሳት መጽሐፍት ስልጣናቸውን በቀጥታ ከእግዚአብሔር አግኝተዋል። ዛሬ ደግሞ የቅዱሳት መጽሐፍት ትርጉም/ፍቺ(interpretation) በተመለከተ በጥቂቱ እናያለን። ማነው ለቅዱሳት መጽሐፍት ትርጉም የሚሰጠው? መጋቢ ነውን? ወይም የስነ-መለኮት ምሁር? ወይስ ክርስቲያን? እነዚህ ሁሉ አይደሉም። 2ኛ ጴጥሮስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁰ "ይህን በመጀመሪያ እወቁ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም፤.." የቅዱሳት መጽሐፍት ባለቤት መንፈስ ቅዱስ ነዉ ስለዚህ ትክክለኛውን ፍቺ መስጠት የሚችለው እርሱ ነዉ። ሰዎች የራሳቸውን ፍቺ የሚሰጡ ከሆነ ሙሉ ምክሩን ማግኘት የማይቻል ነዉ: አብዛኛውን ጊዜ ደግሞ ወደ ስሁት ድምዳሜ የሚያደርስ ነዉ። “ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ።” — 2ኛ ጴጥሮስ 1፥21 መንፈስ ቅዱስ ባለቤት ነዉ ስለዚህ ትርጉም የመስጠቱን ተግባር ለእርሱ እንስጠው። እርሱ የሚሰጠን ፍቺ ያበራል: በብርሃኑም እንሄዳለን! አሜን። ❤ለቅዱሳት መጽሐፍት ትርጉም መስጠት የተገባው መንፈስ ቅዱስ ብቻ ነዉ❤ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

𝙥𝙧𝙖𝙮𝙚𝙧 𝙞𝙨 𝙤𝙪𝙧 𝙘𝙪𝙡𝙩𝙪𝙧𝙚 𝙖𝙣𝙙 𝙢𝙤𝙪𝙣𝙩𝙖𝙞𝙣 𝙞𝙨 𝙩𝙝𝙚 𝙗𝙚𝙨𝙩 𝙥𝙡𝙖𝙘𝙚.... #𝙝𝙤𝙬 𝙞 𝙡𝙤𝙫𝙚 𝙩𝙝�
𝙥𝙧𝙖𝙮𝙚𝙧 𝙞𝙨 𝙤𝙪𝙧 𝙘𝙪𝙡𝙩𝙪𝙧𝙚 𝙖𝙣𝙙 𝙢𝙤𝙪𝙣𝙩𝙖𝙞𝙣 𝙞𝙨 𝙩𝙝𝙚 𝙗𝙚𝙨𝙩 𝙥𝙡𝙖𝙘𝙚.... #𝙝𝙤𝙬 𝙞 𝙡𝙤𝙫𝙚 𝙩𝙝𝙞𝙨 𝙥𝙡𝙖𝙘𝙚𝙨...!

የእግዚአብሔር ልጆች ፈጽሞ እየተለወጥን በትውልዳችን የለውጥ ምክንያቶች መሆን እንድንችል የእግዚአብሔር መንፈስ እና የእግዚአብሔር ቃል የግድ ያስፈልጉናል። በመንፈስ እና በቃል የተሞላን አገልጋዮች ልንሆን ይገባል: ፀጋው ይብዛልን!

☝️ እነዚህን ጽሑፎች አንብቧቸው እምነታችንን ለሌሎች መግለጽ ያስችሉናል ብዬ አምናለሁ በተለይ የመጽሐፍ ቅዱስን ትክክለኝነት በተመለከተ ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስ ይሆናል

# ... መጽሐፍ ቅዱስ የአንድ አመት ስራ አይደለም: የተወሰኑ ሰዎችም በራሳቸው ተነሳስተው የፈጠሩት የታሪክ መጽሐፍም አይደለም: ታሪክ እንደሚያስረዳን በመጀመሪያው የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ እና በመጨረሻው የአዲስ ኪዳን መጽሐፍ መካከል የአንድ ሺህ አምስት መቶ ዓመት የዘመን ልዩነት አለ። የመጀመሪያው መጽሐፍ የሆነው የዘፍጥረት መጽሐፍ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊት 1400 ዓመት ቀድሞ ነበር በሙሴ በኩል የተጻፈው: የመጨረሻው የአዲስ ኪዳን መጽሐፍ ደግሞ ከ 96-98 ዓመተ ምህረት እንደተጻፈ ይታሰባል። ከዚህ የምንረዳው መጽሐፍ ቅዱስን በመጻፍ ሕደት ውስጥ ሰፊ የዘመን ልዩነት እንዳለ ነዉ። ሌላው መጽሐፍ ቅዱስን ለመጻፍ እግዚአብሔር የተጠቀማቸው ሰዎች ከ 40 በላይ ናቸው: እነዚህ ሰዎች ሁሉ የአንድ መንደር ሰዎች አይደሉም: ከተወለዱበት ቤተሰብ እና ምድረ-አቀማመጥ(geography) አንስቶ የአስተዳደግ፤ የባህል፤ የእድሜ፤ በማህበረሰቡ ውስጥ የነበራቸው ቦታ ሁሉ የተለያየ ነበር: አንዳንዶቹ ነገስታት ቤት ያደጉ ሌሎቹ ደግሞ እረኞች፤ አንዳንዶቹ ደግሞ ነገስታት ሌሎቹ ደግሞ አሳ አጥማጆች፤ አንዳንዶቹ በዚህ ዓለም ሚዛን የተማሩ ሌሎቹ ደግሞ ያልተማሩ ተብለው የሚታሰቡ፤ ሐዋሪያው ጳውሎስን ከተመለከትነው ደግሞ በሐይማኖቱ(Judaism) ፍቅር የሰከሩ እና ከእርሱ እምነት ጋር አይስማማም ብሎ የሚያስበውን አድሱን ትምህርት አሳዳጅ... ወዘተ...ነበሩ። በዘመን እና በሰዎቹ መካከል እንደዚህ የሰፉ ልዩነቶች ቢኖሩም ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ አንድም ልዩነት ወይም ግጭት የሌላው መጽሐፍ ነዉ፤ ይህም መጽሐፍ ቅዱስ በፍጹም የሰው ስራ እንዳልሆነ እና ሙሉ በሙሉ በእግዚአብሔር የሃሳብ ባለቤትነት እና በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የተጻፈ መሆኑን በግልጽ የሚያሳይ ነዉ። ይህ በጣም የሚያስገርም ነዉ: ምክንያቱም እንኳን አይደለም ከ 40 በላይ የተለያየ ሰው ተሳትፎበት ይቅርና አንድ ሰው ብቻውን የጻፈው መጽሐፍ ውስጥ እርስ በራሱ የሚጋጭ አመለካከቶች ማየት የተለመደ ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ ግን ፈጽሞ ከራሱ ጋር የማይጋጭ እና ሙሉ በሙሉ የተስማማ ነዉ። ሌላው የመጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር እስትንፋስ( inspiration) ለመጻፉ መረጋገጫ ተብሎ ሊወሰድ የሚችለው: በውስጡ የያዛቸው ትንቢቶች ትክክለኝነት እና ተፈጻሚነት ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ ከግለሰቦች ጀምሮ ስለ ሕዝቦች፤ ስለ መንግስታት፤ ስለ ዘመናት፤ ስለ ምድር... ወዘተ እጅግ በጣም በሚያስገርም መልኩ የተፈጸሙ እና በመፈጸም ላይ ያሉ ትንቢቶች በውስጡ አሉት። ስለ ሁሉም ለማውራት ጊዜ ያጥረናል: ነገር ግን በአጭሩ በብሉይ ኪዳን ይመጣል ተብሎ ትንቢት የተነገረለት መሲሕ የመጽሐፍ ቅዱስ ዋና ትኩረት ነዉ: ሙሴ በሕጉ ዳዊት በመዝሙሩ እና ነቢያትም በትንቢታቸው የተናገሩለት ክርስቶስ እርሱም የሕያው የእግዚአብሔር ልጆ ከሴት በድንግልና ተጸንሶ በድንግልና የመወለዱ የትንቢት ፍጻሜ አንዱ ጉልህ ማሳያ ነዉ📖all scriptures are God breathed📖 amen። -Victor 👇👇👇👇ለመቀላቀል👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔርን ቃል ስልጣን በሕይወታችሁ ይሰራል! የታመማችሁ በኢየሱስ ስም በመገረፉ ቁስል ተፈውሳችኋል! በፍጹም ጤንነት ተመላለሱ! የተጨነቃችሁ በኢየሱስ ስም በነጻነት ልትኖሩ ክርስቶስ ነጻ አውጥቷችኋል! በፍጹም ነጻነት ኑሩ! ስኬት የሌላችሁ በኢየሱስ ስም የእግዚአብሔር በረከት ባለጠጋ ታድርጋችሁ! በፍጹም ብልጽግና ኑሩ!

📖የእግዚአብሔር ቃል📖። ... ክፍል ሁለት... ....በክፍል አንድ የእግዚአብሔር ቃል በጥቅሉ ለሁለቱ ግላዊ ቃል(personal word) እና ለተጻፈው ቃል (written word) ጥቅም ላይ እንደዋለ እና ሁለቱ እርስ በራሳቸው ፈጽሞ የተስማሙ እና የሚደጋገፉ እንደሆኑ ተመልክታናል። ዛሬ ደግሞ የተጻፈው የእግዚአብሔር ቃል ላይ ትኩረታችንን በማድረግ: ጻሐፊውን እና የጽሑፉን ስልጣን እናያለን። የቅዱሳት መጽሐፍት ባላቤት /ሃሳብ አመንጪ/ ማን ነዉ? መንፈስ ቅዱስ ነዉ። “...የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።” — 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥16-17 የግሪኩ ጽሑፍ ከላይ ያለውን ትርጉም በቀጥታ የሚለው "Every scripture is God-Breathed" ነዉ / "ቅዱሳት መጽሐፍት ሁሉ የእግዚአብሔር እስትንፋስ አላቸው" ማለት ነዉ። ከሁሉም የቅዱሳት መጽሐፍት መጻፍ በስተጀርባ የለው የሐሳብ(የቃሉ) ባለቤት እግዚአብሔር ነዉ ማለት ነዉ። “ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ።” — 2ኛ ጴጥሮስ 1፥21 ትንቢት የሚለው የብሉይ ኪዳን መጽሐፍትን ለመግለጽ ጥቅም ላይ የዋለ ቃል ነዉ (ሐዋሪያት 13:15፤ 28: 23) ስለዚህ ከላይ ያለው ቃል የሚናገረው ቅዱሳት መጽሐፍት በፍጹም በሰው ፈቃድ የመጡ እንዳልሆኑ ነዉ። ነገር ግን "ቅዱሳን ሰዎች በእግዚአብሔር ተልከው እና በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው እንደተናገሩት(+እንደጻፉት) የሚያስረዳ ነዉ። ስለዚህ ቅዱሳት መጽሐፍት ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ውጤቶች ናቸው: ይህ ለአዲስ ኪዳን መጽሐፍትም የሚሰራ ነዉ። የመጽሐፍ ቅዱስ ስልጣን ስልጣን የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል "Authority" ነዉ: ይህም "Author" "ደራሲ/ ጸሐፊ" ከሚል ቃል የወጣ ነዉ። ከዚህ መረዳት የምንችለው ነገር አለ: የጽሑፍ ስልጣን በቀጥታ ከጸሓፊው የሚገኝ እና የጽሑፉ ስልጣን እንደ ጸሓፊው መሆኑን ነዉ። ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል የእግዚአብሔር ስልጣን አለው። የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ እግዚአብሔርን ይሰማል! የእግዚአብሔርን ቃል የማይሰማ እግዚአብሔርን አልሰማም: የእግዚአብሔርን ቃል የሚወድ እግዚአብሔርን ይወዳል: የእግዚአብሔርን ቃል የማይወድ እግዘብሔርንም አይወድም። ቅዱሳት መጽሐፍት ሁሉ የእግዚአብሔር ናቸው። የእግዚአብሔር እስትንፋስ አላቸው። ❤All scriptures are God inspired❤ ተቀላቀሉን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ዛሬ ቀኑን ሁሉ የእግዚአብሔር ቃል ትዝታችን ይሁን።አሜን🙏አሜን!

📖የእግዚአብሔር ቃል📖። .... ክፍል አንድ.... ....የእግዚአብሔር ቃል የሚለው ሃረግ በጥቅሉ ለሁለት ነገር ይውላል። የመጀመሪያው ኢየሱስ ክርስቶስ ነዉ። ሁለተኛው ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ነዉ። ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር አካላዊ ቃል( personal word) ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ የተጻፈ(written) የእግዚአብሔር ቃል ነዉ። ሁለቱም አካላዊው የእግዚአብሔር ቃል እና የተጻፈ የእግዚአብሔር ቃል ሙሉ በሙሉ የተስማሙ እና የሚደጋጋፉ ናቸዉ። አካላዊው ቃል የተጻፈውን ቃል ፈጽሞታል። ስለዚህ ከአካላዊው የእግዚአብሔር ቃል ጋር በትክክል ለመግባባት ከተጻፈው የእግዚአብሔር ቃል ጋር በትክክል መግባባት ያስፈልጋል። የተጻፈውን ቃል ከምንወደው በላይም አካላዊውን ቃል ልንወድ አንችልም: ኢየሱስን እወደዋለሁ ግን መጽሐፍ ቅዱስን አልወድም ከልን ኢየሱስንም አንወደውም ማለት ነዉ። ለኢየሱስ ክርስቶስ ጊዜ አለኝ የምንል ከሆነ እና ለመጽሐፍ ቅዱስ ጊዜ ከሌላን ለኢየሱስም ጊዜ የለንም ማለት ነዉ። ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ እራሱ እንደዚህ በማለት ተናግሯል: “ኢየሱስም መለሰ አለውም፦ የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤...” — ዮሐንስ 14፥23 ስለዚህ በግልጽ እንደምናየው ኢየሱስን የምንወደው ከሆነ ቃሉን እንጠብቃለን። ቃሉን ከምንወደው በላይ ኢየሱስን ልንወደው አንችልም። ቃሉን በወደድን ቁጥር ለኢየሱስ ያለን ፍቅር ይጨምራል። ለኢየሱስ ያላችሁ ፍቅር እንዲጨምር ትፈልጋላችሁ? ቃሉን ጠብቁ! ቃሉን የበለጠ ውደዱ😍😍😍። ጉርሻ😁 👉“አቤቱ፥ ሕግህን እንደ ምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው።” — መዝሙር 119፥97 “በትእዛዝህ ደስ ይለኛል፤ ቃልህንም አልረሳም።” — መዝሙር 119፥16 ❤️❤❤ ቃሉን ከምንወደው በላይ ኢየሱስን ልንወደው አንችልም❤❤❤ 👇👇👇Join the chariot👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

The area of imbalance is the get way to the devil. Learn to keep the balance always.

ለመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች እና አስተማሪዎች በሙሉ። በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናትም ሆነ ማስተማር ጊዜ ሚዛን መጠበቅ አለመቻል ስሁት ወደሆነ አስተሳሰብ ይመራል። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መንፈሳዊ እውነቶች የሚሰጠውን እውነት ለገዛ ጥቅማችን መተርጎም አግባብ አይደለም: የመቶርጎም ስራውን ለቃሉ ባለቤት ለመንፈስ ቅዱስ ብንሰጠው። ኢ-ሚዛናዊነት የሃሰተኛ ድምዳሜ ሁሉ መሰረት ነዉ። ለምሳሌ እግዚአብሔር ፍቅር መሆኑ እውነት ነዉ: ይህንን እውነት ስናስተምር ወይም ስንማር መረሳት የሌለበት ነገር እግዚአብሔር የሚያጠፋ እሳት መሆኑን ነዉ: ስለ እግዚአብሔር ምህረት ስንማር: እግዚአብሔር ፈራጅም መሆኑን መርሳት የለብንም። እግዚአብሔር ፍቅር ነዉ የሚለውን እውነት ብቻ ነዉ የምቀበለው እግዚአብሔር የሚያጠፋ እሳት ነዉ የሚለውን አልቀበልም የምንል ከሆነ ኢ-ሚዛናዊነት እያጠቃን ነዉ ማለት ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር የሚያስተምረውን ሁሉ እንደዚያው መማር እና ማስተማር እንድንችል ፀጋው ይርዳን። እግዚአብሔር ፍቅር የመሆኑ እውነት እግዚአብሔር የሚያጠፋ እሳት ከመሆኑ እውነት የሚበልጥም የሚያንስም አይደለም: እግዚአብሔር መሃሪ መሆኑ ፈራጅ ከመሆኑ የሚያንስም የሚበልጥም አይደለም። ሁሉም በጊዜው የሚገለጥ ነወ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Run to the cross....🏃‍♂️🏃‍♀️ Run to Jesus..... i will keep running unto you.... 😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ለ 120'ዎቹ የጸሎት ፕሮጀክት አካላት ሁሉ 🔥🔥ነገ ከማለዳው 12:00 -1:00 ለመመዝገብ 👉 @kbzoe 👉 @GFI777 👉 @Evangelismebyfire

30 ደቀቃ ጸሎት!!🔥🔥🔥🔥🔥🔥 የጥበብና የመገለጥ መንፈስ!!!!!!!!!!Don't miss this this is urgent! from the Spirit! 👉👉አብራችሁኝ የምትጸልዩ ከሆነ ብቻ ስሙት! ክፍላችሁ ገብታችሁ ጸልዩ ለ 30 ደቂቃ ንደዱ!🔥 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት አሁን ባለንበት ወቅት የእግዚአብሔር ልጆች ሁሉ በግላችን የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት የምንችልበት ደረጃ ላይ መድረስ ይጠበቅብናል። የእግዚአብሔር ድምፅ በየትኛውም የሕይወታችን ክልል እግዚአብሔራዊ ስኬት የምናገኝበት የመጀመርያው ቁልፍ ነዉ። የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት ስላችሁ እግዚአብሔር በመንፈሱ፤ በራዕይ፤ በሕልም በድምፅ... በሌሎችም መንገዶች አሁን ስናገር መስማት ማለት ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ በኢዩኤል መጽሐፍ ምዕራፍ ሁለት ላይ እንደዚህ ይላል:- “ከዚህም በኋላ እንዲህ ይሆናል፤ መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈስሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልምን ያልማሉ፥ ጐበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፤” — ኢዮኤል 2:28 ትንቢትም ህልምም ሆነ ራዕይ እግዚአብሔር ለሰዉ ልጅ የሚናገርባቸው መንገዶች ናቸው። ይህ ደግሞ ለተወሰኑ ሰዎች የተሰጠ ሰይሆን መንፈስ ለፈሰሰበት ስጋ ለባሽ ሁሉ የተሰጠ በረከት ነዉ። ነገር ግን በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ሁሉም ነገር የሚሰራው እውቀትን በማግኘት በመሆኑ ብዙ የእግዚአብሔር ልጆች ይህንን እየተለማመዱ አይደለም: ምክንያቱም ሁሉም ነገር የሚሰራው በእውቀት ነዉ። ስለዚህ በዚህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት ላይ በቀጣይነት እውቀት ለመስጠት እና ትምህርቱን የሚከታተሉ የአምላክ ልጆች ሁሉ የእግዚአብሔርን ድምጽ በግላቸው መስማት ወደሚችሉበት መንፈሳዊ ብስለት እንድደርሱ ለማድረግ መንፈስ ቅዱስ እንድናገር አዞኛል። በየትኛውም ጉዳይ ላይ የእግዚአብሔርን ምክር ማግኘት መቻል እንዴት መታደል ነዉ!? የእግዚአብሔር ልጆች እኛ ከእግዚአብሔር ስለተወለድን ድምጹን መስማት በውልደት ያገኘነዉ መብታችን ነዉ: ልጁን ለማነጋገር የማይወድ አባት ማነዉ?። ሁሉን የሚያውቅ አባት አለን ስለ ሁሉም ነገር ያውቃል ስለ አገልግሎት፤ ስለ ትምህርት፤ ስላለፈው ስለሚመጣው፤ ስለቤተሰብ፤ ስለቢዝነስ፤ ስለባለጠግነት ስለመንፈሳዊ ዓለም ስለፍጥራታት ሁሉ የሚያውቅ አባት አለን: ሁሉን ወደሚያውቀው አባታችን ቀርበን ስለ አስፈላጊ ነገር ሁሉ መረጃ መግኘት እንደምንችል ታውቃላችሁ??? ይህ ግን የሚሆነው ድምጹን መስማት የምንችል ከሆነ ነዉ። ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ያስተማረኝን መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሰረት ያለውን እውነት ሁሉ ለማስተማር እየተዘጋጀሁ ነዉ። ለመስማት ተዘጋጁ። እግዚአብሔርን መስማት ያሳርፋል! እግዚአብሔርን መስማት ያድናል! እግዚአብሔርን የመስማት በረከት ብዙ ነዉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መንፈስ ቅዱስ ተማኝ እና ብርቱ ረዳቴ እወድሃለሁ!😍

መንፈስ ቅዱስ በአማኝ ሕይወት! #ራዳትህ/ #ረዳትሽ ነው መነበብ ያለበት 👇👇👇👇 መንፈስ ቅዱስ በአንድ አማኝ ሕይወት እጅግ ብዙ ተግባራት አሉት: እኔ ዛሬ የምነግራችሁ ግን ስለ ረዳትነት ተግባሩ ነዉ። በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 14: 16 ላይ ኢየሱስ ወደ አብ ከተመለሰ በኋላ ስለሚልከው መንፈስ ስናገር: "ἄλλος παράκλητος" - allos parakletos በማለት ገልጾታል። ይህ የግሪክ ቃል በአማርኛው ቅጂ "#ሌላ_አጽናኝ" ተብሎ ተተርጉሟል። ነገር ግን "አጽናኝ" ከሚለው ቃል እጅግ የሰፋ ትርጉም ያለው ቃል ነዉ። የዚህ የግሪክ ቃል አንዱ ትርጉም "ረዳት" ማለት ነዉ። ዛሬ እኔ የምነግራችሁ ስለመንፈስ ቅዱስ የረዳትነት ተግባር በአማኙ ሕይወት ውስጥ ነዉ። ረዳት የሚለው ቃል በግልጽ የሚያስረዳን: መንፈስ ቅዱስ "አድራጊ" አለመሆኑን ነዉ። በያዕቆብ መልእክት ምዕራፍ 1:22 ላይ አማኝ "አድራጊ" የመሆን ሃላፊነት ተሰጥቶታል: "የቃሉ አድራጊዎች ሁኑ!" ይላል። መንፈስ ቅዱስ በፍጹም በችኮላ ወይም አማኙን በማስገደድ ከአማኙ ፈቃድ ውጪ ምንም አይሰራም! አማኙ እንድጀምር ያነሳሰዋል ወይም የ 𝑖𝑛𝑠𝑝𝑖𝑟𝑎𝑡𝑖𝑜𝑛 ምንጭ ይሆናል: አማኙ ታዞ መጀመር ይኖርበታል: በዚህ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ አማኙን መርዳት ይጀመራል: የነገሩም ቀጣይነት በአማኙ አቅም ላይ ሰይሆን በመንፈስ ቅዱስ የረዳትነት ተግባር ላይ ይደገፋል። አንድ ቃል እንመልከት ሐዋርያት ሥራ ሁለት አራት:-“በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ #መንፈስም_ይናገሩ_ዘንድ_እንደ_ሰጣቸው_በሌላ_ልሳኖች_ይናገሩ_ጀመር።” — ሐዋርያት 2:4 ይህ በጴንጤቆስጤ ቀን ሐዋርያቱ በመንፈስ ቅዱስ ከተሞሉ በኋላ ወድያው የሆነው ነዉ። በተለይ የደመቀውን ንባብ በጥንቃቄ ካያችሁት የመንፈስ ቅዱስ ድርሻ እና የአማኙ ድርሻ በግልጽ ይነበባሉ። ➤የመንፈስ ቅዱስ ድርሻ-- "መንፈስም እንድናገሩ በሰጣቸው መጠን" ከዚህ ቃል እንደምንረዳው የመንፈስ ቅዱስ ድርሻ "#እንዲናገሩ_መስጠት" (𝑖𝑛𝑠𝑝𝑖𝑟𝑎𝑡𝑖𝑜𝑛 / 𝑔𝑖𝑣𝑖𝑛𝑔 𝑢𝑡𝑡𝑒𝑟𝑎𝑛𝑐𝑒) ነዉ። ➤የአማኙ ድርሻ-- "ይናገሩ ጀመር" ከሚለው ቃል የምናየው የአማኙን ድርሻ ነዉ። ""መናገር" በነጻ ፈቃድ መናገር። 👉ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ስሰጥ አማኝ ደግሞ በልቡ ፈቃድ አንደበቱን የመክፈት እና የመናገር ሃላፊነት አለበት። ይሄ በሁሉም ላይ የሚሰራ ነዉ: ለምሳሌ መንፈስ ቅዱስ የኃጢአት ልምምድ ውስጥ ያለን አማኝ አስገድዶ እንድወጣ አያደርገውም: የመጀመሪያ ይወቅሰዋል ከዚያም መውጫ መንገዱን ያሳየዋል: በዚህ ጋዜ አማኙ በንስሃ ለመመለስ ከወሰነ እና መውጫውን መንገድ ማጠብጠብ ከጀመረ: መንፈስ ቅዱስ በረዳትነት ራሱን ይገልጣል! እና አማኙ ከዚያ የኃጢአት ልምምድ ለመውጣት በሚያደርገው መጋደል ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ተማኝ እና ብርቱ ረዳት በመሆን ይረዳዋል! መንፈስ ቅዱስ የረዳው ሰው ደግሞ ያለምንም ጥያቄ: የትኛውንም ከኃጢአት ከዓለም እና በዓለም ከለው ጋር የሚደረግን ጦርነት ያሸንፋል! መንፈስ ቅዱስ የረዳው ሰው ያለጥርጥር ያሸንፋል። አሜን! መንፈስ ቅዱስ ታማኝ እና ብርቱ ረዳት ነዉ። join ለማድረግ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መንፈስ ቅዱስ በአማኝ ሕይወት! #ራዳትህ/ #ረዳትሽ ነው። መነበብ ያለበት 👇👇👇👇 መንፈስ ቅዱስ በአንድ አማኝ ሕይወት እጅግ ብዙ ተግባራት አሉት: እኔ ዛሬ የምነግራችሁ ግን ስለ ረዳትነት ተግባሩ ነዉ። በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 14: 16 ላይ ኢየሱስ ወደ አብ ከተመለሰ በኋላ ስለሚልከው መንፈስ ስናገር: "ἄλλος παράκλητος" - allos parakletos በማለት ገልጾታል። ይህ የግሪክ ቃል በአማርኛው ቅጂ "#ሌላ_አጽናኝ" ተብሎ ተተርጉሟል። ነገር ግን "አጽናኝ" ከሚለው ቃል እጅግ የሰፋ ትርጉም ያለው ቃል ነዉ። የዚህ የግሪክ ቃል አንዱ ትርጉም "ረዳት" ማለት ነዉ። ዛሬ እኔ የምነግራችሁ ስለመንፈስ ቅዱስ የረዳትነት ተግባር በአማኙ ሕይወት ውስጥ ነዉ። ረዳት የሚለው ቃል በግልጽ የሚያስረዳን: መንፈስ ቅዱስ "አድራጊ" አለመሆኑን ነዉ። በያዕቆብ መልእክት ምዕራፍ 1:22 ላይ አማኝ "አድራጊ" የመሆን ሃላፊነት ተሰጥቶታል: "የቃሉ አድራጊዎች ሁኑ!" ይላል። መንፈስ ቅዱስ በፍጹም በችኮላ ወይም አማኙን በማስገደድ ከአማኙ ፈቃድ ውጪ ምንም አይሰራም! አማኙ እንድጀምር ያነሳሰዋል ወይም የ 𝑖𝑛𝑠𝑝𝑖𝑟𝑎𝑡𝑖𝑜𝑛 ምንጭ ይሆናል: አማኙ ታዞ መጀመር ይኖርበታል: በዚህ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ አማኙን መርዳት ይጀመራል: የነገሩም ቀጣይነት በአማኙ አቅም ላይ ሰይሆን በመንፈስ ቅዱስ የረዳትነት ተግባር ላይ ይደገፋል። አንድ ቃል እንመልከት ሐዋርያት ሥራ ሁለት አራት:-“በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ #መንፈስም_ይናገሩ_ዘንድ_እንደ_ሰጣቸው_በሌላ_ልሳኖች_ይናገሩ_ጀመር።” — ሐዋርያት 2:4 ይህ በጴንጤቆስጤ ቀን ሐዋርያቱ በመንፈስ ቅዱስ ከተሞሉ በኋላ ወድያው የሆነው ነዉ። በተለይ የደመቀውን ንባብ በጥንቃቄ ካያችሁት የመንፈስ ቅዱስ ድርሻ እና የአማኙ ድርሻ በግልጽ ይነበባሉ። ➤የመንፈስ ቅዱስ ድርሻ-- "መንፈስም እንድናገሩ በሰጣቸው መጠን" ከዚህ ቃል እንደምንረዳው የመንፈስ ቅዱስ ድርሻ "#እንዲናገሩ_መስጠት" (𝑖𝑛𝑠𝑝𝑖𝑟𝑎𝑡𝑖𝑜𝑛 / 𝑔𝑖𝑣𝑖𝑛𝑔 𝑢𝑡𝑡𝑒𝑟𝑎𝑛𝑐𝑒) ነዉ። ➤የአማኙ ድርሻ-- "ይናገሩ ጀመር" ከሚለው ቃል የምናየው የአማኙን ድርሻ ነዉ። ""መናገር" በነጻ ፈቃድ መናገር። 👉ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ስሰጥ አማኝ ደግሞ በልቡ ፈቃድ አንደበቱን የመክፈት እና የመናገር ሃላፊነት አለበት። ይሄ በሁሉም ላይ የሚሰራ ነዉ: ለምሳሌ መንፈስ ቅዱስ የኃጢአት ልምምድ ውስጥ ያለን አማኝ አስገድዶ እንድወጣ አያደርገውም: የመጀመሪያ ይወቅሰዋል ከዚያም መውጫ መንገዱን ያሳየዋል: በዚህ ጋዜ አማኙ በንስሃ ለመመለስ ከወሰነ እና መውጫውን መንገድ ማጠብጠብ ከጀመረ: መንፈስ ቅዱስ በረዳትነት ራሱን ይገልጣል! እና አማኙ ከዚያ የኃጢአት ልምምድ ለመውጣት በሚያደርገው መጋደል ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ተማኝ እና ብርቱ ረዳት በመሆን ይረዳዋል! መንፈስ ቅዱስ የረዳው ሰው ደግሞ ያለምንም ጥያቄ: የትኛውንም ከኃጢአት ከዓለም እና በዓለም ከለው ጋር የሚደረግን ጦርነት ያሸንፋል! መንፈስ ቅዱስ የረዳው ሰው ያለጥርጥር ያሸንፋል። አሜን! መንፈስ ቅዱስ ታማኝ እና ብርቱ ረዳት ነዉ። join ለማድረግ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በዓለም ታሪክ ውስጥ በሃገር ደረጃ ብሎም በዓለሙ ሁሉ ጉልህ ተጽእኖ የፈጠሩ የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴዎች(ሪቫይቫሎች) ከመሆናቸውም በፊት በቁጥር የበዙ ባይሆኑም የተወሰኑ ቅዱሳን የላቀ የመንፈስ ቅዱስን እንቅስቃሴ በመፈለግ በጸሎት ተግተዋል: ይህም በንስሃ ወደ እግዚአብሔር የመመለስ የጸሎት እንቅስቃሴ: እያደገ ግልጽ የሆነ መንፈሳዊ ተጽእኖ ፈጥሯል። በዚህም ህደት እጅግ ብዙ ቁጥር ያለው የቤተክርስቲያን ክፍል ከተኛበት ነቅቷል: ለአገልግሎትም የበቃ ሆኗል: ከዚህም በዘለለ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች የጌታችንን ወንጌል በቃል ብቻ ሰይሆን በስራም በመመልከት በመንፈስ ቅዱስ ወቀሰ ወደ እግዚአብሔር መንግስት ተጨምረዋል። የእነዚያ እንቅስቃሴዎች ተጽእኖ ለእኛም ትውልድ የተረፈ እና ሁልጊዜ የሚባርክ ነዉ። አሁን በእኛም ዘመን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚያከብር ቤተክርስቲያንን የሚያንጽ እና ያልዳኑትን ወደ እግዚአብሔር መንግስት የሚያፋልስ የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልገን እሙን ነዉ። ስለዚህም 120'ዎቹ የተሰኘ የጸሎት ፕሮጀክት እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ተጀምሯል። ይህንንም እንቅስቃሴ እጅግ ብዙ ቀጥር ያላቸው የኢትዮጵያ እና የኤሪትሪያ ወጣቶች ከሁሉም አቅጣጫ እየተቀላቀሉ እና በትልቅ ዝግጅት ላይ ነን! ከዚህ በፊት እንደነበሩት የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴዎች ሁለት ወይም ሦስት ሆነን ቢሆንም የተጀመረው በመጨረሻም አሁን ሃገር አቀፋዊ ሆኖ እንድቀጥል በመወሰን: ብዙዎች ተቀላቅለዋል: እናም በመጪው ሰኞ የካቲት 1 / 2013 ዓ.ም በመላዉ ኢትዮጵያ ልክ 12:00 ጀምሮ እስከ 12:30 ድረስ: በመላው ኢትዮጵያ ያሉ የመቶ ሃያዎቹ አካላት ሁሉ በመጸለይ እንጀምራለን። የጸሎት ትኩረት: 👇👇👇👇👇 ሪቫይቫል በተነሳ ቁጥር የሚነሳ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅስ አለ: የዚህ ቃል አድራጊዎች ስንሆን ሃገራ አቀፋዊ ተጽእኖ የመፍጠር አቅም የጸነሰ መሆኑ ግልጽ ነዉ: ይህ ጥቅስ (2ኛ ዜና 7: 14 ነዉ) “በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።” — 2 ዜና 7፥14 በዚህ የተደላደለ መሰረት ላይ በመቆም በዚህ ቀን ከማለዳው 12:00 ጀምሮ ለ 30 ደቂቃ በእግዚአብሔር ፊት በንስሃ እንመለሳለን: የእኛን እና የምድራችንን ኃጢአት ሁሉ በመናዘዝ: እራሳችንን ትሁት በማድረግ በዚያ ቀን እንጾማለን: የእግዚአብሔርን የመፈወስ ሃይልም በምህረቱ እንቀበላለን። ከዚህ ቀን በኋላ በቀጣይነት በዚህ ቃል ላይ በመመስረት እየጸለይን: ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እና የጸሎት አቅጣጫዎች በቀጣይነት እንቀበላለን: እንጸልያለን። አስፈላጊ ሆኖ ስገኝ ወደ የከተማዎች እየተዘዋወርን ይህንን የጸሎት እንቅስቃሴ እናጠናክረዋለን። እግዚአብሔር በሃይሉ ታላቅን ነገር ያደርጋል። ለመቀላቀል እነዚህን መስመሮች ይጠቀሙ! 👇👇👇 @kbzoe @GFI777 @Evangelismebyfire ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit