ch
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

前往频道在 Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

显示更多
1 810
订阅者
无数据24 小时
无数据7
无数据30
帖子存档
ዛሬ በማለዳ ስለ ዓላማ አስፈላጊነት አሰላስል ነበር እና በድል መኖር የሚፈልግ ሰው ግልጽ ዓላማ መያዝ እንዳለበት ተረዳሁ። ተወዳጆች ሆይ እግዚአብሔር በዚህ ሕይወት ድል አድራጊዎች እንድንሆን ይፈልጋል! ስለዚህ ግልጽ ዓላማ ይኑረን! ዓላማ የሌለው ሰው ሁልጊዜ ተሸናፊ ነው፣ ዓላማ የሌላት ሴት ሁልጊዜ ተሸናፊ ናት! ዓላማ ይኑረን፣ እያንዳንዱ የምናደርገው ነገር ከትንሽ እስከ ትልቅ በዓላማ ይሁን ያኔ አሸናፊዎች ሆነን እግዚአብሔርን ደስ እናሰኘዋለን! ይሄንን የመጋቢ ታምራት ሃይሌን መዝሙር አዳምጡት፣ ተባረኩ! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የመወሰን ሃይል! አምናለሁ ይሄ ለብዙዎች መልስ ነው፣ አሁን ወስኑ እና ለማድረግ የተትረፈረፈ ፀጋን ተቀበሉ። ለመጸለይ፣ ለማንበብ፣ ለመለወጥ፣ ለመቀደስ፣ ለማደግ፣ ለመስራት፣ ከግብ ለማድረስና እግዚአብሔር ደስ ለማሰኘት ወስኑ እና ከመጠን የበዛ ፀጋን ተቀበሉ፣ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም። እኔ እወስናለሁ እግዚአብሔር ደግሞ ፀጋውን ያቀርባል። I make the decision and God supplies the grace. -Bishop David Oyodepo @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

#ቃል#ከቃሉ ኢሳይያስ 55 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰ ዝናብና በረዶ ከሰማይ እንደሚወርድ፥ ምድርን እንደሚያረካት፥ ታበቅልና ታፈራም ዘንድ እንደሚያደርጋት፥ ዘርንም ለሚዘራ እንጀራንም ለሚበላ እንደሚሰጥ እንጂ ወደ ሰማይ እንደማይመለስ፥ ¹¹ ከአፌ የሚወጣ ቃሌ እንዲሁ ይሆናል፤ የምሻውን ያደርጋል የላክሁትንም ይፈጽማል እንጂ ወደ እኔ በከንቱ አይመለስም። አስተውሉ🤔: የእግዚአብሔር ቃል የእግዚአብሔርን መሻት ለመፈጸም ከእግዚአብሔር ተልኮ የመጣ የእግዚአብሔር ሰራተኛ ነው፣ የእግዚአብሔር ቃል የእግዚአብሔርን መሻት እንጂ የእኛን ፍላጎት የሚፈጽም በፍጹም አይደለም። የእግዚአብሔር ቃል በሕይወታችን እንዲሰራ ከፈለግን መሻታችንን እንደ እግዚአብሔር መሻት ማድረግ እግዚአብሔር የሚፈልገውን መፈለግ ይኖርብናል፣ ይሄን ስናደርግ ቃሉ ለእግዚአብሔር የሰራው ስራ ለእኛም የተሰራ ስራ ይሆናል። ጸሎት🙏: የእግዚአብሔር መሻት የእኔም ነው፣ እግዚአብሔር የሚፈልገውን እፈልጋለሁ፣ እርሱ ቅድሚያ ለሰጠው ነገር እኔም ቅድሚያ እሰጣለሁ፣ የእግዚአብሔር ቃል በሕይወቴ ይሰራል! አሜን። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ሆሳዕና አከባቢ ያላችሁ የቻናሌ አባላት ነገ ከ 8 ሰዓት ጀምሮ አይቀርም! 🔥

Jesus your presence makes me whole❤ @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ሆሳዕና ያላችሁ ውድ ወንድሞቼ እና እህቶቼ መልካም ዜና ይዤላችሁ መጥቻለሁ! የፊታችን አርብ፣ ቅዳሜና እሁድ በ Jesus Kingdom int. Church በተዘጋጀው ፕሮግራም ተገኝታችሁ የእግዚአብሔርን
ሆሳዕና ያላችሁ ውድ ወንድሞቼ እና እህቶቼ መልካም ዜና ይዤላችሁ መጥቻለሁ! የፊታችን አርብ፣ ቅዳሜና እሁድ በ Jesus Kingdom int. Church በተዘጋጀው ፕሮግራም ተገኝታችሁ የእግዚአብሔርን ፀጋ እንድትካፈሉ ተጋብዛችኋል። አድራሻ: ከኢየሩሳሌም አደባባይ ወደ ዋቸሞ በሚወስደው የኮብልስቶን መንገድ 50 ሜትር ገባ ብሎ።

ድል ለነሳው... ንጉሳችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመልአኩ ልኮ ለአገልጋዮቹ በገለጠው ራዕይ በግልጽ እና በተደጋጋሚ እንደምንመለከተው የተስፋ ቃል የተሰጠው ድል ለሚነሱ ባሪያዎች ብቻ ነው--- “መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚናገረውን፣ ጆሮ ያለው ይስማ፤ ድል ለሚነሣ በእግዚአብሔር ገነት ካለው ከሕይወት ዛፍ እንዲበላ አደርገዋለሁ።” — ራእይ 2፥7 (አዲሱ መ.ት) “መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚናገረውን ጆሮ ያለው ይስማ፤ ድል የሚነሣም በሁለተኛው ሞት ከቶ አይጐዳም።” — ራእይ 2፥11 (አዲሱ መ.ት) “መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚናገረውን ጆሮ ያለው ይስማ፤ ድል ለሚነሣ ከተሰወረው መና እሰጠዋለሁ፤ ደግሞም ከሚቀበለው ሰው በስተቀር ማንም የማያውቀውን አዲስ ስም የተጻፈበት ነጭ ድንጋይ እሰጠዋለሁ።” — ራእይ 2፥17 (አዲሱ መ.ት) “ድል ለሚነሣና ሥራዬንም እስከ መጨረሻው ለሚፈጽም በአሕዛብ ላይ ሥልጣን እሰጠዋለሁ፤ እርሱም፦” — ራእይ 2፥26 (አዲሱ መ.ት) “ድል የሚነሣም እንደ እነርሱ ነጭ ልብስ ይለብሳል፤ እኔም በአባቴና በመላእክቱ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ ስሙንም ከሕይወት መጽሐፍ አልደመስስም።” — ራእይ 3፥5 (አዲሱ መ.ት) “ድል የሚነሣውን በአምላኬ ቤተ መቅደስ ውስጥ ዐምድ አደርገዋለሁ፤ ከዚያም ከቶ አይወጣም። የአምላኬን ስምና የአምላኬን ከተማ ስም ይኸውም ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን የአዲሲቱን ኢየሩሳሌም ስም በእርሱ ላይ እጽፋለሁ፤ አዲሱን ስሜንም በእርሱ ላይ እጽፋለሁ።” — ራእይ 3፥12 (አዲሱ መ.ት) “እኔ ድል ነሥቼ ከአባቴ ጋር በእርሱ ዙፋን ላይ እንደ ተቀመጥሁ፣ ድል የሚነሣውንም ከእኔ ጋር በዙፋኔ ላይ እንዲቀመጥ አደርገዋለሁ።” — ራእይ 3፥21 (አዲሱ መ.ት) ተወዳጆች ሆይ ድል መንሳት የግድ ነው፣ የተስፋ ቃል የተሰጠው ድል ለሚነሱ(ለሚያሸንፉ) ብቻ ነው። ልፍስፍስ እና ተሸናፊ መንፈስ ከዘመናችሁ ላይ በኢየሱስ ስም ተነቀለ፣ በዘመናችሁ ሁሉ ታሸንፋላችሁ። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የተስፋ ቃልን ፍጻሜ የሚቀበሉ ድል የሚያደርጉ ናቸው! እግዝአብሔር ከጥንት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ለተለያዩ ሰዎች የተሰፋ ቃል እንደሰጠ ከቅዱሳት መጽሐፍትና ከራሳችን ልምምድ የምንረዳው ነው፣ እግዚአብሔር ተስፋን የሚሰጥ አምላክ ነው፣ ነገር ግን ተስፋ ከተሰጣቸው ሰዎች የተስፋውን ቃል ፍጻሜ የተቀበሉ እንዳሉ ሁሉ የተሰጣቸውን የተስፋ ቃል ፍጻሜ ከመቀበል የዘገዩ እና አንዳንዴም ሰይቀበሉ ዘመናቸው የተፈጸመ ሰዎች አሉ። ይሄንን እውነት ለመረዳት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከሚገኙ ከብዙ ምሳሌዎች ከግብጽ አገር የወጡትን የእስራኤልን ልጆች ታሪክ መመልከት በቂ ነው፥ 430 አመት በባርነት በግብፅ ምድር ከተሰቃዩ በኋላ እግዚአብሔር ከአባቶቸቻው ከአብርሃም፣ ከይስሐቅ እና ከያዕቆብ ጋር ያደረገውን ኪዳን አስቦ በጫንቃቸው ላይ የነበረውን ጠንካራ ቀንበር ሰብሮ ከግብፅ አስወጣቸው፣ የሰጣቸው ተስፋ እንደዚህ የሚል ነበር----“ከግብፃውያንም እጅ አድናቸው ዘንድ፥ ከዚያችም አገር ወተትና ማር ወደምታፈስሰው አገር ወደ ሰፊይቱና ወደ መልካሚቱ አገር --- ስፍራ አወጣቸው ዘንድ ወረድሁ።” — ዘጸአት 3፥8 የተስፋው ቃል "ከግብፃውያን እጅ አድናችኋለሁ፥ ከግብፅም አገር ወተትና ማር ወደምታፈስሰው አገር አስገባችኋለሁ" የሚል ነው፥ ይህ የተስፋ ቃል ለእስራኤል ልጆች ሁሉ የተሰጠ ነው፣ ነገር ግን ከግብፅ አገር ወጥተው ወደ ተስፋይቱ ምድር የደረሱት ሁለቱ አሸናፊዎች ካሌብ እና እያሱ ብቻ ናቸው የቀሩት ከሚሊዮን የሚበልጡ የእስራኤል ልጆች የተስፋን ቃል ቢቀበሉም ፍጻሜውን ግን ሳይቀበሉ በምድረበዳ ቀሩ። ካሌብ እና እያሱ የአሸናፊነት መንፈስ ነበራቸው፣ ከነዓን እንዲሰልሉ ከተላኩት መካከል በመልካም ቃል ተናግረው ድልን የሰበኩት ካሌብ እና እያሱ ነበሩ--- “ካሌብም ሕዝቡን በሙሴ ፊት ዝም አሰኘና፦ ማሸነፍ እንችላለንንና እንውጣ፥ እንውረሰው አለ።”— ዘኍልቁ 13፥30 ----አስሩ ተመልሰው የሽንፈት ወሬ በሕዝብ ጆሮ በማውራት የሕዝቡንም ልብ አስፈሩ “ማኅበሩም ሁሉ ድምፃቸውን አንሥተው ጮኹ፤ ሕዝቡም በዚያ ሌሊት አለቀሱ።”— ዘኍልቁ 14፥1 ---በዚህም ምክንያት የድል ሰባኪዎች እና መሪዎች ከሆኑት ከሁለቱ ሰዎች በስተቀር ጠቅላለው ከግብፅ የወጣው ማኅበር በምድረበዳ ወደቀ፣ ካሌብና እያሱ ግን የተስፋውን ቃል ፍጻሜ ተቀበሉ ----“እርሱም፦ በእውነት እግዚአብሔርን ፈጽመው ከተከተሉ ከእነዚህ ከቄኔዛዊው ከዮፎኔ ልጅ ከካሌብና ከነዌ ልጅ ከኢያሱ በቀር፥ ከግብፅ የወጡት ከሀያ ዓመት ጀምሮ ከዚያም በላይ ያሉት ሰዎች እኔን ፈጽመው አልተከተሉምና ለአብርሃምና ለይስሐቅ ለያዕቆብም እሰጥ ዘንድ የማልሁበትን ምድር አያዩም ብሎ ማለ።” — ዘኍልቁ 32፥11-12 የተስፋ ቃል እንደሰማን ፍጻሜውን እንድንቀበል በእግዚአብሔር በመተማመን የአሸናፊነትን መንፈስ እንታጠቅ፣ እጆቻችንን ውጊያ ጣቶቻችንን ጦርነት እናስተምራቸው፣ እንደርሳለን! እንወርሳለን! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የተስፋን ቃል ፍጻሜ የሚቀበሉ ድል ነሺዎች ብቻ ናቸው! የተስፋ ቃል የተሰጣቸው ከሚሊዮን የሚበልጡ የእስራኤል ልጆች፣ የተስፋውን ቃል ፍጻሜ የተቀበሉ አሸናፊ መንፈስ የነበራቸው ሁለቱ የድል ሰባኪዎች እና የድል መሪዎች ብቻ፣ ከሚሊዮን የሚበልጥ ሕዝብ ከግብፅ ምድር ወጥቶ ከመካከላቸው ከነዓን የገቡት ሁለት ሰዎች ብቻ ናቸው! ተስፋ ፍሬ የሚያፈራው ለድል ነሺዎች ብቻ ነው፣ ከእግዚአብሔር የተስፋ ቃልን የተቀበልን ሁላችንም ተዋግቶ ማሸነፍ የግድ ነው።

ጥብቅ መልእክት ሁላችንም እንደምናውቀው ምድር ላይ የተለያዩ ጦርነቶች ተደርገዋል አሁንም እየተደረጉ ነው የእነዚህ ጦርነቶች ዓላማ የተለያየ ቢሆንም በምድር ላይ ያደረሱት ተጽዕኖ ግልጽ ነው፣ አሁን እየተደረገ ያለው የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት እንኳ በሰፊው ዓለም ላይ የቱን ያህል ጥቁር ጥላውን እንዳጠላ እየተመለከትን ነው፣ ነገር ግን አሁን በቁሳዊው ዓለም ላይ እየተደረጉ ካሉ ጦርነቶች ሁሉ በላይ በምድር ነዋሪዎች ላይ አስከፊ ጉዳት እያደረሰ ያለ ስውር ጦርነት እየተካሄደ ነው፣ የዚህ ጦርነት ዓላማ ምድራዊ ድንበር ማስፋፋት ወይም ታላቅ ሆኖ መታየት አይደለም፣ የዚህ ጦርነት ዓላማ የተቻለውን ያህል ብዙ ነፍሳትን መግዛት እና የራስ ማድረግ ነው። ተወዳጆች ሆይ ምድር ላይ እየተካሄዱ ባሉት ውጥረቶች እና የማሳት ዘመቻዎች ትኩረታችን ተበታትኖ ስለነፍሳችን እየተደረገ ያለውን ጦርነት ዘንግተን የሰይጣን ምርኮኛ መሆን አይገባንም። ስለምን ጦርነት ነው የምናገረው? ወደዚህ ምድር የመጡ ሰዎችን ሁሉ በሕይወታቸው ዘመን የገጠማቸው ጦርነት አለ፣ አብዛኛዎቹ ተሸንፈው ምርኮኛ እንደሆኑም ይመስለኛል፣ ጦርነቱን የሚያደርገው ሰይጣን ነው፣ የሰዎችን ነፍስ አጥብቆ ይፈልጋል ስለዚህ ወደዚህ ምድር በሚመጡ ሰዎች ላይ ሁሉ መንፈሳዊ ጦርነት ይከፍታል፣ ለማጥቃት የሚጠቀመውም መሳሪያ በዋናነት ስጋዊ ምኞት ነው፣ የሰዎችን የራሳቸውን ስጋዊ ምኞት በመጠቀም ነፍሳቸውን ይዋጋል፣ ነፍሳቸው የእርሱ ምርኮኛ እስክትሆን ድርስ ይዋጋል። አሁን እኛ ባለንበት ዘመን ሰይጣን ያለውን ሃይል ሁሉ ቀጥሮ እየተዋጋ በመሆኑ ውጊያው በርትቷል፣ ሰይጣን ያለውን ሁሉ ተጠቅሞ የሰዎችን ነፍስ ለማሸነፍ እና የራሱ ለማድረግ እየተዋጋ ነው፣ ብዙዎችም ተሸንፈው እየወደቁ ነው። ሰይጣን በዚህ ጦርነት አሸናፊ ለመሆን ስጋዊነትን የሚያቀነቅኑ እና የሚያነግሱ ተዋጊዎቹን(በተለያየ መንገድ ለሰይጣን የሚሰሩ ሰዎች) በረዘሙ ተራሮች ላይ አቁሟል፣ በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትምና፣ እነሱን እየተመለከተ ትውልዱ ስጋዊ ምኞቱ ተቀስቅሶ እና ተባብሶ ነፍሱን ይወጋል፣ ወደ ልቡ ተመልሶ የማይነቃ ከሆነ የሰይጣን ንብረት ይሆናል፣ ይሄ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የእናንተ መጨረሻ አይሆንም ዛሬ መንቃት ሆኖላችኋል! ነፍስን ለማሸነፍ እና የራስ ለማድረግ እየተደረገ ያለ ጦርነት አለ፣ ይህንን እውነት በሚገባ መረዳት ጦርነቱን ለመመከት እና መልሶ ለማጥቃት የግዴታ አስፈላጊ ነው። ተወዳጆች ሆይ በዚህ ጦርነት ውስጥ አሸናፊ እንድንሆን የሚያስፈልገንን የጦር ዕቃ ሁሉ ተሰጥቶናል፣ የእኛ ሃላፊነት የሚሆነው የተሰጠንን የጦር ልብስ መልበስና ተዘጋጅቶ መቆም ነው --- “ክፉው ቀን ሲመጣ መቋቋም ትችሉ ዘንድ የእግዚአብሔርን ሙሉ የጦር ዕቃ ልበሱ፤ ሁሉን ከፈጸማችሁ በኋላ ጸንታችሁ መቆም ትችላላችሁና።”— ኤፌሶን 6፥13 ወንድሞቼና እህቶች ዛሬ እንንቃ እጃችንን አጣጥፈን ከተቀመጥን እንሸነፋለን፣ የእግዚአብሔር እቃ ጦር ለብሰን ከተዋጋን ግን እናሸንፋለን፣ ብዙዎችን ማዳን እንድንችል ደግሞ ድምጻችን ከተራሮች ላይ ይሰማ። የእግዚአብሔር ፀጋ ከመንፈሳችሁ ጋር ይሁን። 👇👇👇ለመቀላቀል👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ተወዳጆች!🥰 መጽሐፍ ቅዱስን ከፍታችሁ በጸሎት፣ በዝግታ፣ በተደጋጋሚና በቀጣይነት አንብቡ፥ ቃሉንም በትህትና ተቀበሉ ለመንፈሳችሁ ሃሴት፣ ለነፍሳችን እረፍትና ሰላም፣ ለሰውነታችሁም ፈውስ፣ ለምታደርጉት ነገር ሁሉ ደግሞ መልካም ስኬት ስሆን ታያላችሁ! በልበሙሉነት መናገር የምችለው በዚህ መልኩ መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብና የእግዚአብሔርን ቃል መቀበል ከጀመራችሁ በኋላ ሕይወታችሁ በዘላቂነት መለወጥ ይጀምራል! መርሳት የሌለባችሁ የመጽሐፍ ቅዱስ ባለቤት (Author) መንፈስ ቅዱስ ነው፣ ስለዚህ የእርሱን መሪነትና እርዳታ ሁልጊዜ መጠየቅ፣ የቃሉን ደጆች እንዲከፍትላችሁ መጸለይ የግድ መሆኑን ነው። አንብቡ፣ ተቀበሉ ተለወጡ! 👇👇👇ተቀላቀሉን👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የሮሜ ጥናት -ትምህርት ስምንት ሮሜ 6፥1-11 በቀደመው ምዕራፍ ባስተማረው ትምህርት ምክንያት ምንአልባት ከተቃዋሚዎች ልነሳ የሚችል ጥያቄን በመመለስ እና እንደመነሻ በመጠቀም ሐዋሪያው ጳውሎስ ስምንተኛውን ትምህርት ያስተምራል። ሐዋሪያው በቀደመው ምዕራፍ አስተምሮት የነበረው እውነት እንደዚህ የሚል ነው: “... ነገር ግን ኀጢአት በበዛበት ጸጋ አብልጦ የተትረፈረፈ ሆነ፤”— ሮሜ 5፥20 ከዚህ ትምህርቱ ተነስተው ተቃዋሚዎች "ኃጢአት በበዛበት የእግዚአብሔር ፀጋ ተትረፍርፎ የሚገለጥ ከሆነ፣ ብዙ ፀጋ ለማግኘት ኃጢአት እያደረግን መጽናት አለብን ማለት ነው" የሚል የተቃውሞ ሐሳብ እንደሚያነሱ በማሰብ፣ ከእነርሱ ቀድሞ በጽሑፉ ጥያቄውን እራሱ በማንሳት መልስ ይሰጥበታል፣ ይህም መልሱ ስምንተኛው ትምህርት ነው። ከተቃዋሚዎች ወይም "ኃጢአት በበዛበት ፀጋ ተትረፍርፎ በዛ" የሚለውን የቀደመውን ትምህርት በተሳሳተ መንገድ ከተረዱ ሰዎች ልመጣ የሚችለው ጥያቄ ይሄ ነው: “ጸጋ እንዲበዛ ኀጢአት እየሠራን እንኑር?”— ሮሜ 6፥1 ለዚህ ጥያቄ የተሰጠው መልስ “ከቶ አይሆንም፤ ለኀጢአት ሞተናል፤ ታዲያ እንዴት አድርገን ከእንግዲህ በእርሱ እንኖራለን?” — ሮሜ 6፥2 በግልጽ እንደምናነበው መልሱ የእግዚአብሔርን ፀጋ ስንቀበል "ለኃጢአት ሞተናል" የሚል ነው። ለኃጢአት የሞተ ሰው እንዴት አድርጎ ለሞተለት ነገር መኖር ይችላል? በፍጹም አይችልም። ስለዚህ ፀጋ እንዲበዛ ኃጢአትን ማድረግ መቀጠል አለብን ብለው የሚያስቡ ሰዎች የእግዚአብሔር ፀጋ እንዴት እንደሚሰራ ያልተረዱ ሰዎች ናቸው፣ መጽሐፍ ቅዱስ ሰዎችን ለማዳን የተገለጠውን የእግዚአብሔር ፀጋ ኃጢአተኝነትን እና ዓለማዊ ምኞትን የሚያስክድ፣ በተጨማሪም ጌታን መጠበቅን፣ እራስን መግዛትን፣ በጽድቅ መኖርን እና እግዚአብሔርን መምሰልን የሚያስተምር እንደሆነ ይነግረናል: ቲቶ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹¹ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ¹²-¹³ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል። ስለዚህ ኃጢአትን እያበዛ ከእግዚአብሔር ፀጋ የሚቀበል የሚመስለው ሰው እራሱን እያሳተ ነው፣ የእግዚአብሔርን ፀጋ መቀበል የሚቻለው ለኃጢአት በመሞት ነው። በክርስቶስ ኢየሱስ የሆንን ለኃጢአት ሞተናል! 👇👇👇ተቀላቀሉ👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ጥያቄ ለተወደዳችሁ የቻናሌ ተከታታዮች🥰 ከኢየሱስ #ጋር መሞት፣ መቀበር እና ከሙታን መነሳት ማለት ምን ማለት ነው? እንዴትስ ነው የሚቻለው? ምክንያቱም ኢየሱስ የሞተው ከሁለት ሚሌኒየም ወይም ከሁለት ሺ ዓመት በፊት ነው እኛ ደግሞ ያለነው አሁን ነው፣ እንዴት ነው ይህ የሚሆነው? መልሳችሁን comment ውስጥ አስቀምጡ፣ አመሰግናለሁ!

አዲሱን ሰው ልበሱ! የሰው ልጅ ችግሮች ሁሉ በዋናነት እና በቀዳሚነት አመጸኛ ከሆነ ከራሱ ማንነት የሚመነጩ የማንነቱ ወሬዎች እንጂ ውጫዊ ሃይላት የሚጥሉበት ሸክሞች አይደሉም። ሰው እግዚአብሔርን ለመታዘዝ እምቢ በማለቱ ቅጥር እንደሌላትና እሳት ከውስጧ ወጥቶ እራሷን እንደሚበላት ከተማ ነው የሆነው፣ ከውስጥም ከውጭም ጥፋት ብቻ ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት የሌለው ሰው ቅጥር እንደሌለው ከተማ ነው የተወረወረ ቀስት ሁሉ እየወጋ ይጎዳዋል፣ ይገድለዋልም ይሄ ብቻ አይደለም ከውስጡ እሳት እየተነሳ እራሱን እንደሚበላውም ነው። ከሁለቱ የከፋው ግን ከውስጥ የሚነሳው እሳት ነው፥ ሰይጣን ወይም ክፉው ዓለም ከሚወረዉሩት ቀስት በላይ የሰው ልጅ ትልቁ ችግር የራሱ አመጸኛ ማንነት ነው ኃጢአተኛ ተፈጥሮው ነው። እግዚአብሔር ሰይጣንን አልገደለውም እውነት ነው ለፍርድ ቀን ተጠብቋል ነገር ግን አሮጌውን ሰው በመስቀል ላይ ገድሎታል፥ አሮጌው ሰው አመጸኛ ነው ለእግዚአብሔር የማይገዛ ነው፣ አሮጌውን ሰዋችሁን ለማሻሻል አትሞክሩ አንድ መፍትሔ ብቻ ነው ያለው ይህም መግደል ነው። በእግዚአብሔር ቃል እና በኢየሱስ ክርስቶስ ምስክርት ምክንያት ከደረሰባችሁ ችግር ወጭ ለደረሰባችሁ ለየትኛውም ችግር ሰውንም ሰይጣንንም ተጠያቂ አታድርጉ አሮጌ ሰዋችሁ ነው ተጠያቂ ስለዚህ አሮጌውን ሰው አውልቃችሁ በመጣል በክርስቶስ ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ፥ ይሄንን ከደረጋችሁ ውጫዊ ሃይላት፣ የጨለማ ሃይላት ሁሉ ከእግራችሁ በታች ተጥለዋል፣ ቀና ብለው እንኳ አይመለከቷችሁም!😁 “እነሆ፥ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ፥ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ፥ የሚጐዳችሁም ምንም የለም።” — ሉቃስ 10፥19 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ለሰው ልጅ ችግሮች ሁሉ ዘላቂ መፍትሔ እንዴት ይገኛል? የሰው ልጅ መንፈሳዊ፣ ነፍሳዊ፣ አካላዊ፣ ቁሳዊ እና ሌሎችም አያሌ ችግሮች ያሉበት በመጨረሻም ሞት በሚባል በማይቋቋማው ጠላት ተወግቶ የሚወድቅ ምስኪን ፍጡር ሆናል። የምንኖርበት ቁሳዊ ዓለም እንኳ እሾህና አሜኬላ እንድታበቅል የተረገመች ምድር ናት፥ ይሄ የሆነው በሰው አመጸኝነት(ኃጢአት) ምክንያት ነው። የሕዝበ እስራኤል አበው ከነበሩት አንዱ ያዕቆብ ከቤተ-ሰዎቹ ጋር ወደ ግብጽ በወረደ ጊዜ ፈርዖን፣ “ለመሆኑ ዕድሜህ ምን ያህል ነው?” ሲል ጠየቀው፣ ያዕቆብ የሰጠው ምላሽ የሰው ልጆች ሁሉ ድምፅ ይመስላል እንደዚህ ነበር የመለሰለት:-“በምድር ላይ በእንግድነት ያሳለፍኩት ዘመን 130 ዓመት ነው፤ ይህም አባቶቼ በእንግድነት ከኖሩበት ዘመን ጋር ሲነጻጸር አጭር ነው፤ ችግር የበዛበትም ነበር” ሲል መለሰለት።” — ዘፍጥረት 47፥9 "አጭር ነው፤ ችግር የበዛበትም ነበር" በመጀመሪያ በእግዚአብሔር መልክና ምሳሌ ኢሟት ሆኖ ለገዥነት የተፈጠረው ሰው ምስክርነቱ ይሄ ስሆን ማየት የሚያሳዝን ነው፥ ኃጢአት ክፉ በሽታ ነው። እውነት ነው ኃጢአት ወደ ዓለም ባይገባ ኖር ምድር አሁን ከነበረችው ሁኔታ ሚልዮን ጊዜ የተሻለች ትሆን ነበር፣ የሰው ልጅ አሁን ከለበት ሁኔታ ፈጽሞ የተለየ ይሆን ነበር። ኃጢአት አሁን በዓለም አለ በዚህም ምክንያት እጅግ ብዙ ችግሮች በዓለም አሉ ከሁሉም የሚበረታው ችግር ሞት ነው። የመጀመሪያዎቹ ሰዎች አዳምና ሔዋን እርቃናቸውን ለመሸፈን የቅጠል ልብስ እንዳዘጋጁ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ሰዎች ከውጭ ለሚታዩት ችግሮቻቸው መፍትሔ ለማበጀት ስፍጨረጨሩ ማየት የተለመደ ነው፣ መፍትሔው ዘላቂ አይሆንም እንጂ ጊዜያዊ መፍትሔ ማግኘት የተለመደ ነው፣ የሰው ልጅ ላሉበት መንፈሳዊ፣ አእምሮአዊ፣ አካላዊ እና ቁሳዊ ችግሮች መፍትሔ ለማበጀት ስደክም ነው የኖረው፥ ሕይወት እረሱ ችግር የመፍታት ጉዳይ እስኪመስል ሁሉም የሚሯሯጠው ለችግሩ መፍትሔ ለማበጀት ነው፥ ነገር ግን በመጀመሪያም ቢሆን አዳምና ሔዋን እርቃናቸውን ለመሸፈን ያዘጋጁት ቅጠል ዘላቂ መፍትሔ ባለመሆኑ እንስሳ አርዶ ቆዳውን እንደልብስ አዘጋጅቶ ያለበሳቸውና እርቃናቸውን የሸፈነው እግዚአብሔር እራሱ ነበር። ስለዚህ ለሰው ልጅ ችግሮች ሁሉ መፍትሔ የሚሰጠው እግዚአብሔር እራሱ ነው፥ ይህንን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል አድርጎታል። ሰዎች በጊዜ ሂደት ለአካላዊ እና ለቁሳዊ ችግሮቻቸው ዘላቂም ባይሆን መፍትሔ ማበጀት ላይ በጣም የተካኑ ሆነዋል፣ የተለያዩ በሽታዎችን ማከም እና በቁሳዊ ነገሮች ተከቦ መኖር የተለመደ ሆኖል፣ ነገር ግን ሰዎች ማከም የተሳናቸው ነፍሳዊ እና መንፈሳዊ ችግሮቻቸውን ነው፣ ይልቅ እነዚህ ችግሮች እየባሱ እየሄዱ ነው። እነዚህን መንፈሳዊ እና የነፍስ ችግሮች ሰይፈቱ አካላዊና ቁሳዊ ችግሮች መፈታታቸው በራሱ ትልቅ ችግር ነው፥ በመርዝ የተሞላን ብርጭቆ እላይ እንደማጽዳት ነው፥ የሚያገኘው ሁሉ እላዩ ተፀድቶ ሲያይ ንጹሕ ውሃ መስሎት ይጠጣዋል። ኢየሱስ ፈሪሳዊያኑን አጥብቆ ይገስጽ የነበረውም በዚህ ምክንያት ነው፥ የራሳቸውንም ሆነ የተከታዮቻቸውን ውጫዊ መልክ ማሳመር ላይ የተጠመዱ፣ በውስጣቸው ግን በክፋት የተሞሉ ነበሩ። ይሄ በምድር ላይ ያሉ ኃይማኖቶች ሁሉ ችግር ነው፥ ሰዎች በውጫዊ ስርአቶች እና ልምምዶች የውስጥ ችግራቸውን እንዲረሱ ማድረግ። በውሃ በመንጻት፣ በአለባበስ፣ በአመጋገብ፣ በአምልኮ ስርዓት፣ በአንደበት በሚነገሩ ከንቱ ቃላት በልብ ያለን ክፋት መሸፈን፣ በነፍስ ያለን አመጽና ኃጢአት መደበቅ ትልቁ የኃይማኖቶች ችግር ነው። እግዚአብሔር በኢየሱስ በኩል የሰጠን መፍትሔ ግን የዛፉን ቅርንጫፎች ሳይሆን ስር የሚቆርጥ ነው። ለሰው ልጅ ውጫዊ ችግሮች አሁናዊ መፍትሔ በመስጠት የችግሮች ሁሉ ምንጭ የሆነውን መንፈሳዊ ችግር የሚተው አይደለም ወይም በስርዓቶች እና ሕጎች የሸክላውን ወጭ አፅድቶ በውስጥ ያለውን መርዝ የሚተው አይደለም። የኢየሱስ ክርስቶስ መልእክት ስሩን የሚቆርጥ እና የብርጭቆውን ውስጥ የሚያጸዳ ነው። መጥምቁ ዮሐንስ ስለኢየሱስ እና ስለ መልእክቱ ምን እንዳለ እንመልከት: “እነሆ፤ ምሣር የዛፎችን ሥር ሊቈርጥ ተዘጋጅቶአል፤ መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ሁሉ ይቈረጣል፤ ወደ እሳትም ይጣላል።” — ማቴዎስ 3፥10 ምሣሩ የዛፎችን ቅርንጫፍ አይደለም የዛፎችን ሥር ለመቁረጥ ነው የተዘጋጀው። ይሄ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ የሰዎችን ችግር ከምንጭ ለማከም ነው የመጣው ማለት ነው። ዘመኑ "አጭር እና ችግሮች የበዙበት" የሰው ልጅ ከችግሮቹ ሁሉ ነጻ የሚወጣው እና ኢ-ሟት የሚሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ኢየሱስን፣ ያደረገውንና ያስተማረውን ለማወቅ መትጋት ዋጋ ያለው አይመስላችሁም? የእግዚአብሔር ፀጋ ይብዛላችሁ! @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

እግዚአብሔር በአመጽ ላይ ምንድነው የሚያደርገው? ኢየሱስ መስቀል ላይ ምን ይመስል ነበር? ኢሳይያስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ ደግሞስ ዓመፃ እየጨመራችሁ ለምን ገና ትቀሠፋላችሁ? ራስ ሁሉ ለሕመም ልብም ሁሉ ለድካም ሆኖአል። ⁶ ከእግር ጫማ አንስቶ እስከ ራስ ድረስ ጤና የለውም፤ ቍስልና እበጥ የሚመግልም ነው፤ አልፈረጠም፥ አልተጠገነም፥ በዘይትም አልለዘበም። ከላይ ያለው የመጽሐፍ ክፍል እግዚአብሔር በአመጽ ላይ ምን እንደሚያደርግ ወይም ዓመፅን እንዴት እንደሚቀጣ በግልጽ የሚያሳይ ነው። ይህ ክፍል ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ምን ይመስል እንደነበረ የሚያሳይ ትንቢታዊ ምስልም ነው፥ ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ በኃጢአት ምክንያት የእግዚአብሔር ክብር ለጎደለው አመጸኛ ሰው ነው መከራን ተቀብሎ በመስቀል የሞተው። በመጽሐፉ ክፍል መሰረት እግዚአብሔር ዓመፅን የሚቀጣው እንዴት ነው? 👉ራስ ሁሉ ለሕመም፣ 👉ልብም ሁሉ ለድካም ሆኖአል፣ 👉ከእግር ጫማ አንስቶ እስከ ራስ ድረስ ጤና የለውም፣ 👉ቍስልና እበጥ የሚመግልም ነው፣ አልፈረጠም፥ አልተጠገነም፥ በዘይትም አልለዘበም። ይህ በግልጽ በእኔ በዓመፀኛው ምትክ በመስቀል ላይ የተንጠለጠለውን የናዝሬቱን ኢየሱስ የሚያሳይ ምስል ነው!😭 ገና በጌቴሴማኒ እያለ ነበር አእምሮው በጭንቀት ተወጥሮ የደም ላብ ያለበው ከዚያም ተይዞ በራሱ ላይ የእሾህ ጉንጉን ተድርጎለታል፣ ደጋግመው ጭንቅላቱን በበትር ደብድበው ክፉኛ አቁስለውታል፣ አዳኜ የእኔን የአመጽ ዋጋ እየከፈለ ራሱ ታሟል፥ ልቡ በስቃይ ደክሟል፥ ከእግሩ ጀምሮ እስከ ራሱ ድረስ ጨካኞቹ የሮማ ወታደሮች በበትር እና አጥንት ተጨምሮ በተሰሩ ጅራፎቻቸው ስጋው ተበጣጥሶ አጥንቱ እስኪገለጥ ድረስ ገርፈውት ስለነበር አንድም ጤነኛ የሰውነት ክፍል አልነበረውም!😭 ቁስል ብቻ ነበር፣ እብጠት ብቻ ነበር😭 ፈጽሞ የማይፈወስ ይመስል ነበር፥ ወዳጄ ስለ እኔ አመጽ ፊቱ እና መልኩ ሰው እስከማይመስል ድረስ ተጎሳቁሎ እና ቅርጹን አጥቶ ነበር። /ኢሳይያስ 52:14/ አመጸኛው በርባን እኔ ነበርኩ፣ መስቀሉም በትክክል ለእኔ የተሰራ ነበር፣ ነገር ግን በማላውቀው መንገድ እኔ ተፈታሁ፣ ነገሮች ድንገት ተቀያየሩ በእኔም ምትክ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆነ😭 /ማርቆስ 15:7/ ኢየሱስ በእኔ በዓመፀኛው ምትክ ዋጋ ከፍሎ እንጂ እግዚአብሔር እንዲያው ሰላምን አድርጎ አይደለም። “እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።” — ኢሳይያስ 53፥6 ኢየሱስ ያድናል! 👇👇👇ተቀላቀሉ👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ፍርድና ምህረት- እግዚአብሔር ጻድቅ ነው! አሮጌው ሰው መለወጥ ወይም ማሻሻል በጭራሽ በማይቻል መልኩ አመጸኛ ነው፣ በዚህ ምክንያት እግዚአብሔር ከአሮጌው ሰው ጋር ሰላምን አላደረገም ስለዚህ በአሮጌው ሰው ላይ የሞት ፍርድ በመፍረድ ጽድቁን ገልጧል፥ ነገር ግን ለእኛ ለምናምን እግዚአብሔር ምህረቱን የተገለጠው በሁላችንም ምትክ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሲሞት እና አሮጌው ሰዋችን በኢየሱስ ስሞት ነው። አባት ሆይ ተመስገን ከማለት ሌላ ምን ይባላል!? The old man is incorrigibly rebel and God didn't make peace with him, but executed him to death and revealed his own righteousness, but Gods mercy for us who believe is that the execution took place on Jesus and the old man was executed in him. What can we say, but thank you father!🙏 👇👇👇Join us 👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

“እውነትን ግዛ አትሽጣትም፥ ጥበብን ተግሣጽን ማስተዋልንም።” — ምሳሌ 23፥23 “Buy the truth, and sell it not; also wisdom, and instruction, and understanding.” — Proverbs 23፥23 (KJV)

ከኃጢአት ነጻ ለመውጣት ከየትኛውም አይነት የኃጢአት ልምምድ ነጻ ለመውጣት ቁልፉ መሞት ነው። በሰዎች ውስጥ ያለው አሮጌው ሰው ( በመወለድ ከመጀመሪያው አዳም የወረስነው የኃጢአት ሰውነት ) ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር በእምነት ተሰቅሎ ካልሞተ፣ ቤተክርስቲያን የምንመላለስ፣ ምን አልባትም የምንጸልይ እና የተለያዩ ኃይማኖታዊ ስርዓቶችን የምናደርግ ነገር ግን ለኃጢአት የምንገዛ ምስኪን ሰዎች እንሆናለን። ለምሳሌ የሥጋ ሥራዎች:- ዝሙት፥ ርኵሰት፥ መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥ መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስሉ ሌሎች ስራዎችን እያንዳንዱን አንድ በአንድ ለመታገል መሞከር አድካሚ ስህተት ነው፣ ዓሳዎቹን ለማጥፋት ባሕሩን ማድረቅ እንደሚባለው፣ ከእነዚህ የስጋ ስራዎች ፈጽሞ ነጻ ለመሆን ከስጋ (ከኃጢአተኛ ተፈጥሮ) ነጻ መውጣት የግድ ነው። ከላይ የተዘረዘሩት ክፉ ስራዎች ሁሉ ስጋ የሚባል በሰዎች ውስጥ ያለ ክፉ ሰራተኛ የሚሰራቸው ናቸው፥ ሰራተኛውን ሳናስወግድ ክፉ ስራዎቹን አንድ በአንድ ለማጥፋት መሞከር ትርፉ ድካም ነው። ሰራተኛውን አስወግዱት ስራዎቹን ሁሉ ማስወገድ ቀላል ይሆናል፣ ከሰራተኛው ጋር ተጣሉ ስራዎቹን ሁሉ ትጸየፋላችሁ፣ በውስጣችሁ ያለውን አሮጌውን ሰው በእምነት በኢየሱስ መስቀል ግደሉት በዚህ ጊዜ ምንጩ ይደርቃል ዓሳዎቹም በራሳቸው አንድ በአንድ ይሞታሉ። ከየትኛውም አይነት የኃጢአት ልምምድ ለዘላለም ነጻ መውጣት የሚቻልበት መንገድ ከኢየሱስ ጋር መሞት ነው። “...የሞተ ከኀጢአት ነጻ ወጥቶአል።” — ሮሜ 6፥7 (አዲሱ መ.ት) 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

Death to self is the primary requirement of the Christian faith. ኢየሱስ ክርስቶስን መከተል የሚጠይቀው የመጀመሪያው ነገር ለራስ መሞት ነው።