ch
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

前往频道在 Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

显示更多
1 810
订阅者
无数据24 小时
无数据7
无数据30
帖子存档
ቤተክርስቲያን አማኞችን ስለቁሳዊ በለጠግናት ማስተማር አለባት? ይሄ ጥያቄ በአማኞች መካከል በጣም አከራካሪ እና ከፋፋይ ከሆነ ቆይቶል! አንዳንድ ወገኖች ቁሳዊ ብልጥግና ወይም ገንዘብ ነክ ነገሮች ፈጽሞ ቤተ-ክርስትያን ውስጥ ማስተማር አይገባም፥ ይሄንን የሚሰብኩ እና የሚያስተምሩ የራሳቸውን ኪስ የመሙላት አጀንዳ ብቻ ያላቸዉ ወንበዴዎች እንጂ ለቅዱሳንም ሆነ ለእግዝአብሔር ልብ የሌላቸዉ በበግ ለምድ ያሉ ተኩላዎች ናቸዉ የሚል ሃሳብ ይሰነዝራሉ። በሌላ ወገን ያሉ ወገኖች ደግሞ ቁሳዊ ብልጥግና እና ገንዘብ ነክ ነገሮች ቤተ-ክርስትያን ዉስጥ መሰበክ አለባቸዉ፥ "Health እና wealth" እግዚኣብሔር ለሕዝቡ ያለው ሃሳብ ነው ስሉ ይደመጣሉ፥ ከዚህም አልፈዉ ወንጌልን "የብልጽግና ወንጌል" የሚል መጠሪያ ሁሉ ሰጥተውት ይደመጣሉ። ይሄ ሁሉም የሚያዉቀው ነዉ ስለዚህ ስለሁለቱ የሃሳብ ክፍሎች ብዙ ማለት አይጠበቅብኝም። እኔ የሁለቱንም የሃሳብ ክፍሎች ደጋፊም ተቺሚ ከመሆናችን በፊት መጽሐፉ ምን ይላል? ብለን መጠየቅ እንውደድ እላለሁ፥ የተሰበክነዉን ሁሉ "አሜን" ብለን ከመቀበላችን በፊት እንደ ቤሪያ ሰዎች የእግዚአብሔር ቃል ምን ይላል? እንደተሰበክነዉ ነውን? ብለን መመርመር እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ ማመን ይገባናል። ትምህርቴን ከመጀመሬ በፊት አንዳንድ እውነታዎችን ልግለጽ፥ በእነዚህ ላይ እንደ እግዚኣብሔር ቃል የሚሞግተኝ ካለ ተዘጋጅቻለሁ። 1-የእግዚአብሔር ወንጌል እንጂ የብልጽግና ወንጌል የሚባል መጽሐፍ ቅዱስ ዉስጥ የለም። የብልጽግና ወንጌል የሚለዉ ሃሳብ የእግዚአብሔር ጥበብ አይደለም የምድር ነዉ፣ የስጋ ነዉ የአጋንንትም ነዉ። 2-ገንዘብ በፍጹም የኃጢአት ስር አይደለም፥ ገንዘብን መዉደድ እንጂ። በሁለቱ መካከል ያለውን ልዩነት ሕጻን ራሱ የሚረዳዉ ነዉ። 3-ድህነት የትህትናም ሆነ የመንፈሳዊነት ምልክት አይደለም። 4-መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ቁሳዊ ብልጽግናም ወይም ስለ ገንዘብ ያስተምራል፥ ይሄ ማለት እግዚኣብሔር የቅዱሳንን ገንዘብ (ቁሳዊ ብልጥግና) በተመለከተ ግልጽ እቅድ ወይም ሃሳብ አለው ማለት ነዉ። 5-ስለቁሳዊ ብልጽግና መጽሐፍ ቅዱስ የሚለዉን ሁሉ ቤተ-ክርስትያን ለቅዱሳን የማስተማር ሃላፊነት አለባት። @TheDeepThingsOfGod

ይሄንን ጥያቄ አስመልክት ብዙ ወንድምና እህቶች በአስተያየት መስጫ ሰጥንም በዉስጥ መስመርም ያለችሁን ሃሳብ ስለገለጻችሁ አመሰግናለሁ። እንደዚህ አይነት ዉይይቶች እጅግ አስፈላጊ እንደሆኑ አምናለሁ፥ መቼም እኛ ዉስጥ በአንድም መንገድ በሌላ መንፈሳዊ አገልግሎት እየሰጠ ያሉ እና ወደፊት ደግሞ በመንፈሳዊው እና በሌሎች ዘርፎች የኢትዮጵያ በተለይም የበተክርስቲያን መሪዎች የሚሆኑ በዚህ እንዳሉ አምናለሁ፤ በዚህም ምክንያት ነዉ እንደዝህ ያሉ ሃሳቦችን እያነሳን እንድንወያይ ያሰብኩት። በውይይት፣ ሃሳብ በመለዋወጥ እና ሃሳብ ከመጽሐፍ ቅዱስ የተለየ ሆኖ ስገኝ በፍቅር ለማቅናት በትህትና ለመቅናት በለመ መንፈስ በመሞገት ፍጹም የሆነውን የእግዝአብሔር እዉነት መያዝ ይቻላል። በዚህ ዙሪያ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል የሚለውን እኔም የተረዳሁትን አቀርባለሁ የእኔን ትምህርት በእውቀት ስገልጥ ከእግዝአብሔር ቃል ጋር በጥበብ አስተያይታችሁ እንጅ እሱ አለ ብላችሁ እንድትቀበሉ አልወድም። " ማንም የሚናገር እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር" ይላልና ቃሉ የሚሰማም በእግዚአብሔር ቃል መስማት ይገባዋል። @TheDeepThingsOfGod

ሌላ መልስ👇 በትንሹ ለ20 አመታት በአፍሪካ prosperity gospel ተሰብኳል ነገር ግን ከነቢያት እና ከፓስተሮች ውጪ ለተቀረው ህዝብ ያመጣው ለውጥ የለም ። ይልቁን በኢየሱስ ስም ሲነገድ አየን እንጂ @Dagmawi111 አልዋሽም መልስህን ሳይ በጣም ነው የሳኩት 😂 አመሰግናለሁ ሃሳብህን ስለገለጽክ! ሌሎች ወንድምና እህቶች ምንድነዉ የምትሉት? እንወያይ!

የተሰጡት መልሶች የእኔ አይደሉም❗️እዚህ የምለጥፋቸው ሌሎች ወንድምና እህቶች ያላቸውን አስተሳሳብ እንድትመለከቱ እና የእናንተንም እንድታጋሩ ነው። እንወያይ!

ሌላ መልስ 👇 ብልፅግና የሁል ጊዜ ስብከት ሊሆን ይገባል ማለትም ለመበልፀግ የዚች አለም መርህ እና የእግዚአብሔር አለም መርህ እጅግ ይለያል ስለዚህ የእግዚአብሔርን መርህ ለመበልፀግ እና ጤናማ ለመሆን ምን እንደሆነ ማስተማር ተገቢ ነው። መዳናችንን ወይም የክርስቶስን መስቀል ስራ ከሲዖል ከማምለጥ ጋር ብቻ አላያይዘውም ይልቁንስ ሰውን ጨቁኖ ከያዙት ከድህነት ከበሽታ እና ከሞት ከማምለጥ ጋር እንጅ prosperity “የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።” — 2ኛ ቆሮ 8፥9 Devine health “እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።” — ኢሳይያስ 53፥5 ስለዚህ በተለይ እንደ አፍሪካ ብልፅግና መሰበክ ከልክ በላይ ያስፈልገናል ቤተክሪስቲያን ስትበለፅግ ወንጌል ይሮጣል ፣አገልጋዮች አይቸገሩም፣አማኞች አይቸገሩም የመጨረሻም ደግሞ መፅሀፍ እንዲህ ይላል “የመንፈስን ተስፋ በእምነት እንድንቀበል፥ የአብርሃም በረከት ወደ አሕዛብ በኢየሱስ ክርስቶስ ይደርስላቸው ዘንድ።” — ገላትያ 3፥14 የአብርሃም በረከት ደግሞ ምንድነው ብለን ስንመለከት እየባረክሁ እባርክሀለው ** በዚህ ላይ ምንድነው ያላችሁ አስተያየት?

ከወንድም የተሰጠ መልስ 👇 የእግዚአብሔር ቃል" በመጀመሪያ የእግዚአብሔርን መንግስትና ፅድቁን ፈልጉ ሌላው ሁሉ ይጨመሪላችኋል"ይላል። ከዝህ የምንረዳው ቤተ ክርስትያን አማኞች አይናቸውን በጌታ ላይ ተክለው እንድጓዙ ማስተማር ተልዕኮዋ እንደሆነ ነው። ገንዘብና ምድራዊ ሀብት ተልዕኮዋን ለሳተች ቤተ/ን ዋነኛና ቀዳሚ የስብከት ርዕሷ ነው። በዚህ ወቅት ምድራዊ ሀብትን ማካበት የስኬት ሁሉ ጥግ አድርገን እንድናስብ የምያደርጉን ትምህርቶች ተበራክተዋል፥ ይህ ግን መፅሀፍ ቅዱሳዊ አይደለም። የእግዚአብሔርን ሀሳብ በመሰጠት የምናገለግል ከሆነ ከምያስፈልጉን ነገሮች አንድም አይጎድልብንም። እውነተኛ ድህነት ጌታን አለማወቅ ነው!! እውነተኛ ድህነት ራዕይ ኣልባነት ነው!!

ቤተ-ክርስትያን አማኞችን ስለ ቁሳዊ በለጠግነትም ማስተማር አለባት?
Anonymous voting

የሰይጣን ዋና ዋና ዓላማዎች ሁለት ናቸው የመጀመሪያው የሰው ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስን ወደማወቅ እንዳይመጣ መከልከል ነው፥ ይህንንም የምያደርግበት ዋነኛ መንገድ የሰዎችን አሳብ ማሳወር ነው። ሁለተኛው የሰይጣን ዓላማ ኢየሱስ ክርስቶስን ያወቁ ሰዎችን ያነጣጠረ ነው ይህም እግዚኣብሄርን እና እግዚኣብሄር ያዘጋጀላቸዉን መልካም ስራ እንዳይሰሩ ወይም እንዳያገለግሉ የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም ማስቆም ነው፥ ከእነዚህ መንገዶች የተወሰኑትን ልጥቀስ ክስ (ኩነኔ)፣ መንፈሳዊ ዉጊያ እና ፈተናዎች (የአይን አምሮት፣ የስጋ ምኞት እና የሕ?ስለገንዘብ መመካት) እነዚህን በመጠቀም ሰዎች የእግዚአብሔር ሃሳብ አገልጋዮች እንዳይሆኑ ማስቆም ነው። በመጨረሻም በመስረቅ፣ በማጥፋት እና በመግደል ስራውን የመፈጸም እቅድ ነው ያለው። አንተን/አንቺን በየትኛው መንገድ እየተዋጋ ይሆን? ጦርነት ዉስጥ ነዉ ያለነው ማለቴ ነው ነቃ ነቃ እንበል ተዘጋጅተን ድል እንንሳ። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ይህ የሮሜ መልእክት በአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ውስጥ የመሪውን ስፍራ የያዘ ነው እናም በእውነት ንጽሕ ወንጌል ነዉ። አማኞች በልባቸው ቃል በቃል ልያዉቁት ብቻ ሰይሆን እንደ እለት እንጀራቸዉ በየቀኑ በመልእክቱ መጠመድ ይገባቸዋል። የሮሜን መልእክት ከበቂ በለይ አነበብነው ወይም ጨርሰን ተረዳነው ማለት አንችልም፥ ምክንያቱም የበለጠ ስናውቀው የበለጠ ውድ እና ጣፋጭ እየሆነ ይሄዳል። -ማርቲን ሉተር በአእምሮአችሁ መጽሐፍ ቅዱስን እንደ አንድ ታላቅ ዛፍ በዉስጡ ያሉ ቃላትንም በዛፉ ለይ እንዳሉ ቅርንጫፎች ስላችሁ አስቡት፥ እኔ እያንዳንዱን ቅርንጫፍ በእጆቼ እየያዝኩ አነቃንቄዋለው ምክንያቱም ምን እንደሆነ እና ምን እያለ እንደሆነ የማወቅ ታለቅ ፍላጎት ነበረኝ። -ማርቲን ሉተር የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ መቼም ቤተ-ክርስትያን ውስጥ በተለይም ወጣቱ የቤተክርስትያን ክፍል አከባቢ ተሃድሶ እና ሪቫይቫል የሚሉት ቃላት መሰማት ከጀመሩ መቆየታቸውን ሁላችንም የምናውቀው ነው፥ እኔም እራሴ ይሄንኑ እንድመለከት የምጸልይ እና የምናፍቅ ነኝ፤ ነገር ግን ተሃድሶም ሆነ ሪቫይቫል የምንናፍቅ ሁላችን በለፈው ዘመን የተሃድሶ መሪዎች የነበሩትን አባቶች አካሄድ በማስተዋል መመልከት ይኖርብናል ብዬ አምናለሁ። እነዚያ መሪዎች "መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ" የሚሉ ነበሩ፥ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ የእግዚአብሔር ቃል ነው ስለዚህ ይነበብ፣ ይጠና፣ ይኑር፣ ይሰበክ... ቤተ-ክርስትያን ውስጥ ሁሉም አስተሳሳብ፣ ሁሉም ንግግር፣ ሁሉም ድርጊት እና ልምምድ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ሙሉበሙሉ የተስማማ መሆን አለበት፥ ሁሉም ሰው ደግሞ ከመጽሐፍ ቅዱስ ስልጣን በታች መሆን አለበት የሚል ጽኑ እምነት የነበራቸው ነበሩ። ዛሬም ይሄው "መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ" የሚለው እውነት በሕይወታችን፣ በአጥቢያ ቤተ-ክርስትያናችን፣ በመሕበረሰባችን ሁሉ መካከል ተሃድሶን እና ሪቫይቫልን የማምጣት ሃይል እንደለው አምናለሁ። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ተወዳጆች ሆይ ይሄንን መልእክን ከነበባችሁ በኃለ ሁለችሁም ለለችሁበት ግሩፕ ሁሉ አጋሩ ለወደጆቻችሁም አጋሩ፥ ፀጋም ተትረፍርፎ ይበዛላችኃል። እወዳችኃለው።

የሮሜ መልእክት ታላቅነት ሐዋሪያው ቅዱስ ጳዉሎስ የጻፈው የሮሜ መልእክት በሰው ልጅ ታሪክ ከተጻፉ የስነ-ጽሑፍ ስራዎች ሁሉ በላይ በማያሻማ መልኩ እጅግ ታለቅ እና አመክንዮአዊ፥ በጠቀሜታውም ሆነ በተጽእኖው ሃያል ነው። የፍልስፍና ሰው እና በኃላም የስነ-መለኮት አስተማሪ የሆነው በአስገራሚ የጽሑፉ ስራዎቹ በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ በጉልህ ስሙ የሚነሳው ኦገስቲን/ Augustine / በመጀመሪያ ራሱን እጅግ በጣም ምጡቅ የፍልስፍና ሰው አድርጎ የለየ ብሆንም ዓለምን እና በዓለም ያለውን አብዝታ የምትወድ ነፍስ እንደነበረችው እና እጅግ ልቅ በሆነ የዝሙት ልምምድ ውስጥ ሕይወቱ እየባከነ ይኖር እንደነበር፥ በኃላም ነፍሱ በስቃይ ውስጥ ሆነ በአንድ አጋጣም የሮሜን መልእክት ምዕራፍ 13፥ 13-14 እንደነበበና ከዛ ጊዜ ጀምሮ አሮጌ ሕይወቱን አውልቆ በመጣል ሕይወቱን ፈጽሞ ለመለዉጥ መንፈስ ቅዱስ የተጠቀመው የሮሜን መልዕክት እንደሆነ ጽፎል። የ16ኛው ክፍለ ዘመን ክስተት የተሃድሶ መሪ የነበረው ማሪቲን ሉተር መነኩሴ ሆኖ ሰለምን እና ስለ ደህንነቱ እርግጠኝነትን አብዝቶ ይፈልግ ነበር የመነኮሰውም ይህንኑ ፍለጋ ነበር፥ ነገር ግን አንድ ምሽት በሚቀጥለው ቀን ለምያደርገው ንግግር ዝግጅት በማድረግ ላይ ሰለ የራሱን ሕይወት ከዛም በጊዜው የነበረውን የቤተክርስቲያንን አካሄድ ፈጽሞ የለወጠው የእግዝአብሔር ቃል እውነት የሮሜን መጽሐፍ ስያጠና ተገለጸለት። ይሄንን በተመለከተ እንደዝህ ጽፎል " የሮሜን መልእክት በተረዳሁ ጊዜ የገነት ደጆች ተከፈቱልኝ፥ እኔም አልፌ ገበሁባቸው" ‘ጽድቅ በእምነት ብቻ’ ለምለው አድስ ኪዳናዊ አስተምህሮ ሉተር እንድነቃ ያደረገው የሮሜ መልእክት ነበር። በዚህም ምክንያት የሮሜ መልእክት በ16ኛው ክፍለ ዘመን የስነ-መለኮቲዊ መከራከርያ ማዓከል ሆነ ነበር እንደውም "የተሃድሶዉ መጽሓፍ" የሚል ስምም ተስጥቶ ነበር። ታላቁ የሪቫይቫል ሰው ጆን ዌስሊ እንዴት ወደ ወንጌል እምነት እንደመጣ በዚህ መልኩ ጽፎል "አንድ ምሽት በፈቃዴ ሰይሆን Aldersgate street ወደሚባል ስፍራ ሄድኩኝ /ይሄ ስፍራ የሚገኛው ሃገረ እንግሊዝ ነው/ በዚያም አንድ ሰው ማርቲን ሉተር ለሮሜ መልእክት የጻፈውን መቅድም ያነብ ነበር ሰዓቱ 9 ሰዓት ልሆን 25 ደቂቃ ይቀረው ነበር፥ ሰባኪውም በክርስቶስ ኢየሱስ እምነት በኩል እግዝአብሔር በሰዎች ልብ ውስጥ የሚሰራውን የለውጥ ስራ በመግለጽ ለይ ሰለ ልቤ ውስጥ እንግዳ የሆነ ሙቀት ተሰማኝ። በክርስቶስ እንደታመንክ ተሰማኝ፥ ለደህንነት ክርስቶስ ብቻ፤ እናም ኃጢያቴን ከእኔ እንደወሰደው በእርግጠኝነት ታወቀኝ፥ የእኔን ኃጢአት ወስዶታል እናም ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛል።" ይሄንን ታላቅ ሰው ጌታ ያገኘበት መልእክት የሮሜ መልእክት ነው። የሮሜ መልእክት ብዙ ሃያላን የተቆፈሩበት ጉድጋድ እና የተቆረጡበት ዓለት ነው። ዛሬም በእኛ ዘመን እግዝአብሔር ሃያላንን እንደሚያስነሳ አምናለሁ። የእግዝአብሔር ፍቅር የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ እና የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ከሁላችን ጋር ይሁን፥ አሜን። ከታች ያለውን መስፈንጠሪያ በመጫን 👇👇ይቀላቀሉ👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ሰላም ለእናንተ ይሁን የተወደዳችሁ! እንዴት ቆያችሁኝ? እኔ እጅግ ሰላም ነኝ። ለለፉት 8 ወራት ተራርቀን ብንቆይም እንደገና ተመልሻለሁ። በዚህ ቻናል ሳቀርብ የነበረው መንፋሳዊ መልእክት ብዙዎቻችሁን እንዳነጸ አውቃለሁ፥ ነገር ግን በሁኔታዎች ተጠምጄ የእግዚአብሔርን ስራ በቸልተኝነት በለመስራቴ ይቅርታ እጠይቃለሁ። ከዛሬ ጀምሮ የሚኖረን ጊዜ እጅግ በጣም የምንበለጽግበት እንደምሆን አምናለሁ! መጽሐፍ ቅዱስን በብዙ መረዳት እናጠናልን፣ በአሁኑ አለም የእግዚአብሔርን መንግስት በብዙ መረዳት እና ሃይል እናገለግላለን። የእግዚአብሔር አብ ፍቅር፣ የጌታም የኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ እና የመንፋስ ቅዱስ ሕብረት ከሁላችን ጋር ይሁን! @TheDeepThingsOfGod

Follow me on TickTock!🥰

መጽሐፉ በድምቀት ተመርቋል! ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን። በመጽሐፉ ምረቃ ላይ የተገኛችሁ ተጋባዥ እንግዶች፣ የተወደዳችሁ ወንድምና እህቶች ሁሉ እጅግ አድርጌ አመሰግናችኋለሁ። መጽሐፉን መግዛት የ
+3
መጽሐፉ በድምቀት ተመርቋል! ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን። በመጽሐፉ ምረቃ ላይ የተገኛችሁ ተጋባዥ እንግዶች፣ የተወደዳችሁ ወንድምና እህቶች ሁሉ እጅግ አድርጌ አመሰግናችኋለሁ። መጽሐፉን መግዛት የምትፈልጉ ሆሳዕና ያላችሁ አደባባይ ፊት ለፊት በሚገኘው ሌዊ መጽሐፍት ቤት እና ጮራሞ ሞል ፊትለፊት ታገኛላችሁ። ከሆሳዕና ውጭ ያላችሁ መጽሐፉን የሚትፈልጉ በዚህ ስለክ በመደወል ማነጋገር ትችላላችሁ፥ ተባረኩ። 0907217614 ዳንኤል

አንድ ቀን ብቻ ቀረው! ሆሳዕና ያላችሁ በፍጹም መቅረት የሌለባችሁ ፕሮግራም የፊታችን እሁድ ከሰዓት 8 ሰዓት ላይ ሆሳዕና እናት ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን፣ አማርኛ ማንበብ የሚችል ሁሉ ይሄንን ድንቅ መጽሐፍ በገንዘቡ የራሱ እንዲያደርግ እና ለሚወዳቸው ስጦታ እንዲሰጥ ምክሬ ነው። ሆሳዕና ያልሆናችሁ ፕሮግራሙን መካፈል ባትችሉ መጽሐፉን መግዛት የምትፈልጉ ሁሉ በውስጥ መስመር አናግሩኝ!

ትልቅ ነገር የማድረግ ፍላጎት በብዙሃኑ አሳብ ውስጥ አለ፣ ትልቅ ነገር የማድረግ አቅም ግን ከብዙሃኑ የተለየ አካሄድ ላላቸው ነው። ዳን የማክበርን ሕይወት ስለኖርክበት ይህንን መጽሐፍ ስትጽፍ ሃሳቦች
+3
ትልቅ ነገር የማድረግ ፍላጎት በብዙሃኑ አሳብ ውስጥ አለ፣ ትልቅ ነገር የማድረግ አቅም ግን ከብዙሃኑ የተለየ አካሄድ ላላቸው ነው። ዳን የማክበርን ሕይወት ስለኖርክበት ይህንን መጽሐፍ ስትጽፍ ሃሳቦችን ማፍለቅ ንስር ያላየውን እና ኩሩ አውሬ ያልረገጠውን መንገድ እንደመራመድ እንዳልከበደህ አውቃለሁ። አክባሪ አያሳጣኝ ከሚለው ማህበር ነጠል ብለህ አክባሪ ልሁን ብለህ ከብዙሃኑ የተለየ አካሄድ ሄደህ ይሄንን ታላቅ ስራ ስለሰራህ በመጀመሪያ በነገር ሁሉ የረዳህን እግዚአብሔርን በመቀጠል ደግሞ በበዛልህ ፀጋ መጠን የተጋህ በመሆንህ አንተን አመሰግናለሁ። እንኳን ደስ ያለህ! አብራችሁ ለዚህ መጽሐፍ ስራ የተጋችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ! #ግንቦት 13 #ሆሳዕና #እናት #ቃለሕይወት #ተጋብዛችኋል

ይሄ ድንቅ መጽሐፍ በልጅ ዳን(ዳንኤል ብርሃኑ) ተጽፎ እና ተዘጋጅቶ በቅርቡ የሕትመት ስራው አልቆለት ለንባብ የሚውል ይሆናል! በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ትልቅ ትርጉምና ትርፍ ስላለው ስለማክበር የተጻፈ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በሮሜ መልእክት ምዕራፍ 13 ቁጥር 7 ላይ “ለሁሉ የሚገባውን አስረክቡ፤ ግብር ለሚገባው ግብርን፥ ቀረጥ ለሚገባው ቀረጥን፥ መፈራት ለሚገባው መፈራትን፥ ክብር ለሚገባው ክብርን ስጡ።”- ሮሜ 13፥7 እንደሚል በተግባራዊ ክርስትና ውስጥ "ክብርን ለሚገባው መስጠት" ወሳኝ ልምምድ ነው። ይሄንንም ክብርን የመስጠት ጥበብ ከውጤቱ ጋር አጣምሮ በዚህ መልኩ በመጽሐፍ ልጅ ዳን አቅርቦልናል። ልጅ ዳን ትጋትህ ፍሬ ስላፈራ እጅግ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፥ እንኳን ደስ ያለህ። እኔም በጓዳ የተናገርኩት በአደባባይ ስሰማ በማየቴ እጅግ ደስተኛ ነኝ!!!

proud of you son dan!
proud of you son dan!

Carelessness with time is carelessness with life! Time = existence or/and life