ch
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

前往频道在 Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

显示更多
1 810
订阅者
无数据24 小时
无数据7
无数据30
帖子存档
መጽሐፍ ቅዱስ ለአንተ/ ለአንቺ ምንድነው? እንዴት ይገለጻል?

William Tyndale ይባላል በ1523 ዓ.ም የአዲስ ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስን በቀጥታ ከግሪክ ወደ እንግሊዝኛ የመተርጎም ስራ ጀመረ፥ ይህ ድርጊቱ ያስቆጣቸው የቤተክርስቲያን መሪዎች ከፍተኛ ስደት አ
William Tyndale ይባላል በ1523 ዓ.ም የአዲስ ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስን በቀጥታ ከግሪክ ወደ እንግሊዝኛ የመተርጎም ስራ ጀመረ፥ ይህ ድርጊቱ ያስቆጣቸው የቤተክርስቲያን መሪዎች ከፍተኛ ስደት አስነሱበት፥ በዚህ ጊዜ ከእንግሊዝ ወደ ጀርመን በመሄድ የመጀመሪያው የትርጉም ስራውን በከባድ ግፊት ውስጥ ሆኖ በ 1525 ዓ.ም ጨረሰ። ከዛም ወዲያው የብሉይ ቅዱሳት መጽሐፍትን የመተርጎም ስራዉን ጀመረ ነገር ግን መጨረስ አልቻለም፥ ተደብቆ በመተርጎም ላይ እያለ ተያዘ፥ ከቤተክርስቲያን የሚጋጭ ድርጊት አድርጓል በማለት በእሳት ተቃጥሎ እንዲገደል ተፈረደበት፤ በ 1536 በእሳት ተቃጥሎ ተገደለ። ይህም ምንም ወንጀል ስላደረገ አይደለም ወንጀሉ መጽሐፍ ቅዱስን ሁሉም ሰዎች ማንበብ እንዲችሉ ለማድረግ መስራቱ ነበር። እርሱ በ 1536 በእሳት ተቃጥሎ ቢገደልም በመጀመሪያ የጨረሰው የአዲስ ኪዳን ትርጉም 18,000 የሚያክል ቅጅ ተሰራጭቶ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ እኛ ጋር እንዲደርስ የተከፈለውን ዋጋ መረዳት ይቻለን ይሆን😭? @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መጽሐፍ ቅዱስ ለአንተ/ ለአንቺ ምንድነው? እንዴት ይገለጻል?

ትልልቅ ንስሮች እየበረሩ ነዉ፥ የወቅት(season) ለውጥ እየሆነ እንደሆነ ግልጽ ነዉ! Evangelist Billy Graham, Evangelist Reinhard Bonnke, Evangelist Morris Cerullo, Evangelist Ravi Zacharias, Prophet T.B Joshua and today Pastor Cho is gone home! The Eagles are flying, it's a sure sign that seasons and times of the church are changing, expect a fresh move of Gods Spirit!

ቤተክርስቲያን ውስጥ ለሚያገለግሉ ሁሉ አጋሩ፥ በጌታ ፍቅር የምሰጣችሁ ትዕዛዝ ነዉ።

ልጆች እና ጎልማሶች በዚህ በዘመኑ መጨረሻ እግዚአብሔር በእኛ(በልጆች እና በጎልማሶች) ለማድረግ ያቀደው የከበረ ሃሳብ አለው፥ ይህም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ የመጠቅለል ሃሳቡ አካል እንድንሆን እና አብሮ ሰራተኞች እንድንሆን ነዉ። ስለዚህ ምክንያት ምሕረት እንደ ተሰጠን መጠን ይህ አገልግሎት ስላለን አንታክትም።( 2ኛ ቆሮ 4፥1) ነገር ግን የሚያሳፍረውን ስውር ነገር መጣል፣ በተንኮልም መመላለስ ማቆም ይገባናል። ለከንቱ ትርፍ የእግዚአብሔርን ቃል ከውሸት ጋር መቀላቀል ፈጽሞ ልናደርገው የማይገባ ነዉኢያኔስና ኢያንባሬስ የተባሉት የግብፅ ጠንቋዮች ሙሴን እንደተቃወሙት አእምሮአቸው የጠፋባቸው ከእምነትም የተጣሉ ሰዎች እውነትን እንዲቃወሙ፥ ሁልጊዜም እየተማሩ እውነትን ወደማወቅ የማይደርሱ ሞኞችን እንደሚያስቱ የመንፈስ ቅዱስ ምስክርነት ነዉ። በውስጥም በውጭም ባሉ ነፋሶች እንዳትወሰዱ ወንድማዊ ምክሬ ነዉ፥ አጥብቀን የእግዚአብሔርን ቃልና ሃይል የምንፈልግበትም ጊዜ ልሆን እንደሚገባ እረዳለሁ፥ ምክንያቱም ሙሴ ኢያኔስን እና ኢያንባሬስን በቃል ብቻ ሰይሆን በሃይልም ነው የገጠማቸው፥ ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ጢሞቴዎስ በላከው ሁለተኛው መልእክቱ ምዕራፍ ሦስት ላይ ስለመጨረሻው ዘመን ትንቢታዊ የሆነ ትንተና እየሰጠ በኢያኔስ ኢያንባሬስና እና በሙሴ መካከል ስለነበረው ሁኔታ መናገሩ ስውር መልእክት ያዘለ ነዉ፥ ይህም መልእከት በመጨረሻው ዘመን የእውነት ወንጌል አገልጋዮች ከሐሰተኞች ጋር የሚያደርጉት ውጊያ የቃላት ሰይሆን የሃይል መሆን እንዳለበት ነዉ። ሃይል ስል ሃይል ማለቴ ነዉ። የእግዚአብሔር የራሱ አቅም። ከሐሰተኞች ጋር ስነ-መለኮታዊ የሆነ ክርክር በማድረግ አንረታቸውም፥ በቃላት ብልጫም አናሳፍራቸው፥ የግዴታ ሁለቱም ወገን በትሩን መሬት ላይ መጣል ይኖርበታል የበረታው በትር ደካማውን ይውጠዋል። የእግዚአብሔርን ቃል እና ሃይል አጥብቀን እንፈልግ፥ እግዚአብሔር ለሚፈልጉት የሚገኝ አምላክ ነውና። -Victor @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ውኃ ባሕርን እንደሚከድን ምድር የእግዚአብሔርን ክብር በማወቅ ትሞላለችና።” — ዕንባቆም 2፥14

🔥እግዚአብሔር የማወቅ እና የመግለጥ ዘመን🔥

መጽሐፍ ልሻር አይችልም The Scriptures Can't Be Broken “እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ፥ ከሕግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍም፥ ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ።” — ማቴዎስ 5፥18 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳት መጽሐፍት( ᴛʜᴇ ʟᴀᴡ ᴀɴᴅ ᴛʜᴇ ᴘʀᴏᴘʜᴇᴛs) የቱን ያህል የከቡሩ: እና ፈጽሞ የማይሻሩ: ነገር ግን የሚፈጸሙ እንደሆኑ የገለጸበት ቃል ነዉ። በንባቡ ውስጥ ሁለት ነገሮች ተጠቅሰዋል: "የውጣ" እና "ነጥብ" ናቸው። የውጣ በግሪኩ "ἰῶτα" "iota" ነዉ: ይህም በዕብራይስጥ ፊደላት ውስጥ የትንሹ ፊዳል ስም ነዉ። በአማርኛው "ነጥብ" ተብሎ የተተረጎመው ደግሞ κεραία -"keraia" የሚል ድምጽ ያለው የግሪክ ቃል ነዉ: ይህም ደግሞ በዕብራይስጥ ስነፅሁፍ ውስጥ ቅዱሳት መጽሐፍትን ጨምሮ: በሚጻፉበት ጊዜ: ነጠላ ፊደሎችን ከሌሎች ለመለየት የሚጠቀሙት በጣም ትንሽ "ቀንድ" የምትመስል ነጥብ ናት። አሁን አንድ ነገር ተመልከቱ: ጌታችን ኢየሱስ የጠቀሳቸው እነዚህ ሁለቱ "የውጣ" እና "ነጥብ" በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ የመጨረሻ ትንንሾቹ ነገሮች ናቸው! ነገር ግን ጌታ ከእነዚህ ትንንሽ ነገሮች እንኳ አንዳቸውም ሊሻሩ ወይም ሰይፈጸሙ ሊቀሩ እንደማይገባቸው እና እንደማይችሉም ተነግሯል! ይህንንም ቃሉን የበለጠ ለማጠናከር "ሰማይና ምድር እስኪያልፍ" በማለት ተናግሯል! ሃሌሉያ!!! ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን! መጽሐፍ ቅዱስ ጥንታዊ ወይም ዘመናዊ ወይም የሚመጣውም ዘመን መጽሐፍ አይደለም! ዘላለማዊ መጽሐፍ እንጂ! የእግዚአብሔር ልጆች እንዚህን ዘላለማዊ የአምላክ ጽሑፎች እያነበባችሁ እያሰላሰላችሁ እና ድምጻችሁን አሰምታችሁ እየተናገራችሁ መንፈሳችሁ በእግዚአብሔር ሕይወት ይሞላል: ነፍሳችሁ ትድናለች፣ ሰውነታችሁም ፈጽሞ ይለወጣል “ትውልድ ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ተመልከቱ።” — ኤርምያስ 2፥31

ለእኔ እና መንፈስ የሚለውን ለሚሰሙ ሁሉ 2014: የእግዚአብሔርን ቃል/ክብር/ የመፈለግ(Searching) የማግኘት(finding) የማወቅ(knowing) የመለማመድ(experiencing) የመሞላት(carrying) የመግለጥ(manifesting) ዘመን ነዉ። በዚህ መንገድ እኔና እና የሚሰሙኝ ሁሉ ለበጉ ሰርግ እንዘጋጃለን፥ ፍጹም ለውጥን እንለማመዳለን። -Victor

ትንቢት ምንድነው? እንዴትስ ይፈጸማል? What's prophecy? #ከኃጢአት ሽሽ!(Run away from sin!) #ተዋጋ (fight) 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

The quality of information you feed is what determines the level of your elevation in life. -Victor

2 ሰዓት ላይ እለቃለሁ መልእክት፥ ለምትወዷቸው ሰዎች አጋሩ(share)።

🌻መልካም አድስ አመት🌻 እግዚአብሔር ስለ ትልቅ ምህረቱ የተመሰገነ ይሁን።

🚨ዛሬ ማታ አይቀርም፧ 3 ሰዓት በ Open talk: 2014 በትንቢት የተነገሩንን ወይንም በተስፋ ቃል የተሰጡንን ነገሮች ሁሉ እንዴት መጨበጥ እንደምንችል እናገራለሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit በተጨማሪም በየዓመቱ ስለሚነገሩ "ትንቢታዊ አዋጆች" የምናገረው ነገር አለኝ። 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Many are requesting to be part of the ministry school, but i want only 8 to 12 serious men and women who are ready to count the cost pay the price and IMPACT the world for Christ. ብዙዎች የሚንስትሪ ትምህርት ቤት አካል ለመሆን እየጠየቁ ነው፥ ነገር ግን እኔ የምፈልገው የጨከኑ የሚጠይቀውን ሂሳብ ቆጥረው ለመክፈል የተዘጋጁ እና በዓለም ላይ ለክርስቶስ ተጽእኖ ለመፍጠር የወሰኑ ከ 8 እስከ 12 ሰዎች ብቻ ነዉ። አሁን ለይ ብቁ አይደላችሁም ይሆናል፣ ነፍሳችሁን ለመካድ እና ለመማር ከተዘጋጃችሁ ብቻ ተቀላቀሉ። 🚨ምንም አይነት ገንዘብ አይከፈልም🚨

🚨አሁን ሐዋሳ ላሉ ብቻ ነዉ🚨 ለምን ሐዋሳ ብቻ? ብላችሁ የምትጠይቁኝ ወዳጆች፥ ምክንያቱ ትምህርቱን የምሰጠው በአካል ስለሆነ ነዉ። እናም በአካል የምንሰራቸው አያሌ የእግዚአብሔር ስራዎች በመኖራቸው ነው።

🚨አሁን ሐዋሳ ላሉ ብቻ ነዉ🚨

ሐዋሳ ከተጠበቀው በላይ ብዙዎች አለን። እግዚአብሔር ይመስገን! በሐዋሳ ላላችሁ መልካም እና ትልቅ እድል እግዚአብሔር አዘጋጅቷል። በሚቀጥለው ዘመን እግዚአብሔርን ወንጌልን እና ቤተክርስቲያንን በእውነትና በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ማገልገል የምትፈልጉ ይህ እድል የእናንተ ነዉ። ትልቅ ክህደት ባለበት በዚህ ዘመን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራ፣ መንግስትና ትእግስት ለመካፈል በጥልቀት የሚፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ቃልና ለኢየሱስ ክርስቶስ ምስክር ለመሞት እንኳ የተዘጋጁ፥ የእግዚአብሔርን ድምጽ ብቻ የሚያስተጋቡ፣ ልበ ንጹሕ የሆኑ የመጨረሻው ዘመን የክርስቶስ አገልጋዮች እንደሚነሱ በእግዚአብሔር መንፈስ ተረድቻለሁ። ከላይ ያለውን በጥንቃቄ አንብቡት እና ነፍሳችሁን ለመካድ የተዘጋጃችሁ ብቻ አናግሩኝ። ለአሁኑ ከስምንት እስከ አስራሁለት( 8-12) ጨካኝ ሰዎች ብቻ ነው የምፈልገው። ከእናንተ ጋር በግል የእግዚአብሔርን ቃል በጥልቀት እንመረምራለን፥ እናያለን እንለማመዳለን፥ እናገለግላለን። ከ 15 ዓመቴ ጀምሮ ከጌታ ጋር በለኝ መንፈሳዊ ልምምድ እግዚአብሔር የነገረኝን የመጨረሻውን ዘመን ሀሳቡን አካፍላችኋለሁ። በእውነት ለረጅም ጊዜ እግዚአብሔር ለዚህ ጊዜ ያዘጋጃችሁ ሰዎች እንዳላችሁ በእርግጥ አውቃለሁ፥ ዝግጁ ከሆናችሁ ብቻ አናግሩኝ። በዚህ መስመር አናግሩኝ፥ ሐዋሳ ያላችሁ ብቻ 👉 @GFI777

ሐዋሳ የምትኖሩ ወዳጆቼ የእግዚአብሔር ልጆች እስክ ምልክት ስጡኝ?