ch
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

前往频道在 Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

显示更多
1 810
订阅者
无数据24 小时
无数据7
无数据30
帖子存档
በDeepThingsOfGod ቻናል የሚለቀቅ አንድ መዝሙር ስለመንፈስ ቅዱስ መዘመር የሚፈልግ @GFI777 በቆንጆ ድምጽና Recorder በመቅዳት ላኩልኝ አሁን!

🔥እንኳን አደረሳችሁ!🔥 ዛሬ ማታ ሦስት ሰዓት ላይ እንገናኝ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መንፈስ ቅዱስ ማነው? መንፈስ ቅዱስ እሳት🔥 አይደለም! መንፈስ ቅዱስ ሃይል⚡️አይደለም! መንፈስ ቅዱስ ዝናብ🌧 አይደለም! መንፈስ ቅዱስ ደመና☁️ አይደለም! መንፈስ ቅዱስ ማንነት የሌለው ንፋስ አይደለም፤ የራሱ ማንነት ያለው አምላክ ነዉ። እሳትም፣ ሃይልም፣ ደመናም፣ ዝናብም፣ ንፋስም የመንፈስ ቅዱስ መገኘት ተምሳሌታዊ ምልክቶች ናቸው፤ መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ነዉ። መንፈስ ቅዱስ ከአብ እና ከወልድ ያነሰ የስላሴ ሦስተኛው አካል አይደለም፤ እርሱ እግዚአብሔር ነዉ። መንፈስ ቅዱስ እኛ የምንጠቀምበት ሃይል ሳይሆን እኛን መጠቀም የሚገባው እና የሚጠቀመን ጌታ ነዉ። መንፈስ ቅዱስ አምልኮ፣ ክብር፣ ውዳሴ የሚገባው እግዚአብሔር ነዉ። ስለዚህ ስለመንፈስ ቅዱስ ስናስብ የራሱ ማንነት ያለው ከጊዜ ውጭ ዘላለማዊ፣ ከቦታ ውጭ በሁሉም ቦታ የሚገኝ፣ የፍጥረት ፈጣሪ እና ጠብቆ አኗሪ፣ በችሎታው ሁሉን ቻይ( ኤልሻዳይ) ፣ በምግባሩ ፍጹም የሆነ መንፈስ መሆኑን በማወቅ የሚገባውን አክብሮት መስጠት ይኖርብናል። እግዚአብሔር መሆኑንም አጥብቀን ልንረዳ ይገባናል። መንፈስ ቅዱስ ስለራሱ የማይናገር ኢየሱስ ክርስቶስን ለማክበር ከሰማይ የወረደ የእውነት መንፈስ ነዉ። በሕይወታችሁ መንፈስ ቅዱስ እንድሰራ እና እየሰራ እንድቀጥል የምትፈልጉ ከሆነ ኢየሱስ ክርስቶስን በሁሉም ነገር ማእከል(ዋና) አድርጉት።TheDeepThingsOfGod✅ 🔥የበዓለ ኀምሳ ቀን🔥 ዛሬ ምሽት እሁድ 🔥የመንፈስ ቅዱስ ምሽት🔥 እንዳያመልጣችሁ የቃል እና የጸሎት ጊዜ ለምትወዷቸው ሰዎች ሼር አድርጉ Share ♻️ Join ♻️ Share 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

✅TheDeepThingsOfGod✅ 🔥የበዓለ ኀምሳ ቀን🔥 ዛሬ እሁድ ምሽት 🔥የመንፈስ ቅዱስ ምሽት🔥 እንዳያመልጣችሁ የቃል እና የጸሎት ጊዜ ለምትወዷቸው ሰዎች ሼር አድርጉ Share ♻️ Join ♻️ Share 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የሚጸልይ ትውልድ ተነስቷል🔥፣ መንፈስ ቅዱስ የራበው ትውልድ ተነስቷል😭 የእግዚአብሔርን መለኮታዊ አሰራር ለመለማመድ እና ለማየት እንዘጋጅ። በዚህ ጾምና ጸሎት አብረውኝ ከሚጸልዩ አንዱ ነዉ። ከባድ
የሚጸልይ ትውልድ ተነስቷል🔥፣ መንፈስ ቅዱስ የራበው ትውልድ ተነስቷል😭 የእግዚአብሔርን መለኮታዊ አሰራር ለመለማመድ እና ለማየት እንዘጋጅ። በዚህ ጾምና ጸሎት አብረውኝ ከሚጸልዩ አንዱ ነዉ። ከባድ የእግዚአብሔር ክብር እንደሚገለጥበት አምናለሁ @HistoryOfRevivall የተወደድክ የእግዚአብሔር ልጅ እወድሃለሁ!

🔥 ዛሬ የሚደንቅ የጸሎት ቀን ነበር አሁን ከጸሎት መወጣቴ ነዉ። እናንተም ጋር ድንቅ እንደነበር አምናለሁ፤ ስለሁላችሁም ስጸልይ ነበር የጌታ መንፈስ የሚናገረኝን እነግራችኋለሁ! ጾም ጸሎቱ ማታም ነገም ሙሉ ቀን ይቀጥላል🔥 ብዙ ልጆች አብራችሁኝ እየጸለያችሁ እና እየጾማችሁ ነዉ። 🔥መንፈስ ቅዱስ ከእናንተ ጋር ነዉ🔥

ሐዋርያት 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶ ነገር ግን ይህ በነቢዩ በኢዩኤል የተባለው ነው። ¹⁷ እግዚአብሔር ይላል፦ በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ፤ ¹⁸ ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎቼ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ። … ³⁹ የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ ጌታ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉ ሁሉ ነውና አላቸው። ☝️☝️ አብራችሁኝ የምትጾሙ ልጆች በዚህ ቃል መሰረት ጸልዩ።

ቅዳሜና እሁድ የምትጸልዩ እና የምትጾሙ የአባቴ ልጆች ይህንን ስሙ!🔥 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ከፊታችን ያለው እሁድ ከኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ ጀምረን ስንቆጥር አምሳኛው ቀን ነዉ። ይህ ማለት የጴንጤቆስጤ ቀን ነዉ፤ መንፈስ ቅዱስ ወደ ምድር የወረደበት ቀን ነዉ። ስለዚህ ነገና እሁድን ለመንፈስ ቅዱስ እንሰጣለን። እሁድ ቀን ምሽት ስለ መንፈስ ቅዱስ ትምህርት እና ጸሎት አደርጋለሁ ነገና እሁድ እንጾማለን። ነገና እሁድ አብሮኝ የሚጸልይ የሚጾም?

🔥TheDeepThingsOfGod🔥 @የእግዚአብሔር@ጀነራሎች Brother C.S Upthegrove ይባላል። ባለፈው ክፍለ ዘመን የሚያስደንቅ የፈውስ አገልግሎት ያገለግል ከነበረው ከ A.A Allen
+1
🔥TheDeepThingsOfGod🔥 @የእግዚአብሔር@ጀነራሎች Brother C.S Upthegrove ይባላል። ባለፈው ክፍለ ዘመን የሚያስደንቅ የፈውስ አገልግሎት ያገለግል ከነበረው ከ A.A Allen ጋር አብራው ያገለግሉ ነበር፤ እርሱም ራሱ ትልቅ የፈውስ አገልጋይ ነበር። ከላይ የምትመለከቱት ምስል C.S Upthegrove በ 1968 Michigan ከተማ ስያገለግል የተነሳ ፎቶግራፍ ነዉ። ፕሮግራሙ ላይ ስለ ኤልያስ እየሰበከ እንደነበር እና በድንገት በዙሪያው የሚታይ እሳት እንደነበር እራሱ ተናግሯል፤ አንድ ሰውም ይህንን ምስል በጊዜው አንስቶት ነበር፤ ምስሉ እ.እ.አ በ 1968 የተነሳ ነዉ በግልጽ እንደምታዩት የሚታይ እሳት አለ። C.S Upthegrove ይህንን ምስል ጨምሮ ሌሎች ጠብቆ ያቆያቸውን መንፈሳዊ ማስታወሻዎች እ.እ.አ በ 2012 ወደ አፊሪካ በመምጣት ለ ነቢይ ቲ.ቢ ጆሽዋ ሰጥቶት ነበር። "God will use anyone, who is ready to pay the cost." አስገራሚ የሪቫይቫል ታሪኮችን ለማግኘት Join 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በክርስቶስ መስቀል ላይ የሆነውን በእውነት አውቃለሁ? ጨርሼስ ተረድቼዋለሁ? ከተረዳውት የተደረገልኝን በማመን እየተመላለስኩ ነዉ? እነዚህን ጥያቄዎች እራሴን እንድጠይቅ የእግዚአብሔር መንፈስ እንደረዳኝ አምናለሁ። የእውነት አንድ ሰው በክርስቶስ መስቀል የተደረገለትን ስረዳ እና የተረዳውን በማመን ስኖር ፈጽሞ ሕይወቱ የተለወጠ ይሆናል፡ በምንም አይነት መልኩ ከኃጢአት፣ ከሰይጣንና ከዓለም በታች የሆነ ሕይወት አይኖርም። የክርስቶስ መስቀል የእውነተኛ ክርስቲያን ሕይወት ሃይል ምንጭ ነዉ። እውነተኛ የክርስቲያን ሕይወት የሚገለጸው በምንድነው? አንድ ሰው ከኃጢአት፣ ከዓለም እና ከሰይጣን በላይ ሆኖ በእግዚአብሔር ፈቃድ ስኖር እውነተኛ የክርስቲያን ሕይወት ይህ ነዉ። ክርስቶስ በመስቀሉ ለእግዚአብሔር ያደረጋቸው ነገሮች አሉ ለእኛ ለሰው ልጆች ያደረጋቸው አስገራሚ እና በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ እስከ ዛሬ ከነበሩ ወደፊትም ከሚኖሩ ሰዎች አንዳቸውም ለማድረግ የማይችሉትን ነገር በሰው ልጆች ምትክ እና ለሰው ልጆች ሁሉ አድርጓል። ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን እርሱ ያደረገውን ለማድረግ ብቁ ሆኖ የተገኘ ከሰዎች አንድም እንኳ አልነበረም፤ እርሱ ግን አደረገው። ክርስቶስ መስቀል ላይ ለሰው ልጆች ያደረገውን ስንማር ቀናት የሚያልፉ ቢሆንም የተደረገው ነገር ጭብጥ ግን እንደዚህ ይገለጻል:- በመስቀል ኢየሱስ ራሱን ለእግዚአብሔር በሰዎች ምትክ መስዋዕት አድርጎ በማቅረብ የዘላለም ፍጹምነት የሚገኝበትን አድስ መንገድ መርቋል። በሌላ በኩል ደግሞ እጅግ የሚያስገርም በፀጋ የሆነ መለኮታዊ ልውውጥ በኢየሱስ ክርስቶስ እና በሰዎች መካከል ሆኗል ይህ ልውውጥ በእግዚአብሔር ጥንተ ውሳኔ መሰረት የተከወነ እንጂ በሰውኛ ሚዛናዊ ልውውጥ አይመስልም: ለምሳሌ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰዎችን ሁሉ ኃጢአት በራሱ ላይ በመሸከም በእርሱ የሚያምኑ ሰዎች ደግሞ የእርሱን ጽድቅ እንዲቀበሉ አስችሏል: ይህ የልውውጡ አንዱ ገጽታ ብቻ ነዉ ሌሎች እጅግ የሚደንቁ የፀጋ ልውውጦች በክርስቶስ መስቀል ተደርገዋል። ሌላው በክርስቶስ በመስቀል የተደረገው ሰዎችን ነጻ የማውጣት ስራ ነዉ። ይህም ነጻነት በአምስት ተከፍሎ ልታይ የሚችል ነዉ፡ ከሕግ፣ ከአሁን ዓለም አገዛዝ፣ ከስጋ እና ከዓለም የተገኘ ነጻነት በጥቂት ቃል የተገለፀ ቢሆንም እጅግ ሰፊ ትርጉም ያለው እና በምናምን በእያንዳንዳችን ሕይወት የሚንጸባረቅ የሕይወት አይነት ነዉ። እንግዲህ ከላይ የተዘረዘረው ሁሉ በክርስቶስ መስቀል አንድ ጊዜ ለዘላለም የተደረገልን ነዉ። በዚህ እውነት ለመመላለስ እና ይህንን የሕይወት አይነት የራስ ለማድረግ ደግሞ ከእግዚአብሔር የቀረበልን ጥር "በላከው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን" ብቻ ነዉ። ይህ ሁልጊዜ የእግዚአብሔርን ፀጋ ያለማቋረጥ እንድናመሰግን ያደርገናል፡ ክብር ለእግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለዘላለም ይሁን። ይህንን የምታነቡ የተወደዳችሁ ሆይ የክርስቶስን መስቀል ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ አሳስባችኋለሁ፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር በየትኛውም ጊዜ የሚያስፈልጋችሁን ነገር የኖረው በእርሱ ላይ ነዉ። ፀጋ ይብዛላችሁ! ለምትወዷቸው ሰዎች ሼር አድርጉ Share ✅ Join ✅ Share 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#ምስክርነት ሰላም ሀያላን እንዴት ናችሁ? ምስክርነት አለኝ አባቴ መንፈስ ቅዱስ ድንቅ ነገር አደርጎልኛል Praise God hallelujah......! sami እባላለዉ ከሙገር፤ ተማር ነኝ ክርስትያን family ዉስጥ ነዉ ያደኩት በመንፈሳዊ ህይወተም ጥሩ የሚባል ደረጃ ላይ ነበርኩ አገልጋይም ነኝ በወጣቶች fellowship ዉስጥም member እና አገልጋይ ነኝ። የሆነልኝ ነገርም ከመንፈሣዊ ነገር ጋር የተያያዘ ነዉ። እንደሚታወቀዉ በspiritual አለም ዉስጥ ማሠላሠል{MEDITATION} የሚባል ወሳኝ ነገር አለ በእግዚአብሔር ቃል መሰረት አንድ ሰዉ ዳግም ከተወለደ በኋላ መንፈሱ immediately perfect ይሆናል ነፍሱ እና ስጋ ግን በህደት ነዉ። የኔም ችግር የነበረዉ በነፍስ ተሃድሶ ላይ በነበረኝ ስራ ላይ ነዉ። #አስታዉሣለዉ_ከ_6_ወር_ወደዚህ_ግን_ሀሣቤን_መቆጣጠር_አልቻልኩም_ነበር {this is the most dangerous thing in my life} በሕይወቴ በጣም አደገኛው ነገር ይህ ነበር። ከዛም victor'ን በtelegram አዋራዉት ከዛም ፀለየልኝ። ያም ሀሳብ ከኔ እንዳልሆነ እንድቃወመው ዲያብሎስ ማለት ሀሳብ ወርዉሮ የሚከት እንደሆነ ነገረኝ WOW ያ EVIL THINKING ከኔ እንዳልሆነ ነገረኝ ከዚያ በኃላ ነጻ ወጣው ነጻ ወጣዉ HALLELUJAH መርጬ ማሰብ ጀመርኩ ከሚወረወሩው ሀሳብ ይልቅ የመንፈስ ቅዱስን ሀሳብ መያዝ ጀመርኩ አሁን ጥሩ የሆነ MEDITATION አለኝ። አሁን ጥሩ የፀሎት ህይወት እና የመንፈስ ቅዱስ ህልዉና በህይወቴ ላይ አለ PRAISE GOD victor ፀጋ ይብዛልህ። Join👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Read the word, meditate the word, speak the word and let not anyone distract your focus from the word; for the word is your l
Read the word, meditate the word, speak the word and let not anyone distract your focus from the word; for the word is your life. የእግዚአብሔርን ቃል አንብብ፣ አሰላስል፣ ተናገር ማንም እና ምንም ትኩረትህን ከእግዚአብሔር ቃል እንዲከለክል አትፍቀድ፤ ምክንያቱም ሕይወትህ ነዉና። #Victor

የታላላቅ የእግዚአብሔር ሰዎችን ታሪክ ሰማሁ፣ አነበብኩ እነዚህ ሰዎች የሚያስደነግጡ ናቸው "ከእግዚአብሔር ጋር አብሮ ሰራተኞች ነበሩ!" ይሄ ብቻ ነዉ እንደዚህ አይነቶቹን ሰዎች መግለጽ የሚችለው። ባለፈው ክፍለ ዘመን የሚያስደንቅ የእምነት ሃይልን የገለጠ ሰው ነበር E.W KENYON ይህ የእግዚአብሔር ሰው የሞቱ ሰዎችን በፈቃዱ( At Will) በፈለገው ጊዜ ያስነሳ እንደነበር ተጽፏል፤ እርሱ መጋቢ የሆነበት ቤተክርስቲያን አባል ሆኖ ከሰባ ዓመት በታች መሞት አይቻልም ነበር፤ ሰባ ዓመት ሰይሞለው የሞተን የትኛውንም ሰው ከሞት ያስነሳ ነበር፡ ጌታ "ሙታንን አስነሱ"-ማቴዎስ 10:8 በለው ቃል ብርሃን የኖረ ሰው ነበር፤ በአንድ ወቅት ከቤተክርስቲያን አባላት አንዱ በእርሻ ማረሻ መሳሪያ እግሩ ላይ ከባድ አደጋ ደርሶበት E.W KENYON ወደ ሰውዬው በመሄድ ክፉኛ የተጎዳውን እግሩን በትኩረት ስመለከታቸው የተሰባበሩ አጥንቶቹ እዚያው እንደተሰበሰቡ እና ወዲያው በቅጽበት አጥንት ከአጥንት ጋር ስጋ ከስጋ ጋር እንደተያያዘ አነበብኩ። በአገልግሎት ይገለጥ የነበረው የእግዚአብሔር ክብር የተለየ ነበር። E.W KENYON በዚህ ደረጃ የጌታን ሃይል የገለጠበት ሚስጥር ምንድነው? ስለዚህ ሰው ያገኘሁት እና የሃይሉ ሚስጥር የሆነዉ አስገራሚ ነገር ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የነበረው ልምምድ ነዉ። E.W KENYON የእግዚአብሔር ቃል ከምንም በላይ ይወድ ስለነበር መኖሪያ ቤቱ ከበሩ ጀምሮ በተወሰኑ ልዩነቶች በየቦታው መጽሐፍ ቅዱስ ነበር፤ ቤቱ ውስጥ በየቦታው የተመረጡ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ተጽፈው ይቀመጡ ነበር፤ መኖሪያ ቤቱ ውስጥ የትኛውም ክፍል ቢገባ የሚያገኘው እና የሚመለከተው የእግዚአብሔርን ቃል ነበር፤ መኝታ ክፍሉም ሆነ መጸዳጃ ቤቱ ወይም ሳሎኑ ወይም ምግብ ማብሰያው ሁሉም ቦታ በእግዚአብሔር ቃል የተከተበ ነበር። የእግዚአብሔርን ቃል ያለማቋረጥ ሁልጊዜ ከማንበብ፣ ከማሰላሰሉ እና ደጋግሞ ከማወጁ የተነሳ ትልቅ እምነት በሕይወቱ ተፈጥሮ ነበር። “እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።” - ሮሜ 10፥17 አንዱ ሚስጥራዊ የሆነው የቀደመው ጎዳና የእግዚአብሔር ቃል ነዉ፤ ወደ ቀደመው ጎዳና እንመለስ። ፀጋ ይብዛላችሁ። Join 👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መንፈስ ቅዱስ አብሮኝ ሆኖ እንኳ በጣም ይናፍቀኛል ይህንን ሳስብ😥...ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ😭...! እንዴት ነዉ ይህንን ማብራራት የሚቻለው? እንደእኔ የሚሰማው አለ?

ፍጹም መንፈስ( Perfect Spirit) 🔹ቁጥሮች መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚወክሉት ወይም የሚያመለክቱት ነገር አላቸው። 7️⃣ ቁጥር ሁለት ነገሮችን የሚጠቁም ነዉ፤ የመጀመሪያው ፍጹምነትን ስሆን ሌላው መንፈስ ቅዱስን ነዉ። ፍጹምነት ደግሞ ሁልጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ነዉ፡ ማንም ሰው በራሱ ሃይል ፍጹም መሆን አይችልም በመንፈስ ቅዱስ ካልሆነ የትኛውንም ነገር ፍጹም አድርጎ መስራት አይችልም። በዚህ ምክንያት ነዉ ለፍጹምነት የተሰጠው ቁጥር የመንፈስ ቅዱስ ቁጥር የሆነው፤ ይህ ማለት መንፈስ ቅዱስ ፍጹም መንፈስ ነዉ ማለት ነዉ፤ በጣም የሚገርመው ይሄ ፍጹም መንፈስ በአማኞች ህይወት መኖሩ ነዉ። 🔹አንድ አማኝ ራሱንም ሆነ የሚያደርጋቸውን ነገሮች ሁሉ ለመንፈስ ቅዱስ ስልጣን ቢተው ወይም አሳልፎ ቢሰጥ ፍጹም የሆነ ውጤት ይኖረዋል። አማኝ ፍጹም መሆን የሚችለው በትግል አይደለም ራስን ለመንፈስ ቅዱስ ማንነትና ሃይል አሳልፎ በመስጠት ነዉ። "It's not by Struggling it's by yielding to the Holy Spirit." 🔹የተወደዳችሁ ሆይ መታገል አቁሙ ሰዎች በራሳቸው እውቀትና ሃይል ፍጹምነትን ለማምጣት የሚያደርጉት ጥረት ፈጽሞ የሚሳካ አይደለም። ፍጹምነት ፍጹም በሆኑት በሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስት ብቻ ነዉ። 🔹በእያንዳንዱ ጊዜ ለመንፈስ ቅዱስ ራሳችሁን መስጠት ተለማመድ። ፍጹም የሆነውን የእግዚአብሔርን መንፈስ ማወቅ እና መለማመድ እንድትችሉ ፀጋ በሕይወታችሁ ይብዛ። Join 👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔር መንፈስ። -የጌታ መንፈስ። -የጥበብ መንፈስ። -የማስተዋል መንፈስ። -የምክር መንፈስ። -የሃይል መንፈስ። -የእውቀት መንፈስ። -እግዚአብሔርን የመፍራት መንፈስ። 🔹መንፈስ ቅዱስ በሙላት በአንድ አማኝ ሕይወት ውስጥ ስንቀሳቀስ እንደዚህ ነዉ የሚገለጠው። 1️⃣የጌታ መንፈስ -ገዥ ያደርገዋል። 2️⃣የጥበብ መንፈስ - የሚያደርጋቸውን ነገሮች ሁሉ በልህቀት ማድረግ ያስችለዋል። 3️⃣የማስተዋል መንፈስ - ነገሮችን ሁሉ በእውነት መረዳት ያስችለዋል። 4️⃣የምክር መንፈስ - ፍጹም የሆነውን የእግዚአብሔርን ሃሳብ ለሌሎች ማስተማር ያስችለዋል። 5️⃣የሃይል መንፈስ - የእግዚአብሔርን ባሕሪይ የማይገልጹ መለወጥ ያለባቸውን ነገሮች መለወጥ ያስችለዋል። 6️⃣የእውቀት መንፈስ - በእግዚአብሔር ልብ ያለውን ሃሳብ ያሳውቀዋል፤ የተከደነን መግለጥ የተሰወረን ማየት ያስችለዋል። 7️⃣እግዚአብሔርን የመፍራት መንፈስ - የእግዚአብሔርን ማንነት እንዲያውቅ እና ከማወቅም የመነጨ አምልኮ ለእግዚአብሔር እንዲሰጥ ያደርገዋል። #የእግዚአብሔር መንፈስ በሙላት በሕይወታችን እንድንቀሳቀስ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እጸልያለሁ።

Character is the oil that keeps the lamp burning. -Prophet T.B Joshua በሕይወታችሁ መንደድ የጀመረውን የእግዚአብሔርን እሳት እየነደደ እንድቀጥል የሚያደርገው ዘይት የክርስቶስ ባሕሪ ነዉ። የክርስቶስ ባሕሪአንዳንዴ አገልጋዮች በእሳት ጀምረው በውሃ የሚጨርሱት እሳቱን የሚያስቀጥለውን ዘይት(የክርስቶስ ባሕሪ) ስለሚያጡት ወይም ስለሚበርዙት ነዉ። የእግዚአብሔር መንፈስ በሕይወታችን መንቀሳቀስ ስጀምር እና ስም፣ ገንዘብ፣ ክብር ወዘተ የእኛ ስሆኑ የቀደመውን የክርስቶስ ባሕሪ እንዳንጥለው ወይም እንዳንበርዘው መጠንቀቅ ይኖርብናል። እግዚአብሔር ለአገልግሎቱ ከመረጠን ሁልጊዜ በፍቅር፣ በእውነት፣ በትህትና፣ በንጹሕ ልብ እና በርህራሄ ለማገልገል እንዘጋጅ። Join👇 https://t.me/TheDeepThingsOfTheSpirit https://t.me/TheDeepThingsOfTheSpirit

Charaሠባሕርይ is the oil that keeps the lamp burning. -Prophet T.B Joshua በሕይወታችሁ መንደድ የጀመረውን የእግዚአብሔርን እሳት እየነደደ እንድቀጥል የሚያደርገው ዘይት መልካም ባሕሪ ነዉ። የክርስቶስ ባሕሪ። አንዳንዴ አገልጋዮች በእሳት ጀምረው በውሃ የሚጨርሱት እሳቱን የሚያስቀጥለውን ዘይት(የክርስቶስ ባሕሪ) ስለሚያጡት ወይም ስለሚበርዙት ነዉ። የእግዚአብሔር መንፈስ በሕይወታችን መንቀሳቀስ ስጀምር እና ስም፣ ገንዘብ፣ ክብር ወዘተ የእኛ ስሆኑ የቀደመውን የክርስቶስ ባሕሪ እንዳንጥለው ወይም እንዳንበርዘው መጠንቀቅ ይኖርብናል። እግዚአብሔር ለአገልግሎቱ ከመረጠን ሁልጊዜ በፍቅር፣ በእውነት፣ በትህትና፣ በንጹሕ ልብ እና በርህራሄ ለማገልገል እንዘጋጅ። Join👇 https://t.me/TheDeepThingsOfTheSpirit https://t.me/TheDeepThingsOfTheSpirit

በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የጠፋ ነገራችሁ እየፈለጋችሁ ይመጣል። በሃዘን ፈንታ ደስታ በለቅሶ ፈንታ ሳቅ ይሆናል የሚቀጥለው ጊዜ የምስጋና ነዉ። “ የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ ይላቸዋል።” — ሉቃስ 15፥6 የጠፋ የትኛውም ነገራችሁ ያገኛችኋል፤ አንዳንዶቻችሁ ምንም የጠፋ ነገር የለኝም ትሉ ይሆናል፡ ነገር ግን አሁን የእናንተ መሆን ያለበት ግን ያልሆነ የትኛውም ነገር ጠፍቷል ማለት ነዉ። በዚህ ሳምንት በእናንተ ጌታን ማግኘት ያለባቸው ሰዎችም ለጌታ እና ለእናንተ ይገኛሉ። "የጠፋ ነገር ይመጣል ያገኘኛል" እያላችሁ ተናገሩ፤ ተፈጽሟል። https://t.me/TheDeepThingsOfTheSpirit https://t.me/TheDeepThingsOfTheSpirit