ch
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

前往频道在 Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

显示更多
1 810
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
ሲጸልይም የፊቱ መልክ ተለወጠ፤ ልብሱም ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ።” — ሉቃስ 9፥29 የሚያሸንፍ ጸሎት የሚያደርገው ይህንን ነዉ! “And as he prayed, the fashion of his countenance was altered, and his raiment was white and glistering.” — Luke 9፥29 (KJV) This is what a prevailing prayer can do! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

እግዚአብሔር ላሳየን ራዕይ የሚመጥን ዝግጅት ማድረግ! ከጓደኞችህ ጋር ትጸልይ፤ ትጾምና አብረህ ትነድ ይሆናል ነገር ግን የተለያየ እንቁ ስለተሰጣችሁ ዝግጅትህ በእነርሱ ልክ አይሁን! የእግዚአብሔርን መንግስት በወንጌል ስብከት ሰይሆን በሌላ መልኩ ለማገልገል የተጠሩ ጓደኞችህ ሁሉ 1 ሰዓት ከጸለዩ በኃላ ጸሎት ጨርሰናል ብለው ይወጡ ይሆናል፤ እነርሱ ወጡ ብለህ አንተም አትጨርስ። እንደ ጓደኞችህ ሰይሆን እንደ ራዕይህ ተዘጋጅ። የእግዚአብሔር መንግስት በእውቀቱ ለመደገፍ ፍለጎት የለው ወንድም አብሮህ እየጸለየ ከ 40 ደቂቃ በኃላ ያልሰራው የቤት ስራ ትዝ ብሎት "ዋው ድንቅ ጊዜ ነበር! ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!" ከለ በኃላ--አንተ ምን ልል ነዉ ብለህ ስትጠብቅ: "እኔ ጸሎት ጨርሻለሁ የምሰራው ስራ ስላለኝ መሄድ ነዉ።" ይልሃል፤ የዚህን ጊዜ አንተም በቃ አብረን እንውጣ ከልክ ተበልተሃል! እሱና አንተ አንድ አይደላችሁም እሱ በተሰጠው ልክ ሰጥቷል: አንተ ግን ብዙ ይቀርሃል! ስለዚህ እሱም ላይ ሰትፈርድበት "እኔ መቆየት ይገባኛል" ብለህ መንደድህን ቀጥል!🔥 እግዚአብሔር ከአንተ የሚፈልገው ለራስህ በሰጠህ ልክ ነዉ: እንጂ ለጓደኛህ በሰጠው ልክ አይደለም። መቶ ሺዎች እና ሚልዮኖች ስድኑ በሪዕይ አይተህ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ከፍ በለ ደረጃ ስታደርግ እና ስራውን ስትፈጽም በሕልም ተመልክተህ: የሞቱ ስነሱና የታመሙ ሁሉ ስፈወሱ ለማየት እየናፈክ ልብህ ላይ ይህ ሃሰብ ከብዶ: ጸሎትህ "በሰላም ያሳደርከኝ በሰላም አውለኝ!" ከሆነ ከስረሃል! የእግዚአብሔር ልጅ ይህንን በዘመንህ የእውነት ማየት የምትፈልግ ከሆነ: ጸሎት ባሕልህ፤ ቃል መብልህ ጾም ጸሎት የሕይወት ስርዓትህ ይሁን! በዘመንህ ታየዋለህ! ታቅፈዋለህ! ትዳስሰዋለህ! እግዚአብሔር የሰጠህ ራዕይ ምን ያህል ነዉ ክብደቱ? በመንፈስህ የሚመላለሰው እግዚአብሔር የነገረህ ቃል ምንድነው? በሱ ልክ ተዘጋጅ! በሱ ልክ ዋጋ ክፍል! ይፈጸማል! ተኝተህ በህልም ያየሀው ነገር ተነሰትህ ሩጥለት! እስክፈጸም አትድከም! አካል አልብሰው: እና ለትውልድህ በረከት ሁኑ! ሃይልን በሚሰጥህ በክርስቶስ ሁሉን ትችላለህ! “...ብዙም ከተሰጠው ሰው ሁሉ ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል፥ ብዙ አደራም ከተሰጠው ከእርሱ አብዝተው ይሹበታል።” — ሉቃስ 12፥48 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ይሁዳ 1 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁰ እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፤ እጅግ ቅዱስ በሆነው እምነታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ ትጉ፤ በመንፈስ ቅዱስም ጸልዩ። ²¹ ወደ ዘላለም ሕይወት የሚያደርሳችሁን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ ሳለ፣ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ! የሁላችንም ሙሽራ የሆነ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ሙሽሪትን(ቤተክርስቲያንን) እንድወስድ ጊዜው ቅርብ ነዉ! ሙሽሪት ለሙሽራው ራሷን እንደምታዘጋጅ በእግዚአብሔር መንፈስ እና ቃል እራሳችንን መዘጋጀት ይጠበቅብናል። “የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ፣ የእርሱም ሙሽራ ራሷን ስላዘጋጀች፣ ደስ ይበለን፤ ሐሤት እናድርግ ክብርም እንስጠው።” — ራእይ 19፥7 (አዲሱ መ.ት) Rapture Ready!

እኔ እንደዚህ ነበርኩ: ነበርኩ ነው ደግሞ አሁን አይደለም በፊት😂😂 👇👇👇👇👇👇👇👇 FB ላይ Or TG ላይ ነዉ ነገሩ። እሷ: ሃይ ቆንጆ እንዴት ነህ? እኔ: እባክሽ ቆንጆ ብለሽ አትጥርኝ! ስሜ ቪክተር ነዉ። እሷ: ቪክተር ቆንጆ ስም ነው! የት ነው የምትኖረው? እኔ: በምድር ኢትዮጵያ ሐዋሳ: በሰማይ ደግሞ ከክርስቶስ ጋር በእግዚአብሔር ቀኝ። እሷ:ጥሩ: ሕይወት እንዴት ናት? እኔ: ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነዉ። እሷ: ታድያ አንተ እንዴት ነህ? እኔ: እግዚአብሔር ሃይል ነዉና: ደና ነኝ። እሷ:እሽ ምን አድስ ነገር አለ? እኔ: ከፀሐይ በታች አድስ ነገር የለም ይላል ቃሉ። እሷ: ጥሩ: ስራህ ምንድነው? እኔ: የወንጌል አገልጋይ ነኝ: ሌላው ደግሞ ተማሪ ነኝ። እሷ: ኦ በጣም ደስ ይላል እኔም እኳ በጌታ ነኝ: በግዝህ ደስ ይለኛል! እኔ: አመሰግናለሁ! ሃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ። እሷ: ልታወራኝ አትፈልግም? እኔ: እያወራሁ አይደለም? እሷ: መልካም ቆይታ... እኔ: ደና ሰንብች: ፀጋ ይብዛልሽ! እንደ እኔ የሆናችሁ ወንዶች ፀጋ ይብዛላችሁ! ሳታገቡ ቀጥ እንዳላችሁ ንጥቀት ይደርሳል። 🤣😂....ምን ለማለት ነዉ? እጮኛ የምትይዙበት ጊዜያችሁ ከደረሰ: አይናችሁን ከፍታችሁ ተመልከቱ: ንግግራችሁ በጨው እንደተቀመመ በፀጋ ይሁን ለማለት ነዉ😎። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ድንቅ ነው ለኔ ጌታ ድንቅ ነው ለኔ ኢየሱስ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

𝗕𝗘𝗥𝗛𝗔𝗡 𝗪𝗘𝗡𝗚𝗘𝗟 𝗖𝗛𝗢𝗜𝗥 "ድንቅ ነው ለኔ ጌታ"𝗡𝗲𝘄 𝗚𝗼𝘀𝗽𝗲𝗹 𝘀𝗼𝗻𝗴 𝟮𝟬𝟭𝟵 https://www.vidmateapp.com/subpub/yqh5/site?url=aHR0cHM6Ly9tLnlvdXR1YmUuY29tL3dhdGNoP3Y9R2pPOXp6cVp4ZUkmZmVhdHVyZT15b3V0dS5i ZQ==&f=sy 🔥Trending video shared via VidMate🔥 🎉Best downloader for video and image on YouTube, WhatsApp status, Facebook, Instagram... 🎉Platform for FREE latest movies🎥🎥 👇Download VidMate Now!👇 https://www.vidmateapp.com/?subpub=sharing

ሞኝ ነህ ይሉኛል ሰይረዱት ቀርተው፤ ተመለስ ይሉኛል ዋጋ ቢስ አድርገው፤ አልፈልግም ከልኩኝ ጭቅጭቅ ምንድነው፤ እምቢ! አሻፈረኝ ኢየሱስ ጌታ ነዉ።

መንፈሳዊነት ሞኝነት ነዉ???🤔 መንፈሳዊነት ሞኝነት ነዉ ስባል ሰምታችሁ ታውቃላችሁ? እኔ እጅግ ብዙ ጊዜ ክርስቲያኖች እንደውም የመድረክ ላይ አገልጋዮች ሁሉ ይህንን ስናገሩ እሰማለሁ።ቅዱሳት መጽሐፍት ግን ይሄንን አይሉም። ከመጽሐፈ የሰው አስተሳሰብ ያገኙት ጥቅስ መሆን አለበት😂። መንፈሳዊነት ሞኝነት ከሆነ ምን አዋቂነት ልሆን ነዉ🤔??? መልስ እፈልጋለሁ! መንፈሳዊነት ሞኝነት ነዉ የሚሉ ሰዎች በሌላ አነጋገር መንፈሳዊ ሰዎች ሁሉ ሞኞች ናቸው ማለታቸው ነዉ: በዚህ አግባብ ቤተክርስቲያንን ሁሉ የሞኞች ስብስብ አደረጓት ማለት አይደል🙄!? መንፈሳዊነት ኢየሱስ ክርስቶስን ማመንና ስሙን መቀበል ነዉ፤ መንፈሳዊነት በእግዚአብሔር የእውነት እውቀት መኖር ነዉ፤ መንፈሳዊነት እግዚአብሔርን ለመምሰል ማደግ መለወጥ ነዉ: ይህ ደግሞ በዚህኛውም በሚመጣውም ዓለም እጀግ የከበረ ትርፍ ያለው ነዉ። በድጋሚ ልጠይቅ--ታዲያ ይህ መንፈሳዊነት ሞኝነት ከሆነ ብልጠት ምንድነው? ከዚህ የላቀ ብልጥነት፤ አዋቂነት፤ ነቄነት ካለ ንገሩኝ። እኔ: የለም አይኖርምም እላለሁ😎! ክብር ሞኞች ሳይሆን የነቃን ላደረገን ለእግዚአብሔር ይሁን። መንፈሳዊነት ሞኝነት ነዉ የሚለው አስተሳሰብና ስብከት ቤተክርስቲያን ውስጥ: ጠያቂ ትውልድ እንዳይኖር፤ ከመድረክ ላይ ለተባለው ቃል ሁሉ አሜን! አሜን! የሚል ትውልድ እንድኖር አድርጓል። መንፈሳዊነት ሞኝነት ነዉ ብሎ ማሰብ የእግዚአብሔርን ጥልቅ ሚስጥራት እንዳናውቅ፤ ፍጹም የሆኑ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እና መንፈሳዊ እውነቶችን ለመማር ፍላጎት(appetite) እንዳይኖር ከማድረግ ያለፍ ምንም ትርፍ የለውም! ቤተክርስቲያን የሞኞች ስብስብ አይደለችም! ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለን ሰዎች የእውቀት ባለቤት የሆነው መንፈስ ቅዱስ አስተማሪያችን የሆነልን፤ ለመለኮታዊ የማሰብ አቅም(intelligence) የተጋለጥን ሰዎች ነን! ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን! መጽሐፍ ቅዱስ የሚለውን ተመልከቱ: መንፈሳዊ ነገር "ሞኝነት" የሚመስለው ሰው አለ: ይህም ሰው ፍጥረታዊ ሰው ነዉ። “ለፍጥረታዊ ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ነውና አይቀበለውም፤ በመንፈስም የሚመረመር ስለ ሆነ ሊያውቀው አይችልም።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥14 መንፈሳዊነት ምን እንደሆነ ለምናውቅ ለእኛ ግን ከመንፈሳዊነት የበለጠ እውቀት ነቄነት የለም። የእግዚአብሔር ልጆች ሞኞች አይደላችሁም!🤗 Join the channel 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ሁልጊዜ በሁሉም ቦታ እንደ እግዚአብሔር ቃል እናስብ፤ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንናገር፤ እንደ እግዚአብሔር ቃል እናድርግ: እግዚአብሔር በዚህ ደስ ይሰኛል። “ከልጆችሽ አንዳንዶቹ ከአብ በተሰጠን ትእዛዝ መሠረት በእውነት ጸንተው እየሄዱ በማግኘቴ እጅግ ደስ ብሎኛል።” — 2ኛ ዮሐንስ 1፥4 (አዲሱ መ.ት) @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜ ይናገራል፤ እኛም ሁልጊዜ መስማት እንድንችል ጆሮዎቻችን ፈጽሞ ይፈወሱ።

እኔ:-የእውነትን ቃል በትክክል መከፋፈል ያስፈልጋል!😎 ወዳጄ:- የእውነት ቃል ይካፈላል እያልከኝ ነው???🤔 እኔ:- አዎ! የእውነት ቃል ራሱ ህሳብ( mathematics) ነዉ እያልኩህ ነው! ስለዚህ ነዉ እጅግ ብዙ ሰዎች የማይሰሩት😂! ወደ ቁም ነገሩ ስመጣ🤨: ህሳብ እንኳ በትክክሉ መከፋፈል የማይችል ጭንቅላት የእውነትን ቃል የመከፋፈል ሥራ መስጠት እብደት ነዉ። ምን ለማለት ነዉ?🤔 ለቅዱሳት መጽሐፍት ፍቺ የሚሰጠውና እውነትን በትክክሉ የሚከፋፍለው የቃሉ ባለቤት መንፈስ ቅዱስ ነዉ ለማለት ነዉ😎። መንፈስ ቅዱስ አስተማሪያችን መሆኑን አውቀን እንድንማር ፀጋ ይብዛልን! እወዳችኋለሁ😍 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“እንደ ማያፍርና የእውነትን ቃል #በትክክል እንደሚያስረዳ የተመሠከረለት ሠራተኛ፣ ራስህን በእግዚአብሔር ፊት ልታቀርብ ትጋ።” — 2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥15 (አዲሱ መ.ት) “Study to shew thyself approved unto God, a workman that needeth not to be ashamed, rightly #dividing_the_word_of_truth.” — 2 Timothy 2፥15 (KJV) የእግዚአብሔርን ቃል ስናስተምር መጠንቀቅ ያለብን አንዱ በትክክል ቦታ ቦታውን ጠብቀን ስለማስተማራችን ነዉ። በትክክል እያንዳንዱን የእውነት ብልት መከፋፈል(rightly dividing the word of thruth) ያስፈልጋል! ይህንን ጥበብ ከመንፈስ ቅዱስ ከልተቀበለን: እራሳችንንም የሚሰሙንንም እናስታለን😥። የእውነትን ቃል በትክክል መከፋፈል እንድንችል ፀጋ ይብዛልን። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#Repost!

እግዚአብሔርን ለመምሰል ማደግ። ************************* ➤የክርስትና እምነት የመጨረሻ ግብ እናንተን እግዚአብሔርን ራሱን የምትመስሉ ማድረግ ነዉ። የእግዚአብሔር መልክ (ክብር) እና ምሳሌ (ባሕርይ) ያላችሁ ልጆች ማድረግ ነዉ። ➤ቅዱሳት መጽሐፍት “የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል፤” — ቆላስይስ 3፥10 ...ይሉናል። እውቀትን እያገኘ እግዚአብሔርን ለመምሰል በመታደስ የሚለወጥ ማንነት ነዉ ያላችሁ። እውቀት የሁሉም ነገር መጀመሪያ ነዉ። ይህ እውቀት ግን የዓለም እውቀት ሰይሆን የእግዚአብሔር እውቀት ፣ የፈቃዱ እውቀት ፣ የመንፈሳዊ ዓለም እውቀት ፣ በክርስቶስ ያገኛችሁት ማንነት እውቀት ነዉ። “ስለዚሁ እኛ ደግሞ ይህን ከሰማንበት ቀን ጀምረን የፈቃዱ እውቀት መንፈሳዊ ጥበብንና አእምሮን ሁሉ እንዲሞላባችሁ እየለመንን፥ ስለ እናንተ ጸሎትን አልተውንም፤” — ቆላስይስ 1፥9 ➤እውቀት ግን መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ አይደለም። እውቀት በሕይወት የሚገለጥ መሆን ይኖርበታል። እግዚአብሔር በሕይወታችሁ ያለውን የፈቃዱን እውቀት ስታገኙ ሰሚዎች ብቻ ሰይሆን አድራጊዎች ለመሆን ትጉ። ቃሉን አድራጊ መሆን የተቀበልነው ትዕዛዝን ነውና። ➤እግዚአብሔርን መምሰልም በቀጥታ ከዝህ እውነት ጋር የተገናኘ ነዉ። ሐዋርያው ጳውሎስ ለመንፈሳዊ ልጁ ለጢሞቴዎስ ያለውን እንመልከት: “ነገር ግን ለዚህ ዓለም ከሚመችና የአሮጊቶችን ሴቶች ጨዋታ ከሚመስለው ተረት ራቅ። እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ።” — 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥7 እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚወሰዱ ድርጊቶች:- 1-ለዚህ ዓለም ከሚመች ከየትኛውም ትምህርት ፣ አመለካከት እና ልምምድ መራቅ። 2-በእውነት እውቀት እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስን ማስለመድ። 👉እግዚአብሔርን መምሰል ከእግዚአብሔር በመወለድ ብቻ የምትታደሉት በረከት አይደለም። ደግም መወለድ የጉዞው መጀመሪያ እንጅ መጨረሻ አይደለም። መሄድ ያለባችሁ ረጅም መንገድ ከፊታችሁ አለ። “እንግዲህ እነዚህን የመሳሰሉ ብዙ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፣ ሸክም የሚሆንብንን ሁሉ፣ በቀላሉም ተብትቦ የሚይዘንን ኀጢአት አስወግደን በፊታችን ያለውን ሩጫ በጽናት እንሩጥ።” — ዕብራውያን 12፥1 (አዲሱ መ.ት) 👉ስለዚህ እግዚአብሔርንም መምሰል #በመለማመድ የሚመጣ ውጤት እንጂ በአንድ ጀንበር የሚፈጠር ታዓምራት አይደለም። ➤ሐዋርያው እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስን ማስለመድን ከአካል ብቃት ልምምድ ጋር በንጽጽር ያቀርብልናል። የአካል ብቃት የምሰራ ሰው በረጅም ጊዜ ድካም ስጋው ይፈረጥማል። ነገር ግን እንደዚህ ያለ የሰውነት አቋም ለይ ለመድረስ ለረጅም ጊዜ በየቀኑ ማለደ እና ምሽት ክብደት ማንሳት እና አመጋገቡን የተመረጠ መድረግ ይኖርበታል። በዚህ መልኩ ሁሉም ሰው በግልጽ ልመለከተው የምችለው ለውጥ ሰውነቱ ላይ ይመጣል። ➤እግዚአብሔርን መምሰልም እንደዚህ በነጻ ፈቃድ ለይ በተመሰረተ ትጋት የሚመጣ ለውጥ ነዉ። ስፖርተኛው ክብደት ማንሳቱን ከተወ ነገሮች ዝቅ እንደምሉ እኛም እግዚአብሔርን የመምሰል መንፈሳዊ ልምምዳችንን ማቆም የለብንም። ይህ ልምምድ የተባረከው ጌታችን ተመልሶ እስክመጣ በዘላቂነት የምቀጥል ነዉ። ➤በመጨረሻም እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስን ማስለመድ መንፈሳዊ ፈይዳ ብቻ ሰይሆን በዝህም ዓለም እጅግ ብዙ ጥቅም እንዳለው ሐዋርያው ያረጋግጥልናል። “የአካል ብቃት ልምምድ ለጥቂት ነገር ይጠቅማልና፤ ለእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት ራስን ማሠልጠን ግን ለአሁኑም ሆነ ለሚመጣው ሕይወት ተስፋ ስላለው ለሁለቱም ይጠቅማል።” — 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥8 (አዲሱ መ.ት) አስታውሱ: መንፈሳዊ እድገት የሙሉ ጊዜ ስራችን ነዉ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ! በያላችሁበት የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ከእናንተ ጋር ይሁን! እኔ ስለእናንተ ሁልጊዜ እጸልያለሁ! ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያላችሁ ሕብረት የበለጠ እንዲጠነክር እና ክርስቶስን የበለጠ እንድታውቁት: በትውልዳችሁም የክርስቶስ እንደራሴዎች እንዲትሆኑ ሁልጊዜ እጸልያለሁ! ዛሬ ግን እናንተ እንድትጸልዩልኝ ልጠይቃችሁ ነዉ: ፀጋ እንድበዛልኝ: የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ሁልጊዜ ከእኔ ጋር እንዲሆንና ክርስቶስን ፈጽሜ እንዳውቀው: ጸልዮልኝ? በጌታ ስወዳችሁ❤ አሁን ይህንን ስታነቡ ለአብ ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ አሳስቡልኝ!??? “ወንድሞች ሆይ፥ ስለ እኛ ጸልዩ።” — 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥25

ሰላም ደስታ -ደሙ ነዉ! የክርስቶስ ኢየሱስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻል! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔር ቃል በእኛ ይሰራል! ሁላችንም የእግዚአብሔር ቃል ለእኛ ጥቅም እንዲሰራልን እንፈልጋለን። ይህ ትክክለኛ ፍላጎት እና መጽሐፍ ቅዱሳዊም ነዉ: እግዚአብሔር እራሱ ቃሉ እንዲሰራለት ነዉ የሚልከው: “ከአፌ የሚወጣ ቃሌ እንዲሁ ይሆናል፤ የምሻውን ያደርጋል የላክሁትንም ይፈጽማል እንጂ ወደ እኔ በከንቱ አይመለስም።” — ኢሳይያስ 55፥11 የእግዚአብሔር ቃል ግን ለእኛ ከመስራቱ በፊት በእኛ መስራት አለበት። ቀድሞ እራሳችንን መስራት አለበት። እንዴት ነዉ የእግዚአብሔር ቃል በእኛ የሚሰራው? “ስለዚህም የመልእክትን ቃል እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ከእኛ በተቀበላችሁ ጊዜ፥ በእውነት እንዳለ በእናንተ በምታምኑ ደግሞ እንደሚሠራ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንጂ እንደ ሰው ቃል አድርጋችሁ ስላልተቀበላችሁት፥ እኛ ደግሞ እግዚአብሔርን ሳናቋርጥ እናመሰግናለን።” — 1ኛ ተሰሎንቄ 2፥13 የእግዚአብሔር ቃል በእኛ የሚሰራበት ሚስጥር ከላይ ባለው ቃል ውስጥ ተቀምጧል። ሐዋሪያው ጳውሎስ የተሰሎንቄ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል የተቀበሉበትን መንገድ ስናገር "በእውነት እንዳለ በእናንተ በምታምኑ እንደሚሰራ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንጅ እንደ ሰው ቃል አልተቀበላችሁትም" ይላል። የእግዚአብሔርን ቃል የተቀበሉበት መንገድ ቃሉ በእነርሱ እንድሰራ አድርጎታል። አስተውሉ ከጳውሎስ የሰሙትን ቃል የተቀበሉት እንደ እግዚአብሔር ቃል ብቻ አይደለም: ነገር ግን እውነት እንደሆነ እና በእነርሱ እንደሚሰራ እንደ እግዚአብሔር ቃል በማመን ነዉ። የእግዚአብሔር ቃል በእኛ የሚሰራው እውነት እንደሆነ በእኛ እንደሚሰራ እንደ እግዚአብሔር ቃል አምነን ከተቀበልነው ነዉ። የእግዚአብሔር ቃል ስለሆነ ብቻ በእኛ አይሰራም ቃሉን የምንቀበልበት መንገድ በጣም ትልቅ ድርሻ አለው። ለዚህ ነው አንዳንድ ክርስትያኖች ከሌሎች በበለጠ የክርስቶስ መልክ የሚታይባቸው እና በእምነታቸውም ጠንካራ የሆኑት። የተቀበልንበት መንገድ ነዉ ሚስጢሩ። የእግዚአብሔርን ቃል የተቀበላችሁት እንዴት ነዉ? እንደ እግዚአብሔር ቃል ብቻ ነው ወይስ? በእናንተ በምታምኑ እንደሚሰራ እንደ እግዚአብሔር ቃል? ወይስ እንደ ሰው ቃል? የምትሰሙትን የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እውነት እንደሆነ በእናንተ እንደሚሰራ እንደ እግዚአብሔር ቃል በማመን ተቀበሉ: የእግዚአብሔር ቃል በእናንተ ይሰራል። አሜን! ተቀላቀሉን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ፤ ከእንግዲህ እኔ አልኖርም፤ ነገር ግን ክርስቶስ በውስጤ ይኖራል። አሁንም በሥጋ የምኖረው ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን አሳልፎ በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለኝ እምነት ነው።” — ገላትያ 2:20 (አዲሱ መ.ት)

Majesty! Worship His Majesty! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit