ch
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

前往频道在 Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

显示更多
1 810
订阅者
无数据24 小时
无数据7
无数据30
帖子存档
የሮሜ ጥናት አራት ሮሜ 2፥1-16 ሁለተኛው ደረጃ ~ የእግዚአብሔር ፍርድ እግዚአብሔር የሚፈርድባቸው አምስት መርሆች! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት ሦስት ሮሜ ምዕ 1፥18-32 ደረጃ 1 የእግዚአብሔር መገለጥ ፥ የሰዎች እምቢተኝነት እና ውጤቱ። ሁለት የተገለጡ የእግዚአብሔር ባሕሪያት፥ ሁለት የተፈለጉ ምላሾች ፥ ሁለት የእምቢተኝነት ውጤቶች ፥ ሁለት ዉድቀቶች። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት ሁለት ሮሜ ምዕራፍ 1፥1-17 ጳውሎስ ፥ ወንጌል እና በሮሜ ያሉ ክርሲቲያኖች። ሁልጊዜ ዕሮብ እና እሁድ @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ሰላም የተወደዳችሁ በያላችሁበት ፀጋ ይብዛላችሁ ዛሬ ያለንን የሮሜ ጥናት በጉጉት እየጠበቃችሁ እንደሆነ አውቃለሁ፥ ነገር ግን ዛሬ የሚኖረን ጥናት ወደ እሮብ ተዘዋውሯል። ዛሬ ግን የቀደሙትን ትምህርቶች እንድትሰሙ አበረታታለሁ!

ሮሜ 2፥1-16 አምስት እግዚአብሔር ፍርድ የሚሰጥባቸው መርሆች! ያልሰማ ይስማ፣ የሰማ ደግሞ ይስማ ለሌሎችም እናሰማ! ዛሬ ማታ በተለመደው ሰዓት የደረጃ ሁለትን ቀጣይ ክፍል (ከምዕ 2፥17-3፥8) ድረስ እንመለከታለን! አእምሮን የሚያድስ እና ሕይወትን የሚለውጥ ነው፤ የመንፈስን ሕይወት ለመረዳትና ለመኖር የምናደርገውን ጉዞ የሚያፋጥን ነው።

እግዚአብሔር በፀጋው ወዳዘጋጀልን የመንፈስ ሕይወት በሙላት ደርሰን ለመኖር እያንዳንዱን የእውነት ትምህርት በትክክል መረዳት በትህትና መቀበል እና በእምነት መታዘዝ የግድ ነው።

የሮሜ ጥናት 2፥1-16 አምስት የእግዚአብሔር ፍርድ መርሆች! ደጋግማችሁ ስሙት ለሌሎችም አጋሩ: በብዙ መልኩ የሰውን አካሄድ የሚለውጥ ነው። በዚሁ አንድ ነገር ልበላችሁ የክርስትና አስተምህሮዎች በክብር የተሞሉ እና እጅግ ውብ የሆኑ ናቸው።ምንም እንኳ መንፈሳዊና ከዚህኛው ዓለም እውነታ ከፍ ያሉ እውነቶች ቢሆኑም በትክክል እየከፈለ የሚያስተምረን ካህን ከተገኘ ለመረዳት የሚያስቸግሩ ግን አይደሉም። ከእነዚህ እጅግ ከከበሩ ትምህርቶች ሁሉ የሰዎች አእምሮ ለመረዳት የሚቸገረው ስለ "እግዚአብሔር ፍርድ" የተሰጠውን ትምህርት እንደሆነ አውቃለሁ። ሰዎች ከቀደመው ዘመን ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ወደፊትም ጨርሰው መረዳት የማይችሉትና አሜን ብለው የማይቀበሉት አንድ ነገር ቢኖር የእግዚአብሔርን ፍርድ ነው። ሐዋሪያው በዚህ ምክንያት ነው “የእግዚአብሔር የጥበቡና የዕውቀቱ ባለጠግነት እንዴት ጥልቅ ነው! ፍርዱ አይመረመርም፤ ለመንገዱም ፈለግ የለው … " -ሮሜ 11፥33--- በማለት የእግዚአብሔርን ፍርድ የሰዎች አእምሮ ሊረዳው የማይችለው መሆኑን የገለጸው። የእግዚአብሔርን ፍርድ ለመረዳት ስንፈልግ ሙሉበሙሉ ትሁት መሆንና በመንፈስ ቅዱስ ረዳትነት ላይ መደገፍ የሚኖርብን በዚህ ምክንያት ነው። ነገ ማታ 3 ሰዓት በሚኖረን የጥናት ጊዜ የእግዚአብሔርን ፍርድ በተመለከተ ሌሎች ሐሳቦችን እንማራለን። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ስንቶቻችን ይህንን እናውቃለን? “ሁላችንም በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት እንቀርባለንና፤ እያንዳንዱም ሰው በሥጋው ለሠራው በጎ ወይም ክፉ ሥራ ተገቢውን ዋጋ ይቀበላል።” — 2ኛ ቆሮንቶስ 5፥10 (አዲሱ መ.ት)

ወዳጄ:- Victor የሮሜ ጥናት ግን..🙄 እኔ:- ምን ሆነ? ወዳጄ:- ገና ከመጀመሪያው የሰው ዘር የውድቀት ጥልቀት፥ የእግዚአብሔር ፍርድ ፥ አምስት የእግዚአብሔር ፍርድ መርሆች... አረ እየተቀጠቀጥን ነው🙄 እኔ:- ቃሉን በትህትና መቀበል ይኖርብናል እውነት ነውና፥ ውጤቱም የፀጋ ክብር ከፍታ ነው ስለዚህ ታገሰው።😁 ወዳጆቼ ሮሜን በትዕግስትና በትህትና የማይማር እና በእምነት ተቀብሎ ለመታዘዝ ያልወሰነ ሰው ገና የመጀመሪያውን ምዕራፍ ስያጠና ነው መጽሐፉን ዘግቶ የሚነሳው፡ በተለይ ደግሞ አነቃቂ ወተት🤔 ማለቴ ትምህርት😂 እየጠጣ የኖረ ወዳጃችን። የእግዚአብሔርን እውነት በትክክል እያከፋፈልን ማየታችን ያልታደሰ አእምሮአችን የሚቃወመው ቢሆንም የመጨረሻው መዳረሻ በክብር የተሞላ ነውና መንገዱ ዝቅ ከፍ ሲያደርገን በትእግስት እንከተለው እንጂ ተስፋ በመቁረጥ መንገድ እናቁም።

የሮሜ ጥናት 2፥ 1-6 የሞራል እውቀት ( ትክክል በሆነው እና ትክክል ባልሆነው መካከል መለየት መቻል) ብቻውን አንድን ሰው የተለወጠ አያደርገውም። እንደውም እውቀት የለ እግዚአብሔር ፍርሃት ትዕቢተኛ ያደርጋል እንጂ ወደ ንስሃ አይመራም --( 1ኛ ቆሮ 8፥1 ፤ ሮሜ 2፥4) ስለዚህ አንድ ሰው የሞራል እውቀት ባለቤት መሆኑ ብቻውን ከእግዚአብሔር ፍርድ አያድነውም። እንዲያውም በማወቁ ምክንያት የሚቀበለውን ፍርድ የባሰ ያደርገዋል፥ በእግዚአብሔር ፊት የሚጸድቁ ያወቁትን የሚያደርጉ እንጂ የሚያውቁ ብቻ አይደሉም። ይሄ በቀዳሚነት አይሁድን የሚመለከት ቢሆንም አሁን እኛን ክርስቲያኖችንም እንደሚያካትት ግልጽ ነው፤ ምክንያቱም አሁን እንደእኛ የእውነት እውቀት የበዛለት ያለ አይመስለኝም። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት ሮሜ 2፥1-6 --- አምስት የእግዚአብሔር ፍርድ መርሆች። 1- በእውነት ይፈርዳል --- ሮሜ 2፥6 --- እግዚአብሔር በቃሉ ውስጥ ባለው እውነት ይፈርዳል ---ዮሐንስ 17፥17 (የእግዚአብሔር ቃል እውነት ነው) 2-እንደ ስራ ይፈርዳል--ሮሜ 2፥6 ---እግዚአብሔር የሚፈርድበት አንዱ መርህ ስራ ነው ሐዋሪያው ጴጥሮስ እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ እንደ ስራው የሚፈርድ በመሆኑ በዚህ ሕይወት በፍርሃት እንድንኖር ያስተምራል --1ኛ ጴጥሮስ 1፥17-- 3-ያለ አድሎ ይፈርዳል --ሮሜ 2፥11-- እግዚአብሔር የሰዎችን ውጫዊ ሁኔታ እና የሕይወት እርከን በማየት ሰዎችን እያከበረ አይፈርድም፥ ሰዎችን ሁሉ ያለአድሎ ይፈርዳል። 4- በእውቀት(በብርሃን) ይፈርዳል--ሮሜ 2፥12 -- አራተኛው እግዚአብሔር የሚፈርድበት መርህ ብርሃን ነው። እያንዳንዱ ሰው ባገኘው እውቀት (ብርሃን) ልክ ይፈረድበታል፥ ብዙ ብርሃን የተቀበለ ፍርዱም በዛው ልክ ይበዛል። ሕግን የሚያውቁ በሕግ፤ ሕግ የሌላቸው ደግሞ ያለ ሕግ ይፈረድባቸዋል። 5- በልብ እንደለው ሚስጥር ይፈርዳል--ሮሜ 2፥16 -- እግዚአብሔር ሰዎችን ሁሉ በልባቸው ተሰውሮ ባለው ሚስጥር ይፈርዳል። ይህ ሚስጥር ሰዎች ያደረጉትን ሁሉ ያደረጉበት ፥ የተናገሩትን ሁሉ የተናገሩበት መነሻ ምክንያት /Motive & motivation / ነው። ይህንን መነሻ ምክንያት ሰዎች ማየት ስለማይችሉ በማንም ላይ እንዳይፈርዱ ታዘዋል--1ኛ ቆሮ 4፥5-- ነገር ግን ይህ መነሻ ምክንያት በፍርድ ቀን ይጋለጣል በዚህም መሰረት እግዚአብሔር ፍርድ ይሰጣል። @TheDeepThingsOfGod

sticker.webp0.25 KB

የሮሜ ጥናት አራት ሮሜ 2፥1-16 ሁለተኛው ደረጃ ~ የእግዚአብሔር ፍርድ እግዚአብሔር የሚፈርድባቸው አምስት መርሆች! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት ምዕራፍ አንድ #ማጠቃለያ በአጭሩ# ከቁጥር 1-17 / የመልእክቱ መግቢያ/ እነዚህ ቁጥሮች ሦስት* ሐሳቦች ይዘው ማብራሪያ ይሰጣሉ:- የመጀመሪያው የጳውሎስን* ማንነት፥ ሁለተኛው ወንጌልን* ሦስተኛው በሮሜ ያሉ ክርስቲያኖችን። ከቁጥር 18-32 የምዕራፉ ሁለተኛ ክፍል:- የሰው ዘር ሁሉ ወድቆ የገባበት የውድቀት ሸለቆ ጥልቀት/The depth of human depravity./ እነዚህም ቁጥሮች ሦስት ሐሳቦች ይዘዋል:- የመጀመሪያው እግዚአብሔር ለሰው ዘር ሁሉ የገለጠው የራሱ መገለጥ*፥ ሁለተኛው የሰው ዘር ሁሉ እምቢተኝነት እና ሦስተኛው የእምቢተኝነት ውጤቶች* ናቸው። 1-እግዚአብሔር ለሰው ዘር ሁሉ የሰጠው የራሱ መገለጥ:- ዘላለማዊ ሃይሉ እና መለኮትነቱ። 2-የሰዎች እምቢተኝነት:- ለእግዚአብሔር ክብር አለመስጠት፥ ምስጋና አለማቅረብ እና ጣዖት ማምለክየእምቢተኝነት ውጤት:- በመጀመሪያ ሁለት ውጤቶች ክፉ ምኞትና ቅዱስ ያልሆነ ሩካቤ ስጋ(ግብረ ሰዶማዊነት)። ሦስተኛው ውጤት ለማይረባ አእምሮ ታልፎ መሰጠት። የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ ስጋን የሚያረክሱ ናቸው፥ የቀጠለው ውጤት ደግሞ አእምሮን የሚያረክስውጤቱ ውጫዊና ውስጣዊ ውድመት ነው ማለት ነው። ለማይረባ አእምሮ የተሰጡ ሰዎችም 21 እግዚአብሔራዊ ያልሆኑ የሞራልና የባሕሪ ውድቀቶች አሳይተዋል። ምዕራፍ አንድን በዚህ መልኩ ልንረዳው እንችላለን፥ የበለጠ ለመረዳት በድምጽ የቀረቡትን ስሙ እና እናንተም በግላችሁ እያንዳንዱን ቃል በቃል እንድታጠኑት አበረታታለሁ። ፀጋ ይብዛላችሁ! ለሐሳብ ለጥያቄ @GFI777 -Victor @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

☝️የሮሜ መጽሐፍ ጥናት ምዕራፍ አንድ በዚህ መልኩ ቀርቧል ያልሰማችሁ ስሙ፥ የሰማችሁ ደግማችሁ ስሙ ለሌሎችም አሰሙ። ተባረኩ። ዛሬ ማታ 3 ሰዓት ምዕራፍ ሁለትን እና ደረጃ ሁለትን ማጥናት እንጀምራለን።

የሮሜ ጥናት ሦስት ሮሜ ምዕ 1፥18-32 ደረጃ 1 የእግዚአብሔር መገለጥ ፥ የሰዎች እምቢተኝነት እና ውጤቱ። ሁለት የተገለጡ የእግዚአብሔር ባሕሪያት፥ ሁለት የተፈለጉ ምላሾች ፥ ሁለት የእምቢተኝነት ውጤቶች ፥ ሁለት ዉድቀቶች። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት ሁለት ሮሜ ምዕራፍ 1፥1-17 ጳውሎስ ፥ ወንጌል እና በሮሜ ያሉ ክርሲቲያኖች። ሁልጊዜ ዕሮብ እና እሁድ @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ መጽሐፍ ጥናት አንድ~ መግቢያ አንድ። -Victor ቀጣዩን ለመስማት 👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ሮሜ 1፥18-32 ይህ ክፍል እንዴት ነው ምዕራፍ ስምንት ላይ ወደተገለጸው ( ወደ መንፈስ ሕይወት) ለምናደርገው ጉዞ የመጀመሪያ ደረጃ ልሆን የሚችለው? በግልጽ ማወቅ የሚገባን ነገር መጽሐፍ ቅዱስ እውነተኛ የእውነት አስተማሪ መሆኑን ነው ሰዎችን በከንቱ የማነቃቃትም ሆነ የማበረታታት አጀንዳ የለውም፥ የማንንም ምስጋና ለማግኘትም አይናገርም እውነትን ግን በስልጣን ያስተምራል። በተጨማሪም ነገሮችን ከመጀመሪያው አንስቶ እስከ መጨረሻው ሂደቱን ጠብቆ የሚያስተምር በመሆኑ የሰውን ውድቀት ከገለጸ በኃላ ከዚህ የውድቀት ሸለቆ የሰው ልጅ መውጣት የሚችልበትን መንገድ ይገልጣል። ስለዚህ በሮሜ 1፥18-32 ያለው ቃል የሰው ዘር የወረደበትን የውድቀት ሸለቆ ጥልቀት የሚያሳይ ነው። ይህም በቀጣዮቹ ምዕራፎች ውስጥ የምንመለከተውን የእግዚአብሔርን የፀጋ ክብር ከፍታ እንድናደንቅ የሚረዳን ከመሆኑም በላይ የውድቀት ሸለቆ ውስጥ መሆናችንን ማወቃችን ወደ ፀጋው ከፍታ መውጣት እንድንችል የሚያነሳሳና የሚያግዝ ነው፤ ችግርን በትክክል ማወቅ የመፍትሔው አካል እንደሆነም መዘንጋት የለበትም። ይህ ክፍል በቀዳሚነት አሕዛብን የሚመለከት ቢሆንም አይሁዳዊያንንም የሚያካትት ነው። የሰው ልጅ የውድቀት ጥልቀት በእነዚህ ቁጥሮች ውስጥ በብዙ ቃላትና ድርጊቶች ተገልጿል ለምሳሌ ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ባለመስጠት፥ በጣዖት አምልኮና ቅዱስ ባልሆነ ሩካቤ ስጋ...ወዘተ የተገለፀ ቢሆንም ከሁሉም በላይ የውድቀትን ጥልቀት የሚገልጸው ቃል "በሐሳባቸው እግዚአብሔርን ማወቅ አይጠቅምም ማለታቸው (ቁ.28) እና አምላክን የሚጠሉ ናቸው (ቁ. 30) የሚለው ነው። የሰውን ዘር የውድቀት ጥልቀት የተረዳ ሰው የእግዚአብሔር የፀጋ ክብር ከፍታ አለማመስገን አይችልም። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት ሮሜ 1፥18-32 ደረጃ አንድ የእግዚአብሔር መገለጥ ፥ የሰዎች እምቢተኝነትና ውጤቶች። የእግዚአብሔር መገለጥ ለሰዎች ሁሉ:- የማይታየው እግዚአብሔር ለሰዎች ሁሉ በፍጥረቱ በኩል ሁለት የራሱን ባሕሪያት ግልጽ አድርጓል። ዘላለማዊ ሃይሉን እና መለኮትነቱን ይህንን ከገለጠ በኋላ በምላሹ ከሰዎች የፈለገው ምንድነው? ክብር እና ምስጋና የሰዎች እምቢተኝነት:- እግዚአብሔር በእጆቹ ስራዎች በኩል( በተለይ በሰማያት መዝ 19፥1) ለሰዎች የገለጠውን ባሕሪይ ሰዎች ቢያውቁም በእምቢተኝነት ለእርሱ ክብር አልሰጡትም ምስጋናም አላቀረቡለትም። የእምቢተኝነት ውጤት በዚህ ምክንያት ሁለት ችግሮች ሰዎችን ሁሉ ገጠሙ:- ሐሳባቸው ከንቱ ሆነ ፤ የማያስተውል ልባቸውም ጨለመ። በዚህ ምክንያት ሰዎች በራሳቸው እራሳቸውን እንደ ጠቢብ መቁጠር ጀመሩ ነገር ግን ሞኝ ሆኑ፥ ይህም ሞኝነት የተገለጠው:- ጣዖትን በማምለካቸው ወይም በፈጣሪ ፈንታ የተፈጠረውን በማምለካቸው ነው። ጣዖትን በማምለካቸው እና የእግዚአብሔርን ክብር ሙት በሆነው በመለወጣቸው የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ እግዚአብሔር በኃጢአት ለተሞላው ለልባቸው #ምኞት/lust/ እና ለማይረባ አእምሮ/Vain imagination/ አሳልፎ ሰጣቸው። ይህ እጅግ የሚያስፈራ ነው፥ እግዚአብሔር ሰውን ለራሱ አሳልፎ ስሰጥ። ስለዚህ በጣዖት አምልኮ፥ ቅዱስ ባልሆነ ሩካቤ ስጋና በሁሉም አይነት አመጽ የተሞሉ ሆኑ። በጣም የሚያስደነግጠው ሰዎች ማመካኛ የሌላቸው መሆኑ ነው። የእግዚአብሔር ቁጣ ከሰማይ በሚገለጥበት ቀን እውነትን በዓመጽ የሸፈኑ ሰዎች ሁሉ ራሳቸውን መከላከል አይችሉም ምክንያቱም እግዚአብሔርን እንዲያከብሩት፥ እንዲያመሰግኑት እና የበለጠ ለማወቅ እንዲፈልጉ የሚያደርጋቸውን እውቀት እግዚአብሔር እራሱ ግልጽ አድርጎላቸዋል እነርሱ ግን በእብሪት ለመታዘዝ እምቢ አሉ። የሰው የውድቀት ጥልቀት የሚለወጠው በእግዚአብሔር የፀጋ ክብር ከፍታ ብቻ ነው። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod